en
Feedback
LOGOS

LOGOS

Open in Telegram

🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው

Show more
The country is not specifiedThe category is not specified
262
Subscribers
+324 hours
+137 days
+2830 days
Posts Archive
photo content

4_5951763398722062482.mp36.35 MB

ሲ. ኤስ. ሉዊስ በአንድ ወቅት እንዲህ ብሎ ነበር፦
​“ወደ ሃይማኖት የሄድኩት ደስተኛ ለመሆን አይደለም፤ አንድ ጠርሙስ የወይን ጠጅ  ያንን ሊያደርግልኝ እንደሚችል ሁልጊዜ አውቅ ነበር። ሃይማኖት ሙሉ በሙሉ ምቾት እንዲሰጥህ የምትፈልግ ከሆነ፣ ክርስትናን በፍጹም አልመክርህም።”
የዘመኑ ክርስትና ብዙ ጊዜ የሚታሰበው፣ የአምልኮ ሙዚቃ ከበስተጀርባ እንዳለው የራስን ሕይወት ማሻሻያ (self-help) ሴሚናር ተደርጎ ነው። ​“ወደ ኢየሱስ ኑና ሕይወታችሁ ይቀልላል። ወደ ኢየሱስ ኑና ሁልጊዜ ጥሩ ስሜት ይሰማችኋል። ወደ ኢየሱስ ኑና ምቾት ታገኛላችሁ።” ይባላል። ነገር ግን ኢየሱስ በፍጹም ምቾትን ሊሰጠን ቃል አልገባልንም ። እርሱ የሰጠው የተስፋ ቃል መስቀልን ነው። ​ክርስትና ትዕቢትህን ይሰብረዋል። ከኃጢአትህ ጋር ያጋጭሃል። ስጋዊ ማንነትህን ይገድላል። የበደሉህን ሰዎች ይቅር እንድትል ይጠራሃል። ያለህበት ማኅበረሰብ በዚህ ምክንያት ቢጠላህ እንኳን ለእውነት እንድትቆም ይጠይቅሃል። በተቃራኒው ደግሞ፦ በአንድ ጠርሙስ መጠጥ፣ በዕፅ፣ በገንዘብ፣ በፍትወት፣ በምድራዊ ስኬት እንዲሁም በምቾት ዓለም ፍጹም ሊገኙ የማይችሉትን የላቁ ሀብቶች ያጎናጽፍሃል፦እውነት፣ ዓላማ፣ ቤዛነት፣ የዘላለም ሕይወትን... ​ክርስትና መጥፎ ሰዎችን የተሻለ ስሜት እንዲሰማቸው ማድረግ አይደለም፣ ​ሙታንን ሕያው ማድረግ እንጂ።
​“ክርስቶስን መከተል ማለት የራስን ሕይወት ማሻሻል አይደለም፤ የራስን ሕይወት አሳልፎ መስጠት እንጂ። ኢየሱስ ወደ እኔ ኑና ‘የተሻለ ሕይወት ኑሩ’ አላለም፤ ‘መስቀላችሁን ተሸክማችሁ ተከተሉኝ’ ነው ያለው።”
    ጆን ማክአርተር ✍️ The Theologian

📖   1 ቆሮንቶስ 1:8 -9 📖 8 እርሱም ደግሞ በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ቀን ያለ ነቀፋ እንድትሆኑ እስከ ፍጻሜ ድረስ ##ያጸናችኋል። 9 ወደ ልጁ ወደ ጌታችን ወደ ኢየሱስ ክርስቶስ ኅብረት ##የጠራችሁ እግዚአብሔር ##የታመነ ነው።

“እርሱ ግን፣ “ጸጋዬ ይበቃሃል፤ ኀይሌ ፍጹም የሚሆነው በድካም ጊዜ ነውና” አለኝ። ስለዚህ የክርስቶስ ኀይል በእኔ ያድር ዘንድ፣ ይበልጥ ደስ እያለኝ በድካሜ እመካለሁ።” 2 ቆሮንቶስ 12:9 #አቅምእንደሌለንየማመን__ነፃነት ...በዙሪያችን ያለው ባሕል ሁሉ " #ጠንካራ ሁን፣ #ራስህን አስመስክር፣ #ድክመትህን ደብቅ" እያለ ይጮኻል። ጳውሎስ ግን የተማረው ከዚህ ፍጹም ተቃራኒ የሆነውን ነው፦ በድካሙ "በደስታ" መመካትን። ይህ ራስን መታመንን ከራስ ላይ አንስቶ ወደ መድኃኒቱ ማዞር ነው። #እኛ በቂ እንዳልሆንን ስናምን፣ በቂ ለሆነው ለእርሱ ስፍራ እንሰጣለን። እግዚአብሔር ለትሑታን ግን ጸጋን ይሰጣል (ያዕቆብ 4:6)፤ ትሕትና ደግሞ ሁሉንም ነገር እንደተቆጣጠርን አድርጎ ከመምሰል መላቀቅ ይጀምራል። #ይህ_እጅግ ነፃ የሚያወጣ እውነት ነው። የሌለንን መንፈሳዊ ጥንካሬ እንዳለን አድርገን ማስመስከር የለብንም። ፍርሃቶች፣ ፈተናዎችና ውስንነቶች የሌሉ ለማስመሰል መሞከር አያስፈልግም። @coramdeoliving

photo content

        📖📖 ኤፌሶን 2:8-9📖📖 “ 8 #ጸጋው #በእምነት አድኖአችኋልና፤ ይህም የእግዚአብሔር #ስጦታ ነው እንጂ ከእናንተ አይደለም፤ 9 ማንም እንዳይመካ #ከሥራ አይደለም።” የምናመልከው #ለመጽደቅ አይደለም፤ እግዚአብሔር በክርስቶስ #ስላጸደቀን እንጂ። እግዚአብሔርን እናመልከዋለን እንጂ አንረዳውም(አናግዘውም)። ••••••••••••••• ✍️በርክ ፓርሰንስ •••••••••••••••

ወደራሴ ስመለከት፥ እንዴት እንደምድን አይታየኝም፤ ***** ወደ ክርስቶስ ስመለከት ደግሞ፥ እንዴት እንደምጠፋ አይታየኝም። ••••••••••••• ✍️ማርቲን ሉተር •••••••••••••
     📖📖ዮሐንስ 10:28-29📖📖 28 እኔም የዘላለም ሕይወትን እሰጣቸዋለሁ፥ #ለዘላለምም_አይጠፉም፥ ከእጄም ማንም #አይነጥቃቸውም። 29 የሰጠኝ አባቴ ከሁሉ ይበልጣል፥ ከአባቴም  #እጅ_ሊነጥቃቸው ማንም አይችልም።

Repost from LOGOS
ለመዳን በራሳችን ሥራ መታመን፥ የሲዖል የኋላ በር ነው። •••••••••••••• #ኮንራድ_ምቤዌ •••••••••••••• እግዚአብሔር እንዲቀበልህ በመልካም ሥራህ ከተመካህ ኢየሱስ አዳኝህ አይደለም። ••••••• #ቲም_ኬለር •••••••

🏛️የገበሬው ሚስት(አስተማሪ ታሪክ )🏛️       ** አንድ ገበሬ ቆንጆ ልባምና አስተዋይ ሚስት አገባ። በጣም ተዋደውና ተከባብረው ይኖራሉ፡፡ ነገር ግን አንዲት ነገረኛ ጎረቤትም ነበረቻቸው። እቺህ ጎረቤታቸው የገበሬውን ሚስት ስለምትጠላት ስሜቷን የሚጎዱ ነገሮችን ታደርግባት ነበር፡፡ ሁልጊዜም በየቀኑ ቤት በገባችና በወጣች ቁጥር ስድብ ታከናንባታለች። በአንዱ ቀን አጋጣሚም እቺው መከረኛ ጎረቤቷ እንዲህ ትላታለች #"ምን አይነት ማፈሪያ ሴት ነሽ! አባትሽ የተሻለ ሰው አግብተሸ ደህና ቦታ ትደርሻለሽ ብሎ እያሰበ አንቺ ግን አሁን  የምታደርጊው ነገር ቢኖር በእርሻው ውስጥ ለረጅም ሰአት በመቆየት እጅግ የኮሰሱ ላሞችን መንከባከብ ብቻ ነው። አንቺ የከሰርሽ ሴት ነሽ! " በተለያየ ጊዜ ስታገኛትም ለማናደድ እና ሙድ ለመያዝ የማታደርገው ጥረት የለም። ነገር ግን የገበሬዋ ሚስት በጣም የተረጋጋች እና ስድቧም የሚረብሻት ሰው  አይደለችም። ስትሰደብም ከመበሳጨት ይልቅ ሳቅ ትላለች፡፡ ሰላማዊ ነችና ሁልጊዜ ፈገግታዋን ተላብሳ ትታያለች። ታዲያ በዚህ መሃል ጎረቤቷ የገበሬውን ሚስት ለማስቆጣት ያደረገችው ጥረት ሳይሳካላት ስለቀረና  ስድቦቿን ለምን ከቁም ነገር እንዳልቆጠረቻቸው ሊገባት አልቻለም። አንድ ቀን ታዲያ ወደ እርሷ ቀረበችና እንዲህ አለቻት፡- #"ስሰድብሸ ነበር የኖርኩት። ለምንድን ነው 🤔ግን የማትናደጅውና መልስ የማትሰጪኝ? " ስትል ትጠይቃታለች። የገበሬው ሚስትም አንድ ጥያቄ ልጠይቅሽ? 🤔እስቲ የሆነ ነገር ሰጥተሸኝ አልቀበልም ካልኩ ማን ጋር ነው የሚቀረው? " በማለት ጥያቄዋን በጥያቄ አፋጠጠቻት። ጎረቤት ምላሽ ሰጠች #እኔ_ጋር_ይቀራል። የገበሬው ሚስትም 😁ፈገግ ብላ ስድብሽን እስካልተቀበልኩ ድረስ አንቺው ጋር ይቀራሉ ማለት ነው ብላ ነጉሩን ቋጨችው።         🥝ፍሬ ሀሳቡ 🥝 **** ይህች ዓለም እርስ በእርስ በመበላላት፣ በጭቅጭቅ፣ ጥላቻ እና በአጠቃላይ በአሉታዊ ሁነቶች የተሞላች ስፍራ ሆናለች። እነዚህን ነገረኞች ማስቀረት አንችልም። እነዚህ ነገሮች በዙሪያችን እለት በእለት ህይወታችን ውስጥ ያጋጥሙናል። ሆኖም ግን ሰዎች ሲሰድቡን፣ ሲሳለቁብን ወይም ሲነቅፉን መበሳጨት የለብንም፡፡ ሁሌም ቢሆን ስድብ ከተሳዳቢው ዘንድ ቀሪ መሆኑን አስታውስ። ንብረትህ አይደለምና ሲያመጡብህ ተበሳጭተህ አትቀበል። 📖 ከዚህ ሀሳብ ጋር የሚዛመዱ የመፅሐፍ ቅዱስ ጥቅሶች 📖      📖   መክብብ 10:4📖 4 ትዕግሥት ታላቁን ኃጢአት ጸጥ ያደርጋልና... 📖 ምሳሌ 15:1-2📖 1 የለዘበች መልስ ቍጣን ትመልሳለች፡ ሸካራ ቃል ግን ቍጣን ታስነሣለች። 2 የጠቢባን ምላስ እውቀትን ያሳምራል፤ የሰነፎች አፍ ግን ስንፍናን ያፈልቃል።    📖 ምሳሌ 25:15📖 15 በትዕግሥት አለቃ ይለዝባል፥ የገራም ምላስ አጥንትን ይሰብራል። ✍️ወንድም አሻግሬ

ኃጢአት የምንደርገው ነገር ሊሆን ይችላል፤ ነገር ግን የምንገለጽበት ማንነት አይደለም። ያደረግነው ኃጢአት ስህተቶችን ይገልጻል፤ ክርስቶስ ግን ማንነታችንን ይገልጻል። የክርስትና ሕይወት ጉዞ ማለት ኃጢአተኛ ወደ ቅዱስነት ለመለወጥ የሚደረግ ትግል ሳይሆን፣ ቅዱስ የሆነ ሰው ያንን ማንነቱን በየዕለቱ በተግባር መኖርን የሚማርበት የጸጋ ጉዞ ነው። @christcentered7 📖 ቆላስይስ 1:21-22📖 “ እናንተንም ነውርና ነቀፋ የሌላችሁና ቅዱሳን አድርጎ በእርሱ ፊት ያቀርባችሁ ዘንድ፥ በፊት የተለያችሁትን ክፉ ሥራችሁንም በማድረግ በአሳባችሁ ጠላቶች የነበራችሁትን አሁን በሥጋው ሰውነት በሞቱ በኩል አስታረቃችሁ። ”

" #ኃጢአት_ጨካኝና_ጨቋኝ የባሪያ ጌታ ነው፤ #ክርስቶስ_አፍቃሪና_መሐሪ ነው። የኃጢአት ቀንበር ከባድና አስጸያፊ ነው፤ የክርስቶስ ቀንበር "ልዝብ፣" እና ሸክሙም ቀላል ነው።”(ማቴ.11V30) ኃጢአት ባሪያዎቹን በጨለማና በሞት አጥምዶ ይይዛቸዋል፤ ክርስቶስ በእርሱ ላሉት ሁሉ በብርሃኑ ሕያዋን አደረጋቸው። (ቆላ 2V13 ) ኃጢአት ወደ ጥፋትና ስህተት ይመራል፤ ክርስቶስ “መንገድና እውነት ሕይወትም ነው።”( ዮሐ 14V6 ) የኃጢአት ባርነት ጥላቻ፣ ስብራት፣ ፍርሃትና ውርደት የተሞላ ስሆን የክርስቶስ ባርነት በልካምነት፣ በክብር፣ በሐሴት፣ በእውነትና በቅንነት የተሞላ ነው። ..."ክርስቶስ ኃጢአትንና ሰይጣንን በመስቀል ላይ ድል ነሥቷል። በእርሱ ለሚያምኑ ሁሉ የእግዚአብሔርን ቁጣ ሙሉ ቅጣት ተቀብሏል። የእርሱ ሞት ከኃጢአት፣ ከኩነኔ እና ከፍርሃት ነፃ አውጥቶናል።" ..."ከኃጢአት አርነት ወጥተናል። ማለትም ለመታዘዝ፣ በጽድቅ ለመኖር እና ቅድስናን ለመከተል ነፃ ወጥተናል። [አሁን] የክርስቶስ ባሪያዎች ነን። በጣም አስደማሚውና አስደናቂው ነገር ደግሞ የኢየሱስ ክርስቶስ ባሪያ መሆን እውነተኛ ነፃነት ነው።"     __John_MacArthur_(📖 Slave) ✍️ @Gospel_of_God

ከእግዚአብሄር የማይጀምርና በእርሱ የማይፈጸም ሥራ እግዚአብሄርን ሊያስደስተው አይችልም… ከእርሱ ተጀምሮ በእርሱ ተከናውኖ ለእርሱ ክብር ፍጻሜ የሚያመጣ ስራ ሁሉ ግን እርሱን ያስደስተዋል…. ከራሱ ውጪ ከሌላ ወይም በሌላ contingent በሆነ ደስታ መደሰት የሚችል necessary being ስለማይኖር አምላካችንም ፍጹም የሆነ ደስታ የሚያገኘው ከራሱ በራሱ በኩል ብቻ ነው….

“ኢየሱስ የነፍሳችን  መልህቅ፣ የማስተዋላችን  ብርሃን፣ የፍቃዳችን  ደስታ፣ የትዝታችን  ሐሴት ነው”.... Johann Arndt

"በታላቁ ሀኪም ፊት፣ የእኔ ተገቢ ድርሻ ሊሆን የሚችለው፥ ቁስሌን ማሳየት ነው" ---- ፊልፕ ያንሲ
"በታላቁ ሀኪም ፊት፣ የእኔ ተገቢ ድርሻ ሊሆን የሚችለው፥ ቁስሌን ማሳየት ነው" ---- ፊልፕ ያንሲ

መስቀል፣ በጎልጎታ ኮረብታ ላይ ከመተከሉ በፊት በእግዚአብሔር ልብ ውስጥ ተተክሎ ነበረ። መስቀሉ ከጎልጎታ ኮረብታ ቢነቀልም፣ በእግዚአብሔር ልብ ላይ ያለው መስቀል ግን እስካሁንም አለ። _ ጳውሎስ ፈቃዱ፣ የተሰቀለው፣ ገጽ 52

Repost from N/a
ጸልዩለት🥺🥺🥺

sticker.webp0.39 KB

"ተመልከቱ የገረጣ ደረቱ፣የቀላ ጎኑን፣በጥም የደረቀ አንጀቱን፣በሞት የማቀቀ ውብ አይኖቹን፣ክንዶቹ ተወጥረዋል፣የከበረ ፊቱ በደም ተጨማልቋል፣ባቶቹ ተዘርግተዋል፣የተቸነከረው እግሮቹ በከበረው ደሙ እርሰዋል።ተመልከቱ ክቡር አባቱ የውድ ልጁን ሰውነት ሲያይ ደቋል፣ቆስሏል፣ተቦጫጭቋል። አቤቱ፥ እንዲሁ ሰዎችን ወዶ ልጁን መስጠቱን፣ ያለምክንያት አለምን አፍቅሮ ውዱን መሰዋቱን፣ አይቼ አላቅም ያንተን ቅዱስ ፍቅርህን፣ በመስቀል ደም ዋጋ እኔን መግዛትህን። እዩት ውድ መድሀኒቴን በኔ ቦታ የሆነውን፣ በኔ ድርሻ የከፈለውን። አቤት ያንን ፅዋ፣ አቤት ያንን ቁጣ፣ ከእኔ ተቀበሎ ወስዶት የጠጣ ለእኔ አይደለም ወይ? ለጠላቱ ብሎም ለገዳዩ። ይገርመኛል በእኔ ወንጀል አንተ መገረፍህ፣በኔ ትዕቢት አንተ መዋረድህ፣በኔ ትምክህት ራስህን ባዶ ማድረግህ፣በኔ አመፅ እስከሞት መታዘዝህ፣በኔ ሆዳምነት መራብና መጠማትህ።እኔ በበላሁት ፍሬ አንተ ታመምክ፣እኔ በደስታ ስንደባለል አንተ በጦር ተወጋክ፣በእኔ አፍ ውስጥ ያለው ማር በአንተ ሆድ ውስጥ ወደ ሀሞት ተቀየረ።"       አውግስጢኖስ        ፊልጵስዩስ 2:7-8 “... ነገር ግን የባሪያን መልክ ይዞ በሰውም ምሳሌ ሆኖ ራሱን ባዶ አደረገ፥ 8 በምስሉም እንደ ሰው ተገኝቶ ራሱን አዋረደ፥ ለሞትም ይኸውም የመስቀል ሞት እንኳ የታዘዘ ሆነ። ”

Repost from SoulEchoes🪶
ስለ ኪንሱጊ እንደምታውቁ አስባለሁኝ ግን እንዲሁ አጭር ማብራሪያ ይኧው፥ (Kintsugi) ወይም "በወርቅ ማያያዝ" የሚባለው ጥበብ፣ የተሰባበሩ የሸክላ ዕቃዎችን በወርቅ፣ በብር ወይም በፕላቲኒየም ዱ
ስለ ኪንሱጊ እንደምታውቁ አስባለሁኝ ግን እንዲሁ አጭር ማብራሪያ ይኧው፥
(Kintsugi) ወይም "በወርቅ ማያያዝ" የሚባለው ጥበብ፣ የተሰባበሩ የሸክላ ዕቃዎችን በወርቅ፣ በብር ወይም በፕላቲኒየም ዱቄት ከተቀላቀለ የማጣበቂያ ቀለም (lacquer) ጋር በማገናኘት የመጠገን ጥንታዊ የጃፓን ጥበብ ነው። ​ይህ ጥበብ ስብራትን ወይም ጥፋትን ከመደበቅ ይልቅ፣ እንደ ዕቃው ታሪክ አካል አድርጎ በክብር ጎልቶ እንዲታይ ያደርገዋል። ኪንሱጊ ፍልስፍናዊ በሆነ መልኩ "ዋቢ-ሳቢ" (Wabi-sabi) ከሚባለው የጃፓን አስተሳሰብ ጋር የተያያዘ ሲሆን፣ ይህም በጎደሎ ወይም ፍጹም ባልሆነ ነገር ውስጥ ውበትን መፈለግ ማለት ነው።
ብቻ ትላንት ጊቢ ስለ አውግስጢኖስ lecture ነበረን እና ይህን የ ኪንሱጊ ሀሳብ ተነስቶም ነበር ምናምን፥ በብዙ ጉዳይ ተሰብረን ሊሆን ይችላል በብዙ ወድቀን ተንኮታኩተን ደቀንም ሊሆን ይችላል እግዚአብሔር ግን ሊጠገን የማይችል ስብራትን አያውቅም! ይሄ ከኔ በላይ ነው የሚለው ነገር የለም! በነጠፈና በደረቀ ህይወት የለውም በተባለበት ስፍራ ላይ ነፍስን መዝራት ህይወትን ማብቀል ይችላል። አይዞን እግዚአብሔር ይራራልናል ይጠግነናል እንደገና ይሰራናል✨