LOGOS
Open in Telegram
🎯የቻናሉ ዓላማ:LOGOS የሚለው ቃል ከGreek የመጣ ሲሆን፦ትርጉሙም ቃል፣ ምክንያት፣ክርስቶስ (የእግዚአብሔር ቃል ዮሐ 1፥1) በዚህ ቃል እውቀታችንን አሳድገን በኑሮ እንድንተገብር ነው
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
262
Subscribers
+324 hours
+137 days
+2830 days
Posts Archive
262
📌 የማወራቹ ስለ ##ኃይል ነው!
መሬት ላይ ጥሎ እንደ ትል የሚያንፈራፍር አይደለም፣ ቪ ኤይት የሚያሳውጅ አይደለም፣ ያልተፈወሰውን ተፈወሰ የሚያስብል አይደለም።
🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋🔋
የማወራው የክርስትናን ሕይወት እንድትኖሩ ስለሚያደርግ #ኃይል፣ በእውነተኛ ፍቅር ስለሚያራምድ ኃይል፣ ስለ ጸሎት #ኃይል፣ የወንጌል-መስካሪ ስለሚያደርግ #ኃይል ነው።
ይህ ኃይል ነው የሚያስፈልገን።
••••••••••
ፖል ዎሸር
••••••••••
262
ድነት የሚገኘው በሰው ጥረት ወይም በመልካም ሥራ ሳይሆን፣ በእግዚአብሔር ጸጋ ብቻ ነው። የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱም በኢየሱስ ክርስቶስ በኩል ተገልጧል።
እርሱ ኃጢአትህን ይቅር ብሎ፣ በመንፈስ ቅዱስ አዲስ ሕይወት ሰጥቶሃል። ስለዚህ ያለፈው ውድቀትህ የወደፊት ተስፋህን አይወስንም፤ የእግዚአብሔር ጸጋ ከውድቀትህ ይበልጣል፣ ፍቅሩም ከኃጢአትህ ይበልጣል።
ስለዚህ ዛሬ ክርስቶስ በሰራልህ ስራ ብቻ እመን። ያዳነህ ጌታ ዛሬም ህይወትህን ሙሉ ያድሰዋል።
ቲቶ 3:4-5 ነገር ግን የመድኃኒታችን የእግዚአብሔር ቸርነትና ሰውን መውደዱ በተገለጠ ጊዜ፥ እንደ ምሕረቱ መጠን ለአዲስ ልደት በሚሆነው መታጠብና በመንፈስ ቅዱስ በመታደስ አዳነን እንጂ፥ እኛ ስላደረግነው በጽድቅ ስለ ነበረው ሥራ አይደለም፤✍️ #tesfa
262
##እኔ ሁለንተናዬን ለአንተ ሰጥቼሃለሁ እያልኩ ነው ፤ ግን ምንአልባት እኔ ሳላውቅ ለአንተ እየሰጠው የቀረ ማንነት ካለም ውሰዳው ፤
##ሙሉዬን ውሰደው የእኔ የምለው ማንነት አይኑረኝ ሁሉ የአንተ ሆኖ የአንተ የሆነው ሁሉ ደግሞ በአንተ ተዋጅቶ ተመልሶ የኔ ይሁን !
⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐⭐
✍️ወንድም አሻግሬ
📆 15/10/2018 ሰኞ
262
አውቃለሁ አንዳንዶቻችሁ ኢየሱስን መውደድ በምትፈልጉት ልክ ባለመውደዳችሁ ታዝናላቹ።
ለእርሱ ያላችሁን የእናንተን ፍቅር እርሱትና፥ እርሱ ለእናንተ ያለውን ትልቅ ፍቅር አስቡ፤
ያኔ ለእርሱ ያላችሁ ፍቅር ካሰባችሁት በላይ ከፍ ይላል።
•••••••••••••••
ቻርልስ ስፐርጀን
•••••••••••••••
262
🏆ድል ኢየሱስ በእኔ ውስጥ ስኖር ስለ እኔም ሲያሸንፍ ነው !
#እኔ እንድድን በመስቀል ላይ እንደሞተ ሁሉ ፤ ዛሬም #እኔ እንዳሸንፍ በእኔ ውስጥ ይኖራል ።
📚 ድል ነሺ ህይወት
✍️ዎችማን ኒ
ገፅ 84
አሸነፍ ሆንኩኝ በአንተ ተመስገን
ድሌ ነህ አከብርሃለሁ
አንተ ግንዴ እኔም ቅርንጫፍህ ነኝ
በአንተ ብዙ ፍሬ ማፍራት ሆነልኝ ተመስገን
በክርስቶስ በፀጋ ብቻ ድነት ያገኛችሁ ሰዎች ፤ ባዳነችሁ በክርስቶስ የድል ህይወት መኖር ትችላላችሁ
#እንድህ በሉ “ ከክርስቶስ ጋር ተሰቅያለሁ፤ ከእንግዲህ እኔ አልኖርም፤ ነገር ግን ክርስቶስ በውስጤ ይኖራል። ”
📖፨ገላትያ 2፥19-20📖
✍️ወንድም አሻግሬ
262
የእድሜ ልክ ፍለጋዬ
🤲 #ፀሎቴ ሁሉ አንተን የመፈለግ ይሁን ፤ ምክንያቱም ብዙ የፀሎት ጥያቄዎች 🙋 አንተን በመፈለግ ወስጥ መልስ ያገኛሉና !
ለአንተ ሁሉን አጥቼ በአንተ ሁሉ ማግኘት ይሁንልኝ ። ሁሉን ማግኘት ደግሞ አንተን እራስህን ማትረፍ ነውና ። ሁሉን አጥቼ አንተን ማትረፍ ይሁንልኝ። እግዚአብሔር ሆይ #ፀሎቴ ይሄ ነው ። የእድሜ ልክ ፍለጋዬ
🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️🧎♂️
✍️ወንድም አሻግሬ 15/10/2018 ሰኞ
262
Repost from The Theologian
"አምላኬ ሆይ፤ በሕይወቴ ሁሉ፣ ከሰዎች ጋር ባለኝ ግንኙነት ሁሉ ፍጹም ፍቅር ይኑረኝ። የምመርጣቸው ቃላት፣ የምጠቀምባቸው ምልክቶች፣ እና የሰውነቴ እንቅስቃሴዎች ሁሉ ለእኔና ለዓለም ላለህ ፍጹም ፍቅር ምስክሮች ይሁኑ።
ውድ ጌታዬ ሆይ፤ አንተን ለማወቅ፣ ለመውደድ እና በአንተ ለመደሰት ጸጋህን ስጠኝ። ይህንን በምድር ላይ በሙላት ማድረግ ባልችል እንኳን፣ በየቀኑ ወደ ከፍ ያለ ደረጃ እያደግሁ እንድሄድ፣ እስከዚያው ቀን በአንተ ፍጹም ደስታን እስከማገኝበት ጊዜ ድረስ እርዳኝ። በአንተ ላይ ያለኝ እውቀት በየቀኑ ይጨምር፤ ፍቅርህም በውስጤ እያደገ ይሂድ፤ ደስታዬም በአንተ ሙሉ ይሁን። አምላክ ሆይ፤ አንተ የእውነት አምላክ እንደሆንክ አውቃለሁ፤ የገባኸውን ቃል ኪዳን በሕይወቴ ፈጽምልኝ፤ ደስታዬ በአንተ ሙሉ ይሁን።"
ቅዱስ አውግስጢኖስ
262
«FULL OF GRACE AND TRUTH» የሚለው ✍️የዎቺ ማኒ መፅሐፍ ወደ አማረኛ ተተርጉሞ “ ፀጋና እውነት” ከሚለው መፅሐፍ የተወሰደ ድንቅ ታሪክ !
ሰምተችሁ አትርፉበት!
🎤ወንድም አሻግሬ
262
🏆 ##ድል አድራጊ የሆነ ክርስቲያናዊ ህይወት መኖር ከፈለግን ፤ ልናምናቸው የሚገቡ ጠቃሚ ነገሮች አሉ ።
ስለዚህ ከሰይጣንና ከኃጢአት ቀንበር ነፃ የሚያወጣን የእግዚአብሔር እውነት መሆኑን አስታውሱ ።
##በመሆኑም የሚከተሉትን ማመን ይገባናል፦
1.##ድነናል
ኢየሱስን አዳኙ አድርጎ ተቀብሎ ወደ ህይወቱ ያላስገባ ሰው ሰይጣንና ኃጢአትን ሊያሸንፍ አይችልም ። ...
ኢየሱስን ወደ ሕይወታችን ከገባ ፣ እርሱ በእኛ ውስጥ እንደሆነና በእርግጥ ያለ ምንም ጥርጥር ደኅንነት የዘላለም ህይወት እንዳገኘን ሙሉ ማረጋገጫ አለን ማለት ነው ። ( 1ኛ ዮሐንስ 5፡11፣12፣13)
2.##ደኅንነታችንን #ማጣት አንችልም
ሰይጣን «እናንተ እኮ መልካም ሰዎች አይደላችሁም ። ኃጢአት ሰርታችኋል። እንዴት የእግዚአብሔር ልጆች ትሆናላችሁ ?»
በማለት እኛን መሸንገል ያስደስተዋል ።
##ደኅንነታችን እንደ ተወሰደብንና እግዚአብሔርም ከእንግዲህ ወዲያ እንደማይወደን ሊያሳምነን ይፈልጋል ። #የሰይጣንን ሽንገላ ካመንን እንሸነፋለን ፣ #መልካም ፍሬ ማፍራትም ያዳግተናል ። #ጥርጣሬ ወደ ሽንፈት ይመራል ።
#የእግዚአብሔር እውነት ግን ነፃ ያወጣል ( ዮሐንስ 8፡32፣36)።
ሰይጣን ደኅንነታችንን ማጣት እንደምንችል እንድናምን ይፈልጋል ። ምክንያቱም መጠራጠር ከጀመርን በክርስትና ህይወታችን ድል አድራጊዎች እንደማንሆን ስለሚያውቅ ነው። ...
በእውነት ያመንንና ኢየሱስን እንደ አዳኛችን የተቀበልን ከሆነ ደኅንነታችንን ልናጣ እንደማንችል ማመን አለብን ! በእውነት አምነን ከሆነ ፣ እግዚአብሔርን ደስ ለማሰኘት የሚፈልግ ልብ ይኖረናል ...
✍️📚 በክርስቶስ የተገኘ ነፃነት 📚
ገፅ 15 & 16
262
"እስር ቤት ስለሆንክ ብቻ እስረኛ ነህ ማለት አይደለም"
ሪኪ ገና የ18 ዓመት ልጅ ሳለ ባልፈጸመው ወንጀል ምክንያት የሞት ፍርድ ተበየነበት። ለ39 ዓመታት ያህል እስር ቤት ውስጥ ማሰብ የሚከብድ ጊዜን ካሳለፈ በኋላ በመጨረሻ ነጻ ሆነ፤ ሆኖም በፍትሕ መጓደል ምክንያት በእስር ቤት ላሳለፋቸው ዓመታት ዳጎስ ያለም ካሳ ተከፈለው።
ሪኪ ከእስር ከተፈታ በኋላ በእስር ቤት እንዲገባ ምክን ያት ከሆነውን ሰው ጋር ፊት ለፊት ተፋጠጡ ። በአስገራሚ ሁኔታ አቀፈውና "ይቅር ብዬሃለሁ" አለው።
ሪኪ በቃለ መጠይቅ ላይ "እስር ቤት ስለሆንክ ብቻ እስረኛ ነህ ማለት አይደለም" ሲልም ተናግሯል። እውነተኛ ነፃነት የሚገኘው ከውስጥ እንደሆነ ጠቅሷል ። ሕይወት ሰፊ፣ ብዙ ገጽታ ያለው ጉዞ እንደሆነ በማስታወስ ቂምና ጥላቻን መተው እንዳለብንም ገልጿል።
ይቅር ባይነት ለራሳችን የምንሰጥ ውድ ስጦታ ነው ብሎ ያምናል። ይቅርታ ማድረግ ማጣት ሳይሆን፤ ፍቅርን ማሳደግ፣ መልካምነት መገንባት፣ መንፈሳችንን ማደስ ነው ብሎ ያምናል።
ሁላችንም ልባችን ይቅርታን እንዲፈልግ እና ሌሎችን ይቅር ለማለት የሚያስችል ጥበብ ለማግኘት ጥረት እናደርግ ሲልም መል እክቱን አስተላልፏል።
ያለፈ ታሪካችን እስረኞች አንሁን፤ ይልቁንም ነገ የሚያመጣልንን ገደብ የለሽ አማራጮችን እንመልከት!
✍️https://t.me/manbeblelakeastesaseb
📖 ኤፌሶን 4:32📖
32 እግዚአብሔር በክርስቶስ ይቅር እንዳላችሁ፣ እናንተም ይቅር ተባባሉ፤ እርስ በርሳችሁ ቸሮችና ርኅሩኆች ሁኑ።
262
አምላኬ ፍቅርህ በእኔ ሁኔታ ስለልተመሰረተ አመሰግንሃለሁ 👏
በርትቼም ፣ ደክሜም ትወደኛለህ !
በእኔ ላይ ያለው ፍቅርህ ፣ አይጨምርም፣ አይቀንስም ተመስገን 👏
262
🗞️🗞️ ደስታ 🗞️🗞️
ብዙ ገዜ ደስታን የሚንፈልገው በእርኩሰት(በዓለም 🌍) ውስጥ ነው
ለምሳሌ ፦ መጠጥ ፣ መዳራት ፣ ዝሙት ፣ ብዙ መብላት ፣ ፋሺን መቀያየር ፣ ያለ አግባብ ገንዘብ ማከማቸት...
እነዚህን ከመሳሰሉ ነገሮች ደስታን የሚናገኝ ይመስለናል !
ግን ያሳዝናል በእነዚህ ውስጥ ፍፁም ደስታ ልገኝ አይችልም ! ምንአልባት ለቅፅበት ደስታን መሳይ ስሜት ልሰጡ ይችላሉ ፤ ግን የሚከተለው ነፍስን የሚወጋ #የፀፀት መርፌ ነው !
“🌍ዓለም ደስታን መሳይ ስሜት ውስጥ ፣ ከቅፅበት በኃላ ሀዘን ታጠጣለች ! ”ግን የነፍሳችን እረኛ ኢየሱስ እንዲህ ይላል “ 📖 ዮሐ15:11-12📖 11 ደስታዬ በእናንተ እንዲሆንና ደስታችሁም ሙሉ እንዲሆን ይህን ነግሬአችኋለሁ። 12 ትእዛዜ ይህች ናት፤ እኔ እንደ ወደድኋችሁ እናንተም እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ።” ደስታችን ሙሉ የሚሆነው ትዕዛዙን ስንጠብቅ ነው ! #ትዕዛዙም_😒ከባድ አይደለም_ይላል ቃሉ ( 1 ዮሐንስ 5:3-4 3 እግዚአብሔርን መውደድ ትእዛዞቹን መፈጸም ነውና። #ትእዛዞቹም ከባድ #አይደሉም፤ 4 ምክንያቱም ከእግዚአብሔር የተወለደ ሁሉ #ዓለምን ያሸንፋል። #ዓለምን #የሚያሸንፈውም #እምነታችን# ነው።) 📑የአብ ትዕዛዝ በላከው በልጁ ማመን ነው 1 ዮሐንስ 3:23 📑23 ትእዛዙም በልጁ በኢየሱስ ክርስቶስ እንድናምንና እርሱ እንዳዘዘንም እርስ በርሳችን እንድንዋደድ ነው። 📑 ፤📑 የወልድ ደግሞ እርሱ እንደወደደን ሌሎችን እንድንወድ ነው ! # የደሰታ ሀገሩ እግዚአብሔር ነው #የደሰታ ሀገሩ ኢየሱስ ነው #የደሰታ ሀገሩ የእሱን ትዕዛዝ መፈጸም ነው #የደሰታ ሀገሩ ወንድምን መውደድ ነው 💫##ደስታ_በእርኩሰታችን_ውስጥ_ሳይሆን_በእግዚአብሔር_ቅድስና_ውስጥ_ነው_የሚገኘው !
262
🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿
በጣም ጥሩ መልዕክቶች ያሉባቸው መንፈሳዊ 🍿ፊልሞች የሚታላለፉበት YouTube ቻናል ልጠቁማችሁ...
ለሌሎችም share አድርጉ 🙏
በዚህ link ግቡ https://youtube.com/@rehobothartram?si=Y70YhEQ7mpLXhvyV
🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿🍿
262
Repost from Christian Mezmur - ክርስቲያን መዝሙር
ሳይረፍድ ብዙ ሳንከስር የእውነት እንሁን!እግዚአብሔር እያዘነ የምንገነባው ገፅታ የትም አያደርሰንም! በልባችን እንለወጥ! ያልተኖረ የታይታ ገፅታ ምን በሰው ዘንድ ጎሽ ቢያሰኝና ቢገነባ ጊዜ ቆጥሮ ባዶነቱ ይገለጣል ከትወና ህይወት አያልፍም! ብልህ እንጂ ብልጣብልጥ አንሁን! እርሱ ጎሽ ይበለን ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው! ከተገለጠው ድርጊታችን በላይ የልብ አካሄዳችን የነገ ፍሬያችንን ይወስናል! የተገለጠው ድርጊታችን ለሰው ይታያል። ልባችን ግን በእግዚአብሄር ዘንድ ታይቶ ይመዘናል። ምንም ነገር ስናደርግ የምናደርግበት መንፈስ ከድርጊታችን በላይ በእግዚአብሄር ዘንድ ዋጋ አለው ያልተኖረ የታይታ ብቻ ገፅታ ምን በሰው ዘንድ ጎሽ ቢያሰኝና ቢገነባ ጊዜ ቆጥሮ ባዶነቱ ይገለጣል ከትወና ህይወት አያልፍም! እግዚአብሔር እያዘነ የምንገነባው ገፅታ የትም አያደርሰንም። በልባችን እንለወጥ! ብልህ እንጂ ብልጣብልጥ አንሁን! ሳይረፍድ ብዙ ሳንከስር የእውነት እንሁን! የእውነት እንኑር! አንሸነጋገል! የእውነት ልብና ቅንነት ገፅታችን ይሁን! እርሱ ጎሽ ይበለን ሌላው ሁሉ ትርፍ ነው። በእውነት መንፈስ ተባረኩ! ©Hanna Tekle @christian_mezmur
262
Repost from N/a
“እንጀራንም አንሥቶ አመሰገነ ቆርሶም ሰጣቸውና፦ ስለ እናንተ የሚሰጠው ሥጋዬ ይህ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— ሉቃስ 22፥19
“ጌታ ኢየሱስ አልፎ በተሰጠበት በዚያች ሌሊት እንጀራን አንሥቶ አመሰገነ፥ ቆርሶም፦ እንካችሁ ብሉ፤ ይህ ስለ እናንተ የሚሆን ሥጋዬ ነው፤ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥24
“እንደዚሁም ከእራት በኋላ ጽዋውን ደግሞ አንሥቶ፦ ይህ ጽዋ በደሜ የሚሆን አዲስ ኪዳን ነው፤ በጠጣችሁት ጊዜ ሁሉ ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት አለ።”
— 1ኛ ቆሮንቶስ 11፥25
262
ሙሉው ...ይሄው
በጣም አስተማሪ የሆና መንፈሳዊ ፊልም አይታችሁ ተባረከቡት ....
ሙሉውን ...
ዳቩክ (Davuk) ✨🎬
በ 2018 ምሩቃን (GC_BENHANAN) የተዘጋጀ አጭር መንፈሳዊ ፊልም 🎥
262
በጣም አስተማሪ የሆና መንፈሳዊ ፊልም አይታችሁ ተባረከቡት ....
ሙሉውን ...
ዳቩክ (Davuk) ✨🎬
በ 2018 ምሩቃን (GC_BENHANAN) የተዘጋጀ አጭር መንፈሳዊ ፊልም 🎥
🙏ከቻልኩ ሙሉውን እለቃለሁ 🙏🙏
262
ድነት ጥሩ ሰውን የተሻለ ፤ የታመመን ሰው ደህን የማድረግ ጉዳይ አይደለም።
የሞተውን ሰው በክርስቶስ ሕያው የማድረግ እንጂ ።
✍️ ስቴቨን ለውሰን
📖ኤፌሶን 2:1📖
“ 1 እናንተ በበደላችሁና በኀጢአታችሁ ምክንያት #ሙታን ነበራችሁ፤...”
በሽተኞች አልነበርንም ፤ ቃሉ ሙታን ነበራችሁ ነው የሚለው ፤ ከሞት በክርስቶስ አምልጠናል!
262
የሩቅ አላሚ ነኝ ግን የቅርብ አዳሪ
የሩቅ አሳቢ ነኝ ግን የቅርብ ተጓዥ ነዋሪ ሰፋሪ
የፈቃድን ሚስጥር እሻና በብርቱ
ግን ልቤ ሊኖረው አወይ ማመንታቱ
በውስጥ ማንነቴ በራለሁ ከሰማይ
ስጋዬ ጎትቶ ያወርደኛል ከላይ
ፍቅርህ ትዝ ሲለኝ ውስጤ ይነካና
አይኔ እንባ ያፈሳል ትናፍቀኝና
ነፍሴ ተነቃቅታ አንተኑን ስታስብ
መንፈሴ ወዲያውኑ ይጋልባል ሽቅብ
መንፈሳዊነቴ ያኔ ሲበረታ
ሀሌሉያ እያልኩ ከምድር ስፋታ
ያልማል ይመኛል ሰማዩን ምናቤ
ከደመናው በላይ ይሄዳል ሀሳቤ
ያን ግዜ እንዳልደክም ምዬ ተገዝቼ
ፈለግህን ልከተል ለራስ ቃል ገብቼ
በአለም ማዕበል ሲመታ ግለቴ
መች ይታወቀኛል ሲደክም ህይወቴ።
በኑሮ ገጠመኝ ከፍና ዝቅ ስል
በወጣሁበት ልክ እየኝ ሳሽቆለቁል
በረታሁኝ እያልኩ ዝዬ እገኛለሁ
በሁለቱ ክበብ ላይ እሽከረከራለሁ
ከዚህ ሟች ስጋዬ የሚለየኝ ማነው?
ጥማቴም ረሀቤም አንተን ለመምሰል ነው
እንደማትጥለኝ በእርግጥ አውቃለሁ
ግን አንዳንዴ ራሴ ማመን እፈራለሁ።
ድሮም ፀጋህ እንጂ እኔ የቻልኩት ምንድነው?
ሀይልን በምትሰጠኝ ሁሉን እችላለሁ
ድሮም ፀጋህ እንጂ እኔ የቻልኩት ምንድነው
ሀይልን በምትሰጠኝ ሁሉን እችላለሁ
ቢዝል ቢደክም ስጋዬ ዳግም ሊበረታ
በድካሜ ምትራራ ደጉ የኔ ጌታ
እጄን በእጅህ እንደያዝክ እስከ መጨረሻው
እያገዝከኝ በፀጋህ ዘልቄ እሄዳለሁ
ፀጋህ እየረዳኝ እያገዝከኝ
ባንተ ሁሉን እችላለሁ እችላለሁኝ
