Haala Ilaalcha Ortodoksii(ኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ)
Open in Telegram
Waa'ee Mana Kiristaanaa Fi Biyya Keenyaa Haala Ilaalcha Ortodoksiin Hubachuu የቤተክርስቲያናችንና ሀገራዊ ሁኔታዎችን በኦርቶዶክሳዊ ማዕቀፈ እሳቤ መረዳት
Show moreThe country is not specifiedThe category is not specified
273
Subscribers
-124 hours
-57 days
-1530 days
Posts Archive
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ኃላፊው የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ ስለሆኑ ከፍተኛ የኦርቶዶክስ ጥላቻ አለባቸው - የወረዳው ቤተ ክህነት
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአመካ ወረዳ ቤተ-ክህነት ጽሕፈት ቤት ጉዳዩን አስመልክቶ ይፋዊ አቤቱታውን ባቀረበበት ደብዳቤ ላይ በቦታው የሚኖሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ለዘመናት አስከሬን ተሸክመው ከ20 ኪሎ ሜትር በላይ አቋርጠው በመጓዝ ለብዙ ዓመታት መቆየታቸውን አስታውሷል።
አሁን ግን ቁጥራቸው ከ300 በላይ የሆነ ምዕመናን በአካባቢያቸው የቤተክርስቲያን መስሪያና የመቃብር ቦታ ከግለሰብ በስጦታ ማግኘታቸውን ገልጿል።
ቦታው ከሌሎች የእምነት ተቋማት ጋር የድምጽ መረባበሽ እንዳይኖር ህጋዊና ርቀቱን ጠብቀው በስጦታ ባገኙት ቦታ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልፆ ይሁን እንጂ የሌሎች እምነት ተከታዮች ለወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል ብሏል።
ቤተክህነቱ በአካባቢው የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከተዮች እርስ በእርስ በመከባበርና በሰላም አብረው የሚኖሩ ቢሆንም፣ የአመካ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ በመሆናቸው እና ከፍተኛ የሃይማኖት ጥላቻን በሚገልጽ መልኩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጥር እንድታፈርስና በአካባቢው ምንም ዓይነት ልማት እንዳይካሄድበት በማድረግ ከፍርድ ቤት አሰራር ውጪ እና ያለ አግባብ ሥልጣናቸውን በመጠቀም ፍትሕ እንዳናገኝ አድርገዋል ሲል አስታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ የተደራጁ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተዮች ይዞታውንና ንብረቱን ይጠብቁ በነበሩ 6 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ላይ ድገተኛ ጥቃት በመሰንዘር ከፍተኛ አካላዊ ድብደባ’ ፈጽመውባቸዋል ሲል ገልጿል።
በተጨማሪም ድምጽ በሌለው መሣሪያ አማካይነት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ያለ ሲሆን፣ በቦታው ላይ የነበረውን ሕንፃ በማፍረስና ንብረቱንም ሙሉ በሙሉ በማፍረስ ከፍተኛ ውድመት አድርሰዋል ብሏል።
በመሆኑም የወረዳው አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በድርጊቱ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ወንጀለኞችን በፍጥነት ለሕግ እንዲያቀርብና ተገቢው አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ይገባል ሲል ጠይቋል።
አክሎም ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን አስፈላጊውን ሕክምና እንዲያገኙና ለወደመው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በሕግ አግባብ እንዲከፈላቸው እንዲሁም በፈረሰው ቤት ምትክ ሌላ ቤት ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ቤተ-ክህነቱ ጠይቋል።
የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ለቤተ ክርስቲያኗና ለምዕመናን ተገቢው የሕግ ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህ አቤቱታውንም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ለክልሉ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ለሀዲያ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መመሪያ፣ ለዞኑ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዲሁም ለሀዲያ እና ስልጤ ሀገረስብከት ግልባጭ እንደላከ በደብዳቤው ጠቅሷል።
#ቦርከና_ዜና
#ቅዱስ_ቂርቆስና_እናቱ_ቅድስት_ኢየሉጣ (#ሐምሌ_19)
ሐምሌ ዐሥራ ዘጠኝ በዚህች ቀን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስና እናቱ ኢየሉጣ በሰማዕትነት መከራ ተቀበሉ። ይህም ሕፃን ዕድሜው ሦስት ዓመት ሲሆነው ከሮሜ አገር ወደሌላ ሀገር እናቱ ይዛው ሸሸች በዚያም የሸሸችውን መኰንን አገኘችው።
ሰዎችም ነገር ሠሩባት ወደርሱ አስቀረባትና ስለ አምልኮ ጠየቃት እርሷም መኰንን ሆይ ዕድሜው ሦስት ዓመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው።
ሕፃኑም ወደአለበት ጭፍራውን ልኮ ወደርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕፃኑም መልሶ አዎ ለእኔ ደስታ ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ልቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው መጽሐፍ ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው እግዚአብሔር ኃይልና ንግግርን ሰጥቶታልና ብዙ ተናገረ በዚያም ያሉትን እስከ አስደነገጣቸው ድረስ ንጉሡን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሣ አደነቁ።
መኰንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ሥቃይ ታላላቆች የማይችሉትን ታላቅና አስጨናቂ የሆነ ሥቃይን አሠቃየው እናቱንም ከርሱ ጋር እንደ እርሱ አሠቃያት እግዚአብሔርም ያለምንም ጉዳት ያነሣቸው ነበር። ብዙዎች አሕዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም አምነው በሰማዕትነት ሞቱ የሰማዕትነትንም አክሊል ተቀበሉ።
በሕፃኑ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቆችና ተአምራቶችንም አደረገ ብዙዎች በሽተኞችንም አዳናቸው።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ በታላቅ የናስ ጋን ውስጥ ውኃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጐድጓድ ሆነ ያን ጊዜም ፍርሀትና የሃይማኖት ጉድለት በእናቱ ላይ ደረሰባት ሕፃኑም ስለ እናቱ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ።
ያን ጊዜ ጌታችን ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አየች ከዚህም በኋላ ጸናች እግዚአብሔርንም አመሰገነችው ልጅዋንም ልጄ ሆይ ከእንግዲህ አንተ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው።
ያቺ ከኔ የተወለድክባትም ቀን የተባረከች ናት አለች ወደዚያ ወደ ጋኑ ውስጥ በገቡ ጊዜም የውኃው ፍልሐት እንደ ንጋት ጊዜ ውርጭ ቀዘቀዘ ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና።
ከዚህም በኋላ መኰንኑ ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው እንዲጐትቷቸው አዘዘ ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ አዳናቸው መኰንኑም በታላቅ ሥቃይ ያሠቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው።
ያን ጊዜም ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ሕፃኑ ቂርቆስ ወርዶ አጽናናው አረጋጋውም። ስሙን ለሚጠራና መታሰቢያውን ለሚያደርግ ቃል ኪዳን ሰጠው።
ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በከበሩ ሰማዕታት በጸሎታቸው ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
(#ስንክሳር_ዘወርኀ_ሐምሌ ➛ስንክሳር ዘተዋሕዶ ፌስቡክ ገጽ የተወሰደ)
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
ይድረስ ለቅዱስ ፓትርያርክ አባ ማቲያስ
ቅዱስ አባታችን ሆይ፤
በመጀመሪያ በልዑል እግዚአብሔር ስም ሰላምታችንን እያቀረብን፤ ይህን መልእክት ለመላክ የተገደድነው በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እየወረደ ያለው የመከራ ዶፍ ከቀን ወደ ቀን እየተባባሰ በመምጣቱ ምክንያት መሆኑን እንገልጻለን።
ለ ስምንት ዓመታት በየጊዜው የሚወጡ የ"እናዝናለን" መግለጫዎችን መስማትና ማንበብ ሰልችቶናል። እነዚህ መግለጫዎች የሕዝባችንን ሞት፣ ስደት እና የቤተ ክርስቲያናችንን ውድመት ሊያስቆሙልን አልቻሉም። ከቤተ ክህነት እስከ ቤተ መንግሥት ያሉትን ተፅዕኖዎች የምንረዳ ቢሆንም፣ ቅዱስነትዎ እንደ ቅዱሳን ሐዋርያት እውነትን መስክረው ቤተ ክርስቲያንን የማስቀጠል እና ልጆችዎን ከጥፋት የመታደግ መንፈሳዊና አባታዊ ሀላፊነት አለብዎት።
ሥርዐቱ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ላይ እያደረሰ ያለው ተፅዕኖ በመግለጫ እና በልምምጫ ሊቆም እንደማይችል ከእኛ ከልጆችዎ በላይ ጠንቅቀው ያውቃሉ ይረዳሉ።
ስለሆነም የልጆችዎ የጅምላ ፍጅት እና የቤተ ክርስቲያን ውድመት በእውነት የሚያሳስብዎ ከሆነ፤ ከዚህ በታች የተጠቀሱትን አማራጮች ተግባራዊ እንዲያደርጉልን በትሕትና እንጠይቃለን፦
1. ለዓለም አቀፍ ማኅበረሰብ ጉዳዩን ማሳወቅ፦
ሥርዐቱ በቤተ ክርስቲያናችን እና በልጆችዋ ላይ እያደረሰ ያለውን ፍጅት እና በደል በይፋ ለሚከተሉት አካላት በደብዳቤ እንዲያሳውቁልን፦
👉ለአኃት አቢያተ ክርስቲያናት
ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (UN) እና ለሰብአዊ መብት ምክር ቤት
👉ለዓለም አቀፍ ሃይማኖቶች ፓርላማ እና ለምክር ቤቶች
👉ለዓለም ሃይማኖትና እምነት ነጻነት ሲቪል ማኅበራት ኮሚቴ
👉ለዩኔስኮ (UNESCO)
👉ለዓለም አቀፍ ፍትሕ ፍርድ ቤት (ICJ)
👉ለአፍሪካ ኅብረት
👉ለዓለም ሀገራት መሪዎች እና ለዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ
2. መንፈሳዊ ውሳኔ መስጠት፦
ይህን ማድረግ የማይቻል ከሆነ፤ "ልጆቼን መጠበቅም ሆነ መታደግ አልቻልሁም" በማለት መንፈሳዊ ኃላፊነትዎን በመወጣት ወደ ገዳም (ለምሳሌ አቅራቢያ ወደሚገኘው ደብረ ሊባኖስ ገዳም) በመግባት በጸሎት እንዲወሰኑ።
እነዚህን እርምጃዎች መውሰድ ከኅሊና፣ ከታሪክ እና ከእግዚአብሔር ፍርድ ነጻ የሚያወጣ እርምጃ ነው ብለን እናምናለን።
ቅዱስ አባታችን ሆይ፥አሁን ባለው ሁኔታ የ"እናዝናለን" መግለጫ ብቻ እያወጣን እንቀጥላለን ብለው የሚያስቡ ከሆነ ግን እርስዎም ኦርቶዶክሳውያንን የማጥፋት መንግሥታዊ ፕሮጄክቱን ይደግፋሉ ወደ ሚለው ድምዳሜ ለመድረስ እንገደዳለን። አዎ የ"እናዝናለን"መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣
አጥፊን የማይከስስ እና ተጎጂዎችን የማያስክስ የማጭበርበርና ከገዳዮች ጋር የመተባበር ተምሳሌት የሆነ ልፍስፍስ መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣፣ ገዳዩን ሥርዐት የማይከስና ፍትሕን የማያሰፍን መግለጫ መስማት ሰልችቶናል፣እልቂታችንን የማያቆም መግለጫ መስማት ሰልችቶናል።
ለሁለም ይደርስ ዘንድ ሼር በማድረግ እንተባበር
https://t.me/Eyo21e
Repost from "!!!የድምፅ አልባዎች ድምፅ(The Voice Of Voiceless)!!!"
"ትውልዱ ኦርቶዶክስና አማራን እየተበቀለው ነው"~አስቴር በዳኔ
በኢትዮጵያ ምድር ኦርቶዶክስና አማራ ጠልነት የተራ ግለሰቦች ሳይሆን ፦
👉ህገ መንግሥታዊ ነው
👉 እንደ አንድ ወሳኝ ማኅበረሰባዊ ሕይወት መስተጋብር ይቆጠራል
👉 እምነታዊ ነው
👉 ሕዝባዊ ነው
ይኽች በኦርቶዶክስ ጠልነት ያበደች ሴት ስልክ ቁጥሯ +251947428444 ነው መደወል የሚፈልግ ካለ
Repost from Eotc Task Force
የጊዜ ጉዳይ ነው ወገኖቹ ላይ በሚፈጸመው የዘር ማጥፋት ወንጀል ውስጡ ያረረ ወጣት አንድ ቀን መነሳቱ አይቀሬ ነው።ደግሜ እናገራለሁ የጊዜ ጉዳይ ነው ወጣቱ እንደ አንድ ልብ መካሪ እንደ ቃል ተናጋሪ ሆኖ ይነሳል በዓይን ጥቅሻ በከንፈር ንክሻ ይግባባል።የተገፋ ወተት ቅቤ ይወጠዋል። ተገፍተናል በገዛ ሀገራችን ላይ ከ11ቀን ህጻን ጀምሮ እስከ 90 ዓመት አዛውንት በጅምላ ተጭፍጭፈናል፣ተገድለን እንኳ እሬሳችን ማረፍ አልቻለም በእሳት ተቃጥሏል፣ዓለምን የናቁ ገዳማውያን በእስላም ሀገራት ድሮኖች ተጨፍጭፈዋል፣ሆን ተብሎ ታስቦበት በኢኮኖሚ እንድንደቅ ተደርጓል ሕዝባችን በየቦታው ለልመና ተዳርጓል።አዎ በተገው አጋጣሚ ሁሉ ወጣቱን ማንቃት ማበራታት ማጀገን ያስፈልጋል።እግዚአብሔር ሁሌም ከተገፉት ጋር ነው እንደሚረዳን አንጠራጠርም።ብቻ እኛ እንንቃ ከልባችን እንሥራ እንደጋገፍ፣ከመለያየት ይልቅ ኅብሩትን፣ከማስመሰል ይልቅ እውነትን ገንዘብ እናድርግ።ያኔ እግዚአብሔር በመካከላችን ይገኛል።
https://t.me/EotcTaskForce
Repost from Eotc Task Force
+1
ይድረስ ለሀዲያ ስልጤ ሀገረስብከት፣ለአመካ ወረዳ ኦርቶዶክሳውያን
ምንም እንኳ የሚፈጸምብን ጥቃት ከፌዴራል መንግሥት ትእዛዝ ሰጪነት የሚፈጸም ቢሆንም የአጥፊዎችን ስም ማወቅ ያስፈልጋልና፦
👉ጥቃቱን የፈጸሙ አካላት መሉ መረጃ(ስም፣ፎቶ ግራፍ፣ስልክ ቁጥር አድራሻ)
👉 አከባቢው ላይ ያለው ቸርች ከእነ ፓስተሮቹ
👉ጥቃቱን ማስቆም ሲገባቸው ዝም ያሉ የፕሮቴስታንት ሽማግሌዎች ስምና ፎቶ ግራፍ ቢቻል ስልክ ቁጥርም ቢታከልበት
👉 የወረዳው አስተዳዳሪ፣የወረዳው ፖሊስ መምሪያ፣የቀበሌው አስተዳዳሪ ሙሉ መረጃ(ስም፣ፎቶ ግራፍና ስልክ ቁጥር)
እንድትሰጡን እናሳስባለን።
https://t.me/EotcTaskForce
Repost from ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)
👆👆👆አንዳንድ የፕሮቴስታንት ዲኖሚኔሽኖች ጨንብላቸውን ገልጠው ጅሃድ ጀምረዋል!
"ኢየሱስ" እያሉ ክርሰቲያን እየመሰሉ የማጭበርበር ዘመን እያበቃ መሆኑ ነው!
Repost from Addis Maleda - አዲስ ማለዳ
በሀዲያ ዞን በአንድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ይዞታ እና ተከታዮች ላይ በሌላ ሀይማኖት ተከታዮች ጥቃትንና ውድመት መድረሱን ተከትሎ የአመካ ወረዳ ቤተክህነት የሕግ የበላይነት ይከበር ሲል ጥሪ አቀረበ
ዓርብ፣ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም (#አዲስ_ማለዳ)
በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሀዲያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአመካ ወረዳ ቤተ-ክህነት ጽሕፈት ቤት በ ወረዳው “የታኛኛው በታራ” በተባለ ልዩ ቦታ በሚገኝ የቤተ ክርስቲያን ይዞታ ላይ ጥቃትና የንብረት ውድመት “በፕሮቴስታንት አማኞች” ደርሷል ሲል አስታወቀ።
ጉዳዩን አስመልክቶ ይፋዊ አቤቱታው በደብዳቤ ለተለያዩ ተቋማት ልኳል። የወረዳው ቤተክህነት በደብዳቤው ላይ እንደገለጸው በቦታው የሚኖሩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ለዘመናት ሲጠቀሙበት የነበረውንና በአሁኑ ወቅት ቁጥራቸው ከ300 በላይ ለሚሆኑ ምዕመናን አገልግሎት የሚሰጠውን የጸሎት፣ የመሰብሰቢያና የመቃብር ስፍራ በሕጋዊ መንገድ አጥር በማጠርና ለበጎ አድራጎት ሥራዎች በማዋል ሰላማዊ እንቅስቃሴ ሲያደርጉ ቆይተዋል።
ቦታው ከሌሎች የእምነት ተቋማት ጋር የድምጽ መረባበሽ እንዳይኖር ርቀቱን ጠብቀው በስጦታ ባገኙት ቦታ ላይ የተገነባ መሆኑን ገልፆ ይሁን እንጂ የሌሎች እምነት ተከታዮች ለወረዳው ሰላም እና ጸጥታ ቢሮ ተቃውሟቸውን አቅርበዋል ብሏል።
አክሎም በአካባቢው የሚኖሩ የልዩ ልዩ ሃይማኖት ተከተዮች እርስ በእርስ በመከባበርና በሰላም አብረው የሚኖሩ ቢሆንም፣ የአመካ ወረዳ የሰላምና ፀጥታ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የፕሮቴስታንት እምነት ተከተይ በመሆናቸው እና “ከፍተኛ የሃይማኖት ጥላቻን” በሚገልጽ መልኩ የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን አጥር እንድታፈርስና በአካባቢው ምንም ዓይነት ልማት እንዳይካሄድበት በማድረግ ከፍርድ ቤት አሰራር ውጪ እና ያለ አግባብ ሥልጣናቸውን በመጠቀም ፍትሕ እንዳናገኝ አድርገዋል ሲል አስታውቋል።
ይህንንም ተከትሎ ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 7:00 ሰዓት ላይ የተደራጁ ‛‛የፕሮቴስታንት እምነት ተከተዮች ይዞታውንና ንብረቱን ይጠብቁ በነበሩ 6 የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከተዮች ላይ ድገተኛ ጥቃት በመሰንዘር "ከፍተኛ አካላዊ ድብደባ’’ ፈጽመውባቸዋል ሲል ገልጿል።
በተጨማሪም “ድምጽ በሌለው መሣሪያ” አማካይነት ከፍተኛ ጉዳት አድርሰዋል ያለ ሲሆን፣ በቦታው ላይ የነበረውን ሕንፃ በማፍረስና ንብረቱንም “ሙሉ በሙሉ” በማፍረስ ከፍተኛ ውድመት አድርሰዋል ብሏል።
በመሆኑም የወረዳው አስተዳደር ጽሕፈት ቤት በድርጊቱ ላይ ከፍተኛ ትኩረት በመስጠት ወንጀለኞችን በፍጥነት ለሕግ እንዲያቀርብና ተገቢው አስተማሪ እርምጃ እንዲወሰድባቸው ይገባል ሲል ጠይቋል።
አክሎም ጉዳት የደረሰባቸው ምዕመናን አስፈላጊውን ሕክምና እንዲያገኙና ለወደመው ንብረት ተመጣጣኝ ካሣ በሕግ አግባብ እንዲከፈላቸው እንዲሁም በፈረሰው ቤት ምትክ ሌላ ቤት ተገንብቶ ለአገልግሎት እንዲበቃ ቤተ-ክህነቱ ጠይቋል።
በመጨረሻም የሃይማኖት እኩልነትና ነፃነት እንዲረጋገጥ፣ የሕግ የበላይነት እንዲከበርና ለቤተ ክርስቲያኗና ለምዕመናን ተገቢው የሕግ ከለላ እንዲሰጥ ጥሪ ያቀረበ ሲሆን ይህ አቤቱታውንም ለማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ሰላምና ጸጥታ ቢሮ፣ ለክልሉ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ፣ ለሀዲያ ዞን ሰላም እና ጸጥታ መመሪያ፣ ለዞኑ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ እንዲሁም ለሀዲያ እና ስልጤ ሀገረስብከት ግልባጭ እንደላከ በደብዳቤው ጠቅሷል።
ተጨማሪ ዜናዎችንና አዳዲስ መረጃዎችን ለማግኘት የማሕበራዊ ሚዲያ ገጾቻችን ይጎብኙ፦
YouTube ➲ t.ly/vSgS
Telegram ➲ t.ly/SOXU
Facebook ➲ t.ly/flx8
Twitter ➲ t.ly/mxA
Repost from Eotc Task Force
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የድህናታችን ምክንያት ናትና መጥፋት አለባት ብለው ወስነው ነው በጅምላ እየጨፈጨፉን ያሉት።ጭፍጨፋው የሚመሩት ጠቅላይ ሚንስትሩ ናቸው።ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ ኦርቶዶክስን ያንቋሽሻሉ ለጥቃት የሚያጋልጡ ንግግሮችን ያደርጋሉ።
Repost from ኢትዮ ቱንቢ ሚዲያ Ethio Tunbi (Official)
የገዳማውያኑ ጥቃት ሥርዓታዊና ጥላቻን ያዘለው ስልት ቀጣይ ምዕራፍ ነው!
በወቅታዊ ጉዳይ ላይ ከእናት ፓርቲ የተሰጠ የአቋም መግለጫ
ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋድ 4:00 ላይ በአማራ ክልል፣ ደቡብ ወሎ ዞን፣ ቦረና ወረዳ የሚገኘው በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የዓባይ ቅድስት አርሴማ ገዳም ላይ የድሮን ጥቃት ተፈጽሞ 2(ኹለት) መነኮሳይያት እናቶች ወዲያው ሲገደሉ፣ 14(አሥራ አራቱ) እናቶች ደግሞ ክፉኛ ቆስለው መካነ ሰላምና ደሴ ሆስፒታል ተወስደዋል። በጥላቻና ኾነ ተብሎ በሚመስል መልኩ በተፈጸመው ጥቃት የገዳማውያኑ የዓመት ቀለብ እህልና ጥራጥሬ ሙሉ በሙሉ የወደመ ሲኾን፣ ተግባር ቤት፣ ማብሰያ እቃዎች፣ የውሐ ማጠራቀሚያ የኮንክሪት ታንከር፣ የውሐ ማስተላለፊያ ቱቦዎች ሙሉ በሙሉ ወድማል። "በገዳሙ ሥርዓት የጠዋት 3:00 ፀሎት አድርሰን ኹሉም ወደተመደበበት ሥራ ሲሠማራ ድሮን የምትባለው ስትዞርና ድምጿን ሰምተናል፣ አይተናታል። እኛ ገዳማውያን ነን መቸም ቴክኖሎጂ ነው ያዩናል ምንም የሚያጠራጥርና የሚያስፈራን ነገር የለም ብለን ሥራችንን ቀጠልን" የሚሉት እማኝ "ነገር ግን እኛ እንዳስብነው አልነበረም ቆይተው ለሥራ በተሰበሰብንበት መዓት አወረዱብን፣ ያን የመሰለ ጭካኔ ለምን ማድረግ እንዳስፈለጋቸው ማሰብም ማለምም ይከብዳል። በተለይ የቆሰሉት ሲታዩ የሞቱት ይሻላል ያስብላል" ይላሉ።
ገዳሙ እጅግ ከባድ በረሃ ላይ ያለ ነው። በዙሪያው የሚገኝ ታጣቂም ይኹን ወታደር አናውቅም። እንግዲኽ ገዳሙ የቆመውም በእነዚኹ ወጣት መነኮሳይያት እናቶችች ድካም ነበር። ሠሪው ከተገደለ፣ አካሉ ከጎደለና የዓመት ቀለቡ ከወደመ ቀሪውንም የመግደል ያኽል ነው። ተጠንቶ የተደረገ ይመስላል ይላሉ ሌላው እማኝ።
እናት ፓርቲ ይኽ እብሪት የተላበሰ ድርጊት ከድግግሞሹ፣ እያስከተለ ከሚገኘው ጉዳትና በሌሎች አካባቢዎች ደግሞ በታጣቂዎች ሽፋን በእምነቱ ተከታዮች፣ አገልጋዮችና ገዳማት ላይ እየተፈጸመ ያለው ጥቃት ተራ ስህተት ሳይኾን ሥርዓታዊና ከጥላቻ የመነጨ ብሎም የአጥፍቶ መጥፋት ተግባር እንደኾነ በጽኑ ያምናል፤ ድርጊቱንም በጽኑ ያወግዛል። ለሞቱት ገዳማውያንም ሐዘኑን እንገልጻለን።
ስለኾነም፣
1. መላው ኢትዮጵያውያን ይኽን የአጥፍቶ ጠፊ የሽብር ድርጊት በአንድነት እንዲያወግዝ እንጠይቃለን።
2. መንግሥት ለድርጊቱ ሙሉ ኃላፊነቱን እንዲወስድና ድርጊቱ ሲፈጸም የሚያሳይ የፎቶና የቪዲዮ መረጃ ለሕዝብ ይፋ እንዲያደርግ አጥብቀን እንጠይቃለን፡፡
3. ሀገርን ከጥቃት ለመጠበቅ የተቋቋሙ ተቋሟት ሕዝብን ጅምላ ጨረሽ ወደመኾን መሸጋገራቸው መላው ሕዝባችንና ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ እንዲያውቀው እና አጥፊው አካል ተጠያቂ እንዲደረግ አጥብቀን እናሳስባለን፡፡
4. መላው ኢትዮጵያውያን በዚያ ሐሩር ለሀገርና ሕዝብ የሚፀልዩ ገዳማውያን ቀለባቸው እና የመጠጥ ውሐ በጥቃቱ ሙሉ በሙሉ በመውደሙ ቀሪዎቹ በረሃብና ጥም ከማለቃቸው በፊት እንዲደርስላቸው እንጠይቃለን።
ፈጣሪ አገራችን ኢትዮጵያንና ሕዝባን ይጠብቅ!
እናት ፓርቲ
ሐምሌ ፲፯ ቀን ፳፻፲፰ ዓ.ም
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
Repost from Eotc Task Force
ወሀቢያ በክርስቲያኑ ብቻ ሳይሆን በሱፊያ ሙስሊሞች ላይ ጦርነት ማወጅ እንደሚገባ ያውጃል
ክርስቲያኖችንና ይሁዶችን ከመዋጋታችሁ በፊት ሱፊያውን(ነባሩን ሙስሊም)ተዋጉ ይላል
