ch
Feedback
AAU - Muslim Students Union

AAU - Muslim Students Union

前往频道在 Telegram
6 948
订阅者
+1424 小时
+717
+48630

数据加载中...

标签云
无数据
有任何问题?请刷新页面或联系我们的客服
进出提及
---
---
---
---
---
---
吸引订阅者
六月 '26
六月 '26
+542
在104个频道中
五月 '26
+1 118
在57个频道中
Get PRO
四月 '26
+275
在41个频道中
Get PRO
三月 '26
+281
在20个频道中
Get PRO
二月 '26
+77
在5个频道中
Get PRO
一月 '26
+70
在6个频道中
Get PRO
十二月 '25
+112
在12个频道中
Get PRO
十一月 '25
+66
在11个频道中
Get PRO
十月 '25
+179
在18个频道中
Get PRO
九月 '25
+49
在3个频道中
Get PRO
八月 '25
+56
在5个频道中
Get PRO
七月 '25
+41
在3个频道中
Get PRO
六月 '25
+46
在6个频道中
Get PRO
五月 '25
+112
在12个频道中
Get PRO
四月 '25
+142
在11个频道中
Get PRO
三月 '25
+123
在17个频道中
Get PRO
二月 '25
+94
在9个频道中
Get PRO
一月 '25
+160
在15个频道中
Get PRO
十二月 '24
+257
在8个频道中
Get PRO
十一月 '24
+143
在8个频道中
Get PRO
十月 '24
+276
在20个频道中
Get PRO
九月 '24
+389
在17个频道中
Get PRO
八月 '24
+276
在0个频道中
Get PRO
七月 '24
+367
在0个频道中
Get PRO
六月 '24
+301
在7个频道中
Get PRO
五月 '24
+382
在20个频道中
Get PRO
四月 '24
+412
在12个频道中
Get PRO
三月 '24
+441
在7个频道中
Get PRO
二月 '24
+538
在31个频道中
Get PRO
一月 '24
+374
在10个频道中
Get PRO
十二月 '23
+348
在7个频道中
Get PRO
十一月 '23
+197
在8个频道中
Get PRO
十月 '23
+32
在2个频道中
Get PRO
九月 '23
+21
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+32
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+74
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+120
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+76
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+79
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+264
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+131
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+24
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+252
在0个频道中
日期
订阅者增长
提及
频道
29 六月0
28 六月+15
27 六月+48
26 六月+15
25 六月+12
24 六月+2
23 六月0
22 六月+4
21 六月+10
20 六月+6
19 六月+7
18 六月+21
17 六月+69
16 六月+14
15 六月+14
14 六月+126
13 六月+69
12 六月+37
11 六月+19
10 六月+29
09 六月+6
08 六月+1
07 六月+3
06 六月0
05 六月0
04 六月0
03 六月0
02 六月+13
01 六月+2
频道帖子
የሐረማያ፣ AASTU እና አሶሳ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ውይይት በሚደረግበት ታሪካዊ የቲክቶክ መድረክ ለመሳተፍ ተሰናድተዋል። እናንተስ? አንተስ አንቺስ?!
+2
የሐረማያ፣ AASTU እና አሶሳ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄዎች ውይይት በሚደረግበት ታሪካዊ የቲክቶክ መድረክ ለመሳተፍ ተሰናድተዋል። እናንተስ? አንተስ አንቺስ?!

2
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በምርቃቷ ቀን "ሪቫንሽ ላይ የዩኒቨርስቲውን ሎጎ አላደረግሽም!" - በማለት ከእስር ቤት እንድትቆይ ለተደረገችዋ እህት የተላከ ደብዳቤ !
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በምርቃቷ ቀን "ሪቫንሽ ላይ የዩኒቨርስቲውን ሎጎ አላደረግሽም!" - በማለት ከእስር ቤት እንድትቆይ ለተደረገችዋ እህት የተላከ ደብዳቤ !
634
3
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በምርቃታቸው ቀን የታሰሩትን የዩኒቨርሲቲውን ሙስሊም ተማሪዎች ቤታቸው ድረስ በመሄድ ዘየረ ! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ "ሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ የለም!"+2
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት በምርቃታቸው ቀን የታሰሩትን የዩኒቨርሲቲውን ሙስሊም ተማሪዎች ቤታቸው ድረስ በመሄድ ዘየረ ! አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ "ሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ የለም!" - በሚል ምክንያት 12 ሙስሊም ተማሪዎችን በምርቃታቸው ቀን እንዲታሰሩ በማድረግ የደስታ ቀናቸውን ከእስር ቤት እንዲያሳልፍ ማድረጉ ይታወሳል። ተማሪዎቹ ትላንት አመሻሽ ላይ የተፈቱ ሲሆን የዩኒቨርስቲው ጀመዓ ከተማሪዎቹ ቤት በመሄድ በዛሬው እለት ዚያራ አድርጓል። የመጀመሪያ ዚያራ ለተደረገባት ታሳሪ እህት ከጀመዓው በኩል "ጥያቄ አለን!" - የሚል ኬክ፤ "ኒቃቧን እንደለበሰች ትማራለች!" - የሚል ሪቫን እና ባይንደር አንዲሁም ከጀመዓው በኩል የተላከ ደብዳቤ በስጦታ መልክ ደርሷታል። ተማሪዋም "ምርቃቴ ትላንት ሳይሆን ዛሬ ነው። ነፃነትን ከሚነፍገው እና እኩልነት ከሚፀየፈው ሰፊ አዳራሻቸው ይህች ፍትሕ የሰፈነባት ጠባብ ክፍል የተሻለች ናት። ሕመሜን እየተጋራ ስለመብቴ አብሮኝ ከሚታገል ጋር መዋል ምርቃትን ያደምቃል። በጣም ደስተኛ ነኝ። ከድግሪዬ በላይ ጀመዓዬ ስላለ አልሐምዱሊላህ። አላህ ድላችንን ያቅርብ!" - የሚልን መልዕክት አስተላልፋለች። እንዲነጥቁን የምንፈቅደው ደስታ የለንም። በነኩን ቁጥር ተሳስበን፣ ተሰባስበን፣ በአንድነት ራሳችንን እንሰራለን። በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ ብንሆንም ስለመብቶቻችን መጠየቅን አናቆምም፤ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ። ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው።
817
4
Story and Profile challenge ! ! ! ከላይ ያለውን ምስል ስቶሪ እና ፕሮፋይል እናድርግ። ለነገው ፕሮግራም በአንድ ልብ በአንድነት እንሰለፍ። ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው ! ! !
Story and Profile challenge ! ! ! ከላይ ያለውን ምስል ስቶሪ እና ፕሮፋይል እናድርግ። ለነገው ፕሮግራም በአንድ ልብ በአንድነት እንሰለፍ። ይህ የጥያቄ አለን ትውልድ ነው ! ! !
1 036
5
የአዳማ እና ወራቤ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች በነገው ታሪካዊ የቲክቶክ መድረክ ለመታደም ዝግጁ ነን ብለዋል። እናንተስ? አንቺስ? አንተስ? ነገ ሰኞ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም+1
የአዳማ እና ወራቤ ዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች በነገው ታሪካዊ የቲክቶክ መድረክ ለመታደም ዝግጁ ነን ብለዋል። እናንተስ? አንቺስ? አንተስ? ነገ ሰኞ ከምሽቱ 3:00 ጀምሮ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት የቲክቶክ ገፅ አይቀርም። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ታሪካዊ ዳራ፤ ሕጋዊ መሠረት እና መፍትሔዎቹ ውይይት ይደረጋል።
1 102
6
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ነገ ሰኞ ከምሽቱ 3:00 ላይ ነው! ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ታሪካዊ ዳራ፤ ሕጋዊ መሠረት እና አሁናዊ ሁኔታ ከመፍትሔ ጋር በጥልቀት ይዳሰሳል። የድምፃችን ይሰማው ታ
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ነገ ሰኞ ከምሽቱ 3:00 ላይ ነው! ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ታሪካዊ ዳራ፤ ሕጋዊ መሠረት እና አሁናዊ ሁኔታ ከመፍትሔ ጋር በጥልቀት ይዳሰሳል። የድምፃችን ይሰማው ታጋይ ሙባረክ አደም፤ ጠበቃው ሙስጠፋ ሺፋ፤ የንፅፅር መምህሩ የሕያ ኢብኑ ኑሕ፤ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊው ሁሴን ዩሱፍ በመድረኩ ላይ ሀሳቦቻቸውን ያንፀባርቃል። ፨ ፖስተሩን በስቶሪዎቻችን ላይ እናጋራ፤ ፕሮፋይልም እናድርግ ፨ የዩኒቨርስቲ ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አጋሩ ፨ የሀይስኩል ጀመዓዎች መልዕክቱን አድርሱ ፨ በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ ሀገር ያላችሁ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕናዎች፤ ኡስታዞች እና ዳዒዎች መልዕክቱን ለሁሉም አድርሱ ሁሉም ተጋባዥ ነው። አጀንዳው የሁሉም ነውና ሁሉም ይገኝ። ተማሪ፣ የተማሪ ወላጅ፣ መምህር፣ የመንግስት ሰራተኛ ወዘተ ... ማንም እንዳይቀር። 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June) ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! ! @aaumsu
1 850
7
ነስሪያ ከ5ኪሎ ግቢ አሸናፊ ሆናለች። ታሪካዊው ሪቫንም በሽልማት መልክ የሚደርሳት ይሆናል። ጥያቄው፦ "በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?!" የነበረ ሲሆን መልሱ ደግሞ "አንጋፋው እና ራስገዙ አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ !" - የሚል ነው። ጥያቄ ቁጥር ሁለት is loading ... ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
1 299
8
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ከተሰጡት ምላሾች መካከል 4 ሙስሊም ጠልነት የበዛበት፤ ራስገዝ የሆነው፤ በሀገርም በአፍሪካም ስመጥር የተደረገው Addis Ababa University !
1 321
9
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ከተሰጡት ምላሾች መካከል 4 በጭቆና አንጋፋ የሆነው አዲስ አበበ ዩንቨርስቲ አሸናፊው ማን ይሆን?! @aaumsu
1 299
10
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ከተሰጡት ምላሾች መካከል 3 ኢትዮጵያ ውስጥ አሉ ከሚባሉ አንጋፋ እና ታዋቂ ዩኒቨርሲቲዎች ውስጥ አንዱ ነው ተብሎ ብዙ ጊዜ እንደትልቅ ጀብድ የሚወራለት በሃይመኖት ጥላቻ በተሞሉ አስተዳደሮች(የኔ እምነት እንጂ የእስልምና እምነት ተከታይ ተማሪዎች መብት ሊከበር አይገባም በሚሉ) የሚመራው አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ
1 291
11
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ከተሰጡት ምላሾች መካከል 2 እራስ ገዝ ነኝ ብሎ የሚፎክረው,የሙስሊም ጥላቻውን መቆጣጠር አቅቶት ጥላቻው ገንፍሎ ወጥቶበት በምርቃት ቀን ሣይቀር ያስተማራቸውን ተማሪዎች ደስታን ለማደፍረስና የጀመሩትን ትግል ለማደናቀፍ ውሃ በማይቋጥር ምክንያት ሙስሊም  ተማሪዎችን የሚያስረው, ስለ ዲሞክራሲ የሚደሰኩረውና ነገር ግን ፈፅሞ የማይተገብረው,  በሙስሊም ጠልነቱ ፈጽሞ አቻ ያልተገኘለት, የሴኩላሪዝም ጽንሠ ሀሣብ ፈጽሞ የተምታታበትና ሁሌም ሴኩላሪዝም ብሎ የሚያዜመው አ.አ.ዩ ነው:: ሌላ ማን ሊሆን???
1 297
12
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ከተሰጡት ምላሾች መካከል 1 🤘የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲቲቲቲቲ!!!!!😡😡😡 ​የጥቁር ህዝቦች የነጻነት ተምሳሌት የሳይንስና የዕውቀት ማማ... ነበር ይባላል! አሁን ግን የትኩረት አቅጣጫውንና የሳይንስ ሚዛኑን ሙሉ በሙሉ የቀየረ ይመስላል እንኳን ደስ አላችሁ ዩኒቨርሲቲያችን ከዓለም ታላላቅ የምርምር ተቋማት ተርታ ሊሰለፍ የሚችልበትን አዲስ ሳይንሳዊ ግኝት አግኝቷል በጨርቅ ላይ የሎጎ አለመኖር የተማሪዎችን እግር ወደ ወህኒ ያመራል!👏👏👏👏🤬 የሚል አስገራሚ ቀመር ፐፐፐፐፐ ​በሰው ልጅ ታሪክ ታይቶና ተሰምቶ በማያውቅ መልኩ የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ በሚል ሰበብ ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም በሚል የህጻን ልጅ ክምችች ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር መዳረግ ምን የሚሉት የ21ኛው ክፍለ ዘመን የዕውቀት ደረጃ ነው? ለመሆኑ ዩኒቨርሲቲው የመማሪያ ተቋም ነው ወይስ የብራንዲንግና የሎጎ ማስታወቂያ ድርጅት? አረ ተቃጠልኩ😭😭 በኔ ጊዜም ይሔ አለመፈጠሩን እንጃ ያአላሕሕ አላሕ የስራቹን እንደሚሰጣቹ አልጠራጠርም አረ የትሔደን እንተንፍስ  🤲🤞🤬 አሸናፊ ማን ይሆን?! @aaumsu
1 356
13
የሚያሸልም ጥያቄ፦ በሰው ልጅ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ "ሎጎዬን ከሪባናችሁ ላይ አላደረጋችሁም።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን ለእስር የዳረገው ዩኒቨርስቲ ማን ይባላል?! ሽልማቱ፦ የዩኒቨርስቲው ሎጎ ያለውና "ጥያቄ አለን!" - የሚል መልዕክት የሰፈረበት ሪቫን ነው። መልሳችሁን @Aaumuslimstudentsunion1 ላኩልን። ቀድሞ የመለሰ የሚሸለም ይሆናል። @aaumsu
1 525
14
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ህብረት ፕሬዝዳንት የተላለፈ መልዕክት! እአሰላም አለይኩም ወረህመቱላሂ ወበረካቱህ የተከበራችሁና የተወደዳችሁ ተመራቂ ወንድሞቼ እና እህቶቼ፤ የዛሬው ቀን በህይወታችን ውስጥ የማይረሳ ታሪካዊ ቀን ነው። በመጀመሪያ ብዙ ውጣ ውረዶችን አልፋችሁ ለዚህ ታላቅ ቀን ስላደረሳችሁ አላህ (ሱ.ወ) ምስጋና ይገባው። ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉 ብዙ ውጣ ውረድን እና ድካምን አልፋችሁ ዛሬ ላይ ደርሳችኋል። አላህ በስራችሁም ሆነ በዕድሜያችሁ ላይ በረከትን ያድርግ። ዛሬ የሕይወታችሁን አንድ ምዕራፍ ዘግታችሁ ወደ ሌላው የሕይወት ምዕራፍ የምትሸጋገሩበት የጉዞ መጀመሪያ ነው። በቀጣይ የሕይወት ጉዟችሁ፤ ግባችሁን በጽናት፣ በትጋት እና ታላቅ አሻራን በማስቀመጥ እንድትጓዙ ምክሬን እለግሳለሁ። የተፈጠርንበትን ዋና ዓላማ እያስታወሱ፣ ለዲናችንም ሆነ ለኡመተል ኢስላም ጠቃሚ የሆኑ ስራዎችን ለመስራት መትጋት ይጠበቅባችኋል። አላህ ቀጥተኛውን መንገድ ለሁላችንም ይወፍቀን። የዛሬው ደስታችን ከታላቅ ጀግንነት ጋር የተቆራኘ ነበር። ዛሬ የምረቃ መግቢያ በር ላይ፣ "ሃይማኖታዊ መብታችን ይከበር! የእህቶቻችን መብት ይመለስ!" የሚል ህጋዊ እና ፍትሃዊ ጥያቄን በሰላማዊ መንገድ ሪቫን በማንገባቸው ብቻ የታሰሩ ወንድም እና እህቶቻችን ነበሩ። ይህ ድርጊት ምረቃችንን የትግል እና የጽናት አውድማ አድርጎት ውሏል። እነዚህ ጀግና ወንድም እና እህቶቻችን ላለፉት ሁለት ዓመታት ያህል መብታችን ይከበር በማለት ሳይታክቱ እና ወደ ኋላ ሳይሉ ሲጠይቁ ቆይተዋል። ዛሬም ትምህርታቸውን አጠናቀው ከዩኒቨርሲቲው በክብር ሲወጡ እንኳ፣ ያንንኑ የፍትህ እና የመብት ጥያቄ እያሰሙ፣ ለእምነታቸው ዘብ እየቆሙ መውጣታቸው ምን ያህል ለዲናቸው ክብር ቀናዒ እና ጽኑ እንደሆኑ ያሳያል። ትምህርትን አጠናቆ ዲግሪ መቀበል ብቻ ሳይሆን፣ እስከ መጨረሻው ሰዓት ድረስ ለሃቅ እና ለፍትህ ፊት ለፊት መቆም ትልቁ ምረቃ መሆኑን ዛሬ በተግባር አሳይተውናል። ስለሆነም ዛሬ የታሰሩት ለእውነት፣ ለዲናቸው ክብር እና ለእህቶቻቸው መብት ነውና በእነሱ እጅግ ልንኮራ ይገባል። ይህንን የደስታ እና የጽናት ጊዜ እያከበርን፣ ቀጣዮቹን ጀግኖች እና የጀመዓችንን ምሰሶዎች ማመስገን እወዳለሁ፦ ● ዛሬ ታላቅ ጀግንነትንና ጽናትን ያሳያችሁ ወንድም እና እህቶቼ፦ ዛሬ የታሰራችሁት ለእውነት ነው። ታሪክ የማይረሳዉን ደማቅ አሻራ ጥላችኋል፤ አላህ ምንዳችሁን በላጭ አድርጎ ይክፈላችሁ። ሁሌም አንገታችሁን ቀና አድርጉ፣ ደስተኞች ሁኑ፤ በጀነት ጸጋም ተካፋይ ያድርጋችሁ። ● የህብረቱ ፕሬዝዳንት - ማህፉዝ ነጋሽ፦ እንኳን ደስ ያለህ! በፈተና እና በውጣ ውረድ ውስጥ ሆነህ ጀመዓዉን በጥበብ እና በብልሃት ስትመራ ቆይተሃል። ለእኔም ሆነ ለሌሎች በ5 ኪሎ እና በህብረቱ የመሪነትን እና የጽናትን ትምህርት አስተምረኸናል። ● የህብረቱ ምክትል ፕሬዝዳንት - አብዱልሀሚድ አህመድ፦ የመስጂዳችን ኢማም እና ኡስታዛችን በመሆንህ፣ ለጀመዓው ያበረከትከው አስተዋጽኦ እጅግ ከፍተኛ እና የተባረከ ነበር፤ እንኳን ደስ ያለህ። ● የህብረቱ ጸሐፊ - ዘይድ ሳዲቅ፦ እንኳን ደስ ያለህ ወንድሜ! የጀመዓው ደጋፊ እና የጀርባ አጥንት ነህ። በስራህ ታታሪ፣ ደከመኝ የማታውቅ ጀግና ነህ። በ4 ኪሎ ኢማምና አስቀሪ በመሆን ላሳለፍከው ጊዜ አላህ ስራህን ይቀበልህ። ● የ5 ኪሎ ተመራቂ ወንድም እና እህቶቼ፦ በተለይ በጀመዓ ተሳትፎ ላይ የነበራችሁ አንዋር፣ አብዱልፈታህ፣ ኡመር፣ ሐያት፣ ሆረኒየስ፣ ሂክማ፤ እንዲሁም አስቀሪዎቻችን ሙሐመድ በሺር፣ ካሊድ፣ ሀኒም፣ ሳራ... ሁላችሁንም እንኳን ደስ አላችሁ! አላህ ስራችሁን የተባረከ ያድርግ። በኒቃብ ጉዳይ ላይ ስታግሉ ለቆያችሁ፦ ወንድሞች (አብዱረህማን እና ሌሎችም) እና እህቶች (ሃሊ እና ሌሎችም) የዛሬው ትግል የናንተ የትናንት ተጋድሎ ፍሬ ነው። ላደረጋችሁት ጽናት ምስጋናችን ይድረሳችሁ። ● በ6 ኪሎ ዶርም አብረን ላሳለፍናቸው ወንድሞች፦ አሚር፣ አቡበከር፣ አብዱልሀሚድ፣ ሰልማን እና ሌሎችም፤ አላህ ደስታችሁን እጥፍ ያድርግላችሁ። የዛሬው የምረቃ ቀን የትግላችን ማብቂያ ሳይሆን፣ በየትኛውም የህይወት መስክ ዲናችንን እና መብታችንን ለማስከበር በጽናት የምንነሳበት አዲስ ምዕራፍ ነው። የተፈጠርንበትን ዋና ዓላማ እያስታወስን ለዲናችን እና ለኡመተል ኢስላም ጠቃሚ ስራዎችን ለመስራት አላህ ያብቃን። በአጠቃላይ በሁሉም ካምፓስ የምትገኙ ተመራቂዎች፣ አላህ ለስኬት ያብቃችሁ። Congratulations! 🎉🎉🎉🎉🎉🎉 ✍️ ወንድማችሁ ሙሐመድ ኢድሪስ
1 627
15
ከታሰሩት ወንድሞች መካከል ከአንዱ የተላለፈ መልዕክት፦   "አልሐምዱሊላህ! የማይረሳን የምርቃት ፕሮግራም አሳለፍኩ። የምቆጥረው፣ የማስታውሰው፣ ለልጆቼ የምነግረውን ታሪክ አገኘሁ። አላህ ሙዚቃ እና ጫጫታ ከበዛበት መድረክ አርቆ ስለመብቴ፤ ስለአኼራዬ እየተሟገትኩ እንድውል አደረገኝ። አዲስ አለም፤ አዲስ ልምድ እንዳገኝ አደረገኝ። "የምትለብሱት ሪቫን ላይ የፈለኩት መልዕክት መቀመጥ አለበት።" - በሚል ክስ መታሰራችን ስላቅ ቢሆንም ከሐቅ ጎን ሆነን ስለታሪካዊው ሀላፊነታችን መቆማችን ደግሞ መታደል ነበር። አላህ ፍትሁን ያምጣ። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ!" @aaumsu
1 443
16
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ
ታላቁ የቲክቶክ መድረክ ደረሰ _ ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ! ! ! ስለኒቃብ መጠየቅ በምርቃት ቀን እስከ ማሳሰር ከመድረሱ በፊት ጀምሮ ስላለው የሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ በሰፊው ይዳሰሳል። ሕገ- መንግስቱን ጥሰው ስለሚጥሱት መብት ሕጋዊ ቦታ በሰፊው ይተነተናል። ከእኛ ስለሚጠበቀው ነገርም በደንቡን ውይይት ይደረጋል። ሙባረክ አደም፦ በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ፈርቀዳጅ ታጋይ፤ አክቲቪስት፤ ቲክቶከር፤ ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና፤ የሂባ ፋውንዴሽን መስራች ነው። ፕሮግራማችንን በመድረክ መሪነት የሚያስተናብርልን ይሆናል። ሙስጠፋ ሺፋ፦በድምፃችን ይሰማ የመብት ትግል እንቅስቃሴ ወቅት ለታሰሩት ጠበቃ ሆኖ አገልግሏል፤ አሁንም በጥብቃና ሙያው አንቱታን ካተረፉ ባለሙያዎች መካከል ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥያቄ ሕጋዊ መሠረት ያብራራልናል። የሕያ ኢብኑ ኑሕ፦የንፅፅር ትምህርት መምህር፤ የሒዳያ ኢስላማዊ ማህበር መስራች እንዲሁም ተፅዕኖ ፈጣሪ ስብዕና ነው። ስለሙስሊም ተማሪዎች የመብት ጥሰት ታሪካዊ ዳራ ያብራራልናል። ሁሴን ዩሱፍ፦የኢትዮጵያ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሙስሊም ተማሪዎች ሕብረት ፀሐፊ ሲሆን ከማን ምን ይጠበቃል የሚለውን በዝርዝር ያስቀምጣል። መቅረት አይታሰብም። ጀመዓዎች በቻናሎቻችሁ ላይ አሰራጩት። ሁሉም ለሁሉም ያድርስ። በአንድነት በአንድ መድረክ ተሰባስበን ስለመብቶቻችን እውቀትን እንጨብጥ። 🗓 ቀን፡ ሰኞ፣ ሰኔ 22 (Monday, 29 June) ⏰ ሰዓት፡ ከምሽቱ 03፡00 ሰዓት እውቀትን መፈለግ መብት ነው፤ እምነትንም በክብር መተግበር እንዲሁ! የቲክቶክ ገፃችንን Follow በማድረግ ዝግጅቱን ይጠብቁ፦ https://www.tiktok.com/@aaumsu ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
2 927
17
ኒካህ፤ ምርቃት እና እስር በአንድ ቀን!! በዛሬው እለት 20/10/2018 ዓ,ል  ወንድማችን ፋህሚ ናሲር…ከኢኮኖሚክስ ዲፓርትመንት በተመረቀበት እለት በጌታችን አላህ ፈቃድና ውዴታ ከዚሁ ዲፓርትመንት ተመራቂ ከሆነችው እህታችን ኢክራም ሱለይማን ጋር ኒካሃቸውን አድርገዋል። ወንድማችን በዛሬው ዕለት "ሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ የለም" በሚል ዩኒቨርሲቲው እንዲታሰሩ ካደረጋቸው ወንድሞች ነበር። በአንድ ቀን ምርቃትንም፤ ትዳርንም፤ እስርንም አስተናግዷል። አሏህ ትዳራችሁን የኸይር ሁሉ መፍለቂያ ያድርገው። ለኢስላም መስዕዋት በመሆን እንደተጀመረው በዚህ ትዳር የሚወለዱ ልጆች የዑመር አይነት የዲን ታጋዮች ያድርጋቸው። 🎉بارك الله لكما وبارك عليكما وجمع بينكما في خير 🎉 @aaumsu
1 335
18
"በሪቫናችሁ ላይ ሎጎዬ መኖር አለበት።" - በማለት ሙስሊም ተማሪዎችን በምርቃታቸው ቀን ከእስር ቤት ያቆየው ከአለም የመጀመሪያው ዩኒቨርስቲ ማን ነው?!
1 347
19
አሶሳ ላይ መብት የሆነው ኒቃብ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?! አሶሳ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ኒቃባቸውን እንደለበሱ ያስመርቃል፤ ይ+1
አሶሳ ላይ መብት የሆነው ኒቃብ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?!    አሶሳ ዩኒቨርስቲ ኒቃብ ለብሰው ተምረው ከፍተኛ ውጤት ያመጡትን ተማሪዎች ኒቃባቸውን እንደለበሱ ያስመርቃል፤ ይሸልማል። አንጋፋው አዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ደግሞ ኒቃብ ለብሰው ሲማሩ ችግር ይፈጥራል፤ ሊመረቁ ሲመጡ ያሳስራል። በአሶሳ ዩኒቨርስቲ ዩኒቨርስቲ ከHealth Science ከፍተኛ ውጤት ያመጣችዋ ኢማን ዲልሰባ በወርቅ ሜዳልያ ስትመረቅ፤ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ያሉ ኒቃቢስቶች ደግሞ ኒቃብ መብት ነው ብላችሗል ተብለው ከእስር ቤት ውለዋል። አሶሳ ላይ መብት የሆነ አዲስ አበባ ላይ ወንጀል የሚሆነው በምን አግባብ ነው?! ምንም ልዩነት የለውም። ልዩነት የአመራሮቹ ነው። የአመራሮቹ አስተሳሰብ፤ የአመራሮቹ ሙስሊም ጠልነት ነው። ሆኖም ግን አይቀጥልም። ፍትሕ ይሰፍናል።
1 509
20
የታሰሩት ሙሉ ለሙሉ ተፈተዋል። ዝርዝሩን ይዘን እንመለሳለን። ጥያቄ አለን _ ፍትሐዊ መልስ እስኪመጣ ! ! !
3 466