የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ
前往频道在 Telegram
5 794
订阅者
-524 小时
-57 天
-5030 天
帖子存档
👉 ለላጤዎች የቀረበ ጥያቄ
ደቡብ ኮሪያ ዜጎቿ ትዳር እንዲመሠርቱእና ልጅ እንዲወልዱ ገንዘብ እየከፈለች እንደሆነ ተነገረ።
በዓለማችን ዝቅተኛው የወሊድ መጠን የሚገኝባት ደቡብ ኮሪያ፣ የህዝብ ቁጥሯ እንዳይቀንስና የህጻናት ቁጥር እንዲጨምር ትልቅ አዲስ ዘመቻ ጀምራለች!
መንግሥት ወጣቶች እንዲጋቡና ልጅ እንዲወልዱ የሚያበረታቱ የገንዘብ፣ የቤት እና የህጻናት ማደጊያ ድጋፍ ፕሮግራሞችን ይፋ አድርጓል።
ወዲያው ጋብቻ የሚፈፅሙ አዲስ ባለትዳሮች
1ኛ የመኖሪያ ቤት ድጋፍ፣
2ኛ የህጻናት ማደጊያ አበል፣
3ኛ የወሊድ ክፍያ እና የአካባቢ አስተዳደሮች የሚሰጧቸውን ልዩ ልዩ ማበረታቻዎች በአንድ ላይ ሲደመሩ አጠቃላይ የሚያገኙት ድጋፍ ከፍተኛ መጠን ሊደርስ ይችላል።
ኢትዮጵያ ውስጥ ተመሳሳይ የጋብቻና የወሊድ የገንዘብ ማበረታቻ ቢጀመር... እርስዎ ያገባሉን?
ከሰርክል ኢትዮዽያ የተወሰደ
اَلسَلامُ عَلَيْكُم وَرَحْمَةُ اَللهِ وَبَرَكاتُهُ
🌿🌿አስደሳች ዜና🌿🌿
🌿🌹🌲🌴🌷🌸🌹🍀🍁🌺🌼🌻
የሴቶች በሴቶች የሙሀደራ
ፕሮግራም
🌹🍂🍀🌿🌺🌾🌸💐🍁🌻🌺🌴
የሙሀደራ ፕሮግራም ቢላል ኮካ መስጂድ እና መድረሳ ከልደታ ክ/ከተማ መጅሊስ ጋር በመተባበር ስለተዘጋጀ እርሰዎን ከወዳጅ ዘመድዎ ጋር በአክብሮት ጋብዘንዎታል
🎤🎤🎤 በእለቱ የሚቀርበው ርእስ
👉
" وَتَزَوَّدُوا فَإِنَّ خَيْرَ الزَّادِ التَّقْوَىٰ ۚ "
"ተሰነቁም፤ ከስንቅም ሁሉ በላጩ ጥንቃቄ (አላህን መፍራት) ነው "
አል- በቀራ 197
👉 ሌሎችም አጓጊ ፕሮግራሞችን ይዘን እናንተን በመጠበቅ ላይ ነን
📅 የፊታችን እሁድ ሀምሌ 26/ 2018
🕝። ሰዐት ፡- ከጠዋቱ 3፡00-6:30
🕌 አድራሻ ፦ ከአሚን ሆስፒታል ወረድ ብሎ በሚገኘው ቢላል ኮካ መስጂድ እና መድረሳ
ጥብቅ ማሳሰቢያ ፦
🪴ይህንን በአይነቱ ልዩ የሆነ ፕሮግራም
እንዳያመልጥዎ ፕሮግራሞትን ከወዲሁ
በማመቻቸት ከቤተሰብዎ ፣ ከጓደኛዎ፣ ከስራ ባልደረባዎ ጋር ለመታደም ቁጥር አንድ
ፕሮግራምዎ አድርገው ይያዙ ።
🍀 ጥሪን ማክበር ኢስላማዊ ስነ-ምግባር
ነው !!!
ላልሰሙት በማዳረስ የአጅሩ ተካፋይ ይሁኑ።
የሰርግ ቀን ወይም ከሰርግ ዉጭ ወንዶች ሂና መቀባት እንዴት ይታያል?
መልስ
ወንድ ልጅ ሂና መቀባት ክልክል ነዉ
ሂና መቀባት
የሴቶች መለያ ነዉ
ወንዱ ሂና ከተቀበና ከሴትጋ ተመሳሰለ
ወንድ ልጅ በሴት መመሳሳል ከትላላቅ ወንጀል ነዉ
ሴት ወንድን መመሳሰል ከትላልቅ ወንጀል እንደሆነዉ ሁሉ
ነብያችን ሶለሏሁ አለይሂ ወሰለም
ሴት ወንድን የምትመሳሰል
ወንድ ሴትን የሚመሳሰል እረግመዋል
ወንድ ልጅ ለሰርግ ይሁን ከሰርግ ዉጭ ሂና መቀባት የተከለከለ ነዉ
እንደዉም
ከትልልቅ ወንጀል ነዉ
ከሴትጋ መመሳሰል ስላለዉ
👇👇👇
https://t.me/HuzeyfaAhmed
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 154
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 153
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
የሱንና ደረጃ አኢማዎች ዘንድ
قال الإمام الشافعي في الرسالة
"وكل فريضة فرضها الله تعالى في كتابه: كالحج والصلاة والزكاة: لولا بيان الرسول ما كنا نعرف كيف نأتيها ولا كان يمكننا أداء شيئ من العبادات وإذا كان الرسول من الشريعة بهذا المنزلة كانت طاعته على الحقيقة طاعة الله "
ኢማሙ ሻፊኢ በሪሳላቸው እንዲህ ይላሉ
አሏህ ግዴታ ያደረጋቸው ሁሉም ግዴታዎች እንደ ሀጅ ሰላትና ዘካን የመሰሉ የአሏህ መልክተኛ ባያብራሩልን ኖሮ እንዴት መፈፀም እንዳለብን ባላወቅን ነበር ። ከአምልኮት አንደኛውንም መፈፀም ባልቻልን ነበር ። የአሏህ መልክተኛ ለኢስላማዊ ህግና ስርአት ይህን ያክል ቦታ ስላላቸው እሳቸውን በትክክል መታዘዝ አሏህን መታዘዝ ነው
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 152
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 151
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
ዑምራ፡ የመንፈስ ጉዞ ወይስ የዱንያ መዝናኛ?
ዑምራ—የእስልምናን ቅዱሳት ስፍራዎች የመጎብኘት፣ ወንጀልን የማሰሪያ፣ ቀልብን ከዓለማዊ እና ቁሳዊ ሸክም አጥቦ ወደ አላህ ሱብሓነሁ ወተዓላ የመመለሻ ታላቅ መንፈሳዊ ጉዞ ነው። ነገር ግን ከቅርብ ግዜ ወዲህ የሚስተዋሉ አንዳንድ ልማዶችና የቱር አዘጋጆች ዘይቤ፣ የዚህን ታላቅ ዒባዳ ዋና ዓላማ እያሳቱት ይሆን? የሚል እውነተኛ ስጋት እያስነሳ ይገኛል።
1. የዓለማዊ ነገሮች መጎላትና የመንፈሳዊነቱ መቀጨጭ
በዑምራ ጉዞዎች ላይ አሁን አሁን ዋና ትኩረቱ ከዒባዳ ወደ መዝናናት ሲያደላ ይስተዋላል። ፈረስ ግልቢያ፣ የቀስት ውርወራ፣ የባህር ላይ የጀልባ ሽርሽር እና መሰል መዝናኛዎች የጉዞው ዋና ማእከል እየሆኑ መጥተዋል።
ከሁሉም በላይ ግን አሳዛኙ ነገር፡ በአል-ሐረመይን (በመካው መስጂደል ሐራም እና በነቢያችን መስጂድ) አንድ ሰላት መስገድ እስከ 100,000 ሰላት እጥፍ በነቢዩ መስጂድ ደግሞ አንድ ሺህ የሚደርስ ታላቅ ምንዳ (አጅር) እንዳለው እየታወቀ፣ ያንን ሁሉ እድል አግኝቶ በጨዋታና በመዝናናት ጊዜን በማሳለፍ በጀማዓ መስገድን ማስመለጥ ትልቅ ሂርማን (የአጅር ኪሳራ) ነው።
መዝናናት በራሱ የተከለከለ ባይሆንም፣ ቅዱስ ስፍራ ላይ ቆሞ ጊዜን በእንዲህ አይነት ነገሮች ማሳለፍ ግን የዑምራን ዋና መንፈሳዊ ጥቅም እና የልብ መረጋጋት እያመናመነው ይገኛል።
2. የሱህባ እና የሳሊሆች ሚና መዛባት
አንድ ሰው ለዑምራ ሲነሳ ከጎኑ የሚፈልገው አላህን የሚያስታውሱት፣ አምልኮቱን የሚያስተካክሉለት እና ወደ አኼራ የሚጠቁሙትን "ሩፍቀት አስ-ሳሊሃ" (መልካም ጓደኞችን) ነው። አሳዛኙ ነገር ግን፣ የቱር ኤጀንሲዎች ማስታወቂያዎቻቸው ላይ ሸሪዓዊ እውቀት ያላቸውን ረባኒይ መሻይኾች እና ዓሊሞችን መሪ ከማድረግ ይልቅ፣ የቲክቶክ እና የማህበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎችን (Activists) እንደ ዋና ሳቢ ማስታወቂያ ማቅረባቸው ነው።
መንፈሳዊ መሪዎችን በቲክቶክ አክቲቪስቶች መተካት የጉዞውን ሚዛን ያሳስታል። የዑምራ ጉዞ በቪዲዮ እይታና በፎቶ ብዛት ሳይሆን በዕንባ፣ በዱዓ እና በኢኽላስ የሚለካ ተግባር ነው።
የዑምራ አዘጋጆችም ሆኑ ተጓዦች ወደ ህሊናቸው ሊመለሱ ይገባል። ዑምራ የልብ ህክምና እንጂ የካሜራ ትርኢት ወይም የቱሪዝም ሽርሽር አይደለም። የዑምራ ጉዞ እውነተኛ ዓላማውን ሳይስት፣ የአላህን ፍራቻ እና የመንፈስ እድሳትን ማዕከል ያደረገ ይሆን ዘንድ አቀራረባችንን እና አስተሳሰባችንን ልንፈትሽ ይገባል።
ሸይኽ ኢብኑ ኡሰይሚን እንዲህ ይላሉ
« በእናንተ ላይ የሚያልፈው ዓመት ሁሉ ወደ ቀብር የሚያቀርባችሁ ዓመት እና ከህንፃችሁ የሚያርቃችሁ ዓመት ነው»
አዲያኡ ላሚእ 703
▪️قال الشيخ ابن عثيمين رحمه الله:
"كل عام يمر بكم يقربكم من القبور عاما، ويبعدكم عن القصور عاما."
الضياء اللامع ٧٠٣
🔹የሱንና ደረጃ ሰለፎች ዘንድ
قال الإمام الأوزاعي " الكتاب أحوج إلى السنة من السنة إلي الكتاب " البحر المحيط 11/6
አል ኢማሙ አልአውዛኢዮ እንዲህ ይላሉ
«ሱንና ወደ ቁርአን ከሚፈልገው በላይ ቁርአን ወደ ሱንና ይፈልጋል»
በህሩል ሙሂጥ 11/6
T.me/dawudyassin
👆👆👆👆👆👆
ስልክ ለብዙዎች ፈተና ሆኗል
በስልክ ምክንያት ኢማናችን ተፈትኗል
በስልክ ምክንያት ስነምባር ተበላሽቷል
በስልክ ምክንያት ማህበራዊ ቀውስ ተፈጥሯል
በስልክ ምክንያት ልጆቻችን ተበላሽተዋል
።
።
።
ብለው የሚያስቡ ከሆነ ይህን የድምፅ ፋይል ሼር ያድርጉ
🪑የጁሙዓ ኹጥባ
💬ርዕስ: ስልክ በሙስሊም ህይወት ውስጥ
🕌 ፉሪ አቡበክር መስጅድ
🎤በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
📆 ቀን 10 – 2 –1448هـ
ተጨማሪ ዱሩሶች ፣ ኹጥባዎችና ጠቃሚ እውቀቶችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
T.me/dawudyassin
በጁምዓ ቀን መስጂድ ቀድሞ የመግባት ትሩፋት 👇
٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠
🥀 ረሱል ሰለላሁ አለይሒ ወሰለም
እንዲህ ብሏሉ👇
👉በጁምዓ ቀን መስጂድ መግቢያ በር
የሚቆሙና ሰዎችን በቅድሚያ
በቅድሚያ/ እንደየ አመጣጣቸው
የሚመዘግቡ መለዕክቶች አሉ።
🥀በመጀመሪያው ሰአት የመጣው ሰው
ግመል ሰደቃ እንዳቀረበ
ይቆጠርለታል።
🥀ከዛ ቀጥሎ ባለው ጊዜ የመጣን
ሰው በሬ ሶደቃ እንዳቀረበ
ይቆጠርለታል።
🥀ከዛ ቀጥሎ ባለው ጊዜ የመጣ ሰው
በግ ሰደቃ እንዳቀረበ ይቆጠርለታል።
🥀ከዛ ቀጥሎ ባለው ጊዜ የመጣ ሰው
ዶሮ ሰደቃ እንዳቀረበ ይቆጠርለታል።
🥀ከዛ ቀጥሎ ባለው ጊዜ የመጣ ሰው
እንቁላል ሰደቃ እንዳቀረበ
ይቆጠርለታል።
🥀ከዛ ኢማሙ ለኹጥባ ሚምበር ላይ
ስወጣ መልዓክቶች
መዝገባቸውን በመዝጋት
ምክሩን ለማዳመጥ ይቀመጣሉ።
(📚ቡኻሪ ዘግበውታል 929)
➖➖➖➖➖➖➖
✔️አላሁ አክበር❗️ለተጠቀመበት ሰው
ምንኛ የሚያስደስት አጋጣሚ ነው።
አላህ ለሁላችንም ያግራልን። አሚን
🥀ይህ መልዕክት እኛ ጋር እንዳይቀር
ለተለያዩ ወዳጆቻችን በማስተላለፍ
እነሱ የሚያገኙትን አጅር አምሳያ
ለማግኘት እንጣር
٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠٠
🥀 የተለያዩ ጠቃሚ የሆኑ ኢስላማዊ
እውቀቶችን ለማግኘት ከስር ያለውን
ሊንክ በመንካት ቻናሉን ጆይን ብለው
ይቀላቀሉ 👇👇👇👇👇👇👇👇https://t.me/+ZZzCjxcbaso3YzM0
👈 قال الشيخ السعدي في التفسير:
"أن من ترك ما ينفعه، وأمكنه الانتفاع به فلم ينتفع، ابتلي بالاشتغال بما يضره، فمن ترك عبادة الرحمن، ابتلي بعبادة الأوثان، ومن ترك محبة الله وخوفه ورجاءه، ابتلي بمحبة غير الله وخوفه ورجائه، ومن لم ينفق ماله في طاعة الله أنفقه في طاعة الشيطان، ومن ترك الذل لربه، ابتلي بالذل للعبيد، ومن ترك الحق ابتلي بالباطل"
تفسير سورة البقرة ٩٣
🔹 ድንቅ ምክር
👉 ከሸይኽ ሰአዲ
የሚጠቅመውን ነገር የተወ ፣ መጠቀም በሚችልበት ነገር ያልተጠቀመ ፣ በሚጎዳው ነገር በመጠመድ ይፈተናል ።
አልሯህማንን ከማምለክ የተወ ጣኦትን በማምለክ ይፈተናል ፣ አሏህን ከመውደድ ፣ ከመፍራትና ከመከጀል የተወ ከአሏህ ሌላ ያለን በመውደድ ፣ በመፍራትና በመከጀል ይፈተናል ።
ገንዘቡን በአሏህ ትእዛዝ ላይ ያላወጣ በሸይጧን ትእዛዝ ላይ ያወጣዋል ። ለጌታው መዋረድን የተወ ለፍጡር በመዋረድ ይፈተናል ፣ እውነትን የተወ በውሸት ይፈተናል
ከሱረቱል በቀራህ 93 ትርጉም የተወሰደ
ራሳቸውን ወደ ሱና በሚያስጠጉ አካላት ላይ በሰፊው ከሚታዩ ነውረኛ ተግባራት ውስጥ አንዱ ሰዎችን በተመለሱበት ጉዳይ መክሰስ ነው። አንድ ሰው ከሆነ የተሳሳተ አቋም ወይም ጥፋት ከተመለሰ ያንን ጉዳይ #እያወቀ ሆነ ብሎ በሱ ላይ የሚለጥፍ ሰው
1ኛ፦ ዋሾ ነው።
2ኛ፦ ውሸትን የደዕዋው መንገድ አድርጎ የያዘ መጥፎ ሰው ነው።
3ኛ፦ ዓላማው ዲን ሳይሆን ቂም ማወራረድና ብሸሸቅ ነው።
ይሄ ነገር የሰውየውን መመለስ #ሳናውቅ ሊገጥመን ይችላል። መመለሱን ካወቅን በኋላ በተመለሰበት ጉዳይ መወንጀል ግን ያለ ወንጀሉ ሰውን መክሰስ ነው። ቡድናዊ ሽኩቻ ላይ ያነጣጠሩ "ረዶች" በብዛት ይሄ ችግር ጎልቶ ይታይባቸዋል።
ሰውን በተመለሰበት ጥፋት መክሰስ ባልፈፀመው ጥፋት እንደ መክሰስ ነው። ከፍ ያለው አላህ እንዲህ ይላል:-
{ وَٱلَّذِینَ یُؤۡذُونَ ٱلۡمُؤۡمِنِینَ وَٱلۡمُؤۡمِنَـٰتِ بِغَیۡرِ مَا ٱكۡتَسَبُوا۟ فَقَدِ ٱحۡتَمَلُوا۟ بُهۡتَـٰنࣰا وَإِثۡمࣰا مُّبِینࣰا }
"እነዚያንም ምእምናንንና ምእምናነትን ባልሰሩት ነገር (በመዝለፍ) የሚያሰቃዩ ዕብለትንና ግልጽ ኃጢአትን በእርግጥ ተሸከሙ፡፡" [አልአሕዛብ: 58]
ነብያችንም ﷺ እንዲህ ብለዋል፦
من قال في مؤمنٍ ما ليس فيه أسكنه اللهُ رَدْغَةَ الخَبالِ حتّى يخرُجَ ممّا قال
"በአማኝ ላይ የሌለበትን የተናገረ ሰው አላህ የጥፋት ማጥ ውስጥ ያኖረዋል፣ ከተናገረው ነገር እስከሚወጣ ድረስ።" [ሶሒሑ ተርጊብ: 2845]
IbnuMunewor
🌙 የሌሊት ጸጥታና የብቸኝነት ጊዜ...
ሌሊቱ ጸጥ ባለበትና አላህ እንጂ ማንም በማያይህ ብቸኝነት ውስጥ ሆነህ፣ ጊዜውን ሳትጠቀምበት ዝም ብለህ አለማሳለፍህ ትልቅ ተውፊቅ (የአላህ እገዛና ስኬት) ነው። በዚህ ውድ ሰዓት መጨረሻው በማያምርና ፋይዳ በሌለው ዓላማ ስልክህ ላይ አትዘፈቅ!
✨ ከንፈሮችህን በኢስቲግፋር፣ በዱዓ ወይም ቁርኣን በመቅራት አንቀሳቅሳቸው፤ ጥቂትም ቢሆን ተነስተህ ሶላት ስገድ።
በድብቅ (ከሰዎች እይታ ርቆ) የሚደረግ ዒባዳ ከሌሎች የተለየ ትልቅ ደረጃ አለው፤ አላህም ባለቤቶቹን ይወዳል።
ዛሬና ነገ የቡሉጉል መራም ደርስ እንደማይኖረን ራቅ ካለ ቦታ ለሚመጡ ወንድምና እህቶች እንዳይሰተጓጎሎ አሳውቃለው
🪑የጁሙዓ ኹጥባ
💬ርዕስ: የጅህልና በሽታ
🕌 ፉሪ አቡበክር መስጅድ
🎤በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
📆 ቀን 3 – 2 –1448هـ
ተጨማሪ ዱሩሶች ፣ ኹጥባዎችና ጠቃሚ እውቀቶችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
T.me/dawudyassin
