የአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን የመማማሪያ መድረክ
الذهاب إلى القناة على Telegram
نفهم الكتاب والسنة بفهم سلفنا الصالح ቁርአንና ሐዲስን በሰለፎች ግንዛቤ እንገንዘብ
إظهار المزيد5 869
المشتركون
-124 ساعات
-207 أيام
-12030 أيام
أرشيف المشاركات
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 144
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 143
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
🌴አቡ ሓቲም ረሒመሁሏህ እንዲህ አሉ፦
❝አንድ ሰው ጨዋነቱ ሲጨምር ክብሩን ይጠብቃል፣ ስህተቱን ይቀበራል፣ መልካም ምግባሩን ያስፋፋል፣ ጨዋነቱን ያስወገደ ሰው ደስታውን ያስወግዳል፣ ደስታውንም ያስወገደ ሰው ለሰዎች ደንታቢስ ይሆናል ለሰዎችም ደንታቢስ የሆነ ሰው በሰዎች የተጠላ ይሆናልና።❞
📚روضة العقلاء ونزهة الفضلاء١/ ٥٨
══════ ❁ ══════
🪑የጁሙዓ ኹጥባ
💬ርዕስ: የእግር ኳስ ጥፋቶች
🕌 ፉሪ አቡበክር መስጅድ
🎤በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
📆 ቀን 26 –12–1447هـ
ተጨማሪ ዱሩሶች ፣ ኹጥባዎችና ጠቃሚ እውቀቶችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
T.me/dawudyassin
የኸዋሪጆች ፈለግ እና የመገለል አባዜ
"አ’ትተመዩዝ" “አል ኢንዒዛል"
> ከሙስሊሙ ማህበረሰብ (ጀማዐ) ተለይቶ መውጣትንና 'ልዩ ነኝ' ባይነትን (ኢንዒዛልን) በመጀመርያ የፈጠሩት ኸዋሪጆች ናቸው። ይህን ያደረጉትም በ'ሐሩራእ' የራሳቸውን ማህበረሰብ በመመስረትና ወደ እነሱ መሰደድን ግዴታ በማድረግ ነበር፤ ወደ እነሱ ያልተሰደደውንም በኩፍር ፈረጁት። ታዲያ ከሰዎች ተገልሎና ተለይቶ እየኖረ 'ሰዎችን አስገነዝባለሁ (አስተካክላለሁ)' የሚል ሰው ነገር ግራ የሚያጋባ ነው፤ ከማህበረሰቡ ጋር ሳትቀላቀልና ሳትኖር እንዴትስ ሰዎችን ወደ በጎ መንገድ ልትጣራ ትችላለህ?!"
>
###ከሰዎች መገለል (በአካልም ሆነ በስሜት) እና ራስን እንደ ብቸኛ ትክክለኛ አድርጎ መቁጠር ለጽንፈኝነት የመጀመሪያው በር ነው። መልክተኛው ﷺ እንዲህ ብለዋል፦ «ከሰዎች ጋር የሚቀላቀልና በነርሱ አዛ ላይ የሚታገስ አማኝ፣ ከሰዎች ጋር የማይቀላቀልና በነርሱ እንግልት ላይ ከማይታገሰው ይበልጣል»።
ስለሆነም በዳዕዋ ላይ ዋናው መሠረት ሰዎችን መቅረብ፣ መደባለቅና መታገስ እንጂ መገለልና መኮራት አይደለም።
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 142
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 141
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 139
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
📚بلوغ المرام
📚ቡሉጉል መራም
√ዘውትር ሰኞና ማክሰኞ
√ከመግሪብ እስከ ኢሻ
√በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
√ክፍል 139
√በቢላል ኮካ መስጅድ ከአብነት ዝቅ ብሎ ከአሚን አጠቃላይ ሆስፒታል ጀርባ
T.me/dawudyassin
የኡስታዝ ሳዲቅ ሙሐመድ (አቡ ሐይደር) መልእክት፣
📌 ከሐዲሥ ማስተባበል ጀርባ ያለው አስፈሪው እውነታ!
🔈 የጁሙዓህ ኹጥባህ
📖ርዕስ፦እግር ኳስ እና ችግሮቹ!
📍ቦታ፦ ወራቤ ከተማ
🌇መስጅድ፦ ዑመር መስጅድ
🎙 በሸይኽ ኑረዲን ኸሊል
🪑የጁሙዓ ኹጥባ
💬ርዕስ: ስራን ሰለማጥራት/ ኢኽላሱል ዓመል /
🕌 ፉሪ አቡበክር መስጅድ
🎤በአቡ ሱለይማን ዳውድ ያሲን
📆 ቀን 19 –12–1447هـ
ተጨማሪ ዱሩሶች ፣ ኹጥባዎችና ጠቃሚ እውቀቶችን ለማግኘት
👇👇👇👇👇👇👇👇👇
T.me/dawudyassin
በዚህ ፈታኝ ወቅት ለዳዕዋ ሥራችን የቴክኒክ ባለሙያዎች እገዛ እንሻለን!
በቅርቡ ሁላችንም እንደምንታዘበው፣ በክርስቲያን ወገኖቻችን በኩል እስልምናን በተመለከተ የሚነሳው ውዝግብ፣ ትችትና ያልተገባ ንግግር ከምንጊዜውም በላይ ጨምሯል። በዚህ ወሳኝ ሰዓት እምነታችንን በዕውቀት መከላከልና ለሚነሱት ማደናገሪያዎች ትክክለኛውን መረጃ ምላሽ ማድረስ እጅግ አስፈላጊ ነው።
ይህን ታላቅ የዳዕዋ ሥራ በሰፊው ለማድረስ ደግሞ፣ ከፍተኛ ተደራሽነት ያለው መድረክ የግድ ይለናል። እንደምታውቁት ከ100 ሺህ በላይ Followers የነበሩትና፣ በሶስት ወራት ውስጥ ብቻ ከ20 ሚሊዮን በላይ ተደራሽነት ወይንም Reach የነበረው ዋነኛው የፌስቡክ ገጼ ከተዘጋ አሁን ከ3 እስከ 4 ወራት አልፈውታል። ይህ ገጽ በነበረን የዳዕዋ እና የንጽጽር ሥራ ላይ ትልቅ ምሽግ የነበረ ሲሆን፣ አሁን ግን በተለይ በዚህ ጫና በበዛበት ወቅት መዘጋቱ የራሱን ክፍተት ፈጥሯል።
ስለዚህ፣ ይህንን ገጽ በማስመለስ በኩል ሊያግዘኝ የሚችል የቴክኒክ ባለሙያ እፈልጋለሁ። በተለይም የፌስቡክ 'ብሉ ባጅ' (Meta Verification) ያለው እና ከፌስቡክ ኮንታክት ሴንተር ጋር በቀጥታ በመነጋገር ገጹን ማስከፈት የሚችል አቅም ያለው ወንድም ወይም እህት ካለ፣ እባካችሁ አግዙኝ። ይህን በማድረግዎ በግልዎ ለዚህ የዳዕዋ መስመር ትልቅ አሻራዎን እያኖሩ ነው።
ይህንን ማድረግ የምትችሉ ባለሙያዎች፣ እባካችሁ በውስጥ መስመር ወይም በዚህ የቴሌግራም አድራሻ አናግሩኝ፦ @Yahyanuhe1
አላህ ለዲኑ የምንለፋበትን አቅም ይስጠን። ሼር በማድረግ ትክክለኛው ሰው ዘንድ እንዲደርስ ተባበሩኝ!
⚠️ ይድረስ "ቁርኣን ብቻ ይበቃናል" ለሚሉ ቡድኖች ለቁረአኒዮች❓
ለኻሊድ ክብሮም ሹቡሃት (ጥመቶች) ቀጥተኛና ግልጽ ምላሽ የሚሆን፣ የሱናን አስፈላጊነትና የሰለፎችን መንገድ የሚያስረዳ ታላቅ ትምህርት ነው።
"በድሮውም ሆነ በአሁኑ ዘመን ‹ሐዲስን ትተን በቁርኣን ብቻ እንብቃቃ› የሚል አስከፊ ጥሪ የሚያስተጋባ ቡድን ተከስቷል።
ዓላማቸውም የዲኑን ግማሽ አካል ማፍረስ፣ እንዲያውም ዲኑን ሙሉ በሙሉ መናድ ነው። ምክንያቱም ሐዲሶችና ሱናዎች
ችላ ከተባሉ፣ ቁርኣን ለኡማው ትርጉሙ መሰወሩ (ግልጽ አለመሆኑ) እና ተግባራዊነቱ መጥፋቱ የማይቀሬ ሃቅ ነውና። እነሱም ቁረአንን በፈለጉት መልኩ እየጠመዘዙ ለመፈሰርና ስሜታቸውን በሚገጥምላቸው መልኩ ለማስኬድ ነው አላማቸው።
የነቢዩ ﷺ ባልደረቦች (ሶሐባዎች) - አላህ ይውደድላቸውና - በሱናና በሐዲስ የመመገብንና በእርሱም የመስራትን አስፈላጊነት በአንድ ድምፅ (ኢጅማዕ) ተስማምተውበታል። ይህም በቁርኣን ውስጥ በግልጽ ያልተጠቀሱ ጉዳዮችን ጭምር ይጨምራል። ከእነርሱ መካከል በዚህ ጉዳይ ላይ የለያየ አንድም ሰው አናውቅም። ከእነርሱ መካከል አንዳቸው አዲስ ጉዳይ ሲገጥመው መጀመሪያ ፍርዱን ከአላህ መጽሐፍ (ከቁርኣን) ይፈልጋል፤ እዚያ ካላገኘው በሱና ውስጥ ይፈልገዋል፤ እዚያም ካላገኘው በቁርኣን፣ በሱናና በሸሪዓዊ መርሆዎች ገደብ ውስጥ ሆኖ ይተነትናል።
ኢማም አል-ኸጣቢይ ነቢዩ ﷺ ‹እኔ መጽሐፉን (ቁርኣንን) እና መሰሉን (ሱናን) አብሮ ተሰጥቻለሁ› ያሉት ንግግር ሁለት
ትርጉሞችን ይይዛል ይላሉ፦
1. የመጀመሪያው፦ ልክ እንደሚቀራውና ግልጽ እንደሆነው ወሕይ (ቁርኣን) ሁሉ፣ የማይቀራ ግን ደግሞ ውስጣዊ የሆነ ወሕይ (ሱና) ተሰጥቷቸዋል ማለት ነው።
2. ሁለተኛው፦ ቁርኣን እንዲወርድላቸውና በዚያው ልክ ደግሞ ቁርኣኑን የማብራራት (ተብዪን) ስልጣን ተሰጥቷቸዋል ማለት ነው። ይህም በቁርኣን ውስጥ ያለን ጠቅላላ ንግግር መለየት (ማጥበብ)፣ መጨመርና ማብራራት ነው። በመሆኑም በሱና መስራትና መቀበል ልክ በቁርኣን እንደመስራት ግዴታ ነው።
አላህም እንዲህ ብሏል፦
{وَمَا آتَاكُمُ الرَّسُولُ فَخُذُوهُ وَمَا نَهَاكُمْ عَنْهُ
فَانْتَهُوا}
“መልክተኛውም የሰጧችሁን (ማንኛውንም ነገር) ያዙት፤ ከእርሱም የከለከሏችሁን ተከልከሉ (ራቁ)።” (አል-ሐሽር 7)
ይህ አንቀጽ በቁርኣን ውስጥ ላልተጠቀሱ ነገር ግን በሱና ለመጡ ሕግጋት ሁሉ ትልቅ መሠረት (አስል) ነው። ከሶሐባዎች በኋላ
የመጡ የታላላቅ የዲንና የእውቀት መሪዎች (አኢማዎች) መንገድም ይኸው ነው።"
ከዚህ በመነሳት ለኻሊድ ክብሮም ሹቡሃቶች የሚሰጠው ሦስት ታላላቅ ምላሾች አሉ፦
1. የኻሊድ ክብሮም ዓላማ ዲኑን መናድ መሆኑ ግልፅ ነው ፦ ፅሁፉ በግልጽ እንደሚለው " ቁረአን ብቻ ይበቃናል ሐዲስ አያስፈልግም" የሚል ሰው ዓላማው የዲኑን ግማሽ አካል ማፍረስ ነው። ኻሊድ ክብሮም "ቁርኣን በራሱ ተብራርቷል" ሲል፣ ኡማው ሶላቱን እንዴት እንደሚሰግድ፣ ዘካውን እንዴት እንደሚከፍልና ሌሎች ሕግጋትን እንዴት እንደሚተገብር ግራ እንዲጋባ (እንዲጠፋ) እያደረገ ነው። ሱና ከሌለ ቁርኣን ለኡማው "አዕጀሚ" (ትርጉሙ የማይታወቅ) ይሆናል።
2. "መሰሉን ተሰጥቻለሁ" የሚለው ሐዲስ ትርጉም አልባ ለማድረግ ነው አላማው ፦ ኻሊድ ክብሮም ይህንን ሐዲስ ውድቅ ሊያደርግ ቢሞክርም፣ ኢማም አል-ኸጣቢይ ግን ሐዲሱ የነቢዩን ﷺ የማብራራት ስልጣንና ሱና ራሱን የቻለ "ወሕይ" መሆኑን እንደሚያረጋግጥ ገልጸዋል። አላህ ለነቢዩ ﷺ ቁርኣንን ብቻ ሳይሆን፣ ቁርኣኑን የሚተረጉሙበትን ጥበብ (ሒክማ/ሱና) አብሮ ሰጥቷቸዋል።
3. የሶሐባዎች መንገድ (መንሐጅ) መፃረር ነው፦ ኻሊድ ክብሮም ራሱን "ቁርኣን አዋቂ" አድርጎ ቢሰይምም፣ ከሶሐባዎች መንገድ ግን የወጣ መሆኑን ፅሁፉ ያረጋግጣል። ሶሐባዎች ቁርኣን ላይ የሌለን ነገር ከሱና ይይዙ ነበር። ኻሊድ ክብሮም ግን "ቁርኣን ላይ የሌለ በሱና የመጣን ነገር አልቀበልም" ማለቱ፣ ከሶሐባዎችና ከሰለፎች መንገድ የወጣ "አዲስ መጤ" (ሙብተዲዕ) መሆኑን ያሳያል።
ይህ ግለሰብ (ኻሊድ ክብሮም) "ቁርኣንን አብራራለሁ" እያለ ቁርኣንን እየካደ ነው። ምክንያቱም ቁርኣን "ነቢዩን ተከተሉ" እያለ፣ እርሱ ግን "አያስፈልጉም" እያለ ነውና። ኡማው ከእንዲህ ዓይነት የዘመናችን "ቁርኣንዮች" (ሐዲስ ነቃፊዎች) ራሱን ሊጠብቅ ይገባል።
አቡ ሂበቱላሂ
🔹 የአያሙ አት-ትሽሪቅ (ሑጃጆች ሚና ላይ የመቆያ ቀናት) ትርጉምና ደረጃ
ምስጋና ለአላህ ይሁን። የአያሙ አት-ትሽሪቅ ቀናት ማለት አላህ በቁርኣኑ፦ "አላህንም በታወቁት (በተቆጠሩት) ቀናት ውስጥ አውሱት" (አል-በቀራህ፡ 203) በማለት የጠቀሳቸው ቀናት ናቸው። እነሱም ከዕርዱ ቀን (ከዒድ አል-አድሃ) በኋላ ያሉ ሶስት ቀናት ሲሆኑ፤ 11ኛው፣ 12ኛው እና 13ኛው ቀናት ናቸው።
ከእነዚህ ቀናት ውስጥ በላጩ መጀመሪያው ቀን (11ኛው ቀን) ነው። ምክንያቱም የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
> "አላህ ዘንድ ከቀናት ሁሉ የላቀው ቀን የዕርዱ (የዒድ) ቀን ነው፣ ከዚያም ‘የቀር’ር’ (ሑጃጆች ሚና ላይ የሚቆዩበት ቀናት) ቀን ነው"
>
እሱም 11ኛው ቀን ነው።
## የእነዚህ ቀናት ትሩፋት እና ተግባራት
የአላህ መልእክተኛ (ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም) እንዲህ ብለዋል፦
> "የዐረፋ ቀን፣ የዕርዱ ቀን እና የአያሙ አት-ትሽሪቅ ቀናት ለእኛ ለኢስላም (ህዝቦች) በዓሎቻችን ናቸው፤ እነሱም የመብያና የመጠጫ ቀናት ናቸው።"
>
ስለሆነም በእነዚህ ቀናት ውስጥ የሚከተሉትን ማድረግ ይደነገጋል (ይወደዳል)፦
* አላህን ማውሳት (ዚክር ማድረግ)፦ የእስልምናን መገለጫዎች ማሳየት፣ መደሰት እና ሀሴት ማድረግ።
* ዝምድናን መቀጠል፦ ከቤተሰብና ከዘመድ ጋር መዘያየር።
* የተገደበ ተክቢራ (አት-ተክቢር አል-ሙቀየድ)፦ ከግዴታ ሶላቶች በኋላ የሚደረገው ተክቢራ እስከ 13ኛው ቀን የዐስር ሶላት ማብቂያ ድረስ ይቀጥላል።
* አጠቃላይ ተክቢራ (አት-ተክቢር አል-ሙጥለቅ)፦ በማንኛውም ሰዓት፣ ሁኔታ እና ቦታ ላይ የሚደረገው ተክቢራም እንዲሁ ይቀጥላል።
* የኡድሂያ እንስሳትን ማረድ፦ በእነዚህ ቀናት ውስጥ የዒድ መሥዋዕት ይታረዳል።
* መጾምን መከልከል፦ በእነዚህ ቀናት መጾም አይፈቀድም፤ ነገር ግን (በሐጅ ላይ ሆኖ) የመሥዋዕት (ሀድይ) እንስሳ ማቅረብ ላልቻለ ሰው ብቻ መጾም ይፈቀድለታል።
ከዒደል አድሓ ቀጥሎ ያሉት ሶስቱ ተከታታይ ቀናት ሐጅ ላይ ላልሆነ ሰው የዒዱ ድባብ የሚከተላቸው የመብላት የመጠጣት ቀናት ናቸው። ስለዚህ ሐጅ ላይ ላልሆነ አካል ሊፆማቸው አይገባም።
ይህንን ማስታወሻ የፃፍኩት እነዚህን ቀናት መፆም እንደሚቻል የተናገርኩበት የተሳሳተ ምላሽ የቅርብ ወንድም ልኮልኝ ነው። ስለዚህ ደግሜ የምናገረው በድምፅ የተናገርኩት ስህተት ነው።
ከኢብኑ ሙነወር
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
