ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 373 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 753,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 530

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 373 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 131,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.97%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.25% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 211 次浏览,首日通常累积 2 039 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 375
订阅者
+424 小时
+707
+13130
帖子存档
Consultancy Service for Construction Supervision of Road Projects

EOI For Consultancy Service Of Road Projects

የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ከስራ ተቆራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች ጋራ ዉይይት አደርገ። የውይይት መርሃ ግብሩ የተካሄደው በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በምንገድ ስራ ከተሰማሩ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ
+4
የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ከስራ ተቆራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች ጋራ ዉይይት አደርገ። የውይይት መርሃ ግብሩ የተካሄደው በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በምንገድ ስራ ከተሰማሩ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች ጋር በጅግጅጋ ከተማ ነው። በመርሃ ግብሩ ላይም የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ታድመዋል። በመድረኩ ላይም ኮንትራክተሮች አማካሪ ድርጅቶች ለስራ እንቅፋት ሆነውብናል ያሉትን ችገሮች አንስተዋል ። የወሰን ማስከበር የካሳ ከፍያ አለመቀላጠፍ የስላም እና ፀጥታ ችግር ፤ የሰዉ ሃይል እጥረት እና መሰል ተግዳሮቶች ፕሮጀክቶችን በግዜው ላለመፈጸም ምክንያት መሆናቸውንም አንስተዋል። በተለያዩ ምክንያቶች የተባሉት ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ያነሱት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ተግዳሮቶቹን ለመፍታት የሚያስችሉ የጋራ የቤት ስራዎችን መስራት የግድ ይላል ብለዋል፤ በተለይም የወሰን ማስከበር እና የከሳ ከፍያ ሂደቶች በተቀላጠፈ መልኩ ለመፍታት የሚያስችል ተቋማዊ የአሰራር ማሻሻያ እየተተገበረ መሆኑን የነሱት ዋና ዳሬክተሩ ይህን ሙሉ ለሙሉ ለመፈጸም የክልል የስራ ሃላፊዎችና በየደረጃው የሚገኙ የወረዳ ብሎም የቀበሌ መዋቅሮች ሚናቸው የጎላ መሆኑን አስገንዘበዋል። የስራ ተቋራጮችና አማካሪዎችም ችግር ፈቺ ስርዓትን በመዘርጋት ለግንበታ መዘግይት ምክንያት እንዳይኖር ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። በመድረኩ የተሳተፉት የሶማሌ ክልል የስራ ሃለፊዎች በበኩላቸው የክልሉን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ከስራ ተቆራጮች ጋር በትብብር እና በቅርበት የሚሰራ ኮሚቴ መቋቋሙን አንስተዋል።

ከጅግጅጋ እስከ ሀረሙከሌ መገንጠያ 104 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ስራ ጥቅምት 02/ 2012 ዓ.ም በይፋ ተጀመረ፡፡ የመንገዱ ግንባታ በብር 1,551,507,344.53 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ አምሳ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ አርባ አራት) የሚፈጅ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነዉ። ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮረፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) ጨረታዉን አሸንፎ ወደ ስራ የገባዉ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራዉን የሚያከናዉን ኤስ.ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ. (S G Consulting Engineers PLC) ነዉ፡፡ የመንገዱ ፕሮጀክት በከተማ 22.5 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት የለዉ ሲሆን አጠቃላይ ግንባታዉም በ 3 (ሶስት) ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የአካባቢዉን ማህበረሰብ የተሳለጠ የትራንስፖርት ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የሚሰራ ነዉ :: በነባሩ መንገድ ከመሃል ጅግጅጋ እስከ ሃረሙከሌ መገንጠያ (ድሬዳዋ ደወሌ የክፍያ) መንገድ ለመድርስ 202 ኪ.ሜ የሚፈጅ መሆኑ ይታወቃል ነገርግን አዲሱ የመንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቅ ከጅግጅጋ እስከ ሃረሙከሌ መገንጠያ (ድሬዳዋ ደወሌ የክፍያ) መንገድ ለመድርስ 104 ኪ.ሜ መጎዝ ብቻ ነዉ የሚጠበቅባቸዉ፤ ይህም የመንገዱን ረቀት በ99 ኪ.ሜ በመቀነስ የተሽከርካሪዎችን የጉዞና የጊዜ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ የምርትና የሸቀጣ ሸቀጥ ልውውጥ ያለምንም እንግልት እንዲከናወን ከማድረግ አንፃር የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነዉ፡፡ #madebo

ከ1.8 ቢልየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የዋርዴር-ቀብሪደሐር መንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ። የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ ም/ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂ.ሀብታሙ ተገኘ ፣ ከፌደራል ጥሪ የተደረገላቸው ባለስልጣናት እንዲሁም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት መንገዱን በይፋ የማስጀመር ስነ-ስርዓቱ ተካሂዷል። 138.8 ኪ.ሜ ርዝመት ያለውን የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ፕሮጀክት የሚያከናውነው ማክሮ የተባለ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚከናውኑት ደግሞ ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፒልሲ እና ሂቴክ ኮንሰልቲንግ በጋራ በመሆን ነው። የዋርዴር-ቀብሪደሐር መንገድ ፕሮጅክት የጎን ስፋት በዞን 21.5 በወረዳ 19ሜትር እና በቀበሌ 12 ሜትር ስፋት ሲሆን በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። ይህ የመንገድ በኮንትራት ውሉ መሰረት በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ ወጪም በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ደረጃ መገንባቱ በዋነኝነት የሚኖረው ጠቀሜታ ከዚህ ቀደም ከዋርዴር ተነስቶ ቀብሪደሐር ለመድረስ ከ3 ስዓት በላይ ይፈጅ የነበረ ሲሆን መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ይወስድ የነበረውን ጊዜ በግማሽ እንደሚያሳጥር ይጠበቃል። በአጠቃላይ በቂ የሆነ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረውን የአካባቢውን ሕብረተሰብ የዘመናዊ ትራንስፖርት ተጠቃሚ በማድረግ ከፊል አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮችን ምርታቸውን በቀላሉና በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ለማመላለስ ያስችላል። #meron

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ ጉዳት በመድረሱ አሽከርካሪዎች በጊዜያዊ ተለዋጭ መንገድ እንድትጠቀሙ የሚያስችል ግንባታ እያከናወነ ነው። ከሐረር ወደባቢሌ መስመር 20 ኪ.ሜ ዕርቀት ላይ የሚገኘው በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ ሳቢያ ጉዳት ደርሷል። በዚህም ምክንያት ተለዋጭ መንገድ እየተሰራ ይገኛል። ተለዋጭ መንገዱ በተወሰነ ደረጃ ተሽከርካሪዎችን በማሳለፍና ግዚያዊ መፍትሄ ለመስጠት እየተስራ ሲሆን በቀጣይ ጉዳት የደረሰበትን ድልድይ በመጠገን ዘለቄታዊ አገልግሎትን እንዲቀጥል ይደረጋል። በመስመሩ ተጓዦችና አሽከርካሪዎች ለሚያጋጥማችሁ እንግልት የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ይቅርታ እየጠየቀ የተለዋጭ መንገዱ ግንባታ በአፋጣኝ እየተሰራ ሲሆን አሽከርካሪዎች በትግስት በመጠበቅና በቅደም ተከተል በመተላለፍ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃልን።

አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ
+4
አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ

ለአንድ ቀን ተዝግቶ የነበረው የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የደብረማርቆስ ዲስትሪክት ዳሬክተር ኢንጂነር ጥሩነህ እንደገለፁልን የ
ለአንድ ቀን ተዝግቶ የነበረው የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የደብረማርቆስ ዲስትሪክት ዳሬክተር ኢንጂነር ጥሩነህ እንደገለፁልን የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ የመንገድ ፕሮጀክት 100 ኪ.ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን ኪሎ ሜትር 71 ላይ መስከረም 21 ቀን 2012 ዓ.ም በአካባቢው በጣለው ከባድ ዝናብ በተፈጠረው የካባ መናድ ምክንያት ለአንድ ቀን ዝግ እንደነበረ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ይህን የመንገድ ግንባታ ከሚያካሄደው CCC ከተባለው የቻይና የስራ ተቋራጭ ጋር በመነጋግር በአፋጣኝ መንገዱን በመጥረግ ለትራፊክ ክፍት እንዲሆን ተደርጓል። በተጨማሪም ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ያለ ሲሆን በቅርቡ ርክክብ እንደሚደረግ ገልፀዋል። #Meron

አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ በቅርብ ቀን Share @ethioroads
አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ በቅርብ ቀን Share @ethioroads

የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ! ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካ
የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ! ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም። መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ተስፋዬ ‹‹ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች የመንገድ ጠረጋ እየተከናወነ ነው፤ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት ደግሞ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንብ ይሠራል›› ብለዋል፡፡ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንቡ ከደሴ ዋጃ ያለውን መንገድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥመው ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ቆቦ መንገድ ከአዲስ አበባ በደሴ-ወልድያ-ቆቦ-መቀሌ የሚገባ ነው፡፡ መንገዱ ክልል ከክልል የሚያገናኝና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡ Via #AMMA

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ ማርቆስ፣ ጅማ፣ ነቀምት እና ኮምቦልቻ የሚገነቡ ሲሆን አዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድን ጨምሮ በከተማዋ እና በፈጣን መንገዶች መገናኛ ቦታዎች ላይ የማሻሻያ ሥራዎችን የሚጨምር ነው። # Addis Maleda

55 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍነው የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሺመልስ አብዲሳ ፣ የኢመባ ዋና
+3
55 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍነው የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሺመልስ አብዲሳ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ እና ሌሎች የፌዴራል እና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ ተጀመረ ። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3484609148246717

እንኳን አደረሳችሁ
እንኳን አደረሳችሁ

EOI for Dilla – Bulle – Haro Wachu Road Project.pdf1.21 KB

Invitation of tender for generator and solar Please share

Notice of Invitation for Bid Construction Works of Bridge Projects

Notice of Invitation for Bids Road Construction Project (Package I, II)

Notice Of Invitation for Bids Road Safety Works