uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 373 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 753-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 530-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 373 obunachiga ega bo‘ldi.

21 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 131 ga, so‘nggi 24 soatda esa 4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 38.97% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.25% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 211 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 039 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 11 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 22 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 375
Obunachilar
+424 soatlar
+707 kunlar
+13130 kunlar
Postlar arxiv
Consultancy Service for Construction Supervision of Road Projects

EOI For Consultancy Service Of Road Projects

የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ከስራ ተቆራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች ጋራ ዉይይት አደርገ። የውይይት መርሃ ግብሩ የተካሄደው በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በምንገድ ስራ ከተሰማሩ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ
+4
የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ከስራ ተቆራጮች እና አማካሪ ድርጅቶች ጋራ ዉይይት አደርገ። የውይይት መርሃ ግብሩ የተካሄደው በምስራቁ የሀገራችን ክፍል በምንገድ ስራ ከተሰማሩ የስራ ተቋራጮችና አማካሪ ድርጅቶች ጋር በጅግጅጋ ከተማ ነው። በመርሃ ግብሩ ላይም የኢትዮጵያ መንገዶች ባስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ እና የሶማሌ ክልል ከፍተኛ አመራሮች ታድመዋል። በመድረኩ ላይም ኮንትራክተሮች አማካሪ ድርጅቶች ለስራ እንቅፋት ሆነውብናል ያሉትን ችገሮች አንስተዋል ። የወሰን ማስከበር የካሳ ከፍያ አለመቀላጠፍ የስላም እና ፀጥታ ችግር ፤ የሰዉ ሃይል እጥረት እና መሰል ተግዳሮቶች ፕሮጀክቶችን በግዜው ላለመፈጸም ምክንያት መሆናቸውንም አንስተዋል። በተለያዩ ምክንያቶች የተባሉት ችግሮች እንደሚያጋጥሙ ያነሱት የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሰልጣን ዋና ዳሬክተር ኢንጅነር ሀብታሙ ተገኝ ተግዳሮቶቹን ለመፍታት የሚያስችሉ የጋራ የቤት ስራዎችን መስራት የግድ ይላል ብለዋል፤ በተለይም የወሰን ማስከበር እና የከሳ ከፍያ ሂደቶች በተቀላጠፈ መልኩ ለመፍታት የሚያስችል ተቋማዊ የአሰራር ማሻሻያ እየተተገበረ መሆኑን የነሱት ዋና ዳሬክተሩ ይህን ሙሉ ለሙሉ ለመፈጸም የክልል የስራ ሃላፊዎችና በየደረጃው የሚገኙ የወረዳ ብሎም የቀበሌ መዋቅሮች ሚናቸው የጎላ መሆኑን አስገንዘበዋል። የስራ ተቋራጮችና አማካሪዎችም ችግር ፈቺ ስርዓትን በመዘርጋት ለግንበታ መዘግይት ምክንያት እንዳይኖር ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸውም አሳስበዋል። በመድረኩ የተሳተፉት የሶማሌ ክልል የስራ ሃለፊዎች በበኩላቸው የክልሉን ሰላምና ደህንነት በማስጠበቅ ከስራ ተቆራጮች ጋር በትብብር እና በቅርበት የሚሰራ ኮሚቴ መቋቋሙን አንስተዋል።

ከጅግጅጋ እስከ ሀረሙከሌ መገንጠያ 104 ኪ.ሜ የሚረዝመው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ የግንባታ ስራ ጥቅምት 02/ 2012 ዓ.ም በይፋ ተጀመረ፡፡ የመንገዱ ግንባታ በብር 1,551,507,344.53 (አንድ ቢሊዮን አምስት መቶ አምሳ አንድ ሚሊዮን አምስት መቶ ሰባት ሺህ ሦስት መቶ አርባ አራት) የሚፈጅ ሲሆን ሙሉ ለሙሉ የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነዉ። ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮረፖሬሽን (China Civil Engineering Construction Corporation (CCECC) ጨረታዉን አሸንፎ ወደ ስራ የገባዉ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራዉን የሚያከናዉን ኤስ.ጂ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ.የተ.የግ.ማ. (S G Consulting Engineers PLC) ነዉ፡፡ የመንገዱ ፕሮጀክት በከተማ 22.5 ሜትር እና በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት የለዉ ሲሆን አጠቃላይ ግንባታዉም በ 3 (ሶስት) ዓመት ዉስጥ ተጠናቆ ለህዝብ አገልግሎት መስጠት ይጀምራል፡፡ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ በአጠቃላይ የአካባቢዉን ማህበረሰብ የተሳለጠ የትራንስፖርት ተጠቃሚ ለማድረግ ታስቦ የሚሰራ ነዉ :: በነባሩ መንገድ ከመሃል ጅግጅጋ እስከ ሃረሙከሌ መገንጠያ (ድሬዳዋ ደወሌ የክፍያ) መንገድ ለመድርስ 202 ኪ.ሜ የሚፈጅ መሆኑ ይታወቃል ነገርግን አዲሱ የመንገድ ፕሮጀክት ሲጠናቅ ከጅግጅጋ እስከ ሃረሙከሌ መገንጠያ (ድሬዳዋ ደወሌ የክፍያ) መንገድ ለመድርስ 104 ኪ.ሜ መጎዝ ብቻ ነዉ የሚጠበቅባቸዉ፤ ይህም የመንገዱን ረቀት በ99 ኪ.ሜ በመቀነስ የተሽከርካሪዎችን የጉዞና የጊዜ ወጪን በከፍተኛ ደረጃ በመቀነስ የምርትና የሸቀጣ ሸቀጥ ልውውጥ ያለምንም እንግልት እንዲከናወን ከማድረግ አንፃር የሚያበረክተው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነዉ፡፡ #madebo

ከ1.8 ቢልየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የዋርዴር-ቀብሪደሐር መንገድ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ። የሶማሌ ብሔራዊ ክልላዊ ም/ ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፌ መሀመድ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢንጂ.ሀብታሙ ተገኘ ፣ ከፌደራል ጥሪ የተደረገላቸው ባለስልጣናት እንዲሁም የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች በተገኙበት በዛሬው ዕለት መንገዱን በይፋ የማስጀመር ስነ-ስርዓቱ ተካሂዷል። 138.8 ኪ.ሜ ርዝመት ያለውን የአስፋልት መንገድ ግንባታ ስራ ፕሮጀክት የሚያከናውነው ማክሮ የተባለ ሀገር በቀል የስራ ተቋራጭ ድርጅት ነው። የማማከርና የቁጥጥር ስራ የሚከናውኑት ደግሞ ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፒልሲ እና ሂቴክ ኮንሰልቲንግ በጋራ በመሆን ነው። የዋርዴር-ቀብሪደሐር መንገድ ፕሮጅክት የጎን ስፋት በዞን 21.5 በወረዳ 19ሜትር እና በቀበሌ 12 ሜትር ስፋት ሲሆን በገጠር የመንገድ ትከሻን ጨምሮ 10 ሜትር ስፋት ይኖረዋል። ይህ የመንገድ በኮንትራት ውሉ መሰረት በአራት ዓመት ጊዜ ውስጥ ይጠናቀቃል ተብሎ የሚጠበቅ ሲሆን፣ የፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ ወጪም በኢትዮጵያ መንግስት ይሸፈናል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ደረጃ መገንባቱ በዋነኝነት የሚኖረው ጠቀሜታ ከዚህ ቀደም ከዋርዴር ተነስቶ ቀብሪደሐር ለመድረስ ከ3 ስዓት በላይ ይፈጅ የነበረ ሲሆን መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ይወስድ የነበረውን ጊዜ በግማሽ እንደሚያሳጥር ይጠበቃል። በአጠቃላይ በቂ የሆነ የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረውን የአካባቢውን ሕብረተሰብ የዘመናዊ ትራንስፖርት ተጠቃሚ በማድረግ ከፊል አርሶ አደሮችና አርብቶ አደሮችን ምርታቸውን በቀላሉና በተቀላጠፈ ሁኔታ ወደተለያዩ የአገሪቱ ክልሎች ለማመላለስ ያስችላል። #meron

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ ጉዳት በመድረሱ አሽከርካሪዎች በጊዜያዊ ተለዋጭ መንገድ እንድትጠቀሙ የሚያስችል ግንባታ እያከናወነ ነው። ከሐረር ወደባቢሌ መስመር 20 ኪ.ሜ ዕርቀት ላይ የሚገኘው በኤረር ወንዝ ድልድይ ላይ በአካባቢው በጣለው ከፍተኛ ዝናብ ምክንያት በተከሰተው ጎርፍ ሳቢያ ጉዳት ደርሷል። በዚህም ምክንያት ተለዋጭ መንገድ እየተሰራ ይገኛል። ተለዋጭ መንገዱ በተወሰነ ደረጃ ተሽከርካሪዎችን በማሳለፍና ግዚያዊ መፍትሄ ለመስጠት እየተስራ ሲሆን በቀጣይ ጉዳት የደረሰበትን ድልድይ በመጠገን ዘለቄታዊ አገልግሎትን እንዲቀጥል ይደረጋል። በመስመሩ ተጓዦችና አሽከርካሪዎች ለሚያጋጥማችሁ እንግልት የባለሥልጣን መስሪያ ቤቱ ይቅርታ እየጠየቀ የተለዋጭ መንገዱ ግንባታ በአፋጣኝ እየተሰራ ሲሆን አሽከርካሪዎች በትግስት በመጠበቅና በቅደም ተከተል በመተላለፍ የበኩላችሁን አስተዋፅዖ እንድታደርጉልን በትህትና እንጠይቃልን።

አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ
+4
አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ

ለአንድ ቀን ተዝግቶ የነበረው የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የደብረማርቆስ ዲስትሪክት ዳሬክተር ኢንጂነር ጥሩነህ እንደገለፁልን የ
ለአንድ ቀን ተዝግቶ የነበረው የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ መንገድ ለትራፊክ ክፍት ሆነ። የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን የደብረማርቆስ ዲስትሪክት ዳሬክተር ኢንጂነር ጥሩነህ እንደገለፁልን የኢንጅባራ - ቻግኒ - ፓዊ መገንጠያ የመንገድ ፕሮጀክት 100 ኪ.ሜትር ርዝማኔ ያለው ሲሆን ኪሎ ሜትር 71 ላይ መስከረም 21 ቀን 2012 ዓ.ም በአካባቢው በጣለው ከባድ ዝናብ በተፈጠረው የካባ መናድ ምክንያት ለአንድ ቀን ዝግ እንደነበረ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት ይህን የመንገድ ግንባታ ከሚያካሄደው CCC ከተባለው የቻይና የስራ ተቋራጭ ጋር በመነጋግር በአፋጣኝ መንገዱን በመጥረግ ለትራፊክ ክፍት እንዲሆን ተደርጓል። በተጨማሪም ይህ የመንገድ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ያለ ሲሆን በቅርቡ ርክክብ እንደሚደረግ ገልፀዋል። #Meron

አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ በቅርብ ቀን Share @ethioroads
አለምገና ማሠልጠኛ ማዕከል የሚሰጣቸውን ስልጠና አይነትና የሚፈጀው ጊዜ በቅርብ ቀን Share @ethioroads

የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ! ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካ
የወልድያ-ቆቦ መንገድ በደለል ምክንያት መዘጋቱ ተገለፀ! ከወልዲያ ቆቦ የሚወስደው ዋና የአስፓልት መንገድ በጎርፍ ምክንያት በተደጋጋሚ የሚዘጋ ነው። ዛሬም በጣለው ዝናብ ከቀላል እስከ ከባድ ተሽከርካሪዎች መንቀሳቀስ አልቻሉም። መንገዱ የተዘጋው ከተራራማ ቦታዎች የሚወርድ ደለልን መከላከል የሚያስችል ደጋፊ የግንብ አጥር ባለመኖሩ ነው። በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የኮምቦልቻ መንገድ ዝርጋታ ዳይሬክተር አቶ ሳምሶን ተስፋዬ ‹‹ችግር በተፈጠረባቸው አካባቢዎች የመንገድ ጠረጋ እየተከናወነ ነው፤ በዘላቂነት ችግሩን ለመፍታት ደግሞ ከሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት በመመደብ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንብ ይሠራል›› ብለዋል፡፡ የጎርፍ መከላከያ ደጋፊ ግንቡ ከደሴ ዋጃ ያለውን መንገድም ተመሳሳይ ችግር እንዳይገጥመው ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የወልድያ ቆቦ መንገድ ከአዲስ አበባ በደሴ-ወልድያ-ቆቦ-መቀሌ የሚገባ ነው፡፡ መንገዱ ክልል ከክልል የሚያገናኝና በኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን የሚተዳደር ነው፡፡ Via #AMMA

የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ
የኢትዮጵያ መንገዶች ባለሥልጣን አዲስ አበባን ከክልል ከተሞች ጋር የሚያገናኙ አራት ፈጣን መንገዶችን ለመገንባት በዝግጅት ላይ እንደሚገኝ ገለፀ። ፈጣን መንገዶቹ አዲስ አበባን መዳረሻ በማድረግ ደብረ ማርቆስ፣ ጅማ፣ ነቀምት እና ኮምቦልቻ የሚገነቡ ሲሆን አዲስ አበባ አዳማ ፈጣን መንገድን ጨምሮ በከተማዋ እና በፈጣን መንገዶች መገናኛ ቦታዎች ላይ የማሻሻያ ሥራዎችን የሚጨምር ነው። # Addis Maleda

55 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍነው የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሺመልስ አብዲሳ ፣ የኢመባ ዋና
+3
55 ኪ.ሜ ርዝመት የሚሸፍነው የቢሾፍቱ-ጨፌ ዶንሳ-ሰንዳፋ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ ሺመልስ አብዲሳ ፣ የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሃብታሙ ተገኘ እና ሌሎች የፌዴራል እና የክልል ባለስልጣናት በተገኙበት በይፋ ተጀመረ ። https://www.facebook.com/www.era.gov.et/posts/3484609148246717

እንኳን አደረሳችሁ
እንኳን አደረሳችሁ

EOI for Dilla – Bulle – Haro Wachu Road Project.pdf1.21 KB

Invitation of tender for generator and solar Please share

Notice of Invitation for Bid Construction Works of Bridge Projects

Notice of Invitation for Bids Road Construction Project (Package I, II)

Notice Of Invitation for Bids Road Safety Works