ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 373 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 532

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 373 名订阅者。

根据 21 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 131,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 38.97%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.25% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 211 次浏览,首日通常累积 2 039 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 22 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 375
订阅者
+424 小时
+707
+13130
帖子存档
Invitation for Bid Consultancy Service for Concept Design and Feasibility Study of Expressway Road Projects /International Competitive Bidding/

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ሥራ በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል፡፡ የግንባታ ሥራውን ማስጀመሪያ ሥነሥርዓት ላይ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመሰገን ጥሩነህ፣ የትራንስፖርት ሚኒስተር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ፣ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢነጂነር ሃብታሙ ተገኘ እንዲሁም የፌደራል የክልል የስራ ሃላፊዎችና የአካባቢው ነዋሪዎች ተገኝተዋል። አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ገጽታ * የውል ስምምነት ፡- መጋቢት 18 ቀን 2011 ዓ.ም * የሥራ ተቋራጭ ፡- አለማቀፉ የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ /CCCC/ China communication construction company * አማካሪ ድርጅት ፡- ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ አማካሪ ድርጅት ከስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ድርጅት ከተባለ አገር በቀል ንኡስ አማካሪ ጋር በጋራ በመሆን ያከናውኑታል /Botek Bosporus techni￾cal consulting in JV with Stadia Engineering Worksconsultant plc. * የግንባታ ወጪ ፡- 1,437,000,000 ብር * የግንባታውን ወጪ የሚሸፍነው፡- በኢትዮጵያ መንግስት ተሸፍኗል፡፡ * የግንባታው አይነት ፡- ዲዛይንና ግንባታ /ተቋራጭ ድርጅቱ ዲዛይና ግንባታን በጋራ አካቶ የሚሰራበት የኮንትራት ውል አይነት ነው/፡፡ * የድልድዩ አይነት ፡- የተንጠልጣይና የሳጥን ቅርፅ ያላቸውን ረጃጅም ድልድዮችን ዲዛይን በማዋሀድ በአዲስ የዲዛይን ጥበብ የሚገነባው ኤክስትራዶስድ extradosed የተባለውን አይነት ድልድይ ነው፡፡ * ርዝመት ፡- 380 ሜትር * የጎን ስፋት ፡- 43 ሜትር የጎን ስፋት ያለው ሲሆን በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ ይችላል፡፡ በተጨማሪም የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር በሁለቱም አቅጣጫ እንዲሁም 5 ሜትር የእግረኛ መሄጃን ያካተተ ነው ፡፡ * የድልድዩ ግንባታ ስራ፡- ከድልድዩ ግንባታ ጎን ለጎን ተያያዥ የኮንክሪት ስትራክቸር ስራዎችና፣ የተሽከርካሪ መወጣጫ /ramp/ ፣ የትራፊክ ምልክቶች፣ የድልድይ ላይ መብራቶች ስራም ያካተተ ነው ፡፡ * ለግንባታ የተሰጠው ጊዜ ፡- ሶስት አመት የኘሮጀክቱ ሁለንተናዊ ፋይዳ * በአሁኑ ወቅት ከአቅሙ በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘውን ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ ላይ ይደርስ የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ እና ጫና ያስቀራል፡፡ * ከባህርዳር ከተማ እድገት እና ውበት ጋር ያልተመጣጠነ የነበረውን እና ረጅም እድሜ ያስቆተረውን ድልድይ በመተካት ከዘመኑ ጋር አብሮ የሚሄድ ደረጃውን የጠበቀ የመሠረተ ልማት ተጠቀሚ እንዲሆን የበኩሉን ድርሻ ይወጣል፡፡ * አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ከሀገራዊ ፋይዳውም አልፎ ከጎረቤት ሀገር ሱዳን ጋር የሚያገናኝ በመሆኑ የሁለቱን ሀገሮች የንግድና የህዝብ ለህዝብ ግንኙነት ይበልጥ ያስተሳስራል፡፡ * ለሀገሪቱ የገቢ ወጪ የንግድ እንቅስቃሴም የበኩሉን አስተዋጽዖ ያበረክታል። * ድልድዩን ለሚያቋርጡ እግረኞች የትራፊክ አደጋ ሳያሰጋቸው በተዘገጀላቸው 5 ሜትር ስፋት ባለው መሄጃ ላይ በመጠቀም ከስጋት ነጻ ያደርግላቸዋል፡፡ * ብስክሌት ለሚጠቀሙ የአካባው ነዋሪዎችም ሆኑ ቱሪስቶች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። * በተጨማሪም በባህርዳር ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቅረፍ የበኩሉን ሚና ይጫወታል፡፡ * ብዙ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ላላት ባህርዳር እና አካባቢዋ አዲሱ ድልድይ እራሱን የቻለ የቱሪስት መስህብ በመሆን አወንታዊ ሚናውን ይወጣል፡፡

የባህርዳር -ጢስ እሳት የመንገድ ፕሮጀክት ግንባታ ዛሬ ተጀመረ፡፡ የመንገድ ግንባታውን ያስጀመሩት ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን ናቸው፡፡ በመርሃ ግብሩ ላይ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመሰገን ጥሩነህ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢነጂነር ሃብታሙ ተገኘ መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡ እንዲሁም የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ ጨምሮ ሌሎች የፌደራል የክልል የስራ ሃላፊዎች፣ የሃይማኖት አባቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች የፕሮግራሙ ታዳሚዎች ነበሩ። ጢስ እሳት በአማራ ክልል ከባህርዳር ከተማ በቅርብ ርቀት የምትገኝ ታሪካዊ ከተማ ናት። ከተማዋ ምንም እንኳን ልዩ ልዩ ተፈጥሮዓዊ የቱሪስት መስህቦች እና ከፍተኛ የግብርና ምርቶች መገኛ ብትሆንም፤ የአካባቢው ነዋሪዎች ለዘመናት በመንገድ መሰረተ ልማት ችግር ሲንገላቱ መቆየታቸዉ ሀቅ ነዉ፡፡ መንግስት ይህንን ችግር ከግንዛቤ በማስገባት እና ችግሩን በዘላቂነት ለመፍታት የባህርዳር ጢስ እሳት የመንገድ ፕሮጀክትን በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ለመገንባት ዛሬ ስራ ጀምሯል፡፡ ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የአገር ዉስጥና የዉጭ ጎብኚዎችን ቁጥር በመጨመር ለአካባቢዉ ብሎም ለክልሉ ህዝብ ገቢ በማስገኝት ረገድ የላቀ ሚና ይጫዎታል፡፡ ይህን የመንገድ ፕሮጀክት አገር በቀሉ ሜልኮን ኮንስትራክሽን ከ767 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የሚያከናውን ሲሆን ሙሉ ወጪውም በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፍን ይሆናል፡፡ በተጨማሪም በዚህ አካባቢ ጤፍ፤ በቆሎ እና ሌሎች የአዝዕርት ምርቶች የሚመረቱ ሲሆን፣ ይህ መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የአካባቢው አርሶ አደር ያመረተውን ምርት በአቅራቢያው ወደ ሚገኝ ገበያ ወይም የንግድ ማዕከል በማውጣት ካለ ምንም እንግልት ከምርቱ ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችለዋል፡፡

የባህር ዳር - ዘማ ወንዝ -ፈለገብርሃን አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ደመቀ መኮንን በተገኙበት በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል፡፡ በሁለት ኮንትራት ተከፍሎ ግንባታው ሲካሄድ የቆየው የባህርዳር -ዜማወንዝ -ፈለገ ብርሃን 175 ኪ.ሜ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ስራ ነው ዛሬ የተመረቀው፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ሙሉ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ሲሆን ከ2.4 ቢሊየን ብር በላይ የግንባታ ወጪንም ጠይቋል፡፡ የዚህ መንገድ የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው የባህርዳር -ዜማወንዝ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ሲኖሃይድሮ በተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲከናወን የቆየ ሲሆን፣ የምህንድስ የቁጥጥርና የማማከር ስራውን ሲያካሂድ የቆየው ደግሞ አገር በቀሉ ኔት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ነው፡፡ በተጨማሪም የዚህ መንገድ ቀጣይ ኮንትራት የሆነው የዜማ ወንዝ-ፈለገብርሃን የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ China Railway 7th Group በተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ድርጅት ሲከናወን የቆየ ሲሆን፣ አገር በቀሉ አይኮን ኢንጂነሪንግ ደግሞ የመንገዱን የምህንድስና ቁጥጥርና የማማከር ስራ ሲያካሂድ ቆይቷል፡፡ የባህርዳር -ዜማ ወንዝ-ፈለገብርሃን መንገድ የቀድሞ ገፅታ ለትራንስፖርት አመቺ ያልነበረ በመሆኑ ተሽከርካሪዎች ለተደጋጋሚ ብልሽት ይዳረጉ ነበር፡፡ ከዚህ ቀደም ከባህርዳር -ደብረማርቆስ -አዲስአበባ ለመድረስ 540 ኪ.ሜ መጓዝ ይጠይቅ ነበር፤ ይህ መንገድ ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ ይህን ርቀት በ80 ኪ.ሜ የሚያሳጥር በመሆኑ ከዚህ ቀደም በነዋሪዎችና በአሽከርካሪዎች ላይ ይደርስ የነበረውን እንግልት እና የትራንስፖርት ወጪ ከመቀነስ አንፃር የሚጫወተው ሚና ከፍተኛ ነው፡፡ በመሆኑም የዚህ መንገድ ግንባታ መጠናቀቅ ከዚህ በፊት የነበረውን የትራንስፖርት ችግር በመቅረፍየ አካባቢው ነዋሪ በተመጣጣኝ ዋጋ ወደ ፈለገው ቦታ የሚንቀሳቀስበትን ሁኔታ የሚያመቻች ከመሆኑም በተጨማሪ፣ የቀዬው አርሶ አደሮች ምርታቸውን ካለምንም ችግር በአፋጣኝ ወደ ማዕከላዊ እና የውጭ ገበያ በማውጣት ተጠቃሚ እንዲሆኑ ያስችላቸዋል፡፡ የዚህ ፕሮጅክት እውን መሆን ጠቀሜታና ደስታው ለአካባቢው እና ለክልሉ ብቻም ሳይሆን ለሀገራችን የገበያ መረጋጋት ጭምር እንድምታው ላቅ ያለ ነው፡፡ ከዚህም ባሻገር የአካባቢው ትንንሽ መንደሮች በከተማ ደረጃ እንዲስፋፉ ከማድረግ እንዲሁም የጤና፣ የትምህርት እና ሌሎች የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት እንዲስፋፉ ከማድረግ አኳያ የሚኖረው ሚናም ከፍተኛ ነው፡፡ በሞጣ ከተማ በተካሄደው የመንገድ ምረቃት መርሃግብር ላይ የአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ርዕሰ መስተዳደር አቶ ተመሰገን ጥሩነህ፣ የትራንስፖርት ሚኒስትር ወ/ሮ ዳግማዊት ሞገስ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ኢነጂነር ሃብታሙ ተገኘ መልዕክት አስተላልፈዋል እንዲሁም የፌደራል የክልል የስራ ሃላፊዎችና የሃይማኖት አባቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች የፕሮግራሙ ታዳሚዎች ነበሩ ።

እንኳን አደረሳችሁ መልካም አዲስ አመት 🌼🌼🌼
እንኳን አደረሳችሁ መልካም አዲስ አመት 🌼🌼🌼

እንኳን ለ2012 አዲስ አመት አደራሣችሁ መልዕክት የኢመባ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር ሀብታሙ ተገኘ አስተላልፈዋል ።

Gohatsion Dejen road

Invitation for Stakeholder discussion To Whom It May Concern
+1
Invitation for Stakeholder discussion To Whom It May Concern

Invitation for Stakeholder discussion To Whom It May Concern
+1
Invitation for Stakeholder discussion To Whom It May Concern

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር - Telegram 频道 @ethioroads 的统计与分析