ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。
根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 95,过去 24 小时变化为 18,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 485 次浏览,首日通常累积 2 032 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 331
订阅者
+1824 小时
+417 天
+9530 天
帖子存档
13 331
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ
አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡
በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡
የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡
በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡
በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡
ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
ማሳሰቢያ!!
7ኛው የመንገድ ምርምር ኮንፍረንስ
በቃሊቲ የመንገድ ምርምር ማዕከል ማክሰኞ ነሃሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ፡ 30 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
13 331
በተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደት ቁጥጥር ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ
አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 11 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደትን ለመወሰንና ለመቆጣጠር የወጣዉን ደንብ ቁጥር 491/2014 የተመለከተ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።
በዉይይቱ ላይ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል አዲሱን የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደት ለመቆጣጠር የወጣውን ደንብ የተመለከተ ሰነድ ቀርቧል።
የቀረበው ሰነድ በዋናነት በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን ክብደት ለመቆጣጠር እና የአዲሱን ደንብ አተገባበር አስመልክቶ ግንዛቤን ለመፍጠር ያለመ ነው።
በዕለቱም በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የመሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንዲሁም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ከመጠን በላይ የሆነ ጭነትን ለመቆጣጠር እና የአገሪቱን የትራንስፖርት ህጎች ያለአግባብ በሚጠቀሙ የሀገር ውስጥም ሆነ አህጉራዊ የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ቁጥጥር ለማድረግ በወጣው ደንብ አጠቃላይ ትግበራ ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደርጓል ።
በምክክሩም ተሽከርካሪዎች በህግ የተፈቀደላቸውን ክብደት በተመለከተ የወጣዉን የጭነት ደንብ በመንገዶች ላይ የማስከበር ኃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑም ተገልጿል።
በመድረኩ የተገኙ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አዲሱን አዋጅ የተመለከቱ እና ከደንቡ ቀጣይ አተገባበር ጋር የሚያያዙ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
በተለይም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ባሉት የተሽከርካሪዎች ክብደት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ወጥነት ያለው አሰራር መዘርጋት ይገባዋል ተብሏል ።
በተጨማሪም መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን እና ቅንጅታዊ አሰራርን በመፍጠር በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የጋራ ጥረቶች ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል።
ደንቡ በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ እየደረሱ የሚገኙ ጉዳቶችን መቆጣጠር እንዲቻል በዲዛይን ወቅት ታሳቢ የተደረገላቸውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል::
በተጨማሪም የሀገራችን የተሽከርካሪዎች የክብደት ወሰን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ስለሚሆን ሀገራችን ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርገውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያግዛል፡፡
አዲሱ ደንብ በተሽከርካሪዎች ላይ የሚስተዋለውን ከተቀመጠው የክብደት ወሰን በላይ የመጫን ችግር ከምንጩ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋፆ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
Facebook
Log in or sign up to view
See posts, photos and more on Facebook.
13 331
በተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደት ቁጥጥር ላይ ያጋጠሙ ችግሮችን የተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ
አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 11 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደትን ለመወሰንና ለመቆጣጠር የወጣዉን ደንብ ቁጥር 491/2014 የተመለከተ የዉይይት መድረክ ተካሄደ።
በዉይይቱ ላይ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል አዲሱን የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደት ለመቆጣጠር የወጣውን ደንብ የተመለከተ ሰነድ ቀርቧል።
የቀረበው ሰነድ በዋናነት በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን ክብደት ለመቆጣጠር እና የአዲሱን ደንብ አተገባበር አስመልክቶ ግንዛቤን ለመፍጠር ያለመ ነው።
በዕለቱም በከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር የመሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር ወንድሙ ሴታ እንዲሁም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል።
በመድረኩ ከመጠን በላይ የሆነ ጭነትን ለመቆጣጠር እና የአገሪቱን የትራንስፖርት ህጎች ያለአግባብ በሚጠቀሙ የሀገር ውስጥም ሆነ አህጉራዊ የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ ላይ ቁጥጥር ለማድረግ በወጣው ደንብ አጠቃላይ ትግበራ ዙሪያ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር ምክክር ተደርጓል ።
በምምክሩም ተሽከርካሪዎች በህግ የተፈቀደላቸውን ክብደት በተመለከተ የወጣዉን የጭነት ደንብ በመንገዶች ላይ የማስከበር ኃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑም ተገልጿል።
በመድረኩ የተገኙ የተለያዩ ባለድርሻ አካላት አዲሱን አዋጅ የተመለከቱ እና ከደንቡ ቀጣይ አተገባበር ጋር የሚያያዙ ጥያቄዎችን አቅርበዋል።
በተለይም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ባሉት የተሽከርካሪዎች ክብደት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች ወጥነት ያለው አሰራር መዘርጋት ይገባዋል ተብሏል ።
በተጨማሪም መሰል ግንዛቤዎችንና ቅንጅታዊ አሰራር በመፍጠር በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ የጋራ ጥረቶች ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል።
ደንቡ በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ እየደረሱ የሚገኙ ጉዳቶችን መቆጣጠር እንዲቻል በዲዛይን ወቅት ታሳቢ የተደረገላቸውን አገልግሎት እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል::
በተጨማሪም የሀገራችን የተሸከርካሪዎች የክብደት ወሰን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ስለሚሆን ሀገራችን ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርገውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያግዛል፡፡
አዲሱ ደንብ በተሽከርካሪዎች ላይ የሚስተዋለውን ከተቀመጠው የክብደት ወሰን በላይ የመጫን ችግር ከምንጩ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋፆ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።
13 331
ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ተግባር መፈጸም የሁላችንም ኃላፊነት እንደሆነ የሚዘነጋ ጉዳይ አይደለም።
መንገዶችን ለብልሽት ከሚዳርጉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው ከተፈቀደው ክብደት በላይ በመጫን መጓዝ (Axels load) ነው ።
በዚህም ረገድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከባድ ጭነትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ሚዛን ጣቢያዎችን በማቋቋም እንደሚሰራ ይታወቃል።
የተሽከርካሪዎችን ክብደት የመቆጣጠር ዋና አላማ በመንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸዉ የአክስል ክብደት መጠን በላይ ጭነዉ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመንገድ አዉታሮች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ የመከላከል እንዲሁም መንገዶች እና ድልድዮች ሳይበላሹ በዲዛይኑ መሰረት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነዉ፡፡
በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሚዛን ጣቢያዎች እና መገኛ ቦታቸው፡-
14 ሚዛን ጣቢያዎች በተለያዩ ቦታዎቸ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ፣ መገኛ አካባቢያቸውም፡- ሞጆ ፣ ሆሎታ ፣ ሱሉልታ ፣ ሠንዳፋ ፣ ዲማ (ሰበታ) ፣ ጂማ ፣ ሻሸመኔ ፣ አዋሽ ፣ ሠመራ ፣ደንገጎ ፣ ኮምቦልቻ ፣ ጢቅ (ደጀን) ፣ወረታ ፣ ኩይሓ (መቀሌ) ናቸው።
በተለይም የአዋሽ 7 እና የሠመራ የሚዛን ጣቢያዎች ከፍተኛ የሆነ የወጪ እና ገቢ ንግድን ያስተናግዳሉ። ይህ መስመር ከባባድ መኪኖች ከጅቡቲ ወደ መሃል ሀገር የሚመላለሱበት እና በቀን ውስጥ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ዋና አውራ ጎዳና ነው። በመስመሩ ከተፈቀደው መጠን በላይ በመጫን የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች የሚስተዋሉ በመሆኑ መንገዱ ለከፍተኛ ጉዳት እየተዳረገ ይገኛል፡፡
ይህንን ክፍተት ለመዝጋት ትርፍ የጫነ ተሽከርካሪ ጉዞውን መቀጠል የሚችለው ለጫነው ትርፍ ጭነት ተገቢውን የቅጣት ክፍያ ከከፈለ በኋላ ትርፉን እንዲያራግፍ አሊያም በሌላ ተሽከርካሪ ጭኖ እንዲወስድ ህጉ ይደነግጋል፡፡
ለእያንዳንዱ አክስል የሚፈቀድ የክብደት መጠን
I. የነጠላ አክስል (Axle) ሁለት ወይም ሶስት ጎማዎች የተገጠሙለት ተሽከርካሪ የፊት እና የኋላ የአክስል (Axle) ክፍሎች ጠቅላላ የክብደት መጠን የሚከተለዉ ነዉ፡-
ሀ) የፊት አክስል (የመሪ አክስል) Steering Axle የማይፈቀድ የክብደት መጠን ከ7.7 ቶን (77 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ፤
ለ) ከመሪዉ አክስል (Steering Axle) ዉጪ ሆኖ ነጠላ ጎማ የተገጠመለት ተሸከርካሪ ከሆነ ጠቅላላ ክብደቱ ከ8 ቶን (80 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡
ሐ) የኃላዉ የአክስል ክፍል አራት ጎማዎች የተገጠሙለት ከሆነ የአክስል ክብደቱ ከ10 ቶን (100 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡
II. የተሸከርካሪዉ የአክስል ክፍል ባለ ሁለት (Tandem Axle Unit) ወይም ባለሶስት (Tri-dem axle) ሲሆን ፣ ለተሽከርካሪዉ የማይፈቀድ የአክስል (Axle) የክብደት መጠን እንደሚከተለዉ ነዉ፡-
ሀ) የጥንድ አክስል (Steering Tandem Axle) ክብደት ሳይጨምር ጠቅላላ የኋላ የአክስል ክብደቱ በአንድ ላይ ተደምሮ ከ18 ቶን (180 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡
በመሆኑም ሁሉም የተሽከርካሪ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች እንዲሁም የመንገድ ተጠቃሚዎች ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በመተባበር ከፍተኛ የሃገር ሃብት የፈሰሰበትን የመንገድ መሰረተ ልማት ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ ለማሳሰብ እንወዳለን።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 331
የሶዶ - አረካ መገንጠያ እና የሶዶ ከተማ - ዎሊ መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው
አዲስአበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2016 (ኢ መ አ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን የሶዶ - ታርጫ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሶዶ - አረካ መገንጠያ እና የሶዶ ከተማ - ዎሊ ምዕራፍ-3 መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው።
ግንባታውን የሚያከናውነው ዓለም-አቀፉ ቻይና ፈርስት ሀይዌይ እንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ፥ አሁን ላይ ለግንባታው የሚያስፈልጉ የካምፕ ግንባታ እንዲሁም የሰው ኃይል እና ማሽነሪ የማደራጀት የቅየሳ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመሥራት ላይ ነው፡፡ የጥራት እና ቁጥጥር ሥራው በሀገር-በቀሎቹ ጂ እና ዋይ ኢንጅነሪንግ ከደውል ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጋራ ያከናውናሉ።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 13 ነጥብ 57 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የሚገነባው። ለግንባታው የተመደበው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል።
ይህ የሶዶ ከተማ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ በተለይም ከተማዋ በቅርቡ የተቋቋመው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ መሆኗን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በበቂ መልኩ ማስተናገድ የሚያስችል ነው። ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ውበት እና ሁለንተናዊ ዕድገት በእጅጉ የሚያሳልጥ ይሆናል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ የከርብ ስቶን እና ከልቨርቶችን ጨምሮ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ እንዲሁም የመኪና ማሳረፊያ ግንባታ ሥራዎችን ያካትታል።
በፕሮጀክቱ የመንገድ ወሰን ክልል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ንብረቶች የሚገኙ በመሆኑ፣ ኅብረተሰቡም ሆነ በየመዋቅሩ የሚገኙ የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ ኢ መ አ ይጠይቃል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
