ar
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

الذهاب إلى القناة على Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

تُعد قناة ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 13 331 مشتركاً، محتلاً المرتبة 1 756 في فئة النقل والمرتبة 2 537 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 13 331 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 17 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 95، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 18، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 41.14‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.24‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 5 485 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 032 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 16.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 18 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة النقل.

13 331
المشتركون
+1824 ساعات
+417 أيام
+9530 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የአንድ ጀንበር የአረንጓዴ አሻራ መርሐ-ግብር አካሄደ አዲስአበባ ፣ ነሐሴ 17/2016 ዓ.ም (ኢመአ) የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተከናወነ የሚገኘውን የአንድ ጀንበር አረንጓዴ ዐሻራ ችግኝ ተከላ ዘመቻን በእንጦጦ የጠፈር ምርምር አካባቢ አካሄደ፡፡ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ በሚገኘው የችግኝ ተከላ ዘመቻ ላይ የኢመአ የስራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች አረንጓዴ ዐሻራቸውን አኑረዋል፡፡ የኢመአ ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን የአካባቢን የአየር ንብረት ሚዛን የሚጠብቁ እና ለምግብነት የሚውሉ የተለያዩ ችግኞች መተከላቸውን ተናግረዋል፡፡ አክለውም በመንገድ ግንባታ ሂደት ወቅት የተነሱ ዛፎችን በመተካት ፤ የአካባቢውን ስነ-ምህዳር ለመጠበቅ ሁሉም የተቋሙ ማህበረሰብና ባለድርሻ አካላት የበከላቸውን አስተዋጽኦ ሊወጡ እንደሚገባም ገልፀዋል፡፡ በዚሁ መርሃ ግብር ላይ የተገኙ ምክትል ዋና ዳይሬክተሮች በበኩላቸው በሀገር አቀፍ ደረጃ የታቀደውን በአንድ ጀንበር 600 ሚሊዬን ችግኞችን የመትከል መርሃ-ግብር ላይ እንደ ተቋም በመሳተፍ ሀገራዊ ግዴታቸውን በመወጣታቸው ደስተኛ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡ አክለውም ከመትከል ባሻገር ተገቢውን እንክብካቤ በማድረግ ለመጪው ትውልድ የሚያኮራ ተግባር ማስተላለፍ ይገባልም ብለዋል ፡፡ በተከላው መረሃግብር የተሳተፉ ሰራተኞችም ዘርፈብዙ ጠቀሜታ ያላቸው ችግኞች መትከላቸውን ጠቅሰው ችግኞቹ ሲፀድቁ እንደሀገር ያለንን የደን ሽፋን ከመጨመር ባሻገር የምግብ ዋስትናችንን የሚያረጋግጡ ይሆናሉ ብለዋል፡፡ ተቋሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የሚተገበረው የአረንጓዴ አሻራ ዘመቻ አካል በመሆን በዋናው መስሪያ ቤት ፣ በሁሉም የመንገድ ማስተባበሪያ ፕሮጀክት ጽ/ቤቶች ፣ በዲስትሪክቶች እንዲሁም በመንገድ ምርምርና ማሰልጠኛ ማዕከላት ሰራተኞቹ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆኑ በማድረግ በእቅድ የተያዘው ግብ እንዲሳካ ከፍተኛ ድጋፍና ክትትል ሲያደርግ ቆይቷል ፤ ይህን ተግባርም አጠናክሮ የሚቀጥል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ማሳሰቢያ!! 7ኛው የመንገድ ምርምር ኮንፍረንስ በቃሊቲ የመንገድ ምርምር ማዕከል ማክሰኞ ነሃሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ፡ 30 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡
ማሳሰቢያ!! 7ኛው የመንገድ ምርምር ኮንፍረንስ በቃሊቲ የመንገድ ምርምር ማዕከል ማክሰኞ ነሃሴ 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2 ፡ 30 ጀምሮ ይካሄዳል፡፡

በተሽከርካሪዎች መጠንና  ክብደት  ቁጥጥር  ላይ  ያጋጠሙ  ችግሮችን የተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ አዲስአበባ ፣  ነሐሴ 11 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደትን ለመወሰንና ለመቆጣጠር የወጣዉን ደንብ ቁጥር 491/2014 የተመለከተ የዉይይት መድረክ ተካሄደ። በዉይይቱ  ላይ  በኢትዮጵያ  መንገዶች  አስተዳደር  በኩል   አዲሱን  የተሽከርካሪዎች መጠንና  ክብደት ለመቆጣጠር  የወጣውን   ደንብ  የተመለከተ ሰነድ  ቀርቧል። የቀረበው ሰነድ በዋናነት በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን  ክብደት  ለመቆጣጠር  እና  የአዲሱን  ደንብ  አተገባበር  አስመልክቶ  ግንዛቤን  ለመፍጠር  ያለመ ነው። በዕለቱም  በከተማና  መሰረተ ልማት ሚኒስቴር  የመሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር  ወንድሙ  ሴታ እንዲሁም  የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ከመጠን በላይ የሆነ ጭነትን ለመቆጣጠር እና የአገሪቱን የትራንስፖርት  ህጎች ያለአግባብ በሚጠቀሙ  የሀገር ውስጥም ሆነ አህጉራዊ የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ  ላይ ቁጥጥር ለማድረግ  በወጣው  ደንብ  አጠቃላይ  ትግበራ  ዙሪያ  ከሚመለከታቸው  ባለድርሻ  አካላት   ጋር  ምክክር  ተደርጓል ። በምክክሩም ተሽከርካሪዎች በህግ የተፈቀደላቸውን ክብደት በተመለከተ የወጣዉን የጭነት  ደንብ  በመንገዶች ላይ የማስከበር  ኃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑም ተገልጿል። በመድረኩ የተገኙ  የተለያዩ ባለድርሻ አካላት  አዲሱን አዋጅ የተመለከቱ እና ከደንቡ ቀጣይ አተገባበር  ጋር  የሚያያዙ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። በተለይም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ባሉት  የተሽከርካሪዎች ክብደት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች  ወጥነት ያለው አሰራር  መዘርጋት ይገባዋል  ተብሏል ። በተጨማሪም  መሰል የግንዛቤ ማስጨበጫዎችን እና ቅንጅታዊ  አሰራርን በመፍጠር በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ  የሚያጋጥሙ  ችግሮችን ለመቅረፍ  የጋራ ጥረቶች ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል። ደንቡ  በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ እየደረሱ  የሚገኙ  ጉዳቶችን መቆጣጠር እንዲቻል በዲዛይን ወቅት ታሳቢ የተደረገላቸውን አገልግሎት  እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል:: በተጨማሪም የሀገራችን የተሽከርካሪዎች የክብደት ወሰን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ስለሚሆን ሀገራችን ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርገውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያግዛል፡፡ አዲሱ ደንብ  በተሽከርካሪዎች ላይ የሚስተዋለውን ከተቀመጠው የክብደት ወሰን በላይ የመጫን ችግር ከምንጩ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋፆ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads Facebook Log in or sign up to view See posts, photos and more on Facebook.

በተሽከርካሪዎች መጠንና  ክብደት  ቁጥጥር  ላይ  ያጋጠሙ  ችግሮችን የተመለከተ የውይይት መድረክ ተካሄደ አዲስአበባ ፣  ነሐሴ 11 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የተሽከርካሪዎች መጠንና ክብደትን ለመወሰንና ለመቆጣጠር የወጣዉን ደንብ ቁጥር 491/2014 የተመለከተ የዉይይት መድረክ ተካሄደ። በዉይይቱ  ላይ  በኢትዮጵያ  መንገዶች  አስተዳደር  በኩል   አዲሱን  የተሽከርካሪዎች መጠንና  ክብደት ለመቆጣጠር  የወጣውን   ደንብ  የተመለከተ ሰነድ  ቀርቧል። የቀረበው ሰነድ በዋናነት በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ ከፍተኛ ጉዳት እያደረሱ የሚገኙ ተሽከርካሪዎችን  ክብደት  ለመቆጣጠር  እና  የአዲሱን  ደንብ  አተገባበር  አስመልክቶ  ግንዛቤን  ለመፍጠር  ያለመ ነው። በዕለቱም  በከተማና  መሰረተ ልማት ሚኒስቴር  የመሰረተ ልማት ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጅነር  ወንድሙ  ሴታ እንዲሁም  የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በመድረኩ ከመጠን በላይ የሆነ ጭነትን ለመቆጣጠር እና የአገሪቱን የትራንስፖርት  ህጎች ያለአግባብ በሚጠቀሙ  የሀገር ውስጥም ሆነ አህጉራዊ የተሸከርካሪዎች እንቅስቃሴ  ላይ ቁጥጥር ለማድረግ  በወጣው  ደንብ  አጠቃላይ  ትግበራ  ዙሪያ  ከሚመለከታቸው  ባለድርሻ  አካላት   ጋር  ምክክር  ተደርጓል ። በምምክሩም ተሽከርካሪዎች በህግ የተፈቀደላቸውን ክብደት በተመለከተ የወጣዉን የጭነት  ደንብ  በመንገዶች ላይ የማስከበር  ኃላፊነት ከሁሉም የሚጠበቅ መሆኑም ተገልጿል። በመድረኩ የተገኙ  የተለያዩ ባለድርሻ አካላት  አዲሱን አዋጅ የተመለከቱ እና ከደንቡ ቀጣይ አተገባበር  ጋር  የሚያያዙ ጥያቄዎችን አቅርበዋል። በተለይም የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ባሉት  የተሽከርካሪዎች ክብደት መቆጣጠሪያ ጣቢያዎች  ወጥነት ያለው አሰራር  መዘርጋት ይገባዋል  ተብሏል ። በተጨማሪም  መሰል ግንዛቤዎችንና ቅንጅታዊ  አሰራር  በመፍጠር በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ  የሚያጋጥሙ  ችግሮችን ለመቅረፍ  የጋራ ጥረቶች ማድረግ እንደሚገባም ተጠቁሟል። ደንቡ  በትርፍ ጭነት ምክንያት በመንገድ መሰረተ ልማት ላይ እየደረሱ  የሚገኙ  ጉዳቶችን መቆጣጠር እንዲቻል በዲዛይን ወቅት ታሳቢ የተደረገላቸውን አገልግሎት  እንዲሰጡ ለማድረግ የሚያስችል ይሆናል:: በተጨማሪም የሀገራችን የተሸከርካሪዎች የክብደት ወሰን ከጎረቤት ሀገራት ጋር ተመሳሳይ ስለሚሆን ሀገራችን ከሌሎች የጎረቤት ሀገራት ጋር የምታደርገውን የንግድ ትስስር በማቀላጠፍ የሀገራችንን ኢኮኖሚ ለመደገፍ ያግዛል፡፡ አዲሱ ደንብ  በተሽከርካሪዎች ላይ የሚስተዋለውን ከተቀመጠው የክብደት ወሰን በላይ የመጫን ችግር ከምንጩ ለማስቀረት ከፍተኛ አስተዋፆ ይኖረዋል ተብሎ ይጠበቃል።

ማሳሰቢያ!!
ማሳሰቢያ!!

ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል፡፡ ይህን ተግባር መፈጸም የሁላችንም ኃላፊነት እንደሆነ የሚዘነጋ ጉዳይ አይደለም። መንገዶችን ለብልሽት ከሚዳርጉ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው ከተፈቀደው ክብደት በላይ በመጫን መጓዝ (Axels load) ነው ። በዚህም ረገድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በተለያዩ የሀገራችን አካባቢዎች ከባድ ጭነትን ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ሚዛን ጣቢያዎችን በማቋቋም እንደሚሰራ ይታወቃል። የተሽከርካሪዎችን ክብደት የመቆጣጠር ዋና አላማ በመንገዶች ላይ የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች ከተፈቀደላቸዉ የአክስል ክብደት መጠን በላይ ጭነዉ በከፍተኛ ወጪ የተገነቡ የመንገድ አዉታሮች ላይ ጉዳት እንዳያደርሱ የመከላከል እንዲሁም መንገዶች እና ድልድዮች ሳይበላሹ በዲዛይኑ መሰረት አገልግሎት መስጠት እንዲችሉ ማድረግ ነዉ፡፡ በሀገራችን የተለያዩ አካባቢዎች አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ የሚዛን ጣቢያዎች እና መገኛ ቦታቸው፡- 14 ሚዛን ጣቢያዎች በተለያዩ ቦታዎቸ ተቋቁመው አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙ ሲሆን ፣ መገኛ አካባቢያቸውም፡- ሞጆ ፣ ሆሎታ ፣ ሱሉልታ ፣ ሠንዳፋ ፣ ዲማ (ሰበታ) ፣ ጂማ ፣ ሻሸመኔ ፣ አዋሽ ፣ ሠመራ ፣ደንገጎ ፣ ኮምቦልቻ ፣ ጢቅ (ደጀን) ፣ወረታ ፣ ኩይሓ (መቀሌ) ናቸው። በተለይም የአዋሽ 7 እና የሠመራ የሚዛን ጣቢያዎች ከፍተኛ የሆነ የወጪ እና ገቢ ንግድን ያስተናግዳሉ። ይህ መስመር ከባባድ መኪኖች ከጅቡቲ ወደ መሃል ሀገር የሚመላለሱበት እና በቀን ውስጥ በርካታ ተሽከርካሪዎችን የሚያስተናግድ ዋና አውራ ጎዳና ነው። በመስመሩ ከተፈቀደው መጠን በላይ በመጫን የሚንቀሳቀሱ ተሽከርካሪዎች የሚስተዋሉ በመሆኑ መንገዱ ለከፍተኛ ጉዳት እየተዳረገ ይገኛል፡፡ ይህንን ክፍተት ለመዝጋት ትርፍ የጫነ ተሽከርካሪ ጉዞውን መቀጠል የሚችለው ለጫነው ትርፍ ጭነት ተገቢውን የቅጣት ክፍያ ከከፈለ በኋላ ትርፉን እንዲያራግፍ አሊያም በሌላ ተሽከርካሪ ጭኖ እንዲወስድ ህጉ ይደነግጋል፡፡ ለእያንዳንዱ አክስል የሚፈቀድ የክብደት መጠን I. የነጠላ አክስል (Axle) ሁለት ወይም ሶስት ጎማዎች የተገጠሙለት ተሽከርካሪ የፊት እና የኋላ የአክስል (Axle) ክፍሎች ጠቅላላ የክብደት መጠን የሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) የፊት አክስል (የመሪ አክስል) Steering Axle የማይፈቀድ የክብደት መጠን ከ7.7 ቶን (77 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ፤ ለ) ከመሪዉ አክስል (Steering Axle) ዉጪ ሆኖ ነጠላ ጎማ የተገጠመለት ተሸከርካሪ ከሆነ ጠቅላላ ክብደቱ ከ8 ቶን (80 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ ሐ) የኃላዉ የአክስል ክፍል አራት ጎማዎች የተገጠሙለት ከሆነ የአክስል ክብደቱ ከ10 ቶን (100 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ II. የተሸከርካሪዉ የአክስል ክፍል ባለ ሁለት (Tandem Axle Unit) ወይም ባለሶስት (Tri-dem axle) ሲሆን ፣ ለተሽከርካሪዉ የማይፈቀድ የአክስል (Axle) የክብደት መጠን እንደሚከተለዉ ነዉ፡- ሀ) የጥንድ አክስል (Steering Tandem Axle) ክብደት ሳይጨምር ጠቅላላ የኋላ የአክስል ክብደቱ በአንድ ላይ ተደምሮ ከ18 ቶን (180 ኩንታል) የበለጠ እንደሆነ ነዉ፡፡ በመሆኑም ሁሉም የተሽከርካሪ ባለንብረቶችና አሽከርካሪዎች እንዲሁም የመንገድ ተጠቃሚዎች ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በመተባበር ከፍተኛ የሃገር ሃብት የፈሰሰበትን የመንገድ መሰረተ ልማት ለመጠበቅ በሚደረገው ጥረት የበኩላችሁን ድርሻ እንድትወጡ ለማሳሰብ እንወዳለን። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጥንቃቄ መልዕክት!!
የጥንቃቄ መልዕክት!!

የሶዶ - አረካ መገንጠያ እና የሶዶ ከተማ - ዎሊ መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ነው አዲስአበባ፣ ሐምሌ 24፣ 2016 (ኢ መ አ):- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ወላይታ ዞን የሶዶ - ታርጫ መንገድ ፕሮጀክት አካል የሆነው የሶዶ - አረካ መገንጠያ እና የሶዶ ከተማ - ዎሊ ምዕራፍ-3 መንገድ ግንባታ በመካሄድ ላይ ነው። ግንባታውን የሚያከናውነው ዓለም-አቀፉ ቻይና ፈርስት ሀይዌይ እንጂነሪንግ ኮ. ሊሚትድ፥ አሁን ላይ ለግንባታው የሚያስፈልጉ የካምፕ ግንባታ እንዲሁም የሰው ኃይል እና ማሽነሪ የማደራጀት የቅየሳ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመሥራት ላይ ነው፡፡ የጥራት እና ቁጥጥር ሥራው በሀገር-በቀሎቹ ጂ እና ዋይ ኢንጅነሪንግ ከደውል ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጋራ ያከናውናሉ። የመንገድ ፕሮጀክቱ 13 ነጥብ 57 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን፥ በአስፋልት ኮንክሪት ደረጃ ነው የሚገነባው። ለግንባታው የተመደበው 2 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል። ይህ የሶዶ ከተማ መንገድ ማሻሻያ ፕሮጀክት፣ በተለይም ከተማዋ በቅርቡ የተቋቋመው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መቀመጫ መሆኗን ተከትሎ ሊፈጠር የሚችለውን ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት በበቂ መልኩ ማስተናገድ የሚያስችል ነው። ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ውበት እና ሁለንተናዊ ዕድገት በእጅጉ የሚያሳልጥ ይሆናል። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከአነስተኛ እስከ ከፍተኛ የፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ የከርብ ስቶን እና ከልቨርቶችን ጨምሮ የእግረኛ መንገድ፣ የመንገድ አካፋይ እንዲሁም የመኪና ማሳረፊያ ግንባታ ሥራዎችን ያካትታል። በፕሮጀክቱ የመንገድ ወሰን ክልል ከፍተኛ ቁጥር ያላቸው ንብረቶች የሚገኙ በመሆኑ፣ ኅብረተሰቡም ሆነ በየመዋቅሩ የሚገኙ የመስተዳድር አካላት አስፈላጊውን ድጋፍ እና ትብብር እንዲያደርጉ ኢ መ አ ይጠይቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads