ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。

根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 95,过去 24 小时变化为 18,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 485 次浏览,首日通常累积 2 032 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 331
订阅者
+1824 小时
+417
+9530
帖子存档
የአዘዞ-ጎንደር መንገድ ግንባታን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 16 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የአዘዞ-ጎንደር የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ቀሪ ሥራዎችን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እንዲቻል ግንባታው በራስ-ኃይል የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እየተከናወነ ነው። አጠቃላይ የመንገዱ ርዝመት 12 ነጥብ 5 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን ፣ የፕሮጀክቱን ቀሪ ሥራዎች በፍጥነት ለማጠናቀቅ እንዲቻል ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ባስቀመጡት አቅጣጫ መሠረት አሁን ላይ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጎንደር መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ግንባታውን ተረክቦ እየሠራ ይገኛል። 21 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ በሚገኘው በዚሁ ፕሮጀክት አሁን ላይ የአስፋልት ፣ የሰብቤዝ ፣ የቤዝኮርስ ፣ የአቃፊ ግንብ እና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው። በዚህ ዓመትም በአንድ አቅጣጫ በኩል ያለውን የመንገዱን ክፍል ሙሉ በሙሉ አስፋልት ለማልበስ ዕቅድ ተቀምጧል። መንገድ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የከተማውን የትራፊክ እንቅስቃሴ የሚያቃልል ከመሆኑም ባሻገር ወደ ሰሜን ጎንደርም ሆነ ወደተለያየ አቅጣጫ የሚጓዙ ተሽከርካሪዎች ውስጥ ለውስጥ መሄድ ሳይጠበቅባቸው በቀጥታ ለማለፍ ያስችላቸዋል። ፕሮጀክቱ የፌደራል መንግስት በመደበው 1 ነጥብ 5 ቢሊዮን ብር ወጪ ነው ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

Notice to consulting firms
Notice to consulting firms

በሀላባ-አንጋጫ-ዋቶ እና ዱራሜ-ደንቦያ መገንጠያ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ እየተሰራ ነው ሶዶ ፣ ሐምሌ 13 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳዳር 65 ኪሎ ሜትር ርዝመትን በሚሸፍነው የሀላባ-አንጋጫ-ዋቶ እና ዱራሜ-ደንቦያ መገንጠያ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ላይ የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ ከባለድርሻ አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው፡፡ ይኸው መንገድ የመንግስት የልማት ድርጅት በሆነው በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን አማካኝነት ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፤ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ የኢትዮጵያ ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን እያከናወነው ይገኛል፡፡ አሁን ላይ በስራ ተቋራጩ የአቅም ውስንነት ምክንያት የመንገዱ የግንባታ ሂደት የዘገየ ሲሆን ፣ ተቋሙ የስራ ተቋራጩን አቅም እና የፕሮጀክቱን አፈፃፀም ሊጨምሩ የሚችሉ በርካታ ስራዎችን እያካሄደ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በክረምት ወቅት የሚያጋጥም የመንገድ መዘጋት እንዳይኖር የስራ ተቋራጩ የመንገድ ጥገና ስራዎችን እንዲያከናውን ከማስገደድ ጀምሮ ተጨማሪ የስራ ተቋራጭ በመመደቡ የተለያዩ ስራዎች በመከናወን ላይ ናቸው፡፡ ከዚህም ጋር በተያያዘ መሳይ ኦሊ ጠቅላላ የስራ ተቋራጭ የተባለ ተጨማሪ የግል ተቋራጭ በመመደብ ቀድሞ ከነበረው ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ስራዎች ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ በመሆን የመንገድ ጥገና ስራው በጋራ እየተሰራ ነው፡፡ ይህ ስራ በሚከናወንበት ወቅት የአከባቢው የዞን እና ወረዳ መስተዳደር አካላት ከኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ጋር በመተባበር ሲያበረክቱት የነበረው አስተዋፅኦ ከፍተኛ ነው፡፡ በዚህም ረገድ በአካባቢው የሚዘንበው ዝናብ ከፍተኛ ቢሆንም የመንግዱ የትራፊክ ፍሰት እንዳይቋረጥ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ የተመደበው 1,980,658,256 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ሰማንያ ሚሊዮን ስድስት ሃምሳ ስምንት ሺህ ሁለት መቶ ሃምሳ ስድስት) ብር በፌደራል መንግስት በጀት የተሸፈነ ነው። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የሀላባ ፣ ከንባታ እና ሃዲያ ዞኖችን የመንገዱ መዳረሻ ከሆነው ሆሳና-ሶዶ መንገድ ጋር ያገናኛል፡፡ በዚህም ረገድ ከሆሳና ወደ ሀላባ እና ሃዋሳ ፤ ከደንቦያ ወደ ዱራሜ ፤ ከሆሳዕና ወደ ዱራሜ እና በአካባቢው ወዳሉ ሌሎች ከተሞች የሚደረገውን ጉዞ ያቀላጥፋል፡፡ ከዚህም ባሻገር በአካባቢው ድንች ፣ ቦቆሎ ፣ ቡና ፣ በርበሬ ፣ ዝንጅብል እና ሌሎች የግብርና ምርቶች በሰፊው ይመረታሉ፡፡ መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ እነዚህን የግብርና ምርቶች በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ አርሶ አደሩ ከምርቱ እንዲጠቀም ያስችለዋል፡፡ በቀጣይም መንገዱ በተገቢው ደረጃ ተገንብቶ እስከሚጠናቀቅ ድረስ የመንገድ ጥገና ስራው ተጠናክሮ የሚቀጥል ሲሆን ፤ የመንገዱን ግንባታ በማስቀጠል አሁን ላይ ለሚስተዋለው ችግር ዘላቂ መፍትሄ ለመስጠት የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር አበክሮ የሚሰራ ይሆናል፡፡

የጅግጅጋ-ቱሊ-ሎዋንጃ-ዱልአድ-ሰመካብ-ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ጅግጅጋ፣ ሐምሌ 12፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የጅግጅጋ ከተማን ከጅቡቲ ወደብ ጋር በአቋራጭ የሚያገናኘው የጅግጅጋ-ቱሊ-ሎዋንጃ-ዱልአድ-ሰመካብ-ሐርሙከሌ መገንጠያ መንገድ ፕሮጀክት በቀጣይ ዓመት ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ 104 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትሮችን የሚሸፍን ሲኾን፥ ከአጠቃላይ የግንባታ ሥራው አሁን ላይ 72 በመቶው ተጠናቅቋል። ከግንባታ ሥራዎች መካከልም የዲዛይን፣ የ101 ኪ.ሜ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ62 ኪ.ሜ ሰብቤዝ፣ የ46 ኪ.ሜ ቤዝኮርስ፣ የ46 ኪ.ሜ አስፋልት ንጣፋ እንዲሁም የ91 በመቶ የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች ተሠርተዋል። በተጨማሪም የስድስት ድልድዮች ግንባታ ሙሉ በሙሉ የተጠናቀቀ ሲኾን፥ የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች ሥራም የፕሮጀክቱ አካል ናቸው። ዓለም-አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጅነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ስታዲያ ኢንጅነሪንግ የግንባታውን ጥራት የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ይሠራል። ለ ፕሮጀክቱ የተመደበው 1,551,507,344.53 (1 ነጥብ 5 ቢሊዮን) ብር ወጪ በፌደራሉ መንግስት በጀት ነው የሚሸፈነው። በመንገድ ወሰን ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳታቸው እንዲሁም የውኃ እጥረት በግንባታው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ችግሮቹን ለመፍታት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በየወረዳው ከሚገኙ የመስተዳድር አካላት ጋር በመቀናጀት ጥረት ተደርጓል። በመኾኑም አሁን ላይ ፕሮጀክቱን በአንድ ዓመት ጊዜ ለማጠናቀቅ በሚያስችል ቁመና ላይ ይገኛል። የመንገዱ ነባር ገጽታ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ ሲኾን፣ ከጅግጅጋ ተነስቶ ሐርሙከሌ መገንጠያ ለመድረስ ከ4 ሰዓታት በላይ ይፈጃል። ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ቀድሞ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ ወደ 1 ሰዓት ተኩል ያሳጥረዋል። ከጅግጅጋ - ጅቡቲ ያለውን ርቀት በማሳጠርም የወጪ እና ገቢ ንግዱን በእጅጉ ያሳልጣል። በመስመሩ የሚገኙትን የቱሊ፣ ሉዋንጃ፣ ዱላድ፣ ሰመካብ እንዲሁም ሐርሙከሌ የተሰኙ አካባቢዎችን በቅርበት በማገናኘት ወደ ከተማነት የሚያድጉበትን ምቹ ዕድል ይፈጥራል። በአካባቢው የሚገኙትን የስንዴ፣ ገብስ እና ማሽላ እንዲሁም የቁም እንስሳቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ በማድረስ የአርሶ-አደሩን እና የአርብቶ-አደሩን ተጠቃሚነት ያሰፋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር  ሰራተኞች እና የስራ ኃላፊዎች " የምትተክል ሃገር የሚያጸና ትውልድ  " በሚል መሪ ቃል  የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄዱ አዲስ አበባ ሐምሌ 10 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የዚህን ዓመት የመጀመሪያ ዙር የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር አካሄደ፡፡  ከችግኝ ተከላ መርሃ-ግብሩ አስቀድሞ በተቋም ደረጃ ከሚያዚያ 15 ቀን ጀምሮ የቦታ ልየታ ፣ የችግኝ ማፍላት እና የጉድጓድ ቁፋሮና መሰል ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ እንደሃገር ለ6ኛ ጊዜ በሚካሄደው የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ላይ የሚሳተፈው ይህ ተቋም በዚህ ዓመት ከ 600,000 በላይ ችግኞችን በኃላፊነት ይተክላል ፡፡  በዛሬው ዕለት በዋናው መስሪያ ቤት ሰራተኞችና የስራ  ኃላፊዎች ከ3,000 በላይ የተለያየ ዓይነት ያላቻው ሃገር በቀል ችግኞች  ተተክለዋል ፡፡ ከዚህም ባሻገር በ22 ፕሮጀክት ማኔጅመንት ጽ/ቤቶች 234,000 እና በአስሩም ዲስትሪክቶች ከ20,000 በላይ ችግኞች ተተክለዋል፡፡ ይህ ተግባር እስከ ጥቅምት መጨረሻ ድረስ ይቀጥላል፡፡ በእንጦጦ ተራራ  በተካሄደው የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ላይ የተገኙት የመስሪያ ቤቱ ሰራተኞችና የስራ  ኃላፊዎች ከዚህ ቀደም እንደሚደረገው  ሁሉ የተከሉትን ችግኞች  በቀጣይ ጊዜአት እንደሚንከባከቡ አረጋግጠዋል። ባለፉት ዓመታት በተቋሙ የአረንጓዴ   አሻራ መርሃ-ግብር በተለያዩ  አካባቢዎች ከ5.4 ሚሊየን በላይ ሀገር በቀል ችግኞች ተተክለዋል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

This cool channel uploads beautiful fashion models and accessories - All 100% generated by AI 🤩 Join here -> https://tglink.io/690abee71a7f

የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 06፣ 2016 (ኢ መ አ):- የኢትዮ -ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር ፕሮጀክት አካል የኾነው የአዳማ - አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል። የከተማና መሠረተ  ልማት  ሚንስትር ዲኤታ ወንድሙ ሴታ (ኢ/ር) እና በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር መሐመድ አብዱራህማን (ኢ/ር) የተመራ የሥራ ኃላፊዎች ቡድን ፕሮጀክቱ የሚገኝበትን ደረጃ ተመልክቷል። የመንገድ ፕሮጀክቱ በተሻለ እንቅስቃሴ ላይ እንደሚገኝ የተገመገመ ሲኾን፣ በሥራ ተቋራጩ በኩል የተነሱ የግንባታው ማነቆዎችን በመቅረፍ በኩል አስፈላጊው ድጋፍ እና ክትትል እንደሚደረግ የሥራ ኃላፊዎቹ አረጋግጠዋል።  ፕሮጀክቱን በተቀመጠለት የጥራት እና የጊዜ ገደብ ከማከናወን ባለፈ፣ ኢትዮጵያዊን ባለሞያዎችን በማሳተፍ እና የዕውቀት ሽግግር እንዲፈጠር በማስቻል ረገድ የሥራ ተቋራጩ እና አማካሪ ማሀንዲሱ ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ሚንስትር ዲኤታው ወንድሙ ሴታ (ኢ/ር) አሳስበዋል። የፍጥነት መንገዱ 61 ነጥብ 55 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ግንባታው ከአፍሪካ ልማት ባንክ እና ከኢትዮጵያ መንግሥት በተገኘ በ 6 ነጥብ 6 ቢሊዮን  ብር ወጪ እየተከናወነ ይገኛል።  ግንባታውን ጂ. ኤም.ሲ  እና  ኤል.አር .ቢ.ሲ.ኤል  የተባሉ ዓለም አቀፍ  ተቋራጮች በጋራ በማከናወን ላይ ይገኛሉ። የቁጥጥር እና የማማከሩን ሥራ ሊ አሶሼትስ  እና  ዩ.ኒ.ኮን በተመሳሳይ በጥምረት ያከናውናሉ። የፕሮጀክቱ አፈጻጸም አሁን ላይ 27 በመቶ የደረሰ ሲኾን፤ ከግንባታ ሥራዎቹ መካከልም የመጀመሪያ ደረጃ የ18 ኪሎ ሜትር የአስፋልት ንጣፍ፣ የሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ የ56 በመቶ የከልቨርቶች እና የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ እንዲሁም የእግረኛ እና የመኪና መተላለፊያ ግንባታ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። በተጨማሪም የኹለት ዋና ድልድዮች ግንባታ ተጠናቅቋል። ከወሰን ማስከበር ጋር የተያያዙ ጉዳዮች፣ የግብአት እጥረት እና የጸጥታ ስጋት ችግሮችን፣ በኢ መ አ በኩል ከየአካባቢው የመስተዳድር እና የጸጥታ መዋቅር አካላት ጋር በመቀናጀት ለመፍታት የቅርብ ክትትል እየተደረገ ነው። የፍጥነት መንገዱ አገናኝ መንገዶችን ፣ ማሳለጫ መንገዶችን ፣ የክፍያ ጣቢያዎችን ፣ የመኪና እና የእግረኛ መሸጋገሪያ ድልድዮችን አካትቷል። ከአዲስ አበባ እስከ አዳማ የሚዘልቀው 80 ኪሎ ሜትር የአዲስ-አዳማ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ተጠናቅቆ አገልግሎት በመስጠት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። የዚህ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ የመስመሩን የትራፊክ ፍሰት ለማቀላጠፍ ብሉም የተሽከርካሪዎች የጉዞ ጊዜና ዋጋ በመቀነስ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይኖረዋል፡፡ የወጪ እና የገቢ ንግዱን በማቀላጠፍም በኩልም ባለሞያዎች ይኖረዋል። ከዚህም ባሻገር የዚሁ የፍጥነት መንገድ አካል ለሆነው የአዋሽ - መኢሶ - ድሬዳዋ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የዓለም ባንክ የ730 ሚሊዮን ዶላር የፋይናንስ ድጋፍ ማጽደቁ የሚታወቅ ሲኾን፥ አሁን ላይ በጨረታ ሂደት ላይ ይገኛል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት እየተካሄደ ይገኛል አዲስ አበባ ሐምሌ 04 ፣ 2016 (ኢ መ አ):- በአማራ ክልል ደቡብ ወሎ ዞን የኮምቦልቻ ከተማ ተለዋጭ መንገድ ግንባታ እየተካሄደ ይገኛል። 7 ነጥብ 58 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የመንገድ ፕሮጀክቱ በአስፋልት ደረጃ ነው እየተገነባ የሚገኘው። በእስካሁኑ የግንባታ እንቅስቃሴ የቅየሳ ፣ የዲዛይን ፣ የአፈር ቆረጣ እና የሙሌት፣ የሰብቤዝ፣ የቤዝ ኮርስ የድጋፍ ግንብ፣ የውኃ ማፋሰሻ ቱባ እንዲሁም የድልድይ ሥራዎች በመሠራት ላይ ናቸው። አነስተኛ እና ከፍተኛ የፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች እና ከልቨርቶችም የግንባታው አካል ናቸው። የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም አሁን ላይ 16 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል። ሀገር በቀሉ ዮንአብ ኮንስትራክሽን ከፌደራል መንግስት በተመደበ አንድ ቢልዮን አንድ መቶ ሰላሳ ስምንት ሚሊዮን ብር ወጪ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ኢትዮ ኢንፍራ ኢንጂነሪንግ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራውን ይሠራል። የጸጥታ ስጋት፣ በመንገድ ወሰን ክልል ውስጥ የውኃ እና መብራት መሠረተ-ልማቶች እንዲሁም ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት የፕሮጀክቱ ፈተና መኾኑ ተመልክቷል። ችግሩን ለመቅረፍ በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የኮምቦልቻ አካባቢ ፕሮጀክት ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየሠራ ይገኛል። የመንገዱ መገንባት ወደ ደረቅ ወደብ የሚገቡና የሚወጡ ከባድ ተሽከርካሪዎች ተለዋጭ መንገዱን ተጠቅመው ወደ መዳረሻቸው በፍጥነት እንዲደርሱ ያስችላል። ከተለያዩ አካባቢዎች የሚመጡ ቁጥራቸው በርከት ያሉ ከባድ ተሸከርካሪዎች ወደ ከተማው መግባት ሳይጠበቅባቸው አቋርጠው ማለፍ ያስችላቸዋል። ከተማዋ የተለያዩ ኢንዱስትሪዎች መዳረሻ እንደመኾኗ የመንገዱ መገንባት ለኢንዱስትሪ ግብዓትና ምርት ማንቀሳቀሻ በመኾን ያገለግላል። ፕሮጀክቱ በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለትራፊክ ክፍት እንዲኾን አሁንም ያልተፈቱ የወሰን ማስከበር ችግሮች በመኖራቸው በአካባቢው የሚገኙ የመስተዳድር አካላት፣ የከተምዋ ነዋሪዎች አስፋላጊውን ትብብር እንዲያደርጉ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ይጠይቃል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads