ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 342 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 342 名订阅者。
根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 91,过去 24 小时变化为 11,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.44% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 491 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 348
订阅者
+1124 小时
+477 天
+9130 天
帖子存档
13 348
20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አሁጋራዊ ኮንፍረንስ በይፋ ተከፈተ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 11/2017 (ኢ መ አ):- 20ኛው የዓለም ሥራ ድርጅት በሥራ ላይ የተመሰረተ የባለሙያዎች ሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ስብሰባ "የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ፦ የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች" በሚል መሪ ሀሳብ በአፍሪካ ኅብረት አዳራሽ በይፋ ተከፍቷል።
በመርሀ ግብሩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የመንግስት ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ የተለያዩ ሀገራት ተወካዮች፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ተገኝተዋል።
የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር ጫልቱ ሳኒ በዚህ ወቅት እንደገለጹት፤ ጉቤኤው የዕውቀት ሽግግር፣ የሥራ እድል ፈጠራን፣ ድህነት ቅነሳንና ፍትሐዊ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ሀሳቦችን በማፍለቅ የጋራ አንድነት እና ቁርጠኝነት የምናሳይበት ነው ብለዋል።
ዓለም በውስብስብ ፈተናዎች ላይ መሆኗን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ በአሁኑ ወቅት ለስራ ፈጠራ ችግር ከሆኑት መካከል የአየር ንብረት ለውጥ፣ የቴክኖሎጂ አቅም ልዩነት፣ ጂኦ ፖለቲካዊ ግጭት ተጠቃሽ መሆናቸውን አንስተዋል።
መንግስት ለኮንስትራክሽን በተለይም ለመንገድ ዘርፍ ልዩ ትኩረት በመስጠት በሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ዘላቂ ልማት እና የማይበገር ማኅበረሰብ በመፍጠር በኩል በትኩረት እየሠራ እንደሆነም ተናግረዋል።
በዚህ ረገድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የሰው ኃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢንቨስትመንት ፕሮግራም አካሄዶች ላይ ፈር-ቀዳጅ መኾኑንም ጠቁመዋል።
በመንገድ ዘርፍ ልማት ፕሮግራም፣ በገጠር መንገድ ትስስር ፕሮግራም፣ በቤቶች ልማት ፕሮግራም እና በኮሪደር ልማት ፕሮግራሞች በሀገር አቀፍ ደረጀ በሺዎች ለሚቆጠሩ ዜጎች የሥራ ዕድል ከመፍጠር ባለፈ የኢኮኖሚ መረጋጋት ለመፍጠር አግዟል ብለዋል።
ጤናማ የሥራ ከባቢን ለመፍጠርም ዘላቂነት ያላቸው አካሄዶችን መከተል ይገባል ያሉት ሚንስትሯ፣ ለዚህም መንግስት፣ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ የግሉ ዘርፍ፣ ሲቪክ ማኅበራት እና የልማት አጋራት በቅንጅት ሊሠሩ ይገባል ብለዋል።
ኢትዮጵያ 17ኛውን አሁገራዊ ኮንፍረንስ ከዚህ ቀደም ማዘጋጀቷ አይዘነጋም።
ቀጥታ ለመከታተል
https://www.youtube.com/live/j7-JoUz5pgA?si=wUFbr9CjaKw-_lg2
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
20ኛው የዓለም የሥራ ድርጅት አህጉራዊ ኮንፍረንስ ይፋዊ የማስጀመሪያ ሥነ-ስርዓት በአፍሪካ ኅብረት የመሰብሰቢያ አዳራሽ እየተካሄደ ይገኛል
በሥነ-ስርዓቱ ላይ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አፈ-ጉባኤ ታገሰ ጫፎ፣ የከተማ እና መሠረተ ልማት ሚንስትር ጫልቱ ሳኒ፣ የዓለም የሥራ ድርጅት ሪጅናል ዳይሬክተር ፋንፋን ሩዋንይንዶ ካይራንጉዋን ጨምሮ ከ50 የአፍሪካ ሀገር ሚኒስትሮች እንዲሁም የተለያዩ ባለሞያዎች እና ባለድርሻ አካላት ታድመዋል።
ኮንፍረንሱን የከተማ እና መሠረተ-ልማት ሚንስቴር እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከዓለም የሥራ ድርጅት ጋር በጋራ በመኾን ያሰናዱት ሲኾን፣ ከግንቦት 11- 15 በአፍሪካ ኅብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ ይካሄዳል።
ቀጥታ ለመከታተል
https://www.youtube.com/live/j7-JoUz5pgA?si=wUFbr9CjaKw-_lg2
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
የመካነ ሰላም የከተማ መንገድ ማስፋት ስራ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ ይገኛል
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 08 ፣ 2017 (ኢመአ)፡- በደቡብ ወሎ ዞን 2 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የመካነ ሰላም ከተማ የመንገድ ማስፋት ስራ በጥሩ እንቅስቃሴ ላይ የሚገኝ ሲሆን በአሁን ወቅት የፕሮጀክቱ ዓፈጻጸም 80.94 በመቶ ደርሷል።
ይህ የከተማ መንገድ ማስፋት ፕሮጀክት መነሻውን ከኮምቦልቻ-መካነሰላም-ግንደወይን መንገድ ላይ በመካነሰላም ከተማ ውስጥ ከ178+510 በማድረግ እስከ ኪሎ ሜትር 181+487 ድረስ የሚዘልቅ ይሆናል ።
በእስካሁኑ የከተማ መንገድ የማስፋት ስራ የአስፋልት ንጣፍ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ እንዲሁም የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለፕሮጀክቱ ግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 97,033,590.00 /ዘጠና ሰባት ሚሊየን ሰላሳ ሶስት ሺህ አምስት መቶ ዘጠና ብር/ የሚሸፈነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ።
የከተማ ማስፋት ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው የኢመአ የኮምቦልቻ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ የኢመአ ኮምቦልቻ መንገድ አውታር ማኔጅመንት ቅ/ጽ/ቤት እያከናወነው ይገኛል።
የከተማ ማስፋት ፕሮጀክቱን ሲጠናቀቅ ለረጅም ዓመታት የነበረውን የህዝብ ጥያቄ የሚመልስና የከተማዋን እድገት በማፋጠን በከፍተኛ ሚናን ይጫወታል።
ህብረተሰቡንም ሆነ የመስመሩን ተጠቃሚዎች ከትራፊክ አደጋ የጸዳ እና በተሻለ ሁኔታ የተሳለጠ የትራፊክ ፍሰት እንዲኖር ያደርጋል።
የቦረና ወርዳ፣ ሳይንት አጅባር፣ ደንሳ፣ ከላላና ለጋምቦ ወረዳዎችን እና የመካነሰላም ከተማ አስተዳደርን ጨምሮ በአስፋልት ኮንክሪት በማገናኘት ተጠቃሚ ያደርጋል ።
የመካነ ሰላም የከተማ መንገድ ማስፋት ፕሮጀክቱ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በከተማ 20.5 ሜትር እና 1.5ሜትር አካፋይ እንዲኖረው ተደርጎ እየተሰራ ነው።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
የድሬዳዋ - ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 84 በመቶ ደረሰ
አዲስ አበባ፣ ግንቦት 04 ፣ 2017 (ኢ መ አ)፡- የድሬዳዋ ከተማን ከሽንሌ ከተማ ጋር የሚያገናኘው የድሬዳዋ - ሽንሌ እና የድሬዳዋ ከተማ ተለዋጭ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት አፈፃፀም 84 በመቶ ደርሷል፡፡
29 ነጥብ 29 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው መንገድ አሁን ላይ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ፣ የቤዝ ኮርስ እና የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
በፕሮጀክቱ የሥራ ሂደት ወቅት ከፍተኛ የሆነ የወሰን ማስከበር ችግር ይስተዋል የነበረ ሲሆን ፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በተደረጉ ተደጋጋሚ ውይይቶች ችግሩ እንዲፈታ በመደረጉ ግንባታው በእቅዱ መሰረት እየተከናወነ ይገኛል፡፡
ዓለም -አቀፉ ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን የመንገዱን ግንባታ እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን ቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬንያ ሊሚትድ የፕሮጀክቱን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራ እየሰራው ነው፡፡
ፕሮጀክቱን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 1,146,143,392 ( አንድ ቢሊዮን አንድ መቶ አርባ ስድስት ሚሊዮን አንድ መቶ አርባ ሶስት ሺህ ሶስት መቶ ዘጠና ሁለት ብር በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው፡፡
መንገዱ በወረዳ 21.5 ሜት ር ፣ በከተማ 25 ሜትር እንዲሁም በገጠር 7 ሜትር አጠቃላይ የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ እየተገነባ ይገኛል፡፡
የመንገዱ መገንባት የድሬዳዋ እና የሽንሌ ከተሞችን የሚያገኛን ከመሆኑም ባሻገር ከጂቡቲ በድሬዳዋ ደወሌ መንገድ በኩል የሚመጡ የጭነት ተሸከርካሪዎች የድሬደዋ ከተማን ሳይነኩ እንዲያልፉ በማድረግ በከተማው ውስጥ ሊፈጠር ሚችለውን የትራፊክ መጨናነቅ ያስቀራል፡፡
በተጨማሪም በአካባቢው በስፋት የሚመረቱ የግብርና ምርቶችን በቀላሉ ወደ ገበያ በማውጣት የገበያ ትስስርን ለመፍጠር ያስችላል፡፡
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
Don’t miss your chance to be part of the 20th ILO Regional Conference for Labor-Based Practitioners! From May 19–23, 2025, policymakers, planners, and practitioners from across the globe will gather in Addis Ababa at the African Union Headquarters to discuss solutions for sustainable livelihoods and resilient communities. Join ILO & ERA in shaping employment and environmental future. Register now!
#ILOEthiopia2025 #FutureOfEmployment #GreenJobs #Collaboration
13 348
የደብረብርሃን - ደነባ - ለሚ መገንጠያ እና ጅሁር - ደነባ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታን ፕሮጀክት በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ነው
በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ውስጥ የሚገኘው 108.25 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው ከደብረ ብርሃን - ደነባ - ለሚ መገንጠያ እና ከደነባ - እነዋሪ - ጅሁር እየተገነባ የሚገኘው የአስፋልት ኮንክሪት መንገድን በአጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሰራ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም የአስፋልት ማልበስ ስራ እየተከናወነ ይገኛል ።
ይህ የመንገድ ፕሮጀክት መነሻውን ደብረ ብርሃን ከተማ ላይ በማድረግ ለሚ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቅ ሲሆን እንዲሁም ከጅሁር ከተማ በመነሳት መዳረሻውን ደነባ ከተማ ላይ ያደርጋል።
በእስካሁኑ የመንገድ ግንባታ ስራ የአስፋልት ንጣፍ፣ አፈር ቆረጣ እና ሙሌት ፣ የድሬኔጅ ስራዎች፣ ሰብ ቤዝ ንጣፍ ፣ ቤዝ ኮርስ ንጣፍ ፣ እንዲሁም የስትራክቸር ስራዎች እየተከናወኑ ይገኛል።
ለግንባታ ማስፈጸሚያ የሚውለውን ገንዘብ 3,613,766,908.69 (ሶስት ቢሊዮን ስድስት መቶ አስራ ሶስት ሚሊዮን ሰባት መቶ ስልሳ ስድስት መቶ ሺህ ዘጠኝ መቶ ስምንት ብር ከ ስልሳ ዘጠኝ ሣንቲም) ብር የሚሸፈ ነው የኢትዮጵያ መንግስት ነው ።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱን እያከናወነ የሚገኘው አገር በቀሉ ሰንሻይን የስራ ተቋራጭ ሲሆን የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ኤቢኤም ኢንጂነርስ እና ንዑስ ኮንሰልታት ፕላስ ኮንሰልት ሃ/የተ/የግ/ማህበር በጋራ እያከናወኑ ይገኛሉ።
የመንገድ የግንባታ ፕሮጀክቱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ ለአካባቢዉ ህብረተሰብም ሆነ ለመስመሩ ተጠቃሚዎች ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ለውጥን በማምጣት ደረጃ ከፍተኛ የሆነ ፋይዳ ይኖረዋል፡፡
በለሚ ሲሚንቶ ፋብሪካ የሚመረተውን ሲሚንቶ ወደ ሌሎች አካባቢዎች በፍጥነት ተደራሽ በማድረግ የግንባታ ኢንዱስትሪውን እድገት ከማፋጠኑም ባሻገር የዋጋ ግሽበትን ያረጋጋል።
በአካባቢው የሚገኙት አርሶ አደሩ ምርቱን ወደ ገበያ ለማውጣት እና የኢንዱስትሪ ውጤቶችንም ወደ ገጠሩ ማህበረሰብ ተደራሽ በማድረግ የገበያ ማረጋጋት ስራ ማከናወን ያስችላል።
የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክቱ የጎን ስፋት ትከሻን ጨምሮ በዞን ከ25.5 - 32.1 ሜትር፣ በቀበሌ 12 ሜትር፣ በወረዳ 19.45 ሜትር ሲሆን በገጠር 11 ሜትር ነው።
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
የጋሸና-ቢልባላ-ሰቆጣ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በይፋ ተጀመረ
በአማራ ክልል ውስጥ የሚገኘው የኮንትራት 1 የጋሸና - ቢልባላ እና የኮንትራት 2 ፡ የቢልባላ - ሰቆጣ የአስፋልት ኮንክሪት ቀሪ ሥራዎችን የማጠናቀቂያ ፕሮጀክት የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አቶ አረጋ ከበደ ፣ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር መሐመድ አብዱራህማን ፣ የክልሉ የዞን እና የወረዳ አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል።
የአማራ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ክቡር አረጋ ከበደ በመርሃ-ግብሩ ላይ ባደረጉት ንግግር የአካባቢዉ ማህበረሰብ በእዉቀቱ፣ በባህሉ እና ባለዉ የተፈጥሮ ሀብት ለሀገር እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያደረገ ነዉ። በመሆኑም አካባቢው ባለዉ ሀብት የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ብሎም ለሀገር ልማት በተገቢዉ መልኩ ለማዋል ዛሬ በይፋ ያስጀመርነዉ መንገድ ጠቀሜታዉ ከፍ ያለ ነዉ ብለዋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው መንገዶቹ ካላቸው ኢኮኖሚያዊ ማህበራዊ ፋይዳ አንጻር ተጠናቀው ተገቢውን አገልግሎት ለመስጠት ይችሉ ዘንድ ፕሮጀክቱን ለማስጀመር የሚያስችሉ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ግንባታው በዛሬው ዕለት በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል።
የፕሮጀክቶቹን ከፍተኛ ጠቀሜታ ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት በተገቢው የጊዜና የጥራት ደረጃ እንዲጠናቀቁ ለማስቻል በትኩረት እንደሚሰራም አስታውቀዋል።
የኮንትራት 1 እና 2 ፕሮጀክት በአጠቃላይ 204.8 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ የሚሸፍን ነው።
በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱን የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ማከናወን የተቻለ ሲሆን ፣በቀጣይም ያልተጠናቀቁ ስራዎች ማለትም የውሃ ማፋሰሻ ትቦዎች ፣ የሰቤዝ ፣ የቤስኮርስ እና የአስፋልት ስራዎችን በአፋጣኝ ለማጠናቀቅም እየተሰራ ይገኛል፡፡
የመንገዱን ግንባታ የአማራ ክልላዊ ብሄራዊ መንግስት የልማት ድርጅት የሆነው ህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከዘመን ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ጋር በጋራ በመሆን ያከናውናሉ።
የኮንትራት 1 ፕሮጀክትን የማማከርና ቁጥጥሩን ሥራ ኢንጂነር ዘውዴ እስክንድር ኃ/የተ/የግ/ማህበር የሚያካሂድ ሲሆን በተመሳሳይ የኮንትራት 2 ደግሞ ቤዛ ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ኃ/የ/የግ/ማህበር ከቤዛ ኢንጂነሪንግ ኬኒያ ሊሚትድ ጋር በጣምራ ያካሂዱታል፡፡
ለግንባታው የሚውለው 5,119,831,284 ( አምስት ቢሊዮን አንድ መቶ አስራ ዘጠኝ ሚሊዮን ስምንት መቶ ሰላሳ አንድ ሺህ ሁለት መቶ ሰማንያ አራት ብር የሚሸፈነው በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ የላሊበላ ከተማን ፣ የላስታ ፣ የመቄትን እና የዋድላ ወረዳዎች እንዲሁም ፣ በዋግህምራ ብሄረሰብ ዞን ጋዝጊብላና ሰቆጣ ወረዳን የሚያገናኝ ነው፡፡
በተጨማሪም በዓለም የቅርስ መዝገብ (UNESCO) ተመዝግቦ የሚገኘውና ከፍተኛ የቱሪስት ፍሰት ያለበት የላሊበላ ፍልፍል አብያተ ክርስቲያኖች እና የተለያዩ አብያተ መዛግብት የሚገኙት በዚሁ የመንገድ ኮሪደር ውስጥ መሆኑ የመንገዱን አስፈላጊነት ከፍ ያደርገዋል፡፡
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 348
20ኛው የዓለም የስራ ድርጅት የሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ኮንፈረንስ በኢትዮጵያ ሊካሄድ ነው
አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 24 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ 20ኛው የዓለም የስራ ድርጅት የሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራዊ ኮንፈረንስ ከግንቦት 11 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ግንቦት 15 ቀን 2017 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ በአፍሪካ ሕብረት መሰብሰቢያ አዳራሽ እንደሚካሄድ የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ፣የአለም ሥራ ድርጅትና የኢትዮጵያ ሰራተኛ ማህበራት ኮንፌደሬሽን በጋራ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አሳወቁ።
ይህን አህጉራዊ ኮንፈረንስ የስራና ከተማ ልማት እና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከአለም የሥራ ድርጅት ጋር በመተባበር ነው የሚያዘጋጁት፡፡
ኮንፈረንሱን አስመልክቶ በተዘጋጀው ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ እንደተገለጸው " የማይበገር ማህበረሰብ እና ጤናማ አካባቢ ፡ የሰው ሃይልን በብዛት የሚጠቀሙ የኢቨስትመንት አካሄዶች የሚል መሪ ሃሳብ አንግቧል ፡፡ ይህም የዘላቂ ልማትን አስፈላጊነት የሚያንጸባርቅ እንዲሁም ሰፋፊ የመሰረተ ልማት ፕሮግራሞች ኢኮኖሚያዊ እድገትን ብቻ ሳይሆን የአካባቢ ጥበቃን ፣ የማህበረሰብ ደህንነትን ፣ አካታችነትን እና ዘላቂ ተጠቃሚነት ሊያረጋግጡ እንደሚገባ አጉልቶ የሚያሳይ ነው ፡፡
በዚህ ኮንፈረንስ ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ ሚኒስትሮች ፣ የዓለም አቀፍ ተቋማት መሪዎች ፣ የዲፕሎማቲክ ማህበረሰብ ተወካዮች ፣ የሲቪክ እና መንግታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች ተወካዮች ፣ የአሰሪዎች እና የሰራተኞች ፌደሬሽኖች ተወካዮች እንዲሁም የዘርፉ ምሁራንና ባለሙያዎች የሚሳተፉ ሲሆን በአጠቃላይ አገራችንን ጨምሮ ከአምስት አህጉራትና ከሃምሳ በላይ አገራት ፣ ከ1500 በላይ ተሳታፊዎች ይጠበቃሉ ፡፡ በኮንፈረንሱ ላይ የዘርፉ ተመራማሪዎች ፣ ፖሊሲ አውጪዎች ፣ እና ባለሙያዎች በሳል የጥናትና ምርምር ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ፡፡ ከግንቦት 11 እሰከ 15 ቀን ዓ.ም በአዲስ አበባ ሊካሄድ የታቀደው 20ኛው የአለም ስራ ድርጅት የሌበር ቤዝድ ፕራክቲሽነርስ አህጉራ ኮንፈረንስ ኢትዮጵያ እንደተለመደው እንግዳ ተቀባይነቷን ከምርም የአፍሪካ የዲፕሎማሲ መዲናና የኮንፈረንስ ማእከል መሆኗን የምታሳይበት እንዲሁም በዓለም አቀፍ መድረክ እንድትደምቅ ሌላ እድል የሚፈጥር ነው ፡፡
በተጨማሪም
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
