ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 348 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 755,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 348 名订阅者。
根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 91,过去 24 小时变化为 11,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.44% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 491 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 19 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 348
订阅者
+1124 小时
+477 天
+9130 天
帖子存档
13 351
የሶዶ-ዲንኬ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል
የዲንኬ-ሳውላ የአስፋልት መንገድ ግንባታን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ስራዎችም በመከናወን ላይ ናቸው
የሶዶ-ዲንኬ-ሳውላ-ሽፍቴ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው የሶዶ-ዲንኬ መንገድ ግንባታ በቻይና ሬይልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ አማካኝነት ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ አንድ ቢሊዮን ሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር የግንባታ ወጪ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ ደግሞ የሱዳኑ ኒውቴክ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ከሀገር በቀሉ ኔት ኮንሰልት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር በጥምረት በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡
በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ማለትም በሶዶ እና ሠላም በር ከተሞች ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተነሱ ጉዳዮች በወቅቱ እልባት አለማግኘታቸው ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት እጥረት እና የዋጋ መናር፣ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረው ቆይተዋል።
እነዚህን ችግሮች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለመቅረፍ ተችሏል፡፡ በዚህም መሰረት በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ስራ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ በዚሁ በጀት ዓመት ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚቀረውን 90 ሜትር የአስፋልት ስራ በማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ስራውን በፍጥነት አጠናቆ ለመጨረስ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡
መንገዱ በከተማ 12 ሜትር የመኪና መንገድ ፣ 2.5 ሜትር የፓርኪንግ መስመር (በሁለቱም አቅጣጫ) ፣ 3.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) እና 2 ሜትር የመንገድ አካፋይ እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ እንዲሁም በወረዳ መቀመጫ 14 ሜትር የመኪና መንገድ እና 2.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) ይኖረዋል፡፡
የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የዲንኬ-ሳውላ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ በግንባታ ሒደት ላይ እያለ ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ ባጋጠሙ ችግሮች ምክንያት ግንባታው እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል፡፡
አሁን ላይ ተቋርጦ የነበረውን ፕሮጀክት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን ፣ ግንባታውን የማስቀጠል ስራ በዚሁ 2016 በጀት ዓመት ይከናወናል፡፡
እነዚህ ፕሮጀክቶች በሚካሄዱባቸው አካባቢ እንደ ቡና ፣ ካዛባ ፣ በቆሎ ፣ ስንዴ እና ጤፍ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶች በስፋት የሚመረቱ በመሆኑ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ሙሉ በሙሉ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆኑ ፣ እነዚህን ምርቶች ወደ መሐል ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖራቸውል ፡፡ ከዚህም ባለፈ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ በመሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎንኝዎች ወደ ፓርኩ የሚያደርጉትን ጉዞ በማቀላጠፍ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት ይጨምራል ተብሎ ይታመናል፡፡
ይህ ፕሮጀክት ተጠናቆ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት የበኩላችሁን አወንታዊ አስተዋፅኦ ታበረክቱ ዘንድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአፅንኦት ያሳስባል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
13 351
የላሬ-ኒው ጅካዎ-ኒንኛንግ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀመረ
አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ) ፦ በጋንቤላ ክልል በኑዌር ዞን በ1.42 ቢሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው 34 ኪሎ ሜትር የላሬ-ኒው ጅካዎ-ኒንኛንግ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ከጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡
የዚህ መንገድ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው በፕሮጀክቱ አካባቢ ያጋጠመውን ለሙሌት የሚሆን የምርጥ አፈር ዕጥረትን ለመቅረፍ የከርሰ ምድር ውሃ ስርገትን የሚከላከል ምንጣፍ ኮምፖስት ጅኦ መምብሬን (Composite Geo-membrane technology treatment) የተባለ አዲስ ቴክኖሎጅ በመጠቀም ሲሆን ፤ ይህ ቴክኖሎጅ በአካባቢው የሚገኘውን ጥቁር አፈር ለሙሌት ስራ መጠቀም የሚያስችል ነው፡፡
ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 862 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከላሬ ከተማ ጀምሮ የጂካዎ ወረዳን አቋርጦ ከአዲስ አበባ በ896 ኪሎ ሜትር ርቀት ኒንኛንግ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡
መንገዱ ከኪሎ ሜትር 0+000 እስከ 17+100 ኪሎ ሜትር ነባር እና ከኪሎ ሜትር 17 እስከ 34 ኪሎ ሜትር ደግሞ በአዲስ መልኩ ግንባታው የሚካሄድ ፕሮጀክት ነው፡፡
ፕሮጀክቱ 165 ጥቃቅን የፍሳሽ ማስወገጃ ስራዎችን ፣ 260 ሜትር ርዝመት ያለው የባሮ ድልድይ ግንባታ እና 34.405 ኪሎ ሜትር አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ስራን ባካተተ መልኩ በመገባት ላይ ይገኛል፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስካሁን ድረስ 73.81% የአፈር ጠረጋ ፣ 25.60% የፍሳሽ ማስወገጃ ፣ 69.42% የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም 44.80% የስትራክቸር ስራዎች ተከናውነዋል፡፡
የዚሁ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝ ኮርስ ፣ የአስፋልት ፣ የድልድይና የግንብ እና የጠጠር መፍጨት ስራዎችን አካቶ አሁናዊ አፈፃፀሙ 13 ኪሎ ሜትር ወይም 37 በመቶ የደረሰ ሲሆን ፣ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ለማስቻል ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአመዛኙ ከዝናብ ወቀት ጋር በተገናኘ የተጎዱ ቦታዎች ጥገና እየተደረገላቸው በመሆኑ ተሽከርካሪዎች መንገዱን በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፡፡
ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው 1.42 ቢሊዮን ብር የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡
በገጠር 10 ፣ በቀበሌ 12 ፣ በወረዳ 19 እና በከተማ ደግሞ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኘው ይኸው ፕሮጀክት አሁናዊ አፈፃፀሙ ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡
የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ጄጃንግ ባዮንግ ሃይዌይ ኢንጂነሪንግ የተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ሲሆን ፣ የማማከርና ቁጥጥር ስራወን ደግሞ ሀገር በቀሉ ልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ከጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
መንገዱ በዋናነት የላሬ እና የጂካዎ ወረዳዎችን እንዲሁም የኑዌር ዞን አስተዳደርን በማስተሳሰር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብራቸውን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይታመናል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
