fa
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

رفتن به کانال در Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

کانال ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 13 348 مشترک است و جایگاه 1 755 را در دسته حمل و نقل و رتبه 2 537 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 13 348 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 18 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 91 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 11 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 41.16% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 15.44% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 491 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 060 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 11 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 19 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته حمل و نقل تبدیل کرده‌اند.

13 348
مشترکین
+1124 ساعت
+477 روز
+9130 روز
آرشیو پست ها
የሶዶ-ዲንኬ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በማጠናቀቂያ ምዕራፍ ላይ ይገኛል የዲንኬ-ሳውላ የአስፋልት መንገድ ግንባታን ለማስቀጠል የሚያስችሉ ስራዎችም በመከናወን ላይ ናቸው የሶዶ-ዲንኬ-ሳውላ-ሽፍቴ አስፋልት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የመጀመሪያ ምዕራፍ የሆነው የሶዶ-ዲንኬ መንገድ ግንባታ በቻይና ሬይልዌይ ሰቨንዝ ግሩፕ አማካኝነት ከአፍሪካ ልማት ባንክ በተገኘ አንድ ቢሊዮን ሃምሳ አራት ሚሊዮን ብር የግንባታ ወጪ እየተካሄደ ይገኛል፡፡ የማማከር እና የቁጥጥሩን ሥራ ደግሞ የሱዳኑ ኒውቴክ ኮንሰልቲንግ ግሩፕ ከሀገር በቀሉ ኔት ኮንሰልት ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ጋር በጥምረት በማከናወን ላይ ይገኛሉ፡፡ በፕሮጀክቱ የከተማ ክልል ማለትም በሶዶ እና ሠላም በር ከተሞች ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዘ የተነሱ ጉዳዮች በወቅቱ እልባት አለማግኘታቸው ፣ ወቅቱን ያልጠበቀ ዝናብ እንዲሁም የግንባታ ዕቃዎች የግብዓት እጥረት እና የዋጋ መናር፣ በግንባታው ሂደት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረው ቆይተዋል። እነዚህን ችግሮች ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ለመቅረፍ ተችሏል፡፡ በዚህም መሰረት በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ የፕሮጀክቱ ስራ በመጠናቀቅ ላይ የሚገኝ ሲሆን ፣ በዚሁ በጀት ዓመት ሶዶ ከተማ ውስጥ የሚቀረውን 90 ሜትር የአስፋልት ስራ በማከናወን አጠቃላይ የግንባታ ስራውን በፍጥነት አጠናቆ ለመጨረስ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ መንገዱ በከተማ 12 ሜትር የመኪና መንገድ ፣ 2.5 ሜትር የፓርኪንግ መስመር (በሁለቱም አቅጣጫ) ፣ 3.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) እና 2 ሜትር የመንገድ አካፋይ እንዲኖረው ተደርጎ በመገንባት ላይ ይገኛል፡፡ እንዲሁም በወረዳ መቀመጫ 14 ሜትር የመኪና መንገድ እና 2.5 ሜትር የእግረኛ መንገድ (በሁለቱም አቅጣጫ) ይኖረዋል፡፡ የዚሁ መንገድ ቀጣይ ምዕራፍ የሆነው የዲንኬ-ሳውላ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ በግንባታ ሒደት ላይ እያለ ከአፈጻጸም ጋር በተያያዘ ባጋጠሙ ችግሮች ምክንያት ግንባታው እንዲቋረጥ መደረጉ ይታወቃል፡፡ አሁን ላይ ተቋርጦ የነበረውን ፕሮጀክት ለማስቀጠል የሚያስችሉ ስራዎች የተጠናቀቁ ሲሆን ፣ ግንባታውን የማስቀጠል ስራ በዚሁ 2016 በጀት ዓመት ይከናወናል፡፡ እነዚህ ፕሮጀክቶች በሚካሄዱባቸው አካባቢ እንደ ቡና ፣ ካዛባ ፣ በቆሎ ፣ ስንዴ እና ጤፍ የመሳሰሉ የግብርና ምርቶች በስፋት የሚመረቱ በመሆኑ ፕሮጀክቶቹ ተጠናቀው ሙሉ በሙሉ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆኑ ፣ እነዚህን ምርቶች ወደ መሐል ገበያ ለማቅረብ ከፍተኛ ፋይዳ ይኖራቸውል ፡፡ ከዚህም ባለፈ መንገዱ የማዜ ብሔራዊ ፓርክ መዳረሻ በመሆኑ የሀገር ውስጥና የውጭ ሀገር ጎንኝዎች ወደ ፓርኩ የሚያደርጉትን ጉዞ በማቀላጠፍ የአካባቢውን የቱሪስት ፍሰት ይጨምራል ተብሎ ይታመናል፡፡ ይህ ፕሮጀክት ተጠናቆ ተገቢውን አገልግሎት እንዲሰጥ የአካባቢው ነዋሪዎችና ባለድርሻ አካላት የበኩላችሁን አወንታዊ አስተዋፅኦ ታበረክቱ ዘንድ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በአፅንኦት ያሳስባል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የላሬ-ኒው ጅካዎ-ኒንኛንግ አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ተጀመረ አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 20 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ) ፦ በጋንቤላ ክልል በኑዌር ዞን በ1.42 ቢሊዮን ብር እየተገነባ የሚገኘው 34 ኪሎ ሜትር የላሬ-ኒው ጅካዎ-ኒንኛንግ የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የአስፋልት ንጣፍ ሥራ ከጥቅምት 5 ቀን 2016 ዓ.ም ጀምሮ በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የዚህ መንገድ ግንባታ እየተከናወነ የሚገኘው በፕሮጀክቱ አካባቢ ያጋጠመውን ለሙሌት የሚሆን የምርጥ አፈር ዕጥረትን ለመቅረፍ የከርሰ ምድር ውሃ ስርገትን የሚከላከል ምንጣፍ ኮምፖስት ጅኦ መምብሬን (Composite Geo-membrane technology treatment) የተባለ አዲስ ቴክኖሎጅ በመጠቀም ሲሆን ፤ ይህ ቴክኖሎጅ በአካባቢው የሚገኘውን ጥቁር አፈር ለሙሌት ስራ መጠቀም የሚያስችል ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ከአዲስ አበባ 862 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ ከላሬ ከተማ ጀምሮ የጂካዎ ወረዳን አቋርጦ ከአዲስ አበባ በ896 ኪሎ ሜትር ርቀት ኒንኛንግ ከተማ ላይ ያበቃል፡፡ መንገዱ ከኪሎ ሜትር 0+000 እስከ 17+100 ኪሎ ሜትር ነባር እና ከኪሎ ሜትር 17 እስከ 34 ኪሎ ሜትር ደግሞ በአዲስ መልኩ ግንባታው የሚካሄድ ፕሮጀክት ነው፡፡ ፕሮጀክቱ 165 ጥቃቅን የፍሳሽ ማስወገጃ ስራዎችን ፣ 260 ሜትር ርዝመት ያለው የባሮ ድልድይ ግንባታ እና 34.405 ኪሎ ሜትር አስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ስራን ባካተተ መልኩ በመገባት ላይ ይገኛል፡፡ ከፕሮጀክቱ ጅማሮ እስካሁን ድረስ 73.81% የአፈር ጠረጋ ፣ 25.60% የፍሳሽ ማስወገጃ ፣ 69.42% የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም 44.80% የስትራክቸር ስራዎች ተከናውነዋል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት የአፈር ቆረጣ ፣ የሰብ ቤዝ ፣ የቤዝ ኮርስ ፣ የአስፋልት ፣ የድልድይና የግንብ እና የጠጠር መፍጨት ስራዎችን አካቶ አሁናዊ አፈፃፀሙ 13 ኪሎ ሜትር ወይም 37 በመቶ የደረሰ ሲሆን ፣ በጥር ወር 2017 ዓ.ም ተጠናቆ ለአገልግሎት ክፍት እንዲሆን ለማስቻል ከፍተኛ እንቅስቃሴ እየተደረገ ይገኛል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ በአመዛኙ ከዝናብ ወቀት ጋር በተገናኘ የተጎዱ ቦታዎች ጥገና እየተደረገላቸው በመሆኑ ተሽከርካሪዎች መንገዱን በመጠቀም ላይ ይገኛሉ፡፡ ለመንገዱ ግንባታ የሚውለው 1.42 ቢሊዮን ብር የግንባታ ወጪ በኢትዮጵያ መንግስት የሚሸፈን ነው፡፡ በገጠር 10 ፣ በቀበሌ 12 ፣ በወረዳ 19 እና በከተማ ደግሞ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ግንባታው በመካሄድ ላይ የሚገኘው ይኸው ፕሮጀክት አሁናዊ አፈፃፀሙ ጥሩ በሚባል ደረጃ ላይ ይገኛል፡፡ የመንገዱን ግንባታ በማካሄድ ላይ የሚገኘው ጄጃንግ ባዮንግ ሃይዌይ ኢንጂነሪንግ የተባለ የቻይና አለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ ሲሆን ፣ የማማከርና ቁጥጥር ስራወን ደግሞ ሀገር በቀሉ ልደት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ከጂ እና ዋይ ኢንጂነሪንግ ኮንሰልት ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ በዋናነት የላሬ እና የጂካዎ ወረዳዎችን እንዲሁም የኑዌር ዞን አስተዳደርን በማስተሳሰር ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብራቸውን ይበልጥ ያጠናክራል ተብሎ ይታመናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et