ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 348 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 755,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 348 名订阅者。

根据 18 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 91,过去 24 小时变化为 11,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.16%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.44% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 491 次浏览,首日通常累积 2 060 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 11

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 19 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 348
订阅者
+1124 小时
+477
+9130
帖子存档
በጅማ-ጭዳ መንገድ ግንባታ ሂደት የሚስተዋሉ ችግሮችን ለመቅረፍ በትኩረት እየተሰራ ነው። ጅማ ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢ መ አ)፥ የኦሮሚያ እና የደቡብ ምዕራብ ክልሎችን በዋናነት የሚያስተሳስረው የጅማ-ጭዳ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በግንባታ ሂደት ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል። መንገዱ በስራ ተቋሯጩ የፕሮጄክት አስተዳደር ችግር እና ከወሰን ማስከበር ጋር በተያያዙ ጉዳዮች በእቅዱ መሰረት ማከናወን ያልተቻለበት ሁኔታዎች ተፈጥረዉ ነበር። የኢትዮጵያ መንገዶች አሰተዳደር የፕሮጄክቱን ግንባታ ከሚያካሂደው ስራተቋራጭ ጋር በመቀናጀት እና ተገቢዉን ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ አሁን ላይ በፕሮጀክቱ የግንባታ ሂደት ላይ አዎንታዊ ለዉጦች መመዝገብ ጅምረዋል። የመንገዱ አጠቃላይ ርዝመት 80 ኪሎ ሜትሮችን የሚሸፍን ሲሆን ፣ በገጠር 10 ፣ በከተማ ደግሞ ከ12.4 እስከ 21.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ ነው በመገንባት የሚገኘው። ግንባታው ቻይና ቲሲጁ ኢንጅነሪንግ ግሩፕ በተባለ የቻይና ዓለም አቀፍ የስራ ተቋራጭ እየተካሄደ የሚገኝ ሲሆን ፣ የማማከርና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ የጃፓኑ ኩዮንግዶንግ ኢንጅነሪንግ ከኦሬንታል ኮንሰልቲንግ ግሎባል እና ከኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጅነርስ ጋር በጋራ በመሆን በማካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ ለመንገዱ ግንባታ ወጪ የሚሆነው 2,422,629,267 ብር ሲሆን ፣ የዚህ ግንባታ ሙሉ ወጪም በአፍሪካ ልማት ፈንድ (African Development Fund) እና በአለም አቀፍ የጃፓን ትብብር ኤጀንሲ (Japan International Cooperation Agency) የተሸፈነ ነው፡፡ መንገዱ ሲጠናቀቅ በኦሮሚያ እና ደበቡብ ምዕራብ ክልሎች የሚገኙ የጅማ ፣ ዋሮ ፣ ኮሎቦ ፣ ኦፎሌ ፣ ዴዶ ፣ ሚጤሶ ፣ ደልቢ ፣ ቂራራ ፣ በቲቲበዱዳ ፣ ንቲቲጎላ እና ጭዳ ከተሞችን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ መስተጋብር ይበልጥ ያጠናክራል። መንገዱ ተገንብቶ ሲጠናቀቅ የትራንስፖርት ተደራሽነቱን በማስፋት በህብረተሰቡ ላይ የሚከሰተውን የትራንስፖርት አገልግሎት መጉላላት ይቀንሳል ተብሎ ይታመናል። በተጨማሪም አካባቢው የቅይጥ ግብርና እና የእንስሳት እርባታ የሚከናወንበት በመሆኑ የመንገዱ ግንባታ መጠናቀቅ እነዚህን የግብርና ውጤቶች ሳይበላሹ በጥራትና በፍጥነት ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል፡፡ ከዚህም ባሻገር መንገዱ የኮይሻ ሃይድሮ ኤሌክትሪክ ሃይል ግድብ ግንባታ ፣ የሃላላ ኬላ ሎጅ እና የኮይሻ ገበታ ለሀገር ፕሮጀክት ( ጨበራ ጩርጩራ ብሔራዊ ፓርክ) መዳረሻ በመሆኑ ግንባታው ሲጠናቀቅ የአካባቢውን የቱሪዝም ዘርፍ ከማሳደግ አኳያም ጉልህ አስተዋፅኦ ያበረክታል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" እንኳን ለ116ኛው የሠራዊት ቀን አደረሳችሁ
"በተፈተነ ጊዜ ሁሉ የሚፀና የድል ሠራዊት" እንኳን ለ116ኛው የሠራዊት ቀን አደረሳችሁ

በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት ላይ ያተኮረ ስልጠና በኢትዮጵያ ሆቴል እየተሰጠ ነዉ በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት የመጀመሪያ ደረጃ የሙያ ማረጋገጫ ስልጠና ከጥቅምት 05/02/16 ዓ.ም ጀምሮ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ መሀንዲሶች እየተሰጠ ይገኛል፡፡ ስልጠናውን ያስጀመሩት የመንገድ ሀብት ማኔጅመንት ምክትል ዋና ዳይሬክተር ኢንጅነር አለማየሁ አየለ ስልጠናው ኢመአ ከሚገነባቸውና ከሚያስተዳድራቸው መንገዶች የተሽከርካሪ እንቅስቃሴ ደህንነት እና የአደጋ ቅነሳ ጋር በተገናኘ የሚስተዋሉ ችግሮችን ላይ መፍትሄ ለማምጣት የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል፡፡ አያይዘውም የመንገድ ደህንነት ቅድሚያ ትኩረት የሚሰጠው ተግባር መሆኑን ጠቁመው ሰልጣኞች በንቃት መከታተልና ራሳቸውን ለበለጠ ውጤት ማዘጋጀት እንደሚገባቸው ገልጸዋል፡፡ በአይነቱ የመጀመሪያ የሆነውና ለአምስት ቀናት የሚቆየው የሰርተፊኬሽን ስልጠና በሁለት ዙሮች ተከፍሎ 50 የተቋሙ መሀንዲሶችን ብቁ ለማድረግ የሚያግዝ ነው፡፡ በመሆኑም ስልጠናው በተለያዩ መንገዶች ላይ በትራፊክ አደጋ ምክንያት የሚከሰቱ የሞትና የንብረት አደጋ መንስኤዎችን ለይቶ በማውጣት ችግሩን ለመቆጣጠርና ለመከላከል የሚያስችሉ ስራዎችን ለመስራትና መፍትሄ ለማምጣት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በመንገድ ደህንነት ኦዲተርና ኢንስፔክተርነት ያተኮረው ስልጠና የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በዘርፉ ልምድ ካለው (ስዊሮድ) የስዊድን ብሔራዊ የመንገድ አማካሪ (Sweroad) Swedish National Road Consulting ጋር በመተባበር የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የባሌ ጎባ-በርበሬ-ዶሎመና ሎት-1 የ133 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ ነው አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 06፣ 2016 (ኢ መ አ):-በኦሮሚያ ክልል ምዕራብ ባሌ ዞን የጎባ-ዶሎመና-ነገሌ ቦረና/ ቢታታ ፕሮጀክት አካል የሆነው የባሌ ጎባ-በርበሬ-ዶሎመና 133 ኪሎ ሜትር አስፋልት መንገድ ግንባታ በመከናወን ላይ ነው፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ዓለማየሁ ከተማ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ሲሆን፥ አሁን ላይ የዲዛይን፣ የቅየሳ፣ የካምፕ ግንባታ እንዲሁም የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት ሥራዎችን በመሥራት ላይ ይገኛል። ቤስት ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ፕሮጀክቱን የማማከር እና የመቆጣጠር ሥራ ይሠራል። ነባሩ መንገድ በጠጠር መንገድ ደረጃ የነበረ እና በአገልግሎት ብዛት በእጅጉ የተጎዳ በመሆኑ፣ ብሎም ካለው በርካታ ሀገራዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና ማኅበራዊ ጠቀሜታ አንፃር በአስፋልት ደረጃ ነው የሚገነባው። ይህ ፕሮጀክት፣ ከአዲስ አበባ - በሻሸመኔ - አዳባ - ባሌ ሮቤ የሚዘልቀው ዋና መንገድ ላይ ከባሌ ሮቤ ተገንጥሎ ወደ ጎባ - ዶሎመና የሚወስደው መንገድ አካል ነው፡፡ የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፣ በምዕራብ ባሌ ዞን የጎባ ከተማ እንዲሁም የጎባ፣ በርበሬ፣ ዶሎመና ወረዳዎችን እና በርካታ ቀበሌዎችን በቅርበት ያገናኛል። በሥፍራው የሚገኘውን የሳነቴ ፓርክ ለጎብኚዎች ምቹ በማድረግ በኩልም የጎላ አስተዋጾዖ ያበረክታል። በዞኑ በስፋት የሚገኘውን የማር እንዲሁም የስንዴ፣ገብስ ጤፍ እና መሰል ምርት ውጤቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ በጥራት እና ፍጥነት ማድረስ ያስችላል። የመንገድ ፕሮጀክቱ አነስተኛ፣ ከፍተኛ ፍሳሽ ማስተላለፊያ ቱቦዎች፣ ከልቨርቶች እንዲሁም የ14 ድልድዮች ግንባታ ሥራ ያካትታል፡፡ መንገዱ፣ የመንገድ ትከሻን ጨምሮ በገጠር 8-10 ሜትር ስፋት ሲኖረው፣ በቀበሌ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 17 ሜትር እንዲሁም በወረዳ የመንገድ አካፋይ፣ የእግረኛ መንገድና የመኪና ማረፊያ ጨምሮ 22.5 ሜትር ስፋት እንዲኖረው ተደርጒ ነው የሚገነባው። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

በወሰን ማስከበርበ ችግር የተጓተተው የአሳይታ - አፋምቦ - ጅቡቲ ድንበር መንገድ Etv በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et