ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር
前往频道在 Telegram
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።
显示更多📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览
频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。
根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 95,过去 24 小时变化为 18,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 485 次浏览,首日通常累积 2 032 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Official ERA Telegram Channal
በዚህ የቴሌግራም ቻናል
የመንገድ ዜናዎችን
የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን
የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。
13 331
订阅者
+1824 小时
+417 天
+9530 天
帖子存档
13 342
በፊቅ-ሰገግ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የፊቅ - ሰገግ - ገርቦ - ደናን መንገድ ፕሮጀክት አካል የኾነው ምዕራፍ አንድ ፊቅ - ሰገግ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተጀምሯል።
የመንገድ ፕሮጀክቱ 90 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፣ ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሥራ አሁን ላይ 45 ነጥብ 13 በመቶው ተጠናቅቋል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ የተሸጋገረ ሲኾን፣ እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከልም የ7 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ፣ የ19 ከ.ሜ ሰብቤዝ፣ የ11 ከ.ሜ ቤዝኮርስ፣ የ75 ኪ.ሜ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ በተጨማሪም የአንድ ድልድይ ግንባታ የተጠናቀቀ ሲኾን፣ ቀሪ የኹለት ድልድዮች ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡
ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ አማካሪ የግንባታውን የቁጥጥር እና የማማከር ሥራ ይሠራል፡፡ ለመንገድ ግንባው 1,422,968,463.00 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ) ብር ከፌደራል መንግስት ተመድቧል፡፡
የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ በፊቅ በኩል ጎዴ ለመጓዝ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 1ሺህ 170 ኪሎ ሜትር መንገድ በ150 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ ከጎዴ-ጅጅጋ-ሐረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡
ዮሆብ፣ ሰገግ እና ሌሎች በርካታ ቀበሌዎችን በቅርበት በማገናኘት ወደ ከተማነት የሚያድጉበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡
የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ኮሪደር ቀጣይ ክፍል የሆኑት ምዕራፍ 2 ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በግንባታ ላይ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው
ጅግጅጋ፣ ሰኔ 24፣ 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በሶማሌ ክልል በ672,098,730 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን) ብር ወጪ የሚገነባው የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው።
የመንገድ ፕሮጀክቱ ከቶጎ-ጫሌ መገንጠያ አንስቶ እስከ ሐረር መውጫ ድረስ ያለውን ሥፍራ የሚሸፍን ሲሆን፣ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር ርዝመት እና 30 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ ግንባታ ያካትታል።
በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራዎች መካከል የ87 ነጥብ 15 በመቶ የአፈር ቆረጣ፣ የ6 ነጥብ 03 ኪሎ ሜትር ሰብቤዝ የ1 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ቤዝኮርስ፣ የ 78 በመቶ ፉካ እና የማፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የ84 በመቶ የ ድልድይ እና የግምብ ሥራዎች ተሠርተዋል።
ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 67 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ ቀሪ የግንባታ ሥራውን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ለዚህም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ ይገኛል።
ግንባታውን የሚያከናውነው ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሲኾን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጥምረት ይሠራሉ። ለግንባታው የተመደበው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው።
የተለዋጭ መንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ እንዲሁም መግቢያና መውጫ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በእጅጉ የሚቀንስ ነው። ከሐረር ወደ ቶጎ ጫሌ እና ቀብሪበያህ ወይም ቀብሪደሀር የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማ መግባት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መሄድ ያስችላቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት እና ውበት በማሳለጥ በኩል ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
የደንገጎ-ሐረር-ቁልቢ-አዋሽ መገንጠያ መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው
ድሬዳዋ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኢ መ አ):- የኢትዮ-ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር አካል የኾነው የደንገጎ-ሐረር-ቁልቢ-አዋሽ መገንጠያ መንገድ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው።
የመንገድ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እያከናወነ ይገኛል።
መንገዱ የሀገሪቱ የገቢ እና ወጪ ንግድ ዋና መስመር እና ከከባድ እስከ ቀላል ተሽክከርካሪዎች የሚተላለፉበት እንደመኾኑ እና ከአነስተኛ እስከ ከባድ መጠን ባላቸው ጉድጎዶች(deep holes) እና ሌሎች እንደ መሰንጠቅ ያሉ የጉዳት ዓይነቶች በመጎዳቱ መደበኛ የጥገና ሥራ እየተከናወነለት ይገኛል።
የጥገና ሥራው የአስፋልት ኦቨርሌይ፣ ሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ አስፋልት ፓቺንግ እንዲሁም ኮንክሪት ፔቭመንት ሥራዎችን አካትቷል።
በመሥመሩ የሚገኙ የከባድ እና የሕዝብ ማመላለሻ መኪና አሽከርካሪዎች፣ የመንገድ ጥገናው እንግልት እና ለመኪና ዕቃ መለዋወጫ የሚወጣውን አላስፈላጊ ወጪ እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል።
ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰቱን ተከትሎ ተለዋጭ መንገድ አለመኖር እንዲሁም የሰው እና የማሽነሪ እጥረት የጥገናው ፈተና መኾኑ ተመልክቷል።
መደበኛ ጥገናው በሦስት ሴክሽኖች ተከፋፍሎ በመገንባት ላይ ይገኛል።
የድሬዳዋ ዲስትሪክት በአጠቃላይ 3 ሺህ 107 ኪሎ ሜትር የሚያካልሉ መንገዶችን የሚያስተዳድር ሲኾን፣ በአምስት የተለያዩ ሴክሽኖች በተለየየ ደረጃ መጠነ ሰፊ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል።
በተጨማሪም የኤርጎኖሚክስ፣ የሚዛን ጣቢያ እንዲሁም የድልድይ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
በነባሩ የአዳማ - አዋሽ መንገድ የከባድ ጥገና ስራ በመካሄድ ላይ ይገኛል
አዳማ፣ ሰኔ 19፣ 2016 (ኢመአ)፦ የኢትዮጵያን 90 ከመቶ በላይ የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ በሚያስተናግደው ነባሩ የአዳማ - አዋሽ መንገድ ላይ የከባድ መንገድ ጥገና ስራ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡
መንገዱ የኢትዮ - ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል ሲሆን በርካታ ከባድ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገዱ ብዛት በመጎዳቱ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ አሁን ላይ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው።
60 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የመንገድ ጥገና አስፋልት ማንሳት ፣ የቤዝኮርስ፣ የአስፋልት ጥገና ፣ የጎርፍ ማፋሰሻ መስመሮችን በጎርፍ ከመሸርሸር መከላከል፣ አስፋልት የማንጠፍና መደረብ እንዲሁም የተለዋጭ መንገድ ሥራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን አሁናዊ አፈፃፀሙ 71 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡
ይኸው የመንገድ ጥገና ስራ በአሁኑ ወቅት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ የሚገኝ በመሆኑ በተቀመጠለት እቅድ መሰረት ለማጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡
የመንገዱን ጥገና ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ ዮንአብ ኮንስትራክሽን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በለስ አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ የቁጥጥርና የማማከሩን ሥራ እየሰራ ነው።
ለጥገናው የሚውለው 816,465,221.84 ስምንት መቶ አስራ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ አንድ ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው።
ለመንገዱ ጥገና መደረጉ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል ብሎም የትራፊክ ፍሰትን በበቂ ሁኔታ ለማስተናገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡
የአዳማ - አዋሽ መንገድ የሀገሪቱን ማእከላዊ ክፍል ከምስራቁ ክፍል ጋር ከማገናኘቱ ጎን ለጎን የአዳማና ቦሰት ወረዳዎችን ፣ ዳቤ ሶሎቄ እና ወለንጪቲ ቀበሌዎችን በቅርበት የሚያስተሳስር ነው።
በተያያዘም በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የግብርና ምርቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እና ወደ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ለሚሄዱ ጎብኝዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣል ።
በተመሳሳይ በነባሩ የአዳማ -አዋሽ መንገድ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ ጫና ለማቃለል እንዲቻል ታስቦ የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ - ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
የአለምገና የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት መደበኛ እና ወቅታዊ የጥገና ስራዎችን በማካሄድ ላይ ነው።
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2016 (ኢመአ)፦ የጥገና ዲስትሪክቱ በ2016 በጀት ዓመት ከሚያስተዳድራቸው 11 የጥገና ፕሮጀክቶች ውስጥ የእንድብር ሴክሽን አንዱ ክፍል ሲሆን ሶስት ሴግመንቶችን ያካትታል። እነዚህም የወልቂጤ - ማዞሪያ፣የማዞሪያ - ሆሳዕና እና ቆሴ - ግልገል ጊቤ - 2 ይገኙበታል።
160 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የእንድብር ሴክሽን መንገድ ጥገና በእስካሁን የፋይናንሻል እና ፊዚካል አፈፃፀም ከበጀት ዓመቱ እቅድ አንፃር ከ95% በላይ ተከናውኗል።
መንገዱ ለተጠቃሚዉ እና ለንብረት የአደጋ ስጋት መሆን የለበትም የሚሉት በአለም ገና መንገድ አዉታር ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ የጥገና ኮንትራት አስተዳደር ፕሮጀክት መሀንዲስ ሮቤል ተፈሪ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል ብለዋል።
አያይዘውም በእንድብር ሴክሽን ከተሰሩ ዋና ዋና ስራዎች የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝ ኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ፣ የፉካ እና የፍሳሽ ቦይ ጠረጋ፣ የመንገድ መንሸራተት መከላከል ድጋፍ ግንብ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ክረምት ከመግባቱ አስቀድመን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል።
የመንገድ ጥገናው ከዘጠና ሰባት ሚሊየን ብር በላይ በጀት ተይዞለት በራስ ሀይል እየተሰራ ይገኛል።
በተመሳሳይ ከፍተኛ የትራፊክ ፍስተን በማሰተናገድና በአገልግሎት ብዛት ለጉዳት የተዳረገው 100 ኪ.ሜትር የሚረዝመው የቡታጅራ - ሆሳዕና መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል።
የቡታጅራ ሴክሽን ቡድን መሪ መሃንዲስ ጊዮን ደሳለኝ ይህ መንገድ ለሀገሪቱ ከሚሰጠው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አኳያ መደበኛ ጥገና ማድረጉ ወሳኝ በመሆኑ ስራው እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።
በአሁን ወቅትም ከአንድ መቶ ሰማኒያ ሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት በራስ ሀይል የከባድ ጥገና ስራው በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው።
ጥገናው የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የአገልግሎት ጊዜው ዘላቂ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ሲሆን በመስመሩ በእጅጉ የተጎዳውን የመንገድ ክፍል በቅድሚያ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን ተደርጓል።
የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የመንገድ ጥገና ስራው በመካሄድ ላይ መሆኑ ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ጠቅሰው ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ሳቢያ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል።
በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን፣ የድንጋይ ከሰልን ጨምሮ በመስመሩ የሚመላለሱ አሸዋ ምርት ወደ መሀል ከተማ በማድረስ ገበያውን በማረጋጋት ሸማቾችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል።
የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የመደበኛ፣ የወቅታዊና የከባድ መንገድ ጥገና እያካሄደ ነው ።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
የጅግጅጋ - ገላልሼ - ደገሕመደው - ሰገግ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 78 በመቶ ተጠናቀቀ።
ጅግጅጋ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል 109 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የጅግጅጋ - ገላልሼ - ደገሕመደው - ሰገግ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል78 በመቶው ተጠናቅቋል።
በፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ97 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ97 ኪሎሜትር ሰብቤዝ፣ የ66 ኪሎሜትር ቤዝኮርስ፣ የ45 ኪሎ ሜትር የአስፋልት እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች ተሠርተዋል። በተጨማሪም የስድስት ድልድዮች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉልም ተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
የፕሮጀክቱን የመጀመሪያውን 55 ኪሎ ሜትር አስፋልት የማንጠፍ ሥራ በሰኔ ወር 2016 ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 78 በመቶ ደርሷል።
መንገዱ ከዚህ ቀደም የእርዳታ መኪኖች የሚመላለሱበት ጠባብ የጠጠር መንገድ የነበረ ሲኾን፥ አሁን ላይ በወረዳ 19 በቀበሌ 12 እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በአስፋልት ደረጃ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው።
ሀገር በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ግንባታውን በማከናወን ላይ ነው፡፡ ሲ-ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ይሳተፋል፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1,773,642,189.12 (አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ሦስት ሚሊዮን) ብር፣ ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል፡፡
በአካባቢው ያለው ከፍተኛ የውኃ እጥረት፣ የግንባታ ግብአት እጥረት እና ዋጋ መናር በግንባታው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። የውኃ እጥረቱን ለመቅረፍ በሥራ ተቋራጩ በኩል ዘጠኝ የውኃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎችን ተዘጋጅተው አገልግሎት እየሰጡ መኾኑን ሥፍራው ድረስ በተደረገ የመስክ ምልከታ መታዘብ ተችሏል።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል የሥራ ተቋራጩ የግንባታ ጥሬ እቃዎችን በቀላሉ የሚያገኝበት ሁኔታ እንዲመቻች ተድርጓል። በመኾኑም የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁን ሰዓት ከእቅዱ አንጻር በመልካም ቁመና ላይ ይገኛል።
የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፥ ከዚህ ቀደም ከጅግጅጋ ወደ ደገሕመደው ከተማ ለመጓዝ፣ በደገሐቡር በኩል ይወስድየነበረውን የ240 ኪሎ ሜትር ርቀት ወደ 195 ኪሎ ሜትር ያሳጥረዋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ ቀደም ይፈጅ የነበረውን 4 ሰዓት ተኩል የጉዞ ጊዜ በሁለት ሰዓት ያሳጥረዋል፡፡
የፋፈን እና ደገሐቡር ዞኖችን በቅርበት በማገናኝት፥ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ-አደሮች እና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችንም ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት ትስስር አካል የኾነው ኮንትራት አንድ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ከዚህ ቀደም ግንባታው ተጠናቅቆ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል።
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
13 342
የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት እና የካሳ ክፍያ አዋጅ 1161/2011 ማሻሻያን የተመለከተ ውይይት ተካሄደ
የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ፣ ካሳ የሚከፈልበትን እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1161/2011ን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡
በውይይቱ የከተማና መሰረተ ልማት ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፣ የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡
በእለቱም አዋጁን መከለስ ያስፈለገበት ምክንያት ፣ቀድሞ ስራ ላይ የነበረውንና የተሻሻለውን አዋጅ ንጽጽር ፣ መሬት እንዲለቀቅለት የተወሰነለት አካል ኃላፊነቶች እና የመሸጋገሪያ ድንጋጌን የሚመለከት ገለፃ ቀርቧል፡፡
በገለጻው መሰረት ማሻሻያ የተደረገበት አዋጅ የመሬት ይዞታ እንዲለቁ ለተደረጉ ባለይዞታዎች ተገቢና የተመጣጠነ ካሳ ለመክፈል ግምት ውስጥ መግባት የሚገባቸውን መሰረታዊ መርሆችን ለይቶ ለመወሰን ፣ካሳውን የመተመን የመክፈልና ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ስልጣንና ኃላፊነት ያለባቸውን አካላት በግልጽ ለማስቀመጥ ያለመ ነው፡፡
በተመሳሳይ ለልማት ተነሺዎች ከሚከፈለው የካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ የመሰረተ ልማት ገንቢው ተቋም ካሳ እንዲፈጽም ፣ የወሰን ማስከበር ስራዎችን እንዲያከናውን እንዲሁም ግንባታዎቸን አንዲገነባ ማድረጉ አላስፈላጊ ጫና እና የጊዜ ብክነት እየፈጠረ በመሆኑ ይህንን ለመቅረፍ የሚያስችል በመሆኑ ነው፡፡
እንዲሁም ክፍያ የተራዘመባቸው ንብረቶች ጊዜን ታሳቢ አድርጎ በተቀላጠፈ መልኩ የማይነሱ በመሆናቸው ፣ህገወጥ ግንባታዎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ፣የፌዴራል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እየተጠናቀቁ ባለመሆናቸው የተነሳ መፍትሄ ለመስጠት ሲባል አዋጁን ማሻሻል አስፈልጓል ተብሏል፡፡
በዚህም ምክንያት የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተገንብተው መስጠት የሚገባቸውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅም እንዲሰጡ ለማስቻል በወሰን ማስከበርና በካሳ ክፍያ ምክንያቶች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል የአዋጁ መሻሻል ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡
እንደሀገር ያለውን የልማት ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታትና ወጥነት ባለው የህግ ማዕቀፍ ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ አዋጁን በሚመለከት ከክልሎች ፣ ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት እንዲሁም ከህብረተሰቡ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጉም ተገልጿል፡፡
አዋጁ ሲጸድቅ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወቅት የሚያጋጥሙትን የወሰን ማስከበር ችግሮች በመቅረፍ በመንገድ ዘርፍ የተያዘውን የልማት ፕሮግራም ለማሳካት የመንገድ ግንባታ ፕሮግራሙ በተቀመጠለት ጊዜ ፣ በጀት እና ጥራት ለማከናወን የሚያስችል ይሆናል፡፡
በተጨማሪ
› አጭር መልዕክት 8561
› ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770
› ድህረገጽ www.era.gov.et
› ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et
› ቴሌግራም https://t.me/ethioroads
› ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd
› ኢሜል communication@era.gov.et
› ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
