uz
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

Kanalga Telegram’da o‘tish

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር analitikasi

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 13 331 obunachidan iborat bo'lib, Transport toifasida 1 756-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 537-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 13 331 obunachiga ega bo‘ldi.

17 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 95 ga, so‘nggi 24 soatda esa 18 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 41.14% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 15.24% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 5 485 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 032 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 16 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 18 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Transport toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

13 331
Obunachilar
+1824 soatlar
+417 kunlar
+9530 kunlar
Postlar arxiv
በፊቅ-ሰገግ መንገድ ፕሮጀክት አስፋልት ማንጠፍ ተጀመረ አዲስ አበባ፣ ሰኔ 28፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል የፊቅ - ሰገግ - ገርቦ - ደናን መንገድ ፕሮጀክት አካል የኾነው ምዕራፍ አንድ ፊቅ - ሰገግ አስፋልት የማንጠፍ ሥራ ተጀምሯል። የመንገድ ፕሮጀክቱ 90 ኪሎ ሜትር የሚሸፍን ሲኾን፣ ከአጠቃላይ የፕሮጀክቱ ሥራ አሁን ላይ 45 ነጥብ 13 በመቶው ተጠናቅቋል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁኑ ወቅት ወደ አስፋልት የማንጠፍ ምዕራፍ የተሸጋገረ ሲኾን፣ እየተከናወኑ ከሚገኙ የግንባታ ሥራዎች መካከልም የ7 ኪ.ሜ የአስፋልት ንጣፍ፣ የ19 ከ.ሜ ሰብቤዝ፣ የ11 ከ.ሜ ቤዝኮርስ፣ የ75 ኪ.ሜ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ በተጨማሪም የአንድ ድልድይ ግንባታ የተጠናቀቀ ሲኾን፣ ቀሪ የኹለት ድልድዮች ግንባታ በሂደት ላይ ይገኛል፡፡ ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ - ተቋራጭ ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ አማካሪ የግንባታውን የቁጥጥር እና የማማከር ሥራ ይሠራል፡፡ ለመንገድ ግንባው 1,422,968,463.00 (አንድ ቢሊዮን ዘጠኝ መቶ ስልሳ ስምንት ሺህ) ብር ከፌደራል መንግስት ተመድቧል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅ ከአዲስ አበባ በፊቅ በኩል ጎዴ ለመጓዝ ቀድሞ ይፈጅ የነበረውን 1ሺህ 170 ኪሎ ሜትር መንገድ በ150 ኪ.ሜ ያሳጥረዋል፡፡ ከጎዴ-ጅጅጋ-ሐረር ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜና የትራፊክ መጨናነቅ ይቀንሰዋል፡፡ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡  ዮሆብ፣ ሰገግ እና ሌሎች በርካታ ቀበሌዎችን በቅርበት በማገናኘት ወደ ከተማነት የሚያድጉበት ምቹ አጋጣሚ ይፈጥራል፡፡ የዚሁ መንገድ ፕሮጀክት ኮሪደር ቀጣይ ክፍል የሆኑት ምዕራፍ 2 ሰገግ-ገርቦ-ዮአለ አስፋልት መንገድ በግንባታ ላይ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው ጅግጅጋ፣ ሰኔ 24፣ 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ በሶማሌ ክልል በ672,098,730 (ስድስት መቶ ሰባ ሁለት ሚሊዮን) ብር ወጪ የሚገነባው የጅግጅጋ ከተማ ተለዋጭ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ፕሮጀክት ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ እየተሠራ ነው። የመንገድ ፕሮጀክቱ ከቶጎ-ጫሌ መገንጠያ አንስቶ እስከ ሐረር መውጫ ድረስ ያለውን ሥፍራ የሚሸፍን ሲሆን፣ 6 ነጥብ 93 ኪሎሜትር ርዝመት እና 30 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በተጨማሪም የእግረኛ እና የብስክሌተኞች መተላለፊያ እንዲሁም የአረንጓዴ ሥፍራ ግንባታ ያካትታል። በእስከአሁኑ የግንባታ ሥራዎች መካከል የ87 ነጥብ 15 በመቶ የአፈር ቆረጣ፣ የ6 ነጥብ 03 ኪሎ ሜትር ሰብቤዝ የ1 ነጥብ 1 ኪሎ ሜትር ቤዝኮርስ፣ የ 78 በመቶ ፉካ እና የማፋሰሻ ቱቦ እንዲሁም የ84 በመቶ የ ድልድይ እና የግምብ ሥራዎች ተሠርተዋል። ፕሮጀክቱ አሁን ላይ ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል 67 በመቶው የተጠናቀቀ ሲኾን፥ ቀሪ የግንባታ ሥራውን ባጠረ ጊዜ ለማጠናቀቅ በትኩረት እየተሠራ ይገኛል። ለዚህም በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል አስፈላጊው ጥብቅ ድጋፍ እና ክትትል እየተደረገ ይገኛል። ግንባታውን የሚያከናውነው ሀገር-በቀሉ ይርጋለም ኮንስትራክሽን ሲኾን፣ የማማከርና የቁጥጥር ሥራውን ኤልዳ አማካሪ ድርጅት ከዳምራ ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጥምረት ይሠራሉ። ለግንባታው የተመደበው ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ነው የተሸፈነው። የተለዋጭ መንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ በከተማዋ ውስጥ እንዲሁም መግቢያና መውጫ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ መጨናነቅ በእጅጉ የሚቀንስ ነው። ከሐረር ወደ ቶጎ ጫሌ እና ቀብሪበያህ ወይም ቀብሪደሀር የሚጓዙ ተሸከርካሪዎች ጅግጅጋ ከተማ መግባት ሳያስፈልጋቸው በቀጥታ መሄድ ያስችላቸዋል፡፡ ከዚህም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት እና ውበት በማሳለጥ በኩል ግንባር ቀደም ሚና ይጫወታል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የደንገጎ-ሐረር-ቁልቢ-አዋሽ መገንጠያ መንገድ ጥገና እየተደረገለት ነው ድሬዳዋ፣ ሰኔ 20፣ 2016 (ኢ መ አ):- የኢትዮ-ጅቡቲ ትራንስፖርት ኮሪደር አካል የኾነው የደንገጎ-ሐረር-ቁልቢ-አዋሽ መገንጠያ መንገድ መደበኛ ጥገና እየተደረገለት ነው። የመንገድ ጥገናውን በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት እያከናወነ ይገኛል። መንገዱ የሀገሪቱ የገቢ እና ወጪ ንግድ ዋና መስመር እና ከከባድ እስከ ቀላል ተሽክከርካሪዎች የሚተላለፉበት እንደመኾኑ እና ከአነስተኛ እስከ ከባድ መጠን ባላቸው ጉድጎዶች(deep holes) እና ሌሎች እንደ መሰንጠቅ ያሉ የጉዳት ዓይነቶች በመጎዳቱ መደበኛ የጥገና ሥራ እየተከናወነለት ይገኛል። የጥገና ሥራው የአስፋልት ኦቨርሌይ፣ ሰብቤዝ እና ቤዝኮርስ፣ አስፋልት ፓቺንግ እንዲሁም ኮንክሪት ፔቭመንት ሥራዎችን አካትቷል።  በመሥመሩ የሚገኙ የከባድ እና የሕዝብ ማመላለሻ መኪና አሽከርካሪዎች፣ የመንገድ ጥገናው እንግልት እና ለመኪና ዕቃ መለዋወጫ የሚወጣውን አላስፈላጊ ወጪ እንዳስቀረላቸው ተናግረዋል። ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰቱን ተከትሎ ተለዋጭ መንገድ አለመኖር እንዲሁም የሰው እና የማሽነሪ እጥረት የጥገናው ፈተና መኾኑ ተመልክቷል። መደበኛ ጥገናው በሦስት ሴክሽኖች ተከፋፍሎ በመገንባት ላይ ይገኛል። የድሬዳዋ ዲስትሪክት በአጠቃላይ 3 ሺህ 107 ኪሎ ሜትር የሚያካልሉ መንገዶችን የሚያስተዳድር ሲኾን፣ በአምስት የተለያዩ ሴክሽኖች በተለየየ ደረጃ መጠነ ሰፊ የጥገና ሥራዎችን እያከናወነ ይገኛል። በተጨማሪም የኤርጎኖሚክስ፣ የሚዛን ጣቢያ እንዲሁም የድልድይ ሥራዎችን በማከናወን ላይ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

በነባሩ የአዳማ - አዋሽ መንገድ የከባድ ጥገና ስራ በመካሄድ ላይ ይገኛል አዳማ፣ ሰኔ 19፣ 2016 (ኢመአ)፦ የኢትዮጵያን 90 ከመቶ በላይ የወጪ ገቢ ንግድ እንቅስቃሴ በሚያስተናግደው ነባሩ የአዳማ - አዋሽ መንገድ ላይ የከባድ መንገድ ጥገና ስራ በመካሄድ ላይ ይገኛል፡፡ መንገዱ የኢትዮ - ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል ሲሆን በርካታ ከባድ ተሽከርካሪዎችን በማስተናገዱ ብዛት በመጎዳቱ መፍትሄ ያገኝ ዘንድ አሁን ላይ ከባድ ጥገና እየተደረገለት ነው። 60 ኪሎ ሜትር በሚረዝመው የመንገድ ጥገና አስፋልት ማንሳት ፣ የቤዝኮርስ፣ የአስፋልት ጥገና ፣ የጎርፍ ማፋሰሻ መስመሮችን በጎርፍ ከመሸርሸር መከላከል፣ አስፋልት የማንጠፍና መደረብ እንዲሁም የተለዋጭ መንገድ ሥራዎች እየተከናወኑ የሚገኙ ሲሆን አሁናዊ አፈፃፀሙ 71 ነጥብ 5 በመቶ ደርሷል፡፡ ይኸው የመንገድ ጥገና ስራ በአሁኑ ወቅት በጥሩ የአፈፃፀም ሂደት ላይ የሚገኝ በመሆኑ በተቀመጠለት እቅድ መሰረት ለማጠናቀቅ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው፡፡ የመንገዱን ጥገና ሀገር በቀሉ የስራ ተቋራጭ ዮንአብ ኮንስትራክሽን እያከናወነ የሚገኝ ሲሆን በለስ አማካሪ ኃ/የተ/የግ/ማ የቁጥጥርና የማማከሩን ሥራ እየሰራ ነው። ለጥገናው የሚውለው 816,465,221.84 ስምንት መቶ አስራ ስድስት ሚሊዮን አራት መቶ ስልሳ አምስት ሺህ ሁለት መቶ ሃያ አንድ ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው። ለመንገዱ ጥገና መደረጉ የተሻለ አገልግሎት መስጠት እንዲቻል ብሎም የትራፊክ ፍሰትን በበቂ ሁኔታ ለማስተናገድ ከፍተኛ ፋይዳ አለው፡፡ የአዳማ - አዋሽ መንገድ የሀገሪቱን ማእከላዊ ክፍል ከምስራቁ ክፍል ጋር ከማገናኘቱ ጎን ለጎን የአዳማና ቦሰት ወረዳዎችን ፣ ዳቤ ሶሎቄ እና ወለንጪቲ ቀበሌዎችን በቅርበት የሚያስተሳስር ነው። በተያያዘም በአካባቢው በስፋት የሚገኙትን የግብርና ምርቶች ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማቅረብ እና ወደ አዋሽ ብሔራዊ ፓርክ ለሚሄዱ ጎብኝዎች ምቹ ሁኔታን በመፍጠር ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጣል ። በተመሳሳይ በነባሩ የአዳማ -አዋሽ መንገድ ላይ የሚስተዋለውን የትራፊክ ጫና ለማቃለል እንዲቻል ታስቦ የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ አዳማ - ኪሎ ሜትር 60 የፍጥነት መንገድ ግንባታ እየተካሄደ መሆኑ ይታወቃል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአለምገና የመንገድ ጥገና ዲስትሪክት መደበኛ እና ወቅታዊ የጥገና ስራዎችን በማካሄድ ላይ ነው። አዲስ አበባ፣ ሰኔ 18፣ 2016 (ኢመአ)፦ የጥገና ዲስትሪክቱ በ2016 በጀት ዓመት ከሚያስተዳድራቸው 11 የጥገና ፕሮጀክቶች ውስጥ የእንድብር ሴክሽን አንዱ ክፍል ሲሆን ሶስት ሴግመንቶችን ያካትታል። እነዚህም የወልቂጤ - ማዞሪያ፣የማዞሪያ - ሆሳዕና እና ቆሴ - ግልገል ጊቤ - 2 ይገኙበታል። 160 ኪሎ ሜትር የሚሸፍነው የእንድብር ሴክሽን መንገድ ጥገና በእስካሁን የፋይናንሻል እና ፊዚካል አፈፃፀም ከበጀት ዓመቱ እቅድ አንፃር ከ95% በላይ ተከናውኗል። መንገዱ ለተጠቃሚዉ እና ለንብረት የአደጋ ስጋት መሆን የለበትም የሚሉት በአለም ገና መንገድ አዉታር ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ቢሮ የጥገና ኮንትራት አስተዳደር ፕሮጀክት መሀንዲስ ሮቤል ተፈሪ ከፍተኛ መዋዕለ ነዋይ የሚፈስበት የመንገድ ሃብት የሚጠበቅበትን አገልግሎት እንዲሰጥ ተገቢ ጥበቃ እና እንክብካቤ ያስፈልገዋል ብለዋል። አያይዘውም በእንድብር ሴክሽን ከተሰሩ ዋና ዋና ስራዎች የተበላሹ የመንገድ ክፍሎችን በአስፋልት የመሙላት፣ የቤዝ ኮርስ ማስተካከል፣ የመንገድ ትከሻ፣ የፉካ እና የፍሳሽ ቦይ ጠረጋ፣ የመንገድ መንሸራተት መከላከል ድጋፍ ግንብ ስራዎች የተሰሩ ሲሆን ቀሪ ስራዎችን ክረምት ከመግባቱ አስቀድመን ለማጠናቀቅ ከፍተኛ ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል። የመንገድ ጥገናው ከዘጠና ሰባት ሚሊየን ብር በላይ በጀት ተይዞለት በራስ ሀይል እየተሰራ ይገኛል። በተመሳሳይ ከፍተኛ የትራፊክ ፍስተን በማሰተናገድና በአገልግሎት ብዛት ለጉዳት የተዳረገው 100 ኪ.ሜትር የሚረዝመው የቡታጅራ - ሆሳዕና መንገድ ጥገና እየተደረገለት ይገኛል። የቡታጅራ ሴክሽን ቡድን መሪ መሃንዲስ ጊዮን ደሳለኝ ይህ መንገድ ለሀገሪቱ ከሚሰጠው ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጠቀሜታ አኳያ መደበኛ ጥገና ማድረጉ ወሳኝ በመሆኑ ስራው እየተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁን ወቅትም ከአንድ መቶ ሰማኒያ ሰባት ሚሊዮን ብር በላይ በጀት ተይዞለት በራስ ሀይል የከባድ ጥገና ስራው በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ ነው። ጥገናው የጥራት ደረጃውን በጠበቀ መልኩ የአገልግሎት ጊዜው ዘላቂ እንዲሆን ትኩረት ተሰጥቶት እየተሰራ ሲሆን በመስመሩ በእጅጉ የተጎዳውን የመንገድ ክፍል በቅድሚያ ጥገናውን በማከናወን የትራፊክ ፍሰቱን ምቹ እንዲሆን ተደርጓል። የዝግጅት ክፍላችን ያነጋገራቸው የመንገዱ ተጠቃሚዎች እና አሽከርካሪዎች በበኩላቸው የመንገድ ጥገና ስራው በመካሄድ ላይ መሆኑ ይበል የሚያሰኝ መሆኑን ጠቅሰው ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ከመቀነሱም ባሻገር በመንገዱ ብልሽት ሳቢያ ይወስድ የነበረውን የጉዞ ጊዜ በእጅጉ ያሳጥረዋል ብለዋል። በየአካባቢዎቹ የሚመረተውን የተለያዩ የግብርና ውጤቶችን፣ የድንጋይ ከሰልን ጨምሮ በመስመሩ የሚመላለሱ አሸዋ ምርት ወደ መሀል ከተማ በማድረስ ገበያውን በማረጋጋት ሸማቾችን በሰፊው ተጠቃሚ ያደርጋል። የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ከመንገድ ፕሮጀክቶች ግንባታ ጎን ለጎን በበርካታ የሀገሪቱ የተለያዩ ክፍሎች የሚገኙትን ጉዳት የገጠማቸውን መንገዶች በራስ ሀይልና በኮንትራክትሮች የመደበኛ፣ የወቅታዊና የከባድ መንገድ ጥገና እያካሄደ ነው ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የጅግጅጋ - ገላልሼ - ደገሕመደው - ሰገግ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት 78 በመቶ ተጠናቀቀ። ጅግጅጋ፣ ሰኔ 11፣ 2016 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል 109 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የጅግጅጋ - ገላልሼ - ደገሕመደው - ሰገግ ኮንትራት ሁለት አስፋልት መንገድ ፕሮጀክት ከአጠቃላይ የመንገዱ ክፍል78 በመቶው ተጠናቅቋል። በፕሮጀክቱ አሁን ላይ የ97 በመቶ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት፣ የ97 ኪሎሜትር ሰብቤዝ፣ የ66 ኪሎሜትር ቤዝኮርስ፣ የ45 ኪሎ ሜትር የአስፋልት እንዲሁም የውኃ መፋሰሻ ሥራዎች ተሠርተዋል። በተጨማሪም የስድስት ድልድዮች ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቋል። የመንገድ ግንባታው የትራፊክ እንቅስቃሴውን እንዳያስተጓጉልም ተለዋጭ መንገድ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። የፕሮጀክቱን የመጀመሪያውን 55 ኪሎ ሜትር አስፋልት የማንጠፍ ሥራ በሰኔ ወር 2016 ውስጥ ለማጠናቀቅ ዕቅድ ተቀምጦ እየተሠራ ይገኛል። በአሁኑ ወቅት የፕሮጀክቱ አጠቃላይ አፈጻጸም 78 በመቶ ደርሷል። መንገዱ ከዚህ ቀደም የእርዳታ መኪኖች የሚመላለሱበት ጠባብ የጠጠር መንገድ የነበረ ሲኾን፥ አሁን ላይ በወረዳ 19 በቀበሌ 12 እንዲሁም በገጠር 10 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ በአስፋልት ደረጃ ነው በመገንባት ላይ የሚገኘው። ሀገር በቀሉ ቤአኤካ ጠቅላላ ንግድ ሥራ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ግንባታውን በማከናወን ላይ ነው፡፡ ሲ-ቴክ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ፕሮጀክቱን በማማከር እና በመቆጣጠር በኩል ይሳተፋል፡፡ ለግንባታው የተመደበው 1,773,642,189.12 (አንድ ቢሊዮን ሰባት መቶ ሰባ ሦስት ሚሊዮን) ብር፣ ወጪ ሙሉ በሙሉ በፌደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል፡፡ በአካባቢው ያለው ከፍተኛ የውኃ እጥረት፣ የግንባታ ግብአት እጥረት እና ዋጋ መናር በግንባታው ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ አሳድረዋል። የውኃ እጥረቱን ለመቅረፍ በሥራ ተቋራጩ በኩል ዘጠኝ የውኃ ማጠራቀሚያ ኩሬዎችን ተዘጋጅተው አገልግሎት እየሰጡ መኾኑን ሥፍራው ድረስ በተደረገ የመስክ ምልከታ መታዘብ ተችሏል። በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በጅግጅጋ አካባቢ ግንባታ ፕሮጀክቶች ማስተባበሪያ ጽ/ቤት በኩል የሥራ ተቋራጩ የግንባታ ጥሬ እቃዎችን በቀላሉ የሚያገኝበት ሁኔታ እንዲመቻች ተድርጓል። በመኾኑም የመንገድ ፕሮጀክቱ በአሁን ሰዓት ከእቅዱ አንጻር በመልካም ቁመና ላይ ይገኛል። የመንገድ ግንባታው ሲጠናቀቅ፥ ከዚህ ቀደም ከጅግጅጋ ወደ ደገሕመደው ከተማ ለመጓዝ፣ በደገሐቡር በኩል ይወስድየነበረውን የ240 ኪሎ ሜትር ርቀት ወደ 195 ኪሎ ሜትር ያሳጥረዋል፡፡ በመሆኑም ከዚህ ቀደም ይፈጅ የነበረውን 4 ሰዓት ተኩል የጉዞ ጊዜ በሁለት ሰዓት ያሳጥረዋል፡፡ የፋፈን እና ደገሐቡር ዞኖችን በቅርበት በማገናኝት፥ በአካባቢው የሚገኙ አርብቶ-አደሮች እና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ የተሰማሩ ባለሀብቶችንም ተጠቃሚ ያደርጋል፡፡ የዚሁ ፕሮጀክት ትስስር አካል የኾነው ኮንትራት አንድ አስፋልት ኮንክሪት መንገድ ከዚህ ቀደም ግንባታው ተጠናቅቆ ደረጃውን የጠበቀ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት እና የካሳ ክፍያ አዋጅ 1161/2011 ማሻሻያን የተመለከተ ውይይት ተካሄደ የመሬት ይዞታ የሚለቀቅበት ፣ ካሳ የሚከፈልበትን እና ተነሺዎች መልሰው የሚቋቋሙበትን ሁኔታ ለመወሰን የወጣውን አዋጅ ቁጥር 1161/2011ን ለማሻሻል የቀረበ ረቂቅ አዋጅ ላይ ውይይት ተካሄደ፡፡ በውይይቱ የከተማና መሰረተ ልማት ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ፣ የህግና ፍትህ ቋሚ ኮሚቴ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባላት እንዲሁም የተቋማት የስራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች ተሳታፊ ሆነዋል፡፡ በእለቱም አዋጁን መከለስ ያስፈለገበት ምክንያት ፣ቀድሞ ስራ ላይ የነበረውንና የተሻሻለውን አዋጅ ንጽጽር ፣ መሬት እንዲለቀቅለት የተወሰነለት አካል ኃላፊነቶች እና የመሸጋገሪያ ድንጋጌን የሚመለከት ገለፃ ቀርቧል፡፡ በገለጻው መሰረት ማሻሻያ የተደረገበት አዋጅ የመሬት ይዞታ እንዲለቁ ለተደረጉ ባለይዞታዎች ተገቢና የተመጣጠነ ካሳ ለመክፈል ግምት ውስጥ መግባት የሚገባቸውን መሰረታዊ መርሆችን ለይቶ ለመወሰን ፣ካሳውን የመተመን የመክፈልና ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ስልጣንና ኃላፊነት ያለባቸውን አካላት በግልጽ ለማስቀመጥ ያለመ ነው፡፡ በተመሳሳይ ለልማት ተነሺዎች ከሚከፈለው የካሳ ክፍያ ጋር በተያያዘ የመሰረተ ልማት ገንቢው ተቋም ካሳ እንዲፈጽም ፣ የወሰን ማስከበር ስራዎችን እንዲያከናውን እንዲሁም ግንባታዎቸን አንዲገነባ ማድረጉ አላስፈላጊ ጫና እና የጊዜ ብክነት እየፈጠረ በመሆኑ ይህንን ለመቅረፍ የሚያስችል በመሆኑ ነው፡፡ እንዲሁም ክፍያ የተራዘመባቸው ንብረቶች ጊዜን ታሳቢ አድርጎ በተቀላጠፈ መልኩ የማይነሱ በመሆናቸው ፣ህገወጥ ግንባታዎች እየተበራከቱ መምጣታቸው ፣የፌዴራል መሰረተ ልማት ግንባታዎች በተያዘላቸው ጊዜና በጀት እየተጠናቀቁ ባለመሆናቸው የተነሳ መፍትሄ ለመስጠት ሲባል አዋጁን ማሻሻል አስፈልጓል ተብሏል፡፡ በዚህም ምክንያት የመንገድ መሰረተ ልማቶች ተገንብተው መስጠት የሚገባቸውን ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥቅም እንዲሰጡ ለማስቻል በወሰን ማስከበርና በካሳ ክፍያ ምክንያቶች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለማቃለል የአዋጁ መሻሻል ከፍተኛ ጥቅም ይኖረዋል፡፡ እንደሀገር ያለውን የልማት ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታትና ወጥነት ባለው የህግ ማዕቀፍ ህዝቡን ተጠቃሚ ለማድረግ አዋጁን በሚመለከት ከክልሎች ፣ ከሚመለከታቸው የባለድርሻ አካላት እንዲሁም ከህብረተሰቡ ጋር ተደጋጋሚ ውይይቶች መደረጉም ተገልጿል፡፡ አዋጁ ሲጸድቅ በፕሮጀክቶች አፈጻጸም ወቅት የሚያጋጥሙትን የወሰን ማስከበር ችግሮች በመቅረፍ በመንገድ ዘርፍ የተያዘውን የልማት ፕሮግራም ለማሳካት የመንገድ ግንባታ ፕሮግራሙ በተቀመጠለት ጊዜ ፣ በጀት እና ጥራት ለማከናወን የሚያስችል ይሆናል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ኢድ ሙባረክ!

በአፋር ኮሪደር እየተገነቡ ያሉ የመንገድ መሰረተ ልማት ትሩፋቶች