ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 331 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 756,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 537

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 331 名订阅者。

根据 17 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 95,过去 24 小时变化为 18,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 41.14%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.24% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 485 次浏览,首日通常累积 2 032 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 16

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 18 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 342
订阅者
+1824 小时
+417
+9530
帖子存档
የሃሙሲት - እስቴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የአፈፃፀም ደረጃ ይገኛል አዲስ አበባ፣ ግንቦት 04፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- 76.64 ኪሎ ሜትር የሚረዝመው የሃሙሲት - እስቴ የአስፋልት ኮንክሪት የመንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመልካም የአፈጻጸም ደረጃ ይገኛል። በመንገድ ግንባታው እስከ አሁን የጠረጋ ፤ የውሃ መፋሰሻ ፤ የአፈር ፤ የሰብ ቤዝ፤ ቤዝ ኮርስ ፤ የአስፋልት ንጣፍ እንዲሁም የስትራክቸር ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡የግንባታው አጠቃላይ አፈጻጸም በአሁን ወቅት 51.66 በመቶ ደርሷል፡፡ በተጨማሪም የአነስተኛ እና ከፍተኛ ከልቨርቶች እንዲሁም የሰባት ድልድዮች ግንባታ ሥራም በፕሮጀክቱ ተካትቷል፡፡ ዓለም አቀፉ ኒንዢያ ኮሚኒኬሽን ኮንስትራክሽን ግንባታውን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ኻቲብ እና አለሚ ኮንሰልቲንግ ከ ኮር ኮንሰልቲንግ ኢንጂነርስ ጋር በጣምራ የግንባታውን ጥራት የመቆጣጠር እና የማማከሩን ሥራ እየሰሩ ይገኛሉ፡፡ ለፕሮጀክቱ ማስፈጸሚያ የሚሆነው 1,394,732,680.97 ብር ወጪ የተሸፈነው በአረብ ባንክ በአፍሪካ ኢኮኖሚ ልማት (BADEA) ፣በኦፔክ ፈንድ ለአለም አቀፍ ልማት (OFID) እና በኢትዮጵያ መንግስት ነው፡፡ የሃሙሲት - እስቴ የአስፋልት ኮንክሪት መንገድ በከተማ ከ21 እስከ 22.5 ሜትር እንዲሁም በገጠር ከ 8 እስከ 10 ሜትር መንገዱን ትከሻ ጨምሮ አጠቃላይ የጎን ስፋት የሚኖረው ይሆናል፡፡ በአካባቢው የሚስተዋለው የጸጥታ ስጋት፣ በመንገድ ክልል ውስጥ የሚገኙ ንብረቶች በወቅቱ አለመነሳት እንዲሁም የካሳ ክፍያ መዘግየት በግንባታው ሂደት ውስጥ የገጠሙ ችግሮች ናቸው፡፡ ችግሮቹን ለመፍታት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በኩል ከአካባቢው ማኅበረሰብ እና የመስተዳድር አካላት ጋር በትብብር እየሰራ ነው፡፡ ፕሮጀክቱ ከፍተኛ የግብርና ምርቶች አምራች የሁኑትን የእስቴ እና ደራ ወረዳን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ የሚያስተሳስር በመሆኑ ከፍተኛ የኢኮኖሚያዊ እና ማህበራዊ ጥቅሞችን የሚሰጥ ነው፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የዱርቤቴ - ቁንዝላ - ገላጎ - መተማ ኮንትራት አንድ እና ሦስት መንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ለማሻሻል እየተሠራ ነው አዲስ አበባ፣ ግንቦት 29፣ 2016 (ኢ መ አ) ፡- በአማራ ክልል ሰሜን ጎጃም ዞንን ከማዕከላዊ እና ምዕራብ ጎንደር ዞኖች ጋር የሚያስተሳስሩት የኮንትራት - አንድ ዱርቤቴ - ቁንዝላ - ሻውራ - ፍንጅት እንዲሁም የኮንትራት - ሦስት የገላጎ - ገንደ ውኃ መንገድ ፕሮጀክቶች አፈጻጸም ለማሻሻል እየተሠራ ነው። የመንገድ ግንባታዎቹ በጥቅሉ 260 ነጥብ 5 ኪሎሜትሮችን የሚሸፍኑ ሲኾን፣ የአዲስ አበባ - ደብረማርቆስ - ባሕርዳር እና የጎንደር - አዘዞ - መተማ ዋና መንገዶችን የሚያገናኙ ናቸው፡፡  አሁን ላይ የዲዛይን፣ የአፈር ቆረጣ እና ጠረጋ፣ የሰቤዝ እንዲሁም የተፋሰስ እና የድልድይ ሥራዎች ተሠርተዋል፡፡ በተጨማሪም የአስፋልት ንጣፍ ለመጀመር የሚያስችሉ የክሬሸር እና የአስፋልት ፕላንት ተከላ ተካሂዷል፡፡    ዜጂአንግ ኮሚኒኬሽን ኮንስትራክሽን ግሩፕ ግንባታዎቹን በማከናወን ላይ ይገኛል፡፡ ለፕሮጀክቶቹ 5 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር የተመደበ ሲኾን፣ ወጪው በፊደራል መንግስት በጀት ይሸፈናል፡፡  በክልሉ በተከሰተው የጸጥታ ችግር ምክንያት ግንባታው አልፎ አልፎ መቋረጡ እና ከዚህም ጋር በተያያዘ የግንባታ ግብዓቶችን በቀላሉ ወደ ፕሮጀክቱ ሥፍራ ማንቀሳቀስ አለመቻሉ እንዲሁም የሥራ ተቋራጩ ደካማ አፈጻጸም በግንባታው ላይ የገጠሙ ፈተናዎች ናቸው፡፡ ከጸጥታ ስጋት ጋር በተያያዘ ከየአካባቢው ሽማግሌዎች እና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመቀናጀት ግንባታው እንዳይቋረጥ ማድረግ ተችሏል፡፡ በሥራ ተቋራጩ በኩል አፈጻጸሙን ለማሻሻል የሚያስችሉ የተለያዩ የእርምት ዕርምጃዎች ተወስደዋል፡፡ በመኾኑም በአሁን ወቅት ፕሮጀክቶቹን ወደ ተሻለ ቁመና ላይ ለማድረስ እየተሠራ ይገኛል፡፡ የመንገድ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የዱርቤቴ፣ ይስማላ፣ ሊበን፣ ቁንዝላ፣ ዱባባ፣ ሽንፋ እና ሌሎች በርካታ ከተሞችን ደረጃውን በጠበቀ መንገድ ያገናኛሉ፡፡ በአካባቢው በስፋት የሚመረቱትን የጤፍ፣ ስንዴ፣ ቦቆሎ፣ ሽንብራ፣ ሰሊጥ፣ ጥጥ እና መሰል የአዝርዕት ምርት ውጤቶችን በቀላሉ ወደ ማዕከላዊ ገበያ ለማድረስ ያስችላል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር በሁለተኛው የ "ቢግ 5 ኮንስትራክት ኢትዮጵያ"  ዓለም አቀፍ ኤክስፖ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል በዛሬው ዕለት በሚሊኒየም አዳራሽ የተከፈተው  ዓለም አቀፍ ኤክስፖው፣ ለሦስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲኾን፣ በከተማ ልማት እና ኮንስትራክሽን ሚንስቴር፣ በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን እና በዓለም አቀፉ ዲ ኤም ጂ ኢሸንትስ በጋራ የተዘጋጀ ነው። ኤግዚብሽኑ የኮንስትራክሽን ዘርፍ የደረሰበትን የቴክኖሎጂ ደረጃ የማስተዋወቅ እና በተለይም ሀገር በቀል የግንባታ ተቋራጮች ዓለም አቀፍ ልምዶችን የሚጋሩበትን ዕድል እንደሚፈጥር ተገልጻል። ከዚህም ባለፈ የኮንስትራክሽን ዘርፍ ማነቆዎች በመለየት እና በመቅረፍ በኩልም ምቹ አጋጣሚ እንደሚፈጥርም ተነግሯል። ለሁለተኛ ጊዜ እየተካሄደ በሚገኘው ኤክስፖ ከ22 ሀገራት የመጡ ዓለም አቀፍ ድርጅቶች እና በኮንስትራክሽን ዘርፍ የተሰማሩ ከ150 በላይ ኩባንያዎች ይሳተፍሉ። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የዱርጊ-ጊቤ ወንዝ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል ሶዶ፣ ግንቦት 14 ቀን 2016 ዓ.ም (ኢመአ)፡ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሚያ ክልል ጋር የሚያገናኘው ኮንትራት ሁለት የዱርጊ - ጊቤ ወንዝ መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት በመጠናቀቅ ላይ ይገኛል፡፡ የፕሮጀክቱ አሁናዊ ሁኔታ በተመለከተ የመንገዱ 25.23 ኪሎ ሜትር የአፈር ቆረጣ ፣ ጠረጋና ሙሌት ስራው አልቆ በሰብ ቤዝ የተሸፈነ ሲሆን ፣ የድልድይ ግንባታ ስራዎችም ተጠናቀዋል፡፡ የመንገዱ አጠቃላይ ርዝመት 27.7 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲሆን ፣ ከዚህም ውስጥ 25 ኪሎ ሜትር ወይም 89 በመቶ ስራው ተጠናቋል፡፡ ግንባታውን በማካሄድ ላይ የሚገኘው ሀገር በቀሉ ብሪጅ ኮንስትራክሽን ኃ/የተ/የግ/ማኅበር ሲሆን የማማከር እና የቁጥጥር ስራውን ደግሞ ቫልዩ ኢንጂነሪንግ ኃ/የተ/የግ/ማኅበር እያከናወነው ይገኛል ፡፡ መንገዱ የሚገነባበት መልክኣ ምድራዊ አቀማመጥ 62% ሜዳማ (Flat) ፣ 28% ወጣ ገባ (Rolling) እና 10% ተራራማ (mountainous) ነው፡፡ ፕሮጀክቱን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 522, 758, 336 (አምስት መቶ ሃያ ሁለት ሚሊየን ሰባት መቶ ሃምሳ ስምንት ሺ ሶስት መቶ ሰላሳ ስድስት ብር) በኢትዮጵያ መንግስት የተሸፈነ ነው ፡፡ ይህ ፕሮጀክት ከመጀመሩ በፊት በአካባቢው ምንም ዓይነት የመንገድ መሰረተ ልማት ያልነበረ በመሆኑ ነዋሪዎቹ የተለያዩ ችግሮችን ሲያስተናግዱ ቆይተዋል፡፡ አሁን ላይ በአስፋልት ደረጃ በመገንባት ላይ የሚገኘው ይኸው ፕሮጀክት ሲጠናቀቅ ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልልን ከኦሮሞያ ክልል ጋር የሚያስተሳስር ከመሆኑም ባሻገር የመንገድ መሠረተ ልማት ተጠቃሚ ያልነበሩት የአካባቢው አርሶ አደሮች አስፋልት መንገድን ተጠቅመው ምርታቸውን ወደ ማዕከላዊ ገበያ በቀላሉ በማድረስ ተገቢውን ጥቅም እንዲያገኙ ያስችላቸዋል፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ብዙ የቱሪስት መስህብ ስፍራዎች ላላት ባህርዳር እና አካባቢዋ አዲሱ ድልድይ እራሱን የቻለ የቱሪስት መስህብ በመሆን አዎንታዊ ሚናውን ይወጣል፡፡ አንዱን አካባቢ ከሌላው ጋር በማስተሳሰር የምርትና የሸቀጥ ልውውጥን ያለእንግልት በቀላሉ እንዲያከናወኑም ይረዳል ፡፡ በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ የአባይ ወንዝ አባይ የናይል ወንዝ ታላቁ ገባር ሲሆን፣ መነሻውም ኢትዮጵያ ነው። አባይ 70 በመቶ የሚሆነው የሀገሪቱን ወንዞች የውሃ መጠን ሲይዝ አጠቃላይ የውሃ ድርሻውም ቢሆን 50 በመቶ የሚጠጋ ነው። ታላቁ የአባይ ወንዝ 1,450 ኪሎ ሜትር አጠቃላይ ርዝመት አለው፡፡ ከዚህ አጠቃላይ ርዝመት ውስጥ 800 ኪ.ሜ. ያህሉን በሀገር ውስጥ ይጓዛል፡፡ ከደቡባዊ የጣና ሀይቅ በመነሳት የሀገሪቱን ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ እየተጠማዘዘ ወደ ሱዳን የሚገባው አባይ 400 ኪ.ሜ. ያህሉን በሸለቆ ውስጥ ስለሚያልፍ ወንዙን ለመሻገር እጅግ አስቸጋሪ በመሆኑ ከቀሪው ግማሽ የሀገሪቱ ክፍል ጋር ያለድልድይ መገናኘት አዳጋች ነው፡፡ ምንም እንኳ ወደ ጣና ሀይቅ የሚገቡ ገባር ወንዞች ቢኖሩም ግሽ አባይ ተብላ የምትታወቅ አንዲት አነስተኛ ምንጭ የአባይ መነሻ እንደሆነች ይታመናል፡፡ የአባይ ወንዝ “ጥቁር አባይ” ወይም “ብሉ ናይል” እየተባለ ቆይቶ የኢትዮጵያን ግዛት ተሻግሮ ወደ ሱዳን በመግባት ካርቱም ከተማ ላይ ነጭ አባይ ከሚባለው አጋሩ ጋር እንደተቀላቀለ ናይል በሚል መጠሪያ ወደ ሜዲትራንያን ባህር ይገባል፡፡ እንግዲህ አባይ በትውልድ ሀገሩ በኢትዮጵያ 800 ኪ.ሜ. ያህል ሲጓዝ ከ17ኛው ክፍለ ዘመን እስከ ቅርብ 2016 ዓ.ም. ድረስ አባይን ለመሻገር 9 ያህል ድልድዮች በተለያዩ ቦታዎች እንደተገነቡለት ታሪክ ይናገራል፡፡ ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ የቀድሞ ገጽታ ግንቦት 7 ቀን 1951ዓ.ም. ግንባታው ተጠናቀቀ፡፡ የግንባታ ስራውን እንዲሁም የቁጥጥር ስራውን ያከናወነው በወቅቱ ስያሜው የኢትዮጵያ ንጉሰ ነገስት መንግስት የአውራ ጎዳና ባለስልጣን በአሁኑ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ነው ፡፡ ድልድዩ 169 ሜትር ርዝማኔ አለው፡፡ የድልድዩ የጎን ስፋት 10 ሜትር ነው፡፡ ይህ በወቅቱ ረጅም የተባለው ድልድይ የተገነባው በኢትዮጵያውያን መሀንዲሶች አማካኝነት ነው፡፡ በዚህም ኢትዮጵያ በሀገሯ ልጆች ረጅም ድልድዮችን ዲዛይን ለማድረግና ለመገንባት ብቃት እንዳላቸው ያሳዩበት ነበር፡፡ ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ ለባህርዳር ከተማ ልዩ መለያና ውበትን በመስጠት ላለፉት 60 አመታት አገልግሏል፡፡ ሆኖም ከእድሜው መርዘም እና በመስመሩ እየጨመረ ከመጣው የትራፊክ ፍሰት አንጻር ተደጋጋሚ ጉዳቶች ሲያጋጥሙት ቆይቷል፡፡ በየጊዜው የሀገሪቷ ወጪና ገቢ ንግድ እያደገ በመምጣቱ ምክንያት ነባሩ የአባይ ድልድይ ላይም ክብደት ያላቸው የጭነት ተሸከርካሪዎች ፍሰት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ በመምጣቱ ድልድዩ ላይ ከፍተኛ ጫና ፈጥረውበታል፡፡ የኢትዮጵያ መንዶች አስተዳደር ነባሩ ድልድይ ሊያጋጥም የሚችለውን አደጋ ለመከላከል ተደጋጋሚ ጥገና ሲያካሂድለት ቆይቷል፡፡ ድልድዩ በቀን ውስጥ ከ24ሺ በላይ ቀላልና እና ከባድ የጭነት እና የህዝብ ማመላሻ ተሸከርካሪዎችን ያስተናግዳል፡፡ በድልድዩ አካል ላይ በገጠመው ጉዳት ሳቢያ መግቢያና መውጫው ላይ ከፍተኛ የትራፊክ መጨናነቅ ሲፈጥር ነበር፡፡ የድልድዩ የጎን ስፋት ጠባብ በመሆኑ ለእግረኛ እና ለብስክሌት ተጠቃሚዎች አመቺ አልነበረም፡፡ ድልድዩ ላይ ያለው የአስፋልት ንጣፍ ምቹ ባለመሆኑ በትራንስፖርት አገልግሎት አሰጣጥ ላይ መጉላላት ሲፈጥር ቆይቷል፡፡ አዲሱ የአባይ ወንዝ ድልድይ ገጽታ የውል ስምምነት፡- መጋቢት 18 ቀን 2011 ዓ.ም. የሥራ ተቋራጭ፡- አለማቀፉ የቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ካምፓኒ አማካሪ ድርጅት፡- ቦቴክ ቦስፈረስ የተባለ የቱርክ አማካሪ ድርጅት ከስታዲያ ኢንጅነሪንግ ስራዎች ድርጅት ከተባለ አገር በቀል ንኡስ አማካሪ ጋር በጋራ በመሆን ያከናውኑታል የግንባታ ወጪ፡- 1,437,000,000 (አንድ ቢሊዮን አራት መቶ ሰላሳ ሰባት ሺህ ብር) የግንባታውን ወጪ የሸፈነው፡- የኢትዮጵያ መንግስት የግንባታው አይነት፡- ዲዛይንና ግንባታ /ተቋራጭ ድርጅቱ ዲዛይንና ግንባታን በጋራ አካቶ የሚሰራበት የኮንትራት ውል አይነት ነው/፡፡ የድልድዩ አይነት፡- የተንጠልጣይና የሳጥን ቅርፅ ያላቸውን ረጃጅም ድልድዮችን ዲዛይን በማዋሀድ በአዲስ የዲዛይን ጥበብ የሚገነባው ኤክስትራዶስድ የተባለውን አይነት ድልድይ ነው፡፡ ርዝመት፡- 380 ሜትር የጎን ስፋት፡- 43 ሜ. የጎን ስፋት ያለው ሲሆን በግራና በቀኝ በአንድ ግዜ 6 ተሽከርካሪዎችን ማስተናገድ ይችላል፡፡ በተጨማሪም የብስክሌት ተጠቃሚዎች መስመር በሁለቱም አቅጣጫ እንዲሁም 5 ሜ. የእግረኛ መሄጃን ያካተተ ነው። የድልድዩ ግንባታ ስራ፡- ከድልድዩ ግንባታ ጎን ለጎን ተያያዥ የኮንክሪት ስትራክቸር ስራዎችና፣ የተሽከርካሪ መወጣጫ /ramp/ ፣ የትራፊክ ምልክቶች፣ የድልድይ ላይ መብራቶች ስራም ያካተተ ነው ፡፡ ይህ ድልድይ ኤክስትራ ዶዝድ የሚባል ስያሜ የተሰጠው ተንጠልጣይ ድልድዮች (ሰስፔንሽን) ከሚባሉት ድልድዮች የተለየና ይልቁን የመኪና ተሸካሚው ዴክ ከፊትና ከሁዋላ ከግራና ከቀኝ በ18 ኬብሎች በአጠቃላይ በ72 ኬብሎች (በገመዶች የተወጠረ) ሆኖ ጠቅላላ ክብደቱ በገመዶቹ አማካይነት ወደ ቋሚው ምሰሶ የሚተላለፍና ከምሰሶውም ወደ መሰረቱ የሚዘልቅ ነው፡፡ ይህ አይነቱ ድልድይ የረጃጅም ኬብል ስቴይድ (በገመድ የተወጠረ) ድልድዮችና የረጃጅም ቦክስ ገርደር አይነት ድልድዮች ውሁድ ሆኖ ስፋታቸው ከ 250 ሜትር እከ 500 ሜትር በሚደርሱ ወንዞች ላይ አመቺና ወጪ ቆጣቢ ሆነው እንዲሰሩ በመጀመሪያ በፈረንሳይ ሀገር የተፈለሰፈ በቀጣይ ግን በብዛት ጃፓን ሀገር ስራ ላይ የዋለ የድልድይ አይነት ነው፡፡ የተጠናቀቀው የድልድዩ የምህንድስና ሰነዶች እንደሚያመለክቱት የቋሚው ምሰሶ ከመሰረት በላይ (piers) 7 ሜትር ከፍታ እና ታወሩ 27 ሜትር ከፍታ ሲኖረው ከውሀና ከመሬት በታች እስከ 24 ሜትር ጥልቀት ባላቸው በርካታ ፓይሎች የተዋቀረ ነው፡፡ ለድልድይ ግንባታው ጥቅም ላይ የዋሉ ዋና ዋና ግብዓቶች የተለያዩ የጥንካሬ ደረጃ (Grade C-30, C-40, C-50, and C-55) ያላቸው አርማታ 54,138.68 ሜ.ኩ የተለያዩ ስፋት እና የጥራት ደረጃ ያላቸው የአርማታ ብረት 9,241.45 ቶን የተለያዩ ስፋት እና የጥራት ደረጃ ያላቸው የማንጠልጠያ እና መወጠሪያ 474.37 ቶን የድልድይ ግንባታ ሥራውን ከዚህ ቀደም በሀገራችን ከተሠሩት የተለየ የሚያደርገው የወንዙን አቅጣጫ የማስቀየስ ሳይከናወን በሀገራችን ብዙም ያልተለመደ እና አዲስ ቴክኖሎጅ (ማለትም ተንሸራታች የሆነ ብረት የድልድይ አቃፊ) ግብዓት በመጠቀም መሠራቱ ድልድዩ በከተማ ውስጥ እንደመሠራቱ የትራፊክ ፍሰቱን ከማሳለጥ ባሻገር የቱሪሰት መስህብ እንዲሆን ታሳቢ ተደርጎ የአካባቢውን ማህበራዊ፣ ተፈጥሮአዊ እሴቶችን በማገናዘብ ቅንጡ ተደርጎ መሠራቱ በድልድዩ መወጠሪያ ገመዶች ላይ የተለየ መስተጋብር መስጠት የሚችሉ መብራት የተገጠመ መሆኑ ይገኙበታል፡፡ የኘሮጀክቱ ሁለንተናዊ ፋይዳ በአሁኑ ወቅት ከአቅሙ በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘውን ነባሩ የአባይ ወንዝ ድልድይ ላይ ይደርስ የነበረውን የትራፊክ መጨናነቅ እና ጫና ያስቀራል፡፡ ለሀገሪቱ የገቢ ወጪ የንግድ እንቅስቃሴም የበኩሉን አስተዋጽዖ ያበረክታል። ድልድዩን ለሚያቋርጡ እግረኞች የትራፊክ አደጋ ሳያሰጋቸው በተዘጋጀላቸው 5 ሜትር ስፋት ባለው መሄጃ ላይ በመጠቀም ከስጋት ነጻ ያደርጋቸዋል፡፡ ብስክሌት ለሚጠቀሙ የአካባቢው ነዋሪዎችም ሆኑ ቱሪስቶች ምቹ ሁኔታ ይፈጥራል። በተጨማሪም በባህርዳር ያለውን የትራፊክ መጨናነቅ ለመቅረፍ የበኩሉን ሚና ይጫወታል፡፡

የባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ጠ/ሚ ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድ በተገኙበት በይፋ ተመረቀ በአማራ ክልል በባሕር ዳር ከተማ የተገነባው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ጠ/ሚ ክቡር ዶ/ር ዐቢይ አሕመድን ጨምሮ ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል ባለሥልጣናት በተገኙበት በዛሬው ዕለት በይፋ ተመርቋል ። በሀገሪቱ ታሪክ በዓይነቱ ልዩ የኾነው ይኽ ድልድይ 380 ሜትር ርዝማኔ እና 43 ሜትር የጎን ስፋት አለው። በአንድ ጊዜ 6 ተሽከርካሪዎችን በግራ እና በቀኝ የማስተናገድ አቅም ያለው ከመኾኑም ባለፈ የብስክሌተኞች መተላለፊያን ጨምሮ 5 ሜትር የእግረኛ መንገድ አካትቷል። እያንዳንዱ የድልድዩ ገመድ አቃፊ ማማዎች ቁመት 27 ሜትር ከፍታ ሲኖረው፣ ከውኃ እና ከመሬት በታች እስከ 24 ሜትር ጥልቀት ባላቸው በርካታ ፓይሎች የተዋቀረ ነው፡፡ 169 ሜትር ርዝመት ያለው ነባሩ የዓባይ ወንዝ ድልድይ ከስልሳ ዓመታት በላይ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኝ ሲኾን፣ ጠባብ እና ለከፍተኛ የትራፊክ እንቅስቃሴ ምቹ ባለመኾኑ ነበር አዲስ ድልድይ እንዲገነባ በመንግስት የተወሰነው። አሁን ላይ ግንባታው የተጠናቀቀው አዲሱ የዓባይ ወንዝ ድልድይ የባሕር ዳር ከተማን በመሐል አቋርጦ የሚያልፍ ሲኾን፣ በተንጠልጣይ ገመዶቹ እና ምሶሶዎቹ ላይ ዘመናዊ መብራት የተገጠመለት በመኾኑ ለአካባቢው ልዩ ድምቅት ከመስጠቱም ባለፈ የከተማዋን ሁለንተናዊ ዕድገት የሚያሳልጥ ነው። ግንባታውን ከፌደራል መንግስት በተመደበ 1 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር በጀት ዓለም አቀፉ ቻይና ኮሙኒኬሽን ኮንስትራክሽን ኩባንያ (cccc) አከናውኖታል፡፡ የቱርኩ ቦቴክ እና ሀገር በቀሉ ስታዲያ ኢንጅነሪንግ የግንባታውን የቁጥጥር እና የማማከር ሥራ በጥምረት ሠርተዋል። የድልድዩ መገንባት ለክልሉ ብሎም ለሀገሪቱ ተጠቃሽ የቱሪስት መስህብ በመሆን አዎንታዊ ሚና ይጫወታል። ከካይሮ እስከ ኬፕታውን የሚደርሰው የትራንስ አፍሪካ አውራጎዳና ላይ ያረፈ በመኾኑም ሀገሪቱ የዚህ ሀይዌይ መስፈርትን የሚያሟሉ ከፍተኛ ክብደት ያላቸውን ተሽከርካሪዎች የሚሸከሙ አስተማማኝ ድልድዮች እንዳሏት ማሳያ ነው። ለድልድዩ መዳረሻ በሁለት አቅጣጫ ከሄኒ ጋርደን አደባባይ እስከ ዘንዘልማ መገንጠያ ድረስ የሚዘልቀው የ4 ነጥብ 7 ኪሎ ሜትር የባሕር ዳር ዓባይ ወንዝ ድልድይ መዳረሻ መንገድ ሀገር በቀሎቹ ሀፍኮን  ከክሮስላንድ ኮንስትራክሽን ድርጅት ጋር በመጣመር ግንባታውን ያከናውናሉ፡፡ የመንገድ ግንባታው ቀሪ ውስን ሥራ በቅርቡ ይጠናቀቃል። ይኽ የመሠረተ-ልማት አውታር በከፍተኛ የሀገር መዋለ-ንዋይ የተገነባ እንደመኾኑ ሁሉም ዜጋ ሊንከባከበው እና በባለቤትነት ስሜት ሊጠብቅው እንደሚገባ የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ያሳስባል። በተጨማሪ › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et › ዩቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads