ch
Feedback
ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር

前往频道在 Telegram

Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

显示更多

📈 Telegram 频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር 的分析概览

频道 ERA ኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር (@ethioroads) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 313 名订阅者,在 交通 类别中位列第 1 759,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 546

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 313 名订阅者。

根据 15 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 88,过去 24 小时变化为 2,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 40.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.41% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 5 352 次浏览,首日通常累积 2 050 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 17

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Official ERA Telegram Channal በዚህ የቴሌግራም ቻናል የመንገድ ዜናዎችን የስራና የመንገድ ጨረታ ማስታወቂያዎችን የመንገድ ፎቶዎች እና አጫጭር ቪዲዮችን ያገኛሉ።

凭借高频更新(最新数据采集于 16 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 交通 类别中的关键影响点。

13 313
订阅者
+224 小时
+297
+8830
帖子存档
የገደብ ወንዝ ድልድይ ከነ ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል ነሐሴ 3 ቀን 2017 ዓ.ም ሌሊት ጮቄ ተራራ ላይ የጣለው ከባድ ዝናብ ባስከተለው ጎርፍ በደረሰበት ጉዳት ምክንያት በተገጣጣሚ ብረት የመገንባቱ ሥራ ሲከናወንለት የቆየው የገደብ ወንዝ ድልድይ በዛሬው ዕለት ሥራው ሙሉ በሙሉ በመጠናቀቁ ከነገ ነገ ነሐሴ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል፡፡ በጎርፍ ምክንያት ድልድዩ ጉዳት ከደረሰበት ጊዜ ጀምሮ ግንባታው እስኪጠናቀቅ በትዕግስት ሲጠባበቁ ለቆዩ መንገደኞችና አሽከርካሪዎች የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ምስጋና እያቀረበ ድልድዩ ሁለት መኪና በአንዴ ማስተላለፍ ስለማይችል በመጠባበቅ እንዲተላለፉ፣ ድልድዩ የሚገኝበት ቦታ ኩርባ ላይ ስለሆነ ፍጥነት በመቀነስ እና ቅድሚያ በመስጠት በትዕግስት እንዲተላልፉ ያሳስባል፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

ከደብረማርቆስ (ከደብረማርቆስ 17 ኪሜ ላይ) - ባህርዳር በሚወስደው መንገድ ላይ የገደብ ወንዝ ድልድይ መጎዳቱንና በአጭር ጊዜ የጥገና ሥራ ተሰርቶ አገልግሎቱን እንዲቀጥል እንደሚደረግ መግለጻችን ይ
+6
ከደብረማርቆስ (ከደብረማርቆስ 17 ኪሜ ላይ) - ባህርዳር በሚወስደው መንገድ ላይ የገደብ ወንዝ ድልድይ መጎዳቱንና በአጭር ጊዜ የጥገና ሥራ ተሰርቶ አገልግሎቱን እንዲቀጥል እንደሚደረግ መግለጻችን ይታወቃል፡፡ በዚህም መሰረት የተገጣጣሚ ብረት በአሁኑ ሰዓት በመጠናቀቅ ላይ ሲሆን ቀሪ ሥራዎች እንደተጠናቀቁ ለአገልግሎት ክፍት ይሆናል፡፡ በመሆኑም ድልድዩ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት መሆኑ እስኪገለጽ የመንገዱ ተጠቃሚዎች በተለመደው ትዕግስት እንዲጠብቁ እየጠየቅን ለአገልግሎት ዝግጁ ሲሆን ወዲያዉኑ ለሕዝብ ግልጽ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ማሳሰቢያ 1) በተለያዩ ማህበራዊ ሚዲያዎች በአሁኑ ሰዓት ድልድዩ ተጠናቅቆ ለአገልግሎት ክፍት እንደሆነ እየተገለጸ ያለው መረጃ መስተካከል ያለበት መሆኑን የመንገዱ ተጠቃሚዎች አውቀው በትዕግስት እንዲጠብቁ፡፡ 2) መንገዱ ለአገልግሎት ክፍት ሲሆንም አላስፈላጊ እሽቅድድም እና ድልድዩ መሸከም ከሚችለው(እስከ 40 ቶን መሸከም ይችላል) በላይ ክብደት በማስወስቀገድ በጉዳት የመከላከል ኃላፊነታችን በጋራ እንዲንወጣ፣ 3) ድልድዩ ሁለት መኪና በአንዴ ማስተላለፍ ስለማይችል በመጠባበቅ እንዲተላለፉ፣ ድልድዩ የሚገኝበት ቦታ ከርባ ላይ ስለሆነ ፍጥነት በመቀነስ እና ቅድሚያ በመስጠት በትዕግስት እንዲተላልፉ፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የወልዲያ - ፍላቂት መንገድ የመልሶ ግንባታ ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 14 ቀን 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የወልዲያ-ፍላቂት ከባድ ጥገና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል በተከሰተ የጸጥታ ምክንያት የተስተጓጎለ ቢሆንም የመልሶ ግንባታ ለማስጀመር ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛል፡፡ የኮምቦልቻ መንገድ አውታር ማኔጅመንት ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የመንገድ ጥገና እና የድልድይ መልሶ ግንባታና ጥገና ስራዎችን በማከናዎን ላይ እንደሚገኝ ይታወቃል:: ከእነዚህም ሥራዎች መካከል የወልዲያ-ፍላቂት ከባድ ጥገና ፕሮጀክት አንዱ ሲሆን፤ ፕሮጀክቱ በህዳር ወር 2011 ዓ.ም በህብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን  የከባድ ጥገና ስራ ተጀምሮለት እንደነበር ይታወቃል፡፡ የአስፋልት ንጣፍ ስራው 20 ኪ.ሜ በ10 ሳ.ሜ ውፍረት እንዲሁም የድልድይ ጥገና ስራዎችን ተከናውነዋል። ሆኖም በሰሜኑ የሃገራችን ክፍል ባጋጠመው የጸጥታ ችግር ምክንያት የስራ ተቋራጩ ለስራ ያስገባቸውን ማሽኖችና ፕላንቶች በመውደማቸው እና ከጦርነቱ ጋር ተያይዞ መንገዱ ተጨማሪ ከፍተኛ ጉዳት በማስተናገዱ የመልሶ ግንባታ ዲዛይን እንደ አዲስ እንዲሰራለት እቅድ ተይዞ የዲዛይን አማካሪ ቅጥር በሂደት ላይ ይገኛል:: የዋናው መልሶ ግንባታ ስራ እስከሚጀመር ድረስም የትራፊክ እንቅስቃሴውን ለማሳለጥ በ2017 በጀት ዓመት የጥቁር ውሀ ድልድይን ጨምሮ ጥገና በማድረግ እና የተጎዱ የመንገድ ክፍሎችን በrockfill እና select fill ጥገና ዓይነቶች  በማድረግ መንገዱ አገልግሎት እየሰጠ ይገኛል፡፡ የጊምቦራ ድልድይም ያጋጠመውን የመሸርሸር አደጋ የመከላከል ስራ ተሰርቷል። ሆኖም ስራውን በመስራት ሂደት ካጋጠሙ ተግዳሮዮች መካከል ረዥም ርቀት ላይ የሚገኙ ግብዓቶችን ለመጠቀም በሚደረገው ሂደት ከጸጥታ ጋር ተያይዞ ችግሮች የሚያጋጥሙ መሆናቸው፣ የወሰን ማስከበር ስራ ጋር ታያይዞ የሚፈጠሩ ችግሮች፣ እና ዝናቡ ከወትሮ በተለየ መልኩ ቀድሞ በሰኔ ወር መጀመሩ ተጠቃሽ ናቸው፡፡ በ2018 በጀት አመት አስፈላጊው በጀት በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ተመድቦ የተጎዱ መንገዶችን በፍጥነት በመጠገን የትራፊክ ሂደቱን ለማሳለጥ ቅድመ ዝግጅት ሥራዎች በመከናወን ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የሚኤሶ - ድሬዳዋ ፍጥነት መንገድ ግንባታ ስራ በይፋ ተጀመረ ድሬዳዋ፣ ነሐሴ 13፣ 2017 (ኢ መ አ):- የኢትዮ - ጅቡቲ የመንገድ ኮሪደር አካል የሆነው የሚኤሶ - ድሬዳዋ ፍጥነት መንገድ ግንባታ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር  ክቡር ተመስገን ጥሩነህ እና ሌሎች ከፍተኛ የፌደራል እና የክልል የመንግስት የሥራ ኃላፊዎች በተገኙበት በይፋ ተጀምሯል፡፡ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክቱ በሁለት ምዕራፎች ተከፋፍሎ የሚገነባ ሲሆን ፣ በአጠቃላይ 144 ነጥብ 5 ኪሎሜትር ይሸፍናል፡፡ በምዕራፍ አንድ ከሚኤሶ - ቢኬ  73 ኪሎሜትር እንዲሁም በምዕራፍ ሁለት ከቢኬ - ደሬዳዋ 71 ነጥብ 4 ኪሎሜትር ርዝመትን ይሸፍናሉ፡፡ ግንባታውን ቻይና ሲቪል ኢንጂነሪንግ ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (CCECC) እና ሲቹዋን መንገድ እና ድልድይ ኮርፖሬሽን ኩባንያ በጥምረት የሚያከናውኑ ሲሆን  ግንባታውን ለማካሄድ አገልግሎት ላይ የሚውለው 62 ነጥብ 6 ቢሊዮን ብር ወጪ ደግሞ  በዓለም ባንክ ይሸፈናል፡፡  የፍጥነት መንገዱ 33 ነጥብ 9 ሜትር የጎን ስፋት እንዲኖረው ተደርጎ የሚገነባ ሲሆን ፣132 መሸጋገሪያ እና መሿለኪያዎችን አካቶ በአንድ ጊዜ በሁለት አቅጣጫ 4 መኪኖችን በሚያስተናግድ መልኩ ይገነባል ። የማሳለጫ ስራዎች በኦሮሚያ ፣ በሶማሌ እና በ6 ከተሞች ማለትም ሚኤሶ ፣ አፍደም ፣ ቢኬ ፣ ኤረር ፣ በመልካጀብዱ እና ድሬዳዋ ከተሞች  ይከናወናሉ ። በተጨማሪም መንገዱ በአስፋልት ደረጃ የሚገነባ ሆኖ በ30 ሳ.ሜ የአስፋልት ውፍረት የሚሰራ ይሆናል፡፡ በማስጀመሪያው መርሃ-ግብሩ ላይ የ ኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስቴር  ክቡር ተመስገን ጥሩነህ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር መንገዱ ኢትዮጵያ ከ90 በመቶ በላይ የወጪ እና የገቢ ንግዷን የምታከናውንበት ዋና ኮሪደር  በመሆኑ ይኸው የፍጥነት መንገድ መገንባቱ በተለይ የንግድ ትራንስፖርት  ፍሰቱን በማቀላጠፍ ረገድ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንደሚኖረው ገልፀዋል፡፡ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም የማይገነባ መንገድ አለመጀመር ፣ ጀምሮ አለማጠናቀቅ እንዲሁም በተገቢው የጥራት  ደረጃ እና ፍጥነት ያለመስራት የማይቻል መሆኑን በመገንዘብ ስራውን በተገቢው መልኩ ማካሄድ እንደሚገባ አሳስበዋል። የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ጫልቱ ሳኒ በበኩላቸው የመንገዱ መጀመር ከፍተኛ ትርጉም እንዳለው በመግለፅ መንገዱ የኢትዮጵያ የኢኮኖሚ የጀርባ አጥንት ከሆኑ ፕሮጀክቶች አንዱ ስለመሆኑም ተናግረዋል ። ሚኒስትሯ አክለውም የመኢሶ - ድሬዳዋ የፍጥነት መንገድ  ፕሮጀክቱ በሚገኝበት አካባቢ የሚገኙ ማህበረሰቦችን ከከተሞች ጋር በማገናኘት አርሶና አርብቶ አደሮች ያለምንም ውጣ ውረድ ምርታቸውን  እንዲያጓጉዙ እና አስፈላጊ አገልግሎቶችን ለማግኘት እንዲችሉ እንደሚያደርግም ተናግረዋል። ይህ መንገድ የኦሮሚያ እና የሶማሌ ክልሎችን እና የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደርን የሚያቆራኝ ወሳኝ የልማት አንቀሳቃሽ መሆኑም ተጠቁሟል ። የኢትዮጵያ  መንገዶች  አስተዳደር  ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በበኩላቸው ፕሮጀክቱን  ለማስጀመር የሚያስችሉ  የቅድመ ዝግጅት ስራዎች ተጠናቀው ግንባታው በዛሬው ዕለት በይፋ መጀመሩን ገልፀዋል። ዋና ዳይሬክተሩ አክለውም መንገዱ በተቀመጠለት የጥራት ደረጃ እና የጊዜ ገደብ ተጠናቆ ተገቢውን አገልግሎት ይሰጥ ዘንድ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እና ትብብር ሊያገርጉ ይገባልም ብለዋል። የCCECC  ፕረዚዳንት  ሚስተር  ቼን ሲቻን  በበኩላቸው ድርጅታቸው የመንገድ ግንባታውን በተቀመጠለት የጊዜ ገደብና የጥራት  ደረጃ በማጠናቀቅ በኢትዮጵያና በቻይና መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር እንደሚሰራ አረጋግጠዋል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የፊቅ - ሰገግ መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 65 በመቶ ደረሰ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 10፣ 2017 (ኢ መ አ):- በሶማሌ ክልል 2 ዞኖችን እና 3 ወረዳዎችን የሚያስተሳስረው የፊቅ - ሰገግ ክፍል -1 መንገድ ግንባታ አፈጻጸም 65 በመቶ ደርሷል። የሰገግ - ገርቦ ክፍል - 2 መንገድ ግንባታም በጥሩ መነቃቃት ላይ ይገኛል። በክፍል - 1 ከፊቅ እስከ ሰገግ በመገንባት ላይ የሚገኘው የመንገድ ፕሮጀክት 90 ኪሎሜትር ይሸፍናል። አሁን ላይ የ23 ኪሎሜትር አስፋልት የማልበስ ሥራ ተሠርቷል። የ54 ኪ.ሜ የአፈር፣ የ51 ኪ.ሜ ሰብቤዝ፣ የ30 ኪ.ሜ ቤዝኮርስ ሥራዎች ተጠናቅቀዋል። በተጨማሪም የ8 ድልድዮች ግንባታ የፕሮጀክቱ አካል ሲኾን፥ 2ቱ ተጠናቅቀው 6ቱ በሒደት ላይ ናቸው። የፕሮጀክቱን መልካም አፈጻጸም አጠናክሮ ለማስቀጠል የሚያስችሉ በማሽነሪ፣ በግብአት እና የባለሞያ አቅርቦት ረገድ አስፈላጊው ዝግጅት እየተደረገ መኾኑን ቦታው ድረስ በተደረገ ቅኝት መመልከት ተችሏል። የመንገድ ግንባታውን ሀገር በቀሉ ድሪባ ደፈርሻ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ በማከናወን ላይ የሚገኝ ሲኾን፥ ቫሊዮ ኢንጅነሪን የማማከር እና የቁጥጥር ሥራውን በማከናወን ላይ ይገኛል። ለግንባታው የተመደበው 1 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር ወጪ በፊደራል መንግስት ወጪ ይሸፈናል። በተመሳሳይ በክፍል - 2 ከሰገግ - ገርቦ 103 ኪሎሜትር የሚሸፍን ሲኾን፥ ግንባታው በሀገር በቀሉ ማክሮ ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ እየተከናወነ ይገኛል። አሁን ላይ የውኃ መፋሰሻ ቱቦ፣ የአፈር ቆረጣ እና ሙሌት እንዲሁም የቤዝኮርስ ጠጠር ማምረት ሥራዎች በዋናነት በመከናወን ላይ ናቸው። በመንገድ ፕሮጀክቱ የገጠሙ የውኃ እጥረት፣ የመዳረሻ መንገዱ ምቹ ባለመኾኑ የግንባታ እቃዎች ወደ ፕሮጀክቱ ስፍራ እንደ ልብ ማንቀሳቀስ አለመቻሉ እንዲሁም የሥራ ተቋራጩ የአቅም ውስንነት ችግሮች ግንባታው ላይ መዘግየቶች እንዲስተዋሉ አድርጓል። ሆኖም ኢ መ አ ችግሮቹን ለመፍታት ከባለድርሻ አካላት ጋር ባደረገው የተቀናጀ ጥረት ፕሮጀክቱ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ አበረታች መሻሻሎችን አሳይቷል። በአጠቃላይ ፕሮጀክቶቹ ሲጠናቀቁ የኤረር እና ዮሆብ ዞኖችን እንዲሁም የፊቅ፣ ሰገግ እና ዮሆብ ወረዳዎችን ማኅበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ትስስር ያጠናክራል። ከሐረር - ጅግጅጋ - ጎዴ ይደረግ የነበረውን ረጅም የጉዞ ጊዜና የትራፊክ መጨናነቅ በመቀነስ በአካባቢው ለሚገኙ አርብቶ አደሮችና በቁም እንስሳት ንግድ ላይ ለተሰማሩ ግለሰቦችም የመንገዱ መገንባት ፋይዳው የጎላ ነው፡፡ በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et > ዮቲዮብ www.youtube.com/@ethioroads

የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ ፕሬዝዳንት ለኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች የሰጡት ሰልጠና https://youtu.be/NIsjS-5Om1I?si=JbXp2BoMxMOBts3d

የኮንስትራሽን ዘርፉን  ወደ ከፍታ የሚያሸጋግር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ ይፋ ሆነ አዲስ አበባ፣ ነሐሴ 5፣ 2017 ዓ.ም (ኢመአ)፡ የኮንስትራሽን ዘርፉን  ወደ ከፍታ ለማሸጋገር በፈረንጆቹ ከ2025 እስከ 2050 ድረስ የሚተገበር የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ትራንስፎርሜሽን ኢኒሼቲቭ ይፋ ተደርጓል ። ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር አቶ ተመስገን ጥሩነህ በዚህ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት ዘመናዊ፣ ተወዳዳሪ እና ዓለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ መፍጠር ያስልጋል። በኮንስትራክሽን ኢንደስትሪ ውስጥ ለመቆየት ተወዳዳሪነት እና ብቃት ወሳኝ በመሆኑ ፕሮጀክቶችን በተያዘላቸው ጊዜ እና ወጪ ማጠናቀቅ አንዱ መገለጫ ሊሆን ይገባል። አሰራሮችን ማዘመን ፣ቴክኖሎጂን መጠቀም፣ እና ዘመናዊ የፕሮጀክት ማኔጅመንት ስርዓትን መከተል ለኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ህልውና እና አስተማማኝ እድገት ለማምጣት ወሳኝ ናቸው። የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው ለሀገራችን እድገት ጉልህ አስተዋጸኦ ሲያበረክት የቆየ እና በቀጠይም ማሳካት ለሚፈለገው ግብ  የማይተካ ሚና ያለው  ከመሆኑም ባሻገር መንገዶች  ለማህበራዊ አገልግሎቶች ያላቸው ተደራሽነት በጣም ከፍተኛ ነው፡፡ ኢንዱስትሪው የሀገር ሥልጣኔ ማሳያ እንደመሆኑ ሥራዎችን በትብብር ማከናወን እንደሚገባ ተገልጿል። በተጨማሪም › አጭር መልዕክት 8561 › ፖስታ ሳጥን ቁጥር 1770 › ድህረገጽ www.era.gov.et › ፊስቡክ https://www.facebook.com/www.era.gov.et › ቴሌግራም https://t.me/ethioroads › ትዊተር https://twitter.com/EthiopiaRoadsAd › ኢሜል communication@era.gov.et

የጥንቃቄ መልዕክት!!
የጥንቃቄ መልዕክት!!