EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 560 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 357,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 160 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 560 名订阅者。
根据 25 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 32,过去 24 小时变化为 -5,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 26.03%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.88% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 052 次浏览,首日通常累积 2 472 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 26 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 560
订阅者
-524 小时
+167 天
+3230 天
帖子存档
15 560
በሪጅኑ የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው
.....//.....
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ሪጅን ለሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና ባለሞያዎች እና ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል።
በማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ቢሮ የሳፕ ትግበራ ኮሚቴ አባልና አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ወልዳይ ገ/ትንሳኤ እንደገለጹት ሥልጠናው በሪጅኑ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የሚደረገውን የጥገና ሂደት ሙሉ ለሙሉ በማዘመንና በማቀላጠፍ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል።
ሥልጠናው የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮችን ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ለመከታተልና አስተማማኝነታቸውን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል።
በሪጅኑ መደበኛ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎችን እንዲሁም ክትትልና የቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር እና በማቀላጠፍ የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እንደሚረዳ ተናግረዋል።
እንደ አቶ ወልዳይ ገለጻ የሞጁሉ መተግበር የጥገና መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን የተሻለ ውሳኔ አሰጣጥ እና ትንበያ እንዲኖር ያስችላል።
ሥልጠናው በጥገና አሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት፣ አስተዳደር እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ለሦስት ሳምንታት የሚሰጥ ይሆናል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ርዕሰ መስተዳድሩ አንዲትም የታወር ብረት እንዳትሰረቅ እንሰራለን አሉ
……...///………
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ የሚያልፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከሚሸከሙ የብረት ምሰሶዎች ላይ አንዲትም ብረት እንዳትሰረቅ ክልሉ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋገጡ፡፡
ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ጋር በስርቆት፣ በወሰን ማስከበር እና ከቢሮ ግንባታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡
የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሸን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለርዕሰ መስተዳድሩ እንዳብራሩት ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት በስርቆትና የተሰረቁ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት ከአንድ ቢሊየን ብር የሚበልጥ ጉዳት ደርሶበታል፡፡
ከዚህ ውስጥ 13 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመተው በሲዳማ ክልል የተፈፀመ ስርቆት በመሆኑ የክልሉ መንግስት እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር ድርጊቱን ለመከላከል ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡
በፓወር ሪፎርም ኢንቨስትመንት እና ሞደርናይዜሽን ፕሮግራም (PRIME) ከሚገነቡት ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል የበንሳ ዳዬ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያርፍበትን ቦታ በአዋጅ ቁጥር 1336/2016 መሰረት ተነሺዎችን የመለየት፣ ካሳ የመክፈልና መልሶ የማቋቋም ሥራዎች ከወዲሁ እንዲጀመሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ የልማት ተነሺዎች የፕሮጀክቱ ፋይናንስ አቅራቢ የዓለም ባንክ በሚያስቀምጠው የመልሶ ማቋቋም መስፈርት መሰረት ቀድሞ ከነበሩበት ህይወት በተሻለ መንገድ መልሶ ለማቋቋም ትኩረት ሊደረግ ይገባል፡፡
ለሪጅኑ ቢሮ መገንቢያ የሚሆን ቦታ ለማግኘት ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ ሲቀርብ የቆየው ጥያቄ እንዲፈፀምም አቅጣጫ እንዲሰጥበት አመልክተዋል፡፡
በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ የደቡብ አንድ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ በበኩላቸው ስርቆቱ በክልሉ በሰሜን ሲዳማ ዞን ብላቴ ዙሪያ ወረዳ ዲን አኖሌ እና ቦሩ ሸወላ ቀበሌዎች በተደጋጋሚ እንደሚፈፀም ተናግረዋል፡፡
በማዕከላዊ ዞን ከይርጋለም - ሻኪሶ በተዘረጋው መስመር ላይም ዳሌ ወረዳ ቤራ ጫሌ እና ዊጮ ቀበሌዎች፤ ከይርጋለም - ዲላ በተዘረጋው መስመር ላይ ደግሞ አዋዳ እና አለታ ጩት ቀበሌዎች እንዲሁም በደቡባዊ ዞን ሳፋ እና ሚሊኒየም ቀበሌዎች ስርቆቱ በስፋት እንደሚስተዋል አንስተዋል፡፡
የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸው ሥራዎች ህብረሰተባችንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆናቸው ከተቋሙ ጋር ተባብሮ መሥራት የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ማህበረሰቡን በማሳተፍ ለመከላከል በሚከናወነው ሥራ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚከታተሉትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች መመሪያ እንደሚሰጡ አስረድተዋል፡፡
በክልሉ የሚያልፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከሚሸከሙ የብረት ምሰሶዎች አንዲትም ብረት እንዳትሰረቅ እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡
ወደፊት ከሚገነባው የበንሳ ዳዬ ማከፋፈያ ጣቢያ ይዞታ ጋር በተያያዘ የሚያስፈልገውን የካሳ ክፍያ እና ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ የአዋጁን መንፈስ ተረድቶ ለመተግበር ውይይት ማድረግና መመካከር እንደሚፈልግ ጠቁመዋል፡፡
የቢሮ መገንቢያ ቦታን በተመለከተም የሐዋሳ ከተማን ደረጃ በሚመጥን መልኩ ጥያቄው ምላሽ የሚያገኝበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
+1
ማስታወቂያ
----///---
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ (ጡረተኛ) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡
በዚሁ መሰረት ጥቅምት 04 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ከተራቁጥር 1 እስከ 8 ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ በመሆኑ ጥቅምት 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ;
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ርብርቡ እንደቀጠለ ነው
………///……….
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን የቆቃ ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማ መልሶ የመትከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማ መልሶ ለመትከል የተጀመረው ሥራ በፈታኝ የአየር ሁኔታ ሳይገታ በርብርብ እየተከናወነ ነው።
ምሰሶውን መልሶ የማቆም ሥራው እንደተጠናቀቀ መስመሩን የማገናኘት ሥራ እንደሚከናወን እና በቀጣዮቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
በሪጅኑ ለኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ ሠራተኞች ጠየቁ
........///........
የደቡብ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች ለኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ ጠየቁ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች ከደቡብ አንድ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች ጋር በሐዋሳ ከተማ ውይይት አካሂዷል።
የሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ እየተፈፀመ ያለው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢነቱ ጨምሯል።
የስርቆት ወንጀሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ መልክና ይዘቱን እየቀየረ መምጣቱን የጠቀሱት የጥገና ሠራተኞቹ ይህም የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት እንዲያጋጥምና ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጦች እንዲከሰቱ ምክንያት ሆኗል ብለዋል።
በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻና ቁጥጥር ሥራዎችን ለማከናወን የካሳ ይገባኛል ጥያቄዎች ማነቆ እየሆኑባቸው መምጣታቸውን የገለፁት ባለሙያዎቹ ተቋሙ ከክልል፣ ዞንና ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ችግሩ መፍትሔ የሚያገኝበትን አሰራር እንዲዘረጋ ጠይቀዋል።
በሪጅኑ የሚገኙ አብዛኞቹ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ በመቆየታቸው ሳቢያ የመለዋወጫ ዕቃዎች፣ የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ እና የቻርጀርና ባትሪ እንዲሁም የዘይት መፈተሻ መሳሪያዎች አቅርቦት እጥረት እንዳለባቸው ነው የውይይቱ ተሳታፊዎች ያብራሩት።
በሪጅኑ ከትምህርትና ሥልጠና፣ ከተሽከርካሪ አቅርቦት እና ከሰው ኃይል አደረጃጀት እንዲሁም ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተቶች እንደሚስተዋሉም ጠቅሰዋል።
በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማስተላለፊያ መስመሮች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ እንደገለፁት እንደ ተቋም የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ነው።
ተቋሙ የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት የመለዋወጫ ዕቃዎችን ከሀገር በቀል አምራቾች ግዥ ለመፈፀም በሒደት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል።
1 ሺህ 700 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ግዥ መፈፀሙን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተገዙ የሥራ ላይ መሳሪያዎችም ለሁሉም ሪጅኖች መከፋፈላቸውን ተናግረዋል።
የሥራ ላይ ደህንነት መሳሪያዎች ለሁሉም የጥገና ባለሙያዎች መሟላት እንዳለባቸው የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ ሠራተኞች በጥገና ወቅት ከሥጋት ቀጠና ራሳቸውን ጠብቀው የሚሰሩበትን መንገድ ለማመቻቸት ትኩረት መደረግ እንዳለበት ገልፀዋል።
በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን በበኩላቸው የጥገና ሠራተኞች በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ ለመፍትሔው በጋራ መስራት አለባቸው።
የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ከዚህ ጋር ተያይዞ እያጋጠሙ የሚገኙ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ችግሮችን ለመቅረፍም የተለያዩ ግዥዎች እየተፈፀሙ እንደሚገኙም አብራርተዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ሪጅኑ የሚገጥሙትን ችግሮች ለመፍታት ይሰራል
….....//……...
በደቡብ አንድ ሪጅን ሥር በሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ።
በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከደቡብ አንድ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሐዋሳ ከተማ ውይይት አካሂዷል።
ውይይቱ በሪጅኑ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ ላይ ትኩረቱን አድርጓል።
በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት ውይይቱ ሪጅኑ በሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያግዛል።
ሪጅኖች የሚያስፈልጓቸውን ድጋፎች ለይቶ ለማቅረብ፣ የቁጥጥርና ግምገማ ሥራዎችን ለማከናወን፣ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ለመከታተልና ኦዲት ለማድረግ መምሪያው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ከሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በተካሄደው ውይይት ሪጅኑ ድጋፍ በሚፈልግባቸው ጉዳዮች ላይ ግብዓት በመሰብሰብ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳም ነው አቶ ጋሻው የጠቀሱት።
የደቡብ አንድ ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ በበኩላቸው ውይይቱ የሪጅኑን የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል።
በሪጅኑ 12 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ጠቅሰው አብዛኞቹ ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት እየሰጡ በመቆየታቸው የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል።
እንደ አቶ ምትኩ ገለፃ ሪጅኑ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ እንዲችል በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ማስቆም ይገባል።
የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻና ቁጥጥር ሥራዎችን ለማከናወን የካሳ ይገባኛል ጥያቄዎች ችግር እየፈጠሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
ከምዘና ሥርዓት፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከሠራተኞች አቅም ግንባታና ከኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም አሳስበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው
………///……….
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ከቆቃ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው ስርቆት በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል።
ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መልሶ ለማቆም የወደቀውን ምሰሶ የመፈታታት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ጎሳዬ ምሰሶውን መልሶ በማቆም በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የሪጅኑ 12 ባለሙያዎች በጥገና ሥራው ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከማዕከላዊ አንድ እና ሦስት ሪጅን እንዲሁም ከምስራቅ አንድ ሪጅን ተጨማሪ ባለሙያዎች ቡድኑን እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡
የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ የማድረግ ሥራው እንደሚቀጥል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ለጥገና ሥራው የቅርብ ድጋፍ እያደረገ ያለውን የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደር እና ከንቲባውን በሪጅኑ ስም አመስግነዋል፡፡
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለመሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እየተከበረ ነው
.........///........
የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ለ17ኛ ጊዜ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች እየተከበረ ይገኛል፡፡
ሰንደቅ ዓላማችን የኢትዮጵያዊነታችን ዓርማ እና የሉዓላዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የኅብረ ብሔራዊ አብሮነታችን ዋስትና በመሆኑ ተገቢው ክብርና ፍቅር ሊሰጠው ይገባል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው
………///……….
በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ።
በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ከቆቃ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው ስርቆት በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል።
ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መልሶ ለማቆም የወደቀውን ምሰሶ የመፈታታት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ጎሳዬ ምሰሶውን መልሶ በማቆም በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
በአሁኑ ወቅት የሪጅኑ 12 ባለሙያዎች በጥገና ሥራው ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከማዕከላዊ አንድ እና ሦስት ሪጅን እንዲሁም ከምስራቅ አንድ ሪጅን ተጨማሪ ባለሙያዎች ቡድኑን እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡
የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ የማድረግ ሥራው እንደሚቀጥል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
ለጥገና ሥራው የቅርብ ድጋፍ እያደረገ ያለውን የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደር እና ከንቲባውን በሪጅኑ ስም አመስግነዋል፡፡
በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለመሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም
15 560
የተቋረጠውን መስመር በመጠገን ኃይል ማቅረብ ተችሏል
..........///.......
በሶማሌ ክልል አዲጋላ ወረዳ ልዩ ስሙ ጨበን በተባለ ቦታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ኃይል መልሶ ማገናኘት መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን ቢሮ አስታወቀ።
የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት ከአዲጋላ ሰብስቴሽን ወደ ኢትዮ ምድር ባቡር በተዘረጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል።
ችግሩ ካጋጠመበት ከመስከረም 22 ቀን 2017 ዓ ም ጀምሮ ለባቡር ጣቢያው በጊዜያዊነት በሌላ አማራጭ መስመር ኃይል በመስጠት አገልግሎቱ እንዳይቋረጥ ተደርጓል።
የወደቀውን የብረት ምሶሶ በመጠገን ተቋርጦ የቆየውን ኃይል ዛሬ ማምሻውን መልሶ ማገናኘት መቻሉን ገልፀዋል።
የሪጂኑ የጥገና ባለሙያዎች ላለፉት ስምትን ቀናት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ተቋርጦ የነበረውን መስመር ኃይል እንዲያገኝ በማድረጋቸው ዳይሬክተሩ ምስጋ ቸው አቅርበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia
ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
