ar
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

الذهاب إلى القناة على Telegram

EEP Communication

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication

تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 560 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 357 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 160 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 560 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 26 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 27، وفي آخر 24 ساعة بمقدار -7، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 26.05‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.01‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 053 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 491 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 8.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
EEP Communication

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 27 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.

15 560
المشتركون
-724 ساعات
+147 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
photo content
+9

በሪጅኑ የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና እየተሰጠ ነው .....//..... በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሰሜን ሪጅን ለሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያ እና ማስተላለፊያ መስመሮች የጥገና ባለሞያዎች እና ኃላፊዎች የሳፕ ፕላንት ሜንቴናንስ ሞጁል የተጠቃሚዎች ስልጠና መሰጠት ተጀምሯል። በማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ኦፕሬሽን ቢሮ የሳፕ ትግበራ ኮሚቴ አባልና አሰልጣኝ የሆኑት አቶ ወልዳይ ገ/ትንሳኤ እንደገለጹት ሥልጠናው በሪጅኑ የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የሚደረገውን የጥገና ሂደት ሙሉ ለሙሉ በማዘመንና በማቀላጠፍ በኩል ጉልህ ሚና ይጫወታል። ሥልጠናው የማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮችን ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ለመከታተልና አስተማማኝነታቸውን ለማረጋገጥ እንደሚያስችል ገልጸዋል። በሪጅኑ መደበኛ የፍተሻ እና የጥገና ሥራዎችን እንዲሁም ክትትልና የቁጥጥር ሥርዓቱን በማጠናከር እና በማቀላጠፍ  የኃይል መቆራረጥን ለመቀነስ እንደሚረዳ ተናግረዋል። እንደ አቶ ወልዳይ ገለጻ የሞጁሉ መተግበር የጥገና መረጃዎችን በመሰብሰብና በመተንተን የተሻለ ውሳኔ አሰጣጥ እና ትንበያ እንዲኖር ያስችላል። ሥልጠናው በጥገና አሰራር ሥርዓት፣ በመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት፣ አስተዳደር እና ተያያዥ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ ለሦስት ሳምንታት የሚሰጥ ይሆናል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 6 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

ርዕሰ መስተዳድሩ አንዲትም የታወር ብረት እንዳትሰረቅ እንሰራለን አሉ ……...///……… የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በክልሉ የሚያልፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከሚሸከሙ የብረት ምሰሶዎች ላይ አንዲትም ብረት እንዳትሰረቅ ክልሉ በትኩረት እንደሚሰራ አረጋገጡ፡፡ ርዕሰ መስተዳድሩ ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሥራ ኃላፊዎች ጋር በስርቆት፣ በወሰን ማስከበር እና ከቢሮ ግንባታ ጋር በተያያዙ ጉዳዮች ላይ ውይይት አድርገዋል፡፡ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሸን መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለርዕሰ መስተዳድሩ እንዳብራሩት ተቋሙ በ2016 በጀት ዓመት በስርቆትና የተሰረቁ የኃይል መሰረተ ልማቶችን መልሶ ለመገንባት ከአንድ ቢሊየን ብር የሚበልጥ ጉዳት ደርሶበታል፡፡ ከዚህ ውስጥ 13 ነጥብ 5 ሚሊየን ብር የሚገመተው በሲዳማ ክልል የተፈፀመ ስርቆት በመሆኑ የክልሉ መንግስት እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር ድርጊቱን ለመከላከል ትኩረት እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡ በፓወር ሪፎርም ኢንቨስትመንት እና ሞደርናይዜሽን ፕሮግራም (PRIME) ከሚገነቡት ማከፋፈያ ጣቢያዎች መካከል የበንሳ ዳዬ ማከፋፈያ ጣቢያ የሚያርፍበትን ቦታ በአዋጅ ቁጥር 1336/2016 መሰረት ተነሺዎችን የመለየት፣ ካሳ የመክፈልና መልሶ የማቋቋም ሥራዎች ከወዲሁ እንዲጀመሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ የልማት ተነሺዎች የፕሮጀክቱ ፋይናንስ አቅራቢ የዓለም ባንክ በሚያስቀምጠው የመልሶ ማቋቋም መስፈርት መሰረት ቀድሞ ከነበሩበት ህይወት በተሻለ መንገድ መልሶ ለማቋቋም ትኩረት ሊደረግ ይገባል፡፡ ለሪጅኑ ቢሮ መገንቢያ የሚሆን ቦታ ለማግኘት ከ2012 ዓ.ም. ጀምሮ ሲቀርብ የቆየው ጥያቄ እንዲፈፀምም አቅጣጫ እንዲሰጥበት አመልክተዋል፡፡ በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ዘርፍ የደቡብ አንድ ሪጅን ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ በበኩላቸው ስርቆቱ በክልሉ በሰሜን ሲዳማ ዞን ብላቴ ዙሪያ ወረዳ ዲን አኖሌ እና ቦሩ ሸወላ ቀበሌዎች በተደጋጋሚ እንደሚፈፀም ተናግረዋል፡፡ በማዕከላዊ ዞን ከይርጋለም - ሻኪሶ በተዘረጋው መስመር ላይም ዳሌ ወረዳ ቤራ ጫሌ እና ዊጮ ቀበሌዎች፤ ከይርጋለም - ዲላ በተዘረጋው መስመር ላይ ደግሞ አዋዳ እና አለታ ጩት ቀበሌዎች እንዲሁም በደቡባዊ ዞን ሳፋ እና ሚሊኒየም ቀበሌዎች ስርቆቱ በስፋት እንደሚስተዋል አንስተዋል፡፡ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ደስታ ሌዳሞ በሰጡት ምላሽ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚያከናውናቸው ሥራዎች ህብረሰተባችንን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በመሆናቸው ከተቋሙ ጋር ተባብሮ መሥራት የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ማህበረሰቡን በማሳተፍ ለመከላከል በሚከናወነው ሥራ የቅድሚያ ትኩረት ሰጥተው እንደሚከታተሉትና በየደረጃው ለሚገኙ አመራሮች መመሪያ እንደሚሰጡ አስረድተዋል፡፡ በክልሉ የሚያልፉ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችን ከሚሸከሙ የብረት ምሰሶዎች አንዲትም ብረት እንዳትሰረቅ እስከ ቀበሌ ባለው መዋቅር በትኩረት እንደሚሰራም አረጋግጠዋል፡፡ ወደፊት ከሚገነባው የበንሳ ዳዬ ማከፋፈያ ጣቢያ ይዞታ ጋር በተያያዘ የሚያስፈልገውን የካሳ ክፍያ እና ተነሺዎችን መልሶ የማቋቋም ሥራ የአዋጁን መንፈስ ተረድቶ ለመተግበር ውይይት ማድረግና መመካከር እንደሚፈልግ ጠቁመዋል፡፡ የቢሮ መገንቢያ ቦታን በተመለከተም የሐዋሳ ከተማን ደረጃ በሚመጥን መልኩ ጥያቄው ምላሽ የሚያገኝበት ሁኔታ ይመቻቻል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

photo content

ማስታወቂያ ----///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ (ጡረተኛ) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚ
+1
ማስታወቂያ ----///--- የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሾፌር-1ኛ (ጡረተኛ) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር ነሐሴ 15 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣታችን ይታወቃል፡፡ በዚሁ መሰረት ጥቅምት 04 ቀን 2017 ዓ.ም የጽሁፍ ፈተና ተፈትናችሁ በመንገድ ትራንስፖርት በሚፈቅደው ህግ እና ደንብ መሰረት 74 እና ከዚያ በላይ ውጤት ያመጣችሁ ከተራቁጥር 1 እስከ 8 ለተግባር ፈተና ያለፋችሁ በመሆኑ ጥቅምት 08 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት መንጃ ፈቃድ በመያዝ ኮተቤ ብረታብረት ፊትለፊት በሚገኘው በዋናው መ/ቤት ተሽከርካሪ ጥገና አስተዳደር ቢሮ የተግባር ፈተና የሚሰጥ በመሆኑ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ      ፌስቡክ↠  https://www.facebook.com/Ethioelectric    ; ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication     ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia     ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com:/@ethiopowermedia      ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power   ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ  www.eep.com.et     ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

ርብርቡ እንደቀጠለ ነው ………///………. በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን የቆቃ ሁርሶ ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማ መልሶ የመትከል ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ማማ መልሶ ለመትከል የተጀመረው ሥራ በፈታኝ የአየር ሁኔታ ሳይገታ በርብርብ እየተከናወነ ነው። ምሰሶውን መልሶ የማቆም ሥራው እንደተጠናቀቀ መስመሩን የማገናኘት ሥራ እንደሚከናወን እና በቀጣዮቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+2

በሪጅኑ ለኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ ሠራተኞች ጠየቁ ........///........ የደቡብ አንድ ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች ለኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ማነቆ የሆኑ ችግሮች እንዲፈቱ ጠየቁ። በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ  የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች  ከደቡብ አንድ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች ጋር በሐዋሳ ከተማ ውይይት አካሂዷል። የሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሥራ ኃላፊዎችና የጥገና ሠራተኞች በውይይቱ ወቅት እንደገለፁት በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶዎች ላይ እየተፈፀመ ያለው የስርቆት ወንጀል አሳሳቢነቱ ጨምሯል። የስርቆት ወንጀሉ ከጊዜ ወደ ጊዜ መልክና ይዘቱን እየቀየረ መምጣቱን የጠቀሱት የጥገና ሠራተኞቹ ይህም የመለዋወጫ ዕቃዎች እጥረት እንዲያጋጥምና ተደጋጋሚ የኃይል መቋረጦች እንዲከሰቱ ምክንያት ሆኗል ብለዋል። በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻና ቁጥጥር ሥራዎችን ለማከናወን የካሳ ይገባኛል ጥያቄዎች ማነቆ እየሆኑባቸው መምጣታቸውን የገለፁት ባለሙያዎቹ ተቋሙ ከክልል፣ ዞንና ወረዳ አመራሮች እንዲሁም ከፀጥታ አካላት ጋር በቅንጅት በመስራት ችግሩ መፍትሔ  የሚያገኝበትን አሰራር እንዲዘረጋ ጠይቀዋል። በሪጅኑ የሚገኙ አብዛኞቹ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት ሲሰጡ በመቆየታቸው ሳቢያ የመለዋወጫ ዕቃዎች፣ የሥራ ላይ ደህንነት መጠበቂያ እና የቻርጀርና ባትሪ እንዲሁም የዘይት መፈተሻ መሳሪያዎች አቅርቦት እጥረት እንዳለባቸው ነው የውይይቱ ተሳታፊዎች ያብራሩት። በሪጅኑ ከትምህርትና ሥልጠና፣ ከተሽከርካሪ አቅርቦት እና ከሰው ኃይል አደረጃጀት እንዲሁም ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ ከማድረግ አንፃር ክፍተቶች እንደሚስተዋሉም ጠቅሰዋል። በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማስተላለፊያ መስመሮች ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ተስፋዬ መንግሥቱ እንደገለፁት እንደ ተቋም የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት እየተሰራ ነው። ተቋሙ  የኃይል ተሸካሚ ምሰሶ አካላት የመለዋወጫ ዕቃዎችን ከሀገር በቀል አምራቾች ግዥ ለመፈፀም በሒደት ላይ እንደሚገኝ ጠቅሰዋል። 1 ሺህ 700 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያለው የኮንዳክተር ሽቦ ገመድ ግዥ መፈፀሙን የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በ1 ነጥብ 4 ሚሊዮን ዶላር ወጪ የተገዙ የሥራ ላይ መሳሪያዎችም ለሁሉም ሪጅኖች መከፋፈላቸውን ተናግረዋል። የሥራ ላይ ደህንነት መሳሪያዎች ለሁሉም የጥገና ባለሙያዎች መሟላት እንዳለባቸው የጠቆሙት አቶ ተስፋዬ  ሠራተኞች በጥገና ወቅት ከሥጋት ቀጠና ራሳቸውን ጠብቀው የሚሰሩበትን መንገድ ለማመቻቸት ትኩረት መደረግ እንዳለበት ገልፀዋል። በሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ የማከፋፈያ ጣቢያዎች  ማስተባበሪያ አንድ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፀጋዬ ጌታሁን በበኩላቸው የጥገና ሠራተኞች በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች የሚስተዋሉ ችግሮችን ለይቶ ለመፍትሔው በጋራ መስራት አለባቸው። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎች መጀመራቸውን ያነሱት ሥራ አስኪያጁ ከዚህ ጋር ተያይዞ   እያጋጠሙ የሚገኙ የመለዋወጫ ዕቃዎች አቅርቦት ችግሮችን ለመቅረፍም የተለያዩ ግዥዎች እየተፈፀሙ እንደሚገኙም አብራርተዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 5 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

photo content
+9

ሪጅኑ የሚገጥሙትን ችግሮች ለመፍታት ይሰራል ….....//……... በደቡብ አንድ ሪጅን ሥር በሚገኙ የኃይል ማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ የሚያጋጥሙ ችግሮችን ለመቅረፍ እንደሚሰራ በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ከደቡብ አንድ ሪጅን የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በሐዋሳ ከተማ ውይይት አካሂዷል። ውይይቱ በሪጅኑ እየተከናወኑ ስለሚገኙ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች እንዲሁም በሚያጋጥሙ ችግሮችና መፍትሔዎቻቸው ዙሪያ ላይ ትኩረቱን አድርጓል። በዘርፉ የሪጅኖች ማስተባበሪያ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ጋሻው እንድሪያስ እንደገለፁት ውይይቱ ሪጅኑ በሚያከናውናቸው የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ላይ እያጋጠሙ የሚገኙ ችግሮችን በመለየት የመፍትሔ አቅጣጫዎችን ለማስቀመጥ ያግዛል። ሪጅኖች የሚያስፈልጓቸውን ድጋፎች ለይቶ ለማቅረብ፣ የቁጥጥርና ግምገማ ሥራዎችን ለማከናወን፣ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎችን ለመከታተልና ኦዲት ለማድረግ መምሪያው ትኩረት ሰጥቶ እየሰራ እንደሚገኝ ተናግረዋል። ከሪጅኑ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በተካሄደው ውይይት ሪጅኑ ድጋፍ በሚፈልግባቸው ጉዳዮች ላይ ግብዓት በመሰብሰብ አፋጣኝ ምላሽ ለመስጠት እንደሚረዳም ነው አቶ ጋሻው የጠቀሱት። የደቡብ አንድ ሪጅን ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ምትኩ ንጉሴ በበኩላቸው ውይይቱ የሪጅኑን የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች ለማሻሻል ያግዛል ብለዋል። በሪጅኑ 12 የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እንደሚገኙ ጠቅሰው አብዛኞቹ ለበርካታ ዓመታት አገልግሎት እየሰጡ በመቆየታቸው የአቅም ማሳደግና ማሻሻያ ሥራዎች እንደሚያስፈልጋቸው ገልፀዋል። እንደ አቶ ምትኩ ገለፃ ሪጅኑ አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ማቅረብ እንዲችል በኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ብረቶች ላይ በተደጋጋሚ እየተፈፀመ ያለውን ስርቆት ማስቆም ይገባል። የውይይቱ ተሳታፊዎች በበኩላቸው በኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የፍተሻና ቁጥጥር ሥራዎችን ለማከናወን የካሳ ይገባኛል ጥያቄዎች ችግር እየፈጠሩ እንደሚገኙ ጠቁመዋል። ከምዘና ሥርዓት፣ ከዕድገትና ዝውውር፣ ከሠራተኞች አቅም ግንባታና ከኃይል ተሸካሚ ምሰሶ ስርቆት ጋር በተያያዘ የሚስተዋሉ ችግሮችን መፍታት እንደሚገባም አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+7

ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው ………///………. በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ከቆቃ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው ስርቆት በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል። ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መልሶ ለማቆም የወደቀውን ምሰሶ የመፈታታት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ጎሳዬ ምሰሶውን መልሶ በማቆም በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሪጅኑ 12 ባለሙያዎች በጥገና ሥራው ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከማዕከላዊ አንድ እና ሦስት ሪጅን እንዲሁም ከምስራቅ አንድ ሪጅን ተጨማሪ ባለሙያዎች ቡድኑን እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ የማድረግ ሥራው እንደሚቀጥል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ለጥገና ሥራው የቅርብ ድጋፍ እያደረገ ያለውን የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደር እና ከንቲባውን በሪጅኑ ስም አመስግነዋል፡፡ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለመሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም

17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እየተከበረ ነው .........///........ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃ
17ኛው ብሔራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን እየተከበረ ነው .........///........ የሰንደቅ ዓላማ ቀን “ሰንደቅ ዓላማችን ለብሔራዊ አንድነታችን፣ ለሉዓላዊነታችንና ለኢትዮጵያ ከፍታ” በሚል መሪ ቃል ለ17ኛ ጊዜ በሁሉም የሀገራችን ክፍሎች እየተከበረ ይገኛል፡፡ ሰንደቅ ዓላማችን የኢትዮጵያዊነታችን ዓርማ እና የሉዓላዊነታችን መገለጫ እንዲሁም የኅብረ ብሔራዊ አብሮነታችን ዋስትና በመሆኑ ተገቢው ክብርና ፍቅር ሊሰጠው ይገባል፡፡  💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 4 ቀን 2017 ዓ.ም

ከቆቃ- ሁርሶ በተዘረጋው መስመር ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠገን ርብርብ እየተደረገ ነው ………///………. በአፋር ክልል አዋሽ ፈንታሌ ወረዳ የወደቀውን ባለ 230 ኪሎ ቮልት ጥምር የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመጠገን ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሁለት ሪጅን የኃይል ማስተላለፊያዎችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽንና ጥገና መምሪያ አስታወቀ። በመምሪያው የማስተላለፊያ መስመር ጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎሣዬ ደምሴ እንደገለፁት ከቆቃ ሁርሶ በተዘረጋው የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ የተፈፀመው ስርቆት በምስራቅ የሀገሪቱ ክፍል ለሚገኙ አንዳንድ ከተሞች የኃይል መቋረጥ ምክንያት ሆኗል። ጉዳት የደረሰበትን የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ መልሶ ለማቆም የወደቀውን ምሰሶ የመፈታታት ሥራ መጀመሩን የተናገሩት አቶ ጎሳዬ ምሰሶውን መልሶ በማቆም በቀጣይ ሳምንት የመጀመሪያዎቹ ቀናት አካባቢዎቹ ኃይል እንዲያገኙ ርብርብ እየተደረገ መሆኑን ገልፀዋል፡፡ በአሁኑ ወቅት የሪጅኑ 12 ባለሙያዎች በጥገና ሥራው ላይ እየተሳተፉ ቢሆንም ሥራውን በፍጥነት ለማጠናቀቅ ከማዕከላዊ አንድ እና ሦስት ሪጅን እንዲሁም ከምስራቅ አንድ ሪጅን ተጨማሪ ባለሙያዎች ቡድኑን እንዲቀላቀሉ እንደሚደረግ አስታውቀዋል፡፡ የጥገና ሥራው ሙሉ በሙሉ እስከሚጠናቀቅ ድረስም ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩ ከተሞችና አካባቢዎች በፈረቃ ኤሌክትሪክ የማድረግ ሥራው እንደሚቀጥል ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡ ለጥገና ሥራው የቅርብ ድጋፍ እያደረገ ያለውን የአዋሽ 7 ኪሎ ከተማ አስተዳደር እና ከንቲባውን በሪጅኑ ስም አመስግነዋል፡፡ በአዋሽ ፈንታሌ ወረዳ በኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ እየተፈፀሙ የሚገኙ የስርቆት ወንጀሎች እየተበራከቱ በመምጣታቸው የአካባቢው ማህበረሰብ፣ የመስተዳድር እና የፀጥታ አካላት ለመሰረተ ልማቶቹ ተገቢውን ጥበቃና ትኩረት እንዲሰጡ ጥሪ አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

የተቋረጠውን መስመር በመጠገን ኃይል ማቅረብ ተችሏል ..........///....... በሶማሌ ክልል አዲጋላ ወረዳ ልዩ ስሙ ጨበን በተባለ ቦታ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ የብረት ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ተቋርጦ የነበረውን ኃይል መልሶ ማገናኘት መቻሉን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የምስራቅ አንድ ሪጅን ቢሮ አስታወቀ። የሪጂኑ ዳይሬክተር አቶ ወርዲ መሀመድ እንደገለፁት ከአዲጋላ ሰብስቴሽን ወደ ኢትዮ ምድር ባቡር በተዘረጋ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የኃይል ማስተላለፊ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ በመውደቁ ምክንያት ኃይል ተቋርጦ ቆይቷል። ችግሩ ካጋጠመበት ከመስከረም 22 ቀን 2017 ዓ ም ጀምሮ ለባቡር ጣቢያው በጊዜያዊነት በሌላ አማራጭ መስመር ኃይል በመስጠት አገልግሎቱ እንዳይቋረጥ ተደርጓል። የወደቀውን የብረት ምሶሶ በመጠገን ተቋርጦ የቆየውን ኃይል ዛሬ ማምሻውን መልሶ ማገናኘት መቻሉን ገልፀዋል። የሪጂኑ የጥገና ባለሙያዎች ላለፉት ስምትን ቀናት ከፍተኛ ርብርብ በማድረግ ተቋርጦ የነበረውን መስመር ኃይል እንዲያገኝ በማድረጋቸው ዳይሬክተሩ ምስጋ ቸው አቅርበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia ቲክቶክ አካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et መስከረም 30 ቀን 2017 ዓ.ም