ch
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

前往频道在 Telegram

EEP Communication

显示更多

📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览

频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 533 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 338,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 162

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 533 名订阅者。

根据 29 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 6,过去 24 小时变化为 -1,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.10%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.85% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 901 次浏览,首日通常累积 2 619 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 8

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
EEP Communication

凭借高频更新(最新数据采集于 30 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。

15 533
订阅者
-124 小时
-167
+630
帖子存档
photo content
+1

በዞኑ የሚገኙ የኤሌትሪክ መሰረተ ልማቶችን በባለቤትነት እንደሚጠብቅ የዞኑ አስተዳደር አረጋገጠ ........///........ በደቡብ ክልል ጋሞ ዞኑ የሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶችን ከስርቆት ለመከላከል በቁርጠኝነት እንደሚሰራ የዞኑ አስተዳደር አስታወቀ። የዞኑ አስተዳዳሪ ልዩ አማካሪ አቶ በርገኔ በቀለ እንደገለጹት የጋሞ ዞን ጉልህ ሀገራዊ ፋይዳ ያላቸው የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች የሚያልፉበት፣ ለአካባቢው ማህበረሰብ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙ የማከፋፈያ ጣቢያዎችና ግንባታቸው የተጀመረ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች የሚገኙበት አካባቢ ነው። በመሆኑም በዞኑ በተለይም በአርባምንጭ ከተማና በዙሪያዋ በሚገኙ የኤሌክትሪክ መሰረተ ልማቶች ላይ ሲፈጸሙ የነበሩ የስርቆት ወንጀሎች በተቋሙ፣ በአስተዳደሩ እና በአካባቢው ማህበረሰብ የጋራ ርብርብ ማስቀረት መቻሉን አማካሪው አስታውሰዋል። የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች በሚያልፉበት ኮሪደር ተቋሙ ተገቢውን ካሳ ከፍሎ ወሰኑን ቢያስከብርም በአንዳንድ አካባቢዎች ላይ በህገ ወጥ መንገድ መልሰው ግለሰቦች መስፈራቸው አግባብ እንዳልሆነ አማካሪው አስረድተዋል። ከካሳ ክፍያና ከወሰን ማስከበር ጋር ተያይዘው የሚስተዋሉ ችግሮችን ባለድርሻ አካላት ያሳተፈ ውይይት በማካሄድና ግንዛቤ በመፍጠር ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት በትኩረት እንደሚሰራ ልዩ አማካሪው አረጋግጠዋል። የዞኑ ኢንቨስመንትና ኢንዱስትሪ መምሪያ ኃላፊ አቶ ሳሙኤል ግርማ በበኩላቸው ዞኑን ላይ ኢንቨስት ማደረግ የሚፈልጉ ባለሀብቶች ከሚጠይቋቸው ቅድመ ሁኔታዎች መካከል አስተማማኝ የኃይል አቅርቦት መኖሩን እንደሆነ አንስተዋል። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የሚገነባቸው አዳዲስና የማስፋፊያ ፕሮጀክቶች በአካባቢው ለታቀዱ የኢንዱስትሪ ፓርክና የፍራፍሬ ማቀነባበሪያ ፋብሪካዎች አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ እንደሚያስችሉ ኃላፊው ገልጸዋል። በአሁኑ ወቅት በዞኑ በግብርና፣ በአገልግሎትና በኢንዱስትሪ ዘርፍ የተሰማሩ ከ240 በላይ የኢንቨስትመንት ፕሮጀክቶች አስተማማኝ ኃይል እያገኙ መሆኑን የገለጹት ኃላፊው በእነዚህ መሰረተ ልማቶች ላይ የሚፈፀሙ የሥርቆት ወንጀሎችን ከተቋሙ ጋር በመሆን ለመከላከል መምሪያቸው ቁርጠኛ መሆኑን ተናግረዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 19 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+4

የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያው በተከናወነለት የማስፋፊያ ሥራ የህብረተሰቡን ጥያቄ በሚገባ መልሷል ........///......... የአርባምንጭ ባለ 132 ኪሎ ቮልት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በተለያዩ ጊዜያት በተደረጉለት የማስፋፊያና የአቅም ማሳደግ ሥራዎች በከተማዋና በአካባቢው ማህበረሰብ ሲነሱ የቆዩትን የኃይል እጥረትና መቆራረጥ ችግር በአግባቡ መፍታቱን የጣቢያው ኃላፊ አስታወቁ። ኃላፊው አቶ ጉዳዩ ምትኩ እንደገለጹት ጣቢያው በዲዝል ጀነሬተር አገልግሎት መስጠት ከጀመረበት ከ1972 ዓ.ም ጀምሮ የተለያዩ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች ተሰርተውለታል። ጣቢያው አገልግሎት መስጠት ሲጀምር 2 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት የማቅረብ አቅም የነበረው በመሆኑ የአርባምንጭ ከተማና የጋሞ ዞንን ዕድገት ተከትሎ እያደገ ለመጣው የኃይል ፍላጎት ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት የማይችልበት ሁኔታ ተፈጥሮ እንደነበር ኃላፊው አስታውሰዋል። እንደ ኃላፊው ገለጻ በጣቢያው ላይ የተከናወኑት የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች ኃይል የመጫን አቅሙን ወደ 49 ሜጋ ዋት ከፍ እንዲል አድርጎታል። በአሁኑ ወቅት ጣቢያው መስጠት ከሚችለው 49 ሜጋ ዋት ኃይል ውስጥ በአማካይ እስከ 16 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ብቻ የኤሌክትሪክ ኃይል እያቀረበ እንደሚገኝ ኃላፊው ጠቅሰዋል ። ማከፋፈያ ጣቢያው ባለ 15 ኪሎ ቮልት ስድስት ወጪ መስመሮች ለከተማዋ ነዋሪዎች፣ ለአርባምንጭ ጨርቃጨርቅ ፋብሪካ፣ ለአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲና ኮሌጆች እንዲሁም ለዱቄት ፋብሪካዎች ኃይል ሲሰጥ በ33 ኪሎ ቮልት ባሉት ሁለት ወጪ መስመሮች ደግሞ ለኮንሶና አካባቢው ፣ለከንባ፣ቦረዳና ብርብር ወረዳዎች አስተማማኝ ኃይል እየሰጠ እንደሚገኝ አብራርተዋል። ማከፋፈያ ጣቢያው አሁን ላይ የሚመጡ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎችን ማስተናገድ የሚችል 32 ነጥብ 5 ሜጋ ዋት ተጨማሪ አቅም እንዳለው ኃላፊው ገልጸዋል። በጣቢያው ላይ የማስፋፊያና አቅም የማሳደግ ሥራዎች በቀጣይም እንደሚሰሩ የገለጹት ኃላፊው ጣቢያውን ከብሔራዊ ኤሌክትሪክ ግሪድ ደቡባዊ ማስፋፊያ ፕሮጀክት ጋር ለማገናኘት ባለ 132 ኪሎ ቮልት የማስፋፊያ ሥራ በቅርቡ አንደሚጀመር ጠቁመዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 17 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content
+3

ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሞግዚት (Child Caregivers) የስራ መደብ ሰራተኞችን አወዳድሮ ለመቅጠር መስከረም 22 ቀን 2016 ዓ.ም የውጪ ማስታወቂያ ማውጣቱ ይታወሳል፡፡ በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች ስማችሁ የተገለጸው አመልካቾች በሙሉ ጥቅምት 21 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ማንነታችሁን የሚገልጽ የታደሰ መታወቂያ በመያዝ ኮተቤ በሚገኘው በተቋሙ ዋና መ/ቤት የማሰልጠኛ አዳራሽ የጽሁፍ ፈተና ስለሚሰጥ ለፈተና እንድትገኙ እናሳስባለን፡፡ የኢትዮጵያ አሌክትሪክ ኃይል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ግሪዱን ማዘመን የሚያስችል ፍኖተ ካርታ እየተዘጋጀ ነው ........///........ ብሔራዊ የኃይል ግሪድን ለማዘመን የሚያስችሉ የፍኖተ ካርታ ዝግጅትና የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች በመከናወን ላይ መሆናቸውን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ አስታወቀ። በዘርፉ የዲጂታላይዜሽን እና አቅም ማሻሻል መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ዳዊት ገ/እግዚአብሔር እንዳስታወቁት በማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ያሉ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን የማዘመንና የቴክኒክ ድጋፎችን የመስጠት ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱ የከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮችና ማከፋፈያ ጣቢያዎችን የኦፕሬሽን ሥራዎች ለማዘመን እና ሠራተኛው ዘመኑ የደረሰበትን ቴክኖሎጂ እንዲጠቀም እንደሚያግዝ ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱ በመጠናቀቅ ላይ ነው ያሉት ዳይሬክተሩ የቴክኒክ ድጋፉ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችና ማስተላለፊያ መስመሮች ላይ የሚከናወኑ የአቅም ማሳደግና ማሻሻል ሥራዎች ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓትን የተከተሉ እንዲሆኑ ያግዛል ብለዋል። እንደ አቶ ዳዊት ገለፃ ግሪዱን ለማዘመን እየተከናወነ ባለው ሥራ ላይ በኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ እየሰሩ የሚገኙ ባለሙያዎችን አቅም ለማሳደግ የሚያስችሉ ሥራዎችን ለማከናወን ታቅዷል። የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎችን ደህንነት ለመጠበቅ የሚያግዙ የመቆጣጠሪያ መሳሪያዎችን የመትከል፣ በአግባቡ መስራታቸውን የመከታተልና የመገምገም እንዲሁም የትራንስፎርመር ዘይቶችን የመፈተሽ ሥራዎች እንደሚሰሩም ዳይሬክተሩ አብራርተዋል። በቴክኒክ ድጋፍ ሥራው በሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የተለያዩ የማዘመን ሥራዎች እንደሚከናወኑ የጠቆሙት ዳይሬክተሩ የተቋሙ ሥራ አመራር የልምድ ልውውጦችንና ተሞክሮዎችን እንዲያገኙ የሚያስችል የአሰራር ሥርዓት እንደሚዘረጋም ጠቁመዋል። የፍኖተ ካርታ ዝግጅቱና የቴክኒክ እገዛ ሥራው ከፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ በተገኘ  የ1 ነጥብ 6 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ድጋፍ የሚከናወን መሆኑን ጠቁመዋል። ከዚህ ውስጥ 4 መቶ ሺህ የአሜሪካን ዶላሩ  ለግሪድ ፍኖተ ካርታ ዝግጅት እንዲሁም 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላሩ ደግሞ በሁሉም የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ ተግባራዊ ለሚደረግ የቴክኒክ ድጋፍ ሥራዎች የሚውል ነው ተብሏል። የፍኖተ ካርታ ዝግጅትና የቴክኒክ ድጋፍ ሥራው አር ቲ ኢ ኢንተርናሽናል (RTE International) በተሰኘ የፈረንሳይ ኩባንያ በመከናወን ላይ እንደሚገኝ እና ሥራዎች ሲጠናቀቁም ችግር ፈቺ ግብዓቶች ይገኙበታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ዳዊት አስታውቀዋል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 15 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

በስርቆት ምክንያት የተቋረጠውን የኃይል አቅርቦት ለመመለስ ጥረቶች ተጀምረዋል ………////………. ከመንዲ አሶሳ በተዘረጋው ባለ 132 ኪሎ ቮልት የከፍተኛ ኃይል ማስተላለፊያ መስመር ላይ በተፈፀመ ስርቆት ምክንያት በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ሙሉ በሙሉ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል፡፡ በክልሉ መንደር 48 በተለምዶ አንበሳ ጫካ ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በኃይል ማስተላለፊያ መስመር ተሸካሚ ምሰሶ አካላት ላይ በተፈፀመ ስርቆት መስመሩን የሚሸከሙ ሁለት የብረት ምሰሶዎች ወይም ታወሮች ወድቀዋል፡፡ በዚሁ የተነሳ ከመስመሩ ኃይል ሲያገኙ የነበሩት የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል መዲና አሶሳ ከተማ እና የአሶሳ ዞን ወረዳዎች በሙሉ የኃይል አቅርቦት ተቋርጧል። ከዚህ በፊትም በክልሉ ባምባሲ በተባለ አካባቢ በሥርቆት የተነሳ ኃይል ተቋርጦ የነበረ ሲሆን አሁን ለኃይል መቋረጥ ምክንያት የሆነው አካባቢ ከአሶሳ ከተማ ወደ 30 ያህል ኪሎ ሜትሮች ርቀት እንዳለው ለማወቅ ተችሏል፡፡ የወደቁ የኤሌክትሪክ ምሰሶዎችን በጊዜያዊነት በእንጨት ምሰሶዎች ለመተካት ጥረቶች የተጀመሩ ሲሆን ጥገናውን አጠናቆ ለአካባቢዎቹ ኃይል ለመስጠት እስከ ሦስት ቀን ድረስ ሊወስድ ይችላል፡፡ የኤሌክትሪክ መሰረተልማቶችን መጠበቅ በየደረጃው ያሉ የሁሉም መስተዳድር አካላት ኃላፊነት በመሆኑ የመስተዳድር አካላቱ ኃላፊነታቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ጥሪ እያደረግን ጥገናው ተጠናቆ ወደአገልግሎት እስኪመለስ ድረስ ህብረተሰቡ በትዕግስት እንዲጠብቀን እንጠይቃለን፡፡ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል! "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም

photo content

ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ ይቀጥላል ……...///…..... የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጠት የጀመረውን ሥራ አጠናክሮ እንደሚቀጥል የተቋሙ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍና ሥርጭት ክትትል ኮሚቴ አስታወቀ። ተቋሙ ማህበራዊ ኃላፊነቱን ለመወጣት በደቡብ ኦሞ ዞን ባሉ አራት ወረዳዎች በአየር ንብረት ለውጥ የተነሳ ለምግብ እጥረት ለተጋለጡ የህብረተሰብ ክፍሎች ያደረገውን የአስቸኳይ የሰብዓዊ እርዳታና ድጋፍ ሥርጭት አፈፃፀም ኮሚቴው ያካሄደውን የመስክ ምልከታ አጠናቋል። የኮሚቴው ሰብሳቢ የተቋሙ የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን እንደገለፁት ተቋሙ በአራቱ ወረዳዎች ያደረገው የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ የነዋሪዎቹን ወቅታዊ ችግር ታሳቢ ያደረገ ነው። የሰብዓዊ እርዳታ ሥርጭቱን ያከናወነው የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር በዘርፉ ልምድ ያለው ተቋም መሆኑን ያሳየበት በመሆኑ በወቅቱ ድጋፉ ለተጠቃሚዎቹ እንዲደርስ አድርጓል ብለዋል፡፡ እንደ አቶ ሞገስ ገለፃ ለሥርጭቱ መሳካት የተቋሙ፣ የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር፣ የክልል፣ የዞን፣ የወረዳና የቀበሌ አመራሮች እንዲሁም የጎሳ መሪዎችና የማህበረሰብ ተወካዮች የነበራቸው አስተዋጽኦ የጎላ ነው። የኮሚቴው አባል ወ/ሪት ሜሮን ዮሐንስ በበኩላቸው የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ በአራቱ ወረዳዎች የሚኖሩ እናቶች፣ ህፃናት እና አቅመ ደካሞች ታሳቢ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል። ተቋሙ በመንግሥት ከተሰጠው ተልዕኮ ባሻገር በአየር ንብረት ለውጥ ሳቢያ ችግር ላይ ለወደቁ የማህበረሰብ ክፍሎች የተለያዩ አስቸኳይ ሰብዓዊ እርዳታ በማድረግ የህዝብ ተቋም መሆኑን አስመስክሯል ያሉት ደግሞ የኮሜቴው አባል አቶ ዋለ ታምሬ ናቸው። በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አማካኝነት በወረዳዎቹ የተከናወነውን የሥርጭት ሥራ ተዟዙረው መመልከታቸውን ያነሱት አቶ ዋለ የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፉ የታለመለትን ዓላማ ማሳካቱን ተናግረዋል። እንደ አቶ ዋለ ገለፃ የእርዳታ ሥርጭት አፈፃፀሙን ተዟዙረው ከተመለከቱ በኋላ በአንዳንድ አካባቢዎች ከፀጥታና መሰል ችግሮች ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭቱ ላይ መጠነኛ ችግሮች እንደነበሩ መታዘባቸውን ገልፀዋል። ሌላው የኮሚቴው አባል አቶ ግዛቸው ደሳለኝ በበኩላቸው ተቋሙ በወረዳዎቹ ለሚገኙ አርብቶ አደሮች በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ድጋፎችን ሲያደርግ መቆየቱን አስታውሰዋል። የአስቸኳይ ጊዜ የሰብዓዊ እርዳታ ድጋፍ ሥርጭቱ በአራቱ ወረዳዎች ለሚኖሩ አርብቶ አደሮች መደረጉ የተቋሙን መልካም ገፅታ ከመገንባት አንፃር አወንታዊ ሚና መጫወቱን ጠቁመዋል። በመስክ ምልከታው ወቅት በወረዳዎቹ ከሚገኙ አመራሮችና አርብቶ አደሮች ጋር በተደረጉ ውይይቶች በአካባቢው የሚስተዋሉትን ችግሮች በዘላቂነት ለመፍታት ተቋሙ የማህበራዊ ልማት ጥናት ዕቅድ ለማዘጋጀት እንቅስቃሴዎች መጀመሩ ተገልጿል። "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric ቴሌግራም↠ https://t.me/EEPCommuication ትዊተር ↠ https://twitter.com/EEPethiopia ዩትዩብ ቻናል↠ https://www.youtube.com/@Ethiopianelectricpower ድረ - ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et ጥቅምት 14 ቀን 2016 ዓ.ም