Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት 的分析概览
频道 Finote Hiwot የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔ ዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት (@finotehiwott) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 373 名订阅者,在 宗教与灵性 类别中位列第 5 571,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 195 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 373 名订阅者。
根据 05 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 30,过去 24 小时变化为 -4,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 22.23%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.08% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 3 418 次浏览,首日通常累积 1 397 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 20。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“የቀጨኔ መድኃኔዓለም ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት ነሐሴ 26/ 1958 ዓ.ም ተመሠረተ።”
凭借高频更新(最新数据采集于 06 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 宗教与灵性 类别中的关键影响点。
15 373
订阅者
-424 小时
-197 天
+3030 天
帖子存档
#holy_Righteous_abraham
#ነሐሴ_፳፰
#እንኳን_ለአባታችን_ለአበ_ብዙኃን_አብርሃም_በዓለ_ዕረፍት_እንዲሁም_ለይስሐቅ_እና_ለያዕቆብ_መታሰቢያ_በስላም_አደረሳቹ
#አበዊነ_አብርሃም
❖
አባታችን አበርሃም የስሙ ትርጓሜ አበ በዙኃን ሲሆን ትርጉሙም የበዙኃን አባት ማለት ነው፡፡ የዕረፍቱ ነገር አንዲህ ነው
❖
አስከ ዕለተ ዕረፍቱ ደረስ በድንኳን የኖረ፣ ስለ ታዛዥነቱ ካራንን ጥሎ የወጣ ፣ አንድ ልጁን እስከ ማረድ የታዘዘ አባት ነው ፡፡
❖
አግዚአበሄር ለአበርሃም ከነበረው ፍቅር ፤ የሞቱን ነገር ሲሰማ አብርሃም እንዲያዝን አልወደደምና ሚካኤልን እንዲያጽናናው ልኮታል፡፡ በሰማይም ስላለው ነገር ወደሰማይ ነጥቆ ያሳየው ነበር ፡፡
❖
ቅዱስ ሚካኤልም በእንግድነት ባደረባት በዚያች ሌሊት ለልጁ ለይስሐቅ የሞቱ ነገር ተገልጦለታል ፡፡ ይስሐቅም በመንፈቀ ሌሊት እያለቀስ ሄዶ አባቱ ካለበት አንኳኳ፤ አባቴ አበርሃም ከእኔ ከመለየትክ በፊት ገብቼ እጅ እነሳክ ዘንድ ፍቀድልኝ ፍቅርህንም እጠግብ ዘንድ ክፍትልኝ አለው ፡፡
አብርሃምም ደንግጦ ከፈተለት ይስሐቅም ወዲያውኑ አባቱን አቅፎ ሳመው ሁለቱም አንገት ለአንገት ተያዘው እጅግ አለቀሱ እንደውም ቅዱስ ሚካኤል ፍቅራቸውን አይቶ አዘነ ፡፡ መጽሐፉ ሚካኤል አብሮዋቸው አለቀሰ ይለዋል ፡፡ርብቃም ለቅሶዋቸውን ሰምታ መጣች አብርሃምም << ከመጣክ ጀምሮ ልቤ ደንግጦብኛል ወንድሜ ሆይ ስለምን ነገር ወደዚ መጣክ አለው >> ሚካኤልም ልጅህ ይስሐቅ ያየውን ይንገር አለው ፡፡ ይሰሐቀም ነገራቸው ፡፡
❖
ቅዱስ ሚካኤልም እነደታዘዘው መለአከ ሞትን አስጠንቅቆ ሰደደው ፡፡ የሞቱ ሰኣት በደረስ ጊዜም ይስሐቀም ያለቅስ ነበር ፤አብርሃምም ልጄ አታቅስ ረዳትህ እግዚአብሄር ነውና እስከምትሞትባት ቀን ድረስ እርሱ ይሁንህ አለው ፡፡ አግዚአብሄርም ዘርህን እንደ ምድር አሸዋ እንደ ሰማይ ከዋክብት አበዛልሃልው ብሎ ቃል ገብቶለታል
❖
#ይቤሎ እግዚአብሄር ለአቡነ አብርሃም ባርኮ አባርከከ ወአበዝህዎ ለዘርእ ፣
ከመ ኮከበ ሰማይ ወከመ ወጻእ ዘደንገገ ባህር ፡፡
❖
የመላእክት ሰራዊት ብፅዕት ነፍስ እያሉ ከገንት አኖሯት ፤ ይስሐቅም እያለቀስሰ በፍጹም ክብር ገንዞ ከኬጢ ልጆች በገዛዉ በሳራ መቃብር ቀበረው ስምንት ቀንም ሃዘን አደረጉለት፡፡
❖
የደጋግ አባቶቻችን የአብርሃም ፣ የይሰሐቅ አና ያዕቆብን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን ፡፡
❖
የአባታችን የአበ በዙኃን አብርሃም በዓል በአዲስ አበባ ወስጥ ብቸኛ በሆነው በ ለቡ ደብረ ታቦር በዓለ ወልድ ና አበ ብዙኃን አብርሃም ገዳም ይከብራል::
#አቅጣጫ ለቡ ፣ኃይሌ ጋርመንት
❖
✞
share share
#ልደቱ_ለአቡነ_ዘርዓ_ብሩክ †
ቀደም ግዮን ሲባል የሚጠራውን ወንዝ ፤ ግሺ #አባይ በማለት ለሰዮሙት ለታለቁ አባት #አቡነ_ዘርዓ_ብሩክ የልደት በዓል አደረሳቹ፡፡
†
የጻድቁ አባታችን #የአቡነ_ዘርዓ_ብሩክ አባት እና እናት የተባረኩ ከቅዱሳን ወገን የሚሆኑ ነበሩ። የአባታቸው ስምም ቅዱስ ደመ ክርስቶስ ሲባል እናታቸው ደግሞ ቅድስት ማርያም ሞገሳ ትባላለች። ጻድቁ አባታችን ገና በእናታቸው ማህጸን እያሉ ነበር ብዙ ተአምራት የሚያደርጉት እግዚአብሔር መርጧቸዋልና።
በኋላም ከክርስቶስ ልደት በኋላ በ8ኛው መቶ ክ/ዘመን መጨረሻ ላይ በነሐሴ 27 ጻድቁ አባታችን ተወለዱ። በ40ኛ ቀናቸውም ተጠምቀው በካህናት አፍ "ጸጋ ክርስቶስ" ተባሉ ከዛም ቤተሰቦቻቸው በጥሩ እድገት አሳደጉአቸው። 7 አመትም በሞላቸው ግዜ "በልጅነቴ የዚን ዓለም ክፋቱን እንዳላይ" ብለው ቢጸልዩ ዓይናቸው ታውሯል።
†
ቤተሰቦቻቸውም ጠቢቡ ሰሎሞን "የእግዚአብሔር ቃል ነውርን ይሸፍናል" እዳለው ትምህርት ሊያስተምሩአቸው አስተማሪ ጋር ቢወስዱአቸው ታመው ተመልሰዋል የእግዚአብሔር ፈቃድ አይደለምና። ነገር ግን የሚያስፈልጋቸውን እውቀት ፈጣሪ አምላክ ራሱ ገልጾላቸዋል:: ክህነትን እስከ ጵጵስና እራሱ መድሃኔ ዓለም ክርስቶስ ሰጥቷቸዋል። 12 አመትም በሞላቸው ግዜ በእግዚአብሔር ፈቃድ አይናቸው በርቶላቸው ታላላቅ ተጋድሎን ማድረግ ጀመሩ።
†
በእግዚአብሔር ዘንድ ጵጵስና እንደተሾሙ የኃጥያት ማሰርያን ያስሩና ይፈቱ ዘንድ ጵጵስናን በሾማቸው ግዜ እግዚአብሔር ያወጣላቸው ሁለተኛ ስም "ዘርዓ ብሩክ" ይባል ነበር። 3ኛውም ስማቸው ደግሞ "ጸጋ እየሱስ" ይባላል:: ጻድቁ አባታችን በዚህ አለም በህይወተ ሥጋ ሳሉ አቡቀለምሲስ እንደሚባል እንደ ሐዋርያው ዮሃንስ .. እግዚአብሔር እሱ ወዳለበት ወደ ሰማይ አውጥቶ በገነት መካከል ያኖራቸው ነበር:: እግዚአብሔር አምላክ ለወዳጁ ለብጹዕ አባታችን ዘርዓ ብሩክ በጎ ነገር እንዳደረገለትና ያለ ድምጽ የሰማይ ደጆችን አልፎ የእሳት ባህርን ተሻግሮ ፈራሽ በስባሽ ሲሆን እንደ ህያዋን መላእክት በፍጥነት ከጽንፍ እስከ ጽንፍ ከአድማስ እስከ አድማስ ይደርስ ዘንድ 12 ክንፍን ሰጣቸው። መላእክትም ለሌሎች ቅዱሳን ያልተሰጠ ይህንን ስልጣን አይተው ለምድራዊ ሰው ይህ ነገር እንዴት ይቻላል? እያሉ አደነቁ።ከዛም በኋላ ጻድቁ አባታችን ከፈጣሪ ዘንድ የመላእክትን አስኬማ፣ የሾህ አክሊል አምሳያ የሆነውን መንፈሳዊ ቆብን,ሰማያዊ ቅናትን እና የደረት ልብስን(ስጋ ማርያም) ተቀብሎ በጾም እና በጸሎት በልመና እና በስግደት እግዚአብሄርን ሲያገለግል ኖረ። ከዛም በላይ ወንጌልን እጅግ ብዙ በማስተማር ደከመ።
†
ከኢትዮጵያም አልፎ ግብጽ ድረስ ገባ የእስክንድርያውን ሊቀ ጳጳስ አባ ዮሐንስን አገኘውና እርስ በርስ ሰላምታን ተለዋውጠው እጅ ተነሳሱ ከዛም ተመልሶ ወደ ሃገሩ መጣ ከዛም ኢትዮጵያ ውስጥ እየተመላለሰ ወንጌልን አስተማረ እጅግ ስጋን በሚያስጨንቅ ትጋትም #የኢትዮጵያን ህዝብ ማርልኝ እያለ እያለቀሰ ይጸልይ ነበር።
#አቡነ_ዘርዓ_ብሩክ "#ዓባይ" እና "ግሽ ዓባይ" የሚሉ ስሞች እንዳወጡ አንድ ቀን አባታችንን የንጉስ ጭፍሮች ሲያሳድዷቸው ግዮን ደረሱ። እንደደረሱባቸው ሲያውቁ ዳዊታቸውንና ለወንጌል ስብከት ሲጠቀሙባቸው የነበሩ 7 መጻሕፍት ሁሉ #ለግዮን ወንዝ አደራ ሰጡዋት። ከ5 አመት በኋላ ሲመለሱ" #ኦ_ግዮን_ግሥኢ መፃሕፍትየ -- #ግዮን_ሆይ_መጻሕፍቴን_ግሺ_መልሺልኝ " (#ግሽ_ዓባይ የተባለውም ከዚሁ በመነሳት ነው ።) _ቢሉአት አንድም የውሃ ጠብታ ሳይኖርባት ዳዊታቸውን ብትመልስላቸው ለደቀ መዝሙራቸው #ዘሩፋኤል አሳዩት ሁለቱም የእግዚአብሔርን ሥራ አደነቁ። ከዛም በኋላ ግዮንን #ባረክዋትና "ይኩን ፈውስ ዓብይ በውስቴትኪ .. .በውስጥሽ ታላቅ ድኅነት ይደረግብሽ" አሉ። ከዛ ጊዜ ጀምሮ መካኖች ይወልዱ፣ ድዉዮች ይድኑ ጀመር "ወእም አሜሃ ተሰምየት ዓባይ ይእቲ ፈለግ ::ከዛ ጊዜ ጀምሮ ይህች ዓባይ ተብላ ተጠራች።" እስካሁንም በዚሁ ስም የሚጠራው ከዚ በመነሳት ነው:: ከዚህም ሌላ ጻድቁ አባታችን በዚሁ ወንዝ አካባቢ ለ 30 አመት ሲጸልዩ ፈጣሪ አምላክ ጸሎታቸውን ሰምቶ እጅግ ልዩ የሆነ ቃል ኪዳን ሰቶአቸዋል።
†
በስተመጨረሻም የሚያርፉበት እለት በደረሰ ሰአት መልአከ ሞት መቶ እስኪደነግጥ እና ወደ ኋላው እስኪያፈገፍግ ድረስ ነው እግዚአብሔር ጸጋውንና ክብሩን ያበዛላቸው: በስተመጨረሻም ጥር በገባ በ13ኛው ቀን በ482 አመታቸው ስጋቸው ከነፍሳቸው ተለይታ ገነትን ወርሰዋል:: በረከታቸው ይደርብን ፣ ምልጃቸው አይለየን ፡፡
†
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
#ታሪከ ወመልክአ አቡነ ሃብተማርያም
እንኳን ለአባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም በዓለ ጽንሰት አደረሳቹ::
#አቡነ_ሃብተማርያም
አባታችን ታላቁ ጻድቅ አባታችን #አቡነ_ሃብተማርያም የተወለዱት በመንዝ አውራጃ ልዩ ስሙ የራዊ በተባለ ቦታ ሲሆን የአባታቸው ስም ፍሬ ብሩክ የእናታቸው ስም ዮስቴና ይባላል፡፡ ሁለቱም በሕግ ጋብቻ ጸንተው ሕገ እግዚአብሔርን ጠብቀው ምግባር ቱሩፋት ሰርተው በንጽህና በቅድስና ይኖሩ ነበር፡፡ ሆኖም ልጅ አለነበራቸውም፡፡ በዚህ ሁኔታ ያዘኑ ቅድስት ዮስቴና ማለት እናታቸው መንነው በአከባቢያቸው ከሚገኝ ጫካ ውስጥ ዋሻ ፈልገው ገብተው ዘጉ፡፡ በዚያም አንድ መናኝ መነኩሴ አግኝተዋቸው እግዚአብሔር በቅድስቲቱ ያለው ድብቅ ነገር ስለገለጠላቸው አንቺ ለምንኩስና የተፈቀደልሽ አይደለሽም ወደ ቤትሽ ግቢ ጸሎቱ ለዓለም ሁሉ የሚጠቅም ሰው ሁሉ የሚማጸነው ስሙ፣ ገድሉ ትሩፋቱ በዓለም ሁሉ የሚነገርለት ወንድ ልጅ ትወልጃለሽ አሏቸው፡፡ የእግዚአብሔርን ድንቅ ተዓምር የሰሙ ቅድስት ዮስቴናም እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቤቸው ተመለሱ፡፡
የተናገረውን የማያስቀር አምላክ በቸርነቱ ጎበኛቸውና ነሐሴ 26 ቀን ጸነሱ፡፡ ግንቦት 26 ቀንም ደም ግባታቸው እንደ ንጋት ኮከብ ያማሩ ሃብተማርያም ተወለዱ፡፡ እግዚአብሔር ለቅድስና ሥራ ስለመረጣቸው በእናተቸው ጀርባ ታዝለው ወደ ቤተክርስቲያን ሄደው በሕጻን አንደበታቸው ከቀዳሹ ካህን ጋር “እግዚኦ ማሐረነ ክርስቶስ” በማለት ይጸልዩ ነበር፡፡ ባደጉም ጊዜ ይህን ጸሎት ደጋግመው ይጸልዩ ነበር፡፡ ላባቸውም እስኪንጠባጠብ ድረስ በመስገድ ይጋደሉ ነበር፡፡ አንድ ቀንም ከአባታቸው ጎን እንደ ተኙ በድንገት እግዚአብሔር በድምጽ “ሀብተማርያም ሆይ! አንተን የተመረጠ ዕቃ አድርጌሃለሁና ቃሌን ለተመረጡ ሰዎች ተናገር” አላቸው፡፡ ይህን ግን የተበሰረላቸው የቤተሰቦቻቸውን ከብቶች በሚጠብቁበት ጊዜ ነበር፡፡ እድሜያቸው እየገፋ ሲሄድ አባታቸው ትምህርት ቤት አስገቡአቸው፡፡ ለአቅመ አዳም በደረሱ ጊዜ ሚስት አጩላቸው፤ እርሳቸው ግን የድንግልናን ህይወት በመምረጥ ከወላጃቸው ቤት ኮብልለው ገዳም ገቡ፡፡
“ልጄ ሆይ እራስህን ለእግዚአብሔር ታስገዛ ዘንድ ወደ ገዳም ብትሄድ ሰውነትህ ለመከራ አዘጋጅ፡፡” መጽሐፈ ሲራክ 2፡1.
በዚያን አባ ሳሙኤል ለሚባሉ በረዳትነት ሲያገለግሉብዙ ገቢረ ተዓምራት ተደርጎላቸዋል፡፡ ዛሬ ይሰበይ ገዳም ተብሎ በሚጠራው ሥፍራ ለሦስት ወራት ጽሙድ እንደበሬ ትጉህ እንደ ገበሬ እንዲሉ በጾም በጸሎት ተጠምደው ሳለ መታሰቢያህን በዚህ ዋሻ አደርግልሃለሁ በማለት እግዚአብሔር ቃል ኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ጊዜ እረፍታቸው በደረሰ ጊዜ ጌታ ተገልጦላቸው ስለ ተጋድሎአቸውና ስለንጽህናቸው ሳባት አክሊል እንደሚቀበሉ ነግሯቸዋል፡፡
በ490 ዓ.ም ህዳር 26 ቀን ዐርፈው በደብረሊባኖስ ገዳም መካነ ቅዱሳን ቀበሯቸው፡፡
የአባታችን የጻድቁ አቡነ ሀብተማርያም ረድኤት፣ በረከት፣ ምልጃና ቃል ኪዳናቸው አይለየን፡፡
✞✞✞✞✞
#አቡነ #ተክለሃይማኖት አና #አቡነ #ሃብተማርያም
✞
#ያን ጊዜ ክቡር የሆነ #አቡነ_ተክለሃይማኖት ጠርቶኝ ልጄ #ሀብተ_ማርያም ሆይ ፈጣሪየ እግዚአብሔር ስለ ወደደህ ብዙ ምህርኮ እንደአገኝህ በአንተ ፈጽሞ ደስ ይለኛል አለኝ ፤
#ነገር ግን የሞለምንክ አንድ ነገር አለና እሽ በለኝ ቢለኝ አቤቱ ጌታዩ ምንድን ነው ነገሩ አልሁት ፣
#ክቡር አባታችን አባ ተክለሃይማኖትም ከተቀበርኩበት ቦታ እንድትቀብር ቃል ኪዳን ግባልኝ አለኝ፤
ይንን አደርግ ዘንድ ስለምን ትለምነኛለህ ብየ ብመልስለት፣ እነሆ በሀገሬ ላይ የታዘዙ አምስ መቅሰፍቶች አሉና ስለዚህ ነው ፤ እሊሁም አንዱ መብረቅ ነው ፣ ሁለተኛው ቸነፈር ነው ፤ ሦስተኛው የረኃብ ጦር ነው ፣ አራተኛ ወረርሽኝ ነው ፡፡ አምስተኛ የእሳት ቃጠሎ ነው ፤ የአንተ አጽም በውስጡ የተቀበረ እንደ ሆነ አጥንቴ የተቀበረባት ሀገር ከእንዚህ መቅስፍታት ትድናለች፣
#……ልጄ ሀብተማርያም ሆይ አንተ የማታውቀው ከፈጣሪያችን ከእግዚአብሄር የተሰጠህ እኔ የማውቀው ክብር አለህና ስለዚህ ነው አለኝ ፣ ይልቁንስ እንዳልኩክ በተቀበርኩበት ቦታ እንተቀበርልኝ ቃል ኪዳን ግባልኝ ብሎ መላልሶ ማለደኝ.
✞ #ከገድላቸው
#አቡነ_ሀብተ_ማርያም በቃል ኪዳናቸው ሀገራችንን ከአምስቱ መቅሰፍታት ይጠብቁልን አሜን !
በአ.አ በዓሉ በድምቀት ከሚከበርባቸው አድባራት አንዱ በቃሌ ተራራ ደብር መድኃኒት አቡነ ሃብተማርያም ገዳም አንዱ ነው ::
አቅጣጫ አስኮ አካባቢ
#ልደታቸው ግንቦት 26
#ዕረፍታቸው ህዳር 26
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ዳግመኛም መልአኩ ‹‹አሁንም እንደልማድሽ ሂጂና ጠይቂው ማን እንደሆነ ይነግርሻል›› አላት፡፡ በዚህን ጊዜ ወደ እርሱ ሄደችና ‹‹እሰግድልህ ዘንድ አንተ ማን ነህ?፣ ስምህስ ማን ይባላል?›› ስትል ጠየቀችው፡፡ ሰይጣንም ‹‹የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነኝ›› አላት፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ከእርሷ ጋር እንዳለ አላወቀም ነበርና፡፡ እርሱ በእርሷ ላይ ተንኮል ለመሥራት እንደተራቀቀ ሁሉ እርሷም ነቃችበት ተራቀቀችበት፡፡ ቀጥሎም ‹‹እንግዲያውስ አንተ ሚካኤል ከሆንክ እስቲ ስለ ጽድቅ ነገር አስተምረኝ›› አለችው፡፡ በዚህም ጊዜ ሰይጣን ፈጽሞ ተደሰተ ከዓላማዋ አሳስቶ በእጁ የገባችለት መስሎታልና፡፡ እንዲህም አላት፡- ‹‹ለምን ሰውነትሽን ታደክሚዋለሽ? ከዛሬ ጀምሮ ከዚህ ኃላፊ ዓለም ድካም ማረፍ ያስፈልግሻል፣ መጾምና መጸለይስ ለምን ይጠቅምሻል? በባሕርስ ውስጥ ቆሞ መጸለይና ሰውነትን ማድከም ማን አስተማረሽ?›› አላት፡፡ በዚያን ጊዜ ‹‹አንተ የምትለውና መጻሕፍት የሚናገሩት የተለያየ ሆነሳ!?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ማነው የለያየን?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹ከአነጋገርህ የተነሣ እኔ ለየኋችሁ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹እስኪ ልዩነታችንን ንገሪኝ?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹መጻሕፍት የጾመ፣ የጸለየ፣ የለመነም ሁሉ ፍጹም ዋጋውን ያገኛል ይላሉ፡፡ አንተ ግን አትጹሙ፣ አትጸልዩ ትላለህ›› አለችው፡፡ ይህንንም ባለችው ጊዜ በእርሷ ላይ ፈጽሞ ተቆጣ፣ እጅግም አድርጎ አስደነገጣት፡፡ ዳግመኛም መለሰችና ‹‹በምን ትሸነፋለህ?›› አለችው፡፡ አሁንም ቁጣውን አወረደባት፡፡ በሦስተኛው ጊዜ ከተቆጣ በኋላ ‹‹በእነዚህ በሦስቱ ነገሮች እሸነፋለሁ›› ሲል መለሰላት፡፡ ‹‹አንደኛ ማንኛውም ሰው በዚህ ዓለም በሚኖርበት ጊዜ ነፍሱ ከሥጋው ከመለየቷ በፊት እንግዳ ተቀብሎ የሚያስተናግድ፤ ሁለተኛው በራሱ ላይ ችግርና መከራ በመጣበት ጊዜ መከራውን ታግሦ የሚኖር፤ ሦስተኛው ቀድሞም ከመሬት የተገኘሁ ነኝ፣ ኋላም ተመልሼ ወደ መሬት እገባለሁ እሞታለሁ እፈርሳለሁ ብሎ በማሰብ ትሕትና የሚሠራና የመሳሰሉትን ሁሉ የሚያደርግ እርሱ ፈጽሞ ያሸንፈኛል›› አላት፡፡ ይህንንም ከተናገረ በኋላ ክንፉን እያማታ ወደ አየር በረረ፡፡ እርሷም ከግርማው የተነሣ ፈጽማ ደነገጠች፤ በመሬትም ላይ ወደቀች፡፡ በዚያን ጊዜ ለጌትነቱ ክብር ምስጋና ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መጥቶ ቅዱሳት በሚሆኑ እጆቹ ከወደቀችበት አነሣት፡፡ ከዚያም ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! አይዞሽ አትፍሪው ነገር ግን ወደ ላይ ወደ ሰማይ አቅንተሽ ተመልከቺ›› አላት፡፡ ወደ ሰማይ አቅንታ በተመለከተች ጊዜ የዲያብሎስ ክንፉ በሰማይ ላይ ከጽንፍ እስከ አጽናፍ ተዘርግቶ (መላው ዓለምን ሞልቶ) አየች፡፡ ቀጥሎም ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹‹በእኔ በባሕርይ አባቴ በአብ በባሕርይ ሕይወቴ በመንፈስ ቅዱስ ያላመነ ሊያሸንፈው አይችልም›› አላት፡፡ ዳግመኛም ‹‹ማንም ሰው ኃጢአት ቢኖርበት ወደ ቀደመ ኃጢአቱ ባለመመለስ ንስሐ ቢገባ ከወጥመዱ ያመልጣል›› አላት፡፡
ከዚህ በኋላ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በቁመቷ ልክ ጉድጓድ አስቆፍራ በአራቱም አቅጣጫ ከፊትና ከኋላ፣ በግራና በቀኝ ሦስት ሦስት የተሳሉ ጦሮችን ተክላ የፊጥኝ ታስራ ስለ ዓለሙ ሁሉ ይልቁንም ስለ ኢትዮጵያ ልጆች ስትጸልይ ኖራለች፡፡ በምትሰግድበትም ጊዜ ጦሩ እየወጋት ከቁስሉ የተነሳ ጦሩ የወጋትና ገመዱ የከረከራት መላ ሰውነቷ እስኪሸትና እስኪተላ ድረስ ለ12 ዓመታት በጉድጓድ ውስጥ በተጋድሎ ኖራለች፡፡ ያረፈችውም በዚሁ ጉድጓድ ውስጥ ቆማ ስለ ዓለሙ ስትጸልይ ነው፡፡ ጌታችንም ክብሯ ከሙሴ፣ ከአሮን፣ ከጴጥሮስ፣ ከጳውሎስ፣ ከሕጻኑ ቂርቆስ፣ ከእንጦንስ፣ ከጊዮርጊስና ከእስጢፋኖስ ጋር የተካከለ መሆኑን በማይታበል ቃሉ ነግሯታል፡፡ በዚህች ምድር ላይም 375 ዓመት ኖራ አባታችን ቅዱስ ተክለሃይማኖት ባረፉበት ዕለት ነሐሴ 24 ቀን በታላቅ ክብር ዐርፋለች፡፡
በዚህችም ዕለት ከማረፏ በፊት መድኃኔዓለም ክርስቶስ ቅድስት እናቱን እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያምንና ሌሎች ቅዱሳንን ሁሉ አስከትሎ ወደ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ዛሬ ከዚህ ከሚያልፈው ዓለም ወደ ማያልፈው ዓለም አሳርፍሽ ዘንድ መጥቻለው›› አላት፡፡ ‹‹ድካምሽ ወደ ዕረፍት፣ ኀዘንሽም ወደ ደስታ ተለውጦልሻልና›› ሲላት እርሷም ‹‹አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! እኔ ባሪያህ በፊትህ ባለሟልነትን አግኝቼ እንደሆን አንድ ነገር እንድናገር ፍቀድልኝ›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ትናገሪ ዘንድ ፈቅጄልሻለው›› ሲላት ‹‹አቤቱ ሥጋዬ የሚቀበርበት ቦታ ወዴት እንዲሆን ታዛለህ?›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹መቃብርሽ በዚህች ደሴት ይሆናል›› ካላት በኋላ የሚከተለውን ቃልኪዳን ሰጣት፡- ‹‹… በስምሽ ለተራበ ያበላ እኔ ዕለተ ዓርብ ከተቆረሰው ሥጋዬ አበላዋለሁ፣ በስምሽ ለተጠማ እፍኝ ውኃ ያጠጣውን እኔ በዕለተ ዓርብ ከጎኔ በፈሰሰው ደሜ አረካዋለሁ፡፡ እውነት እውነት እልሻለሁ ሥጋሽ ከተቀበረበት ሄዶ መካነ መቃብርሽን የተሳለመ የእናቴን የማርያምን መካነ መቃብር እንደተሣለመ ይቆጠርለታል፡፡ ምሕረት ሊደረግለት የማይገባው ሁሉ ወደ አንቺ መጥቶ ዜና ገድልሽን ሊሰማ አይችልም፡፡ ስለሆነም ገድልሽን ለመስማት፣ ትሩፋትሽን ለማየት ወደ አንቺ የሚመጡትን ተስፋ መንግሥተ ሰማያትን እሰጣቸዋለሁ፣ አንቺን የሚያፈቅሩ ሁሉ የተመሰገኑ ናቸው፣ እውነት እውነት እልሻለሁ አንቺን የወደደሽን እኔ ደግሞ እወደዋለሁ፡፡ መኖሪያሽ ከእናቴ ከድንግል ማርያም ጋር ነው፣ እነሆ በትረ ማርያም ብዬ ሰየምኩሽ፣ ደረጃሽን ከእርሷ ቀጥሎ ሁለተኛ አደረግሁልሽ›› ብሏታል፡፡ ከዚያም በፊት የቅዱሳን ገድላቸው ሲነበብ ሐሰት ነው ብለው የሚያቃልሉ ሰዎች ዕጣ ክፍላቸው ከነአርዮስ ጋር መሆኑን ጌታችን ለክርስቶስ ሠምራ ነግሯታል፡፡ ይኸውም ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል በጌታችን ፊት አቁሟት ሳለ እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን ‹‹አቤቱ ጌታዬ የቅዱሳን ገድላቸው ሲነበብ ሐሰት ነው በማለት የማያምኑ ብዙ ሰዎች አሉ፡፡ እንግዲህ እንደነዚህ ያሉትን ትምራቸዋለህ? ወይስ አትምራቸውም?›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹በጥቡዕ ልብ ሆነው ያለመጠራጠር የሚያምኑት ወደ መንግሥቴ ይገባሉ፣ የማያምኑ ቢኖሩ ግን ክፍላቸው ከነ አርዮስና ሰባልዮስ ጋር ነው›› አላት፡፡
✤✣✤
ዳግመኛም ጌታችን በቅድስት ቤተክርስቲያን የሚፈተተው ሥጋና ደሙ አማናዊ ሥጋና ደሙ መሆኑን በተግባር አሳይቷታል፡፡ ይኸውም በመጋቢት 27 ቀን የመድኃኔዓለም በዓል በሚከበርበት ዕለት ሥጋውና ደሙን ለመቀበል እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ወደ ቤተ ክርስቲያን በገባች ጊዜ ድንቅና ረቂቅ ምሥጢርን እንድታይ አድርጓታል፡፡ በዚህች ዕለት እንደ ሕጉ እንደ ሥርዓቱ ካህናት ሥርዓተ ቍርባን ይፈጽሙ ዘንድ ወደ ቤተ መቅደስ ገቡ፡፡ በዚያው ወቅት ዲያቆኑ ሙቀት ያልተለየው ኅብስት በመሶበ ወርቅ ይዞ መጣ፡፡ ያች የወርቅ መሶብ ተለውጣ በድንግልና ያለች ብላቴና ሆነች፣ ኅብስቱም ሕፃን ልጅ ወደመሆን ተለወጠ፡፡ ቄሱ ከዲያቆኑ እጅ በተቀበለው ጊዜ ሕፃኑ ኅብስት ሆነ፣ ብላቴናይቱም መሶበ ወርቅ ሆነች፡፡ ከዚህ በኋላ ቄሱ ሥርዓተ ቅዳሴውን ጀምሮ ሲቀድስ ፈኑ ጸጋ መንፈስ ቅዱስ (የመንፈስ ቅዱስ ጸጋህን ላክልን) ከሚለው ደረሰ፡፡ በዚያን ጊዜ ቍርባኑን (ኅብስቱን) ያከብረው ዘንድ መንፈስ ቅዱስ በነጭ ርግብ አምሳል ወረደ፡፡ ዳግመኛም ይህ ኅብስት ተለውጦ ሕፃን ሆነ፡፡ ከዚያም ሕፃኑን ይሠዋው ዘንድ መልአኩ ለቄሱ ሰይፍ ሰጠውና ቄሱም ሕፃኑን ሠዋው፡፡ ይህንንም መለኮታዊ ምሥጢር በተመለከተች ጊዜ እጅግ አደነቀች፣ ፈጽማም ደነገጠች፣ መሪር ዕንባንም አለቀሰች፡፡
ከዚያም ቅዱስ ሚካኤል መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ምን ያስለቅስሻል ነገር ግን ይህን ድንቅ ምሥጢር ተመልከች እንጂ›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እሺ በጎ›› ብላ ትመለከት ጀመረች፡፡ ዳግመኛም ‹‹ይህ ቄሱ ሥርዓተ ቅዳሴውን በትክክል እንደሚያከናውንና ንጹሕ ካህንም ለመሆኑ ትመለከቺያለሽን?›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹አዎን›› አለችው፡፡ ከዚያም ቄሱ ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ለሕዝቡ ያቀብል ዘንድ ወጣ፡፡ እርሷም ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ተቀበለች፡፡ በምትቀበልበትም ጊዜ በአፍዋ ውስጥ ሥጋው ትኩስ ሥጋ፣ ደሙም ትኩስ ደም ሆኖ ተገኘ፡፡ እንዲሁም ከኅብስቱ አንዱ ከጻሕሉ ላይ ተነሥቶ በዲያቆኑ እጅ ተይዞ ባለው የደም ጽዋ ውስጥ ገብቶ በጽዋው ውስጥ ካለው ደም ጋር ተዋሕዶ ወደ መቅደስ ሲገባ አየች፡፡ ይህን ሁሉ አይታ ፈጽማ አደነቀች፡፡ ከእርሷም ጋር የነበረውን መልአክ ‹‹ይህ የምመለከተው ምሥጢር ምንድን ነው?›› ብላ ጠየቀችው፡፡ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤልም ‹‹ቀድሞ ቄሱ እንደ በግ ሲሰዋው ተመልከተሻል፡፡ የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! አሁንም እንደሰው ሞቶ የሚቀር እንዳይደለ በእውነት እነግርሻለሁ፣ በመለኮቱ ሕያው ነው እንጂ፡፡ መጽሐፍ ‹‹በሰውነትህ አንተ ከሙታን ጋር ትሞታለህ፣ በመለኮትህ ግን ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ሕያው ነህ፡፡ አንተ ሦስት መዓልት፣ ሦስት ሌሊት በከርሠ መቃብር አደርክ ዳሩ ግን በመለኮትህ ከአብ ከመንፈስ ቅዱስ ጋር በዙፋንህ ላይ ትገኛለህ›› ብሎ እንደተናገረ ዳግመኛም በሥጋው ቢሞት በመለኮቱ ሕያው ነው›› አላት፡፡ እርሷም ይህን ባላት ጊዜ ፈጽማ ደስ ተደሰተች፡፡
ከዚህም ሌላ ጌታችን አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ እጅግ አስደናቂ ምሥጢራትን ፈጽሞላታል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ከጎኑ በፈሰሰው ደም ግንባሯ ላይ ቅዱስ ስሙን አትሞባታል፣ በዕለተ ዐርብ በጦር የተወጋ ጎኑንም እንድትጠባ ካደረጋት በኋላ ‹‹ቶማስ የተወጋውን ጎኔን ዳሰሰ፣ አንቺ ግን ጠባሽ›› ብሏታል፡፡ ራሱ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሠራዒ ካህን ሆኖ ቀድሶ ሥጋ ወደሙን አቀብሏታል፡፡ በቸርነቱም የእናቱን ጡቶች እንድትጠባ ስለፈቀላት እመቤታችን ቅድስት የሆኑ ጡቷን አጥብታታለች፡፡ በመጨረሻም ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብዙ አስደናቂ የሆኑ ቃልኪዳኖችን ከገባላትና ዐሥር አክሊላትን ካቀዳጃት በኋላ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታ ቅዱሳን መላእክት በዝማሬ አሳርገዋታል፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን፡፡ እኛንም በአማላጅነታቸው የምንታመን ሁላችንን የአቡነ ተክለ ሃይማኖትን፣ የአቡነ ቶማስ ዘመርዓስን እና የእናታችን የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ረድኤት በረከታቸውን ያሳድርብን፡፡ በጸሎታቸው ይማረን፡፡
✤✣✤
ለተጨማሪ
✤telegram
https://t.me/medihanaelem
✤youtube
https://www.youtube.com/channel/UCWVKGH0mSJl47u44uopEb2w(fenote hiwot)
✤instagram
Finote_hiwot
✤✣✤
ከዕለታት አንድ ቀን በጣና ማዶ መዕቀበ እግዚእ የሚባል አንድ ሰው ነበረና መልአከ ጽልመት ወደ እርሱ ዘንድ መጥቶ ‹‹ፈጣሪውን ክደህ ይህን ዕፅ በሰውነትህ ብትቀብር ሞትና እርጅና አያገኝህም›› አለው፡፡ እርሱም ለዚህ ክፉ ሀሳቡ ፈቃደኝነቱን ስለገለጠለት መልአከ ጽልመት በሰውነቱ ውስጥ ዕፁን ቀብሮለት ሄደ፡፡ መዕቀበ እግዚእም ከዕለታት አንድ ቀን ወደ ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ዘንድ መጥቶ ‹‹ሰላም እልሻለው በጸሎትሽም ተማጽኛለሁ፣ የፈጠረኝን እግዚአብሔርን እስከ መካድ ደርሼ ብዙ ኃጢአት ሰርቻለውና›› አላት፡፡ ቅድስት እናታችንም በዚያን ጊዜ ፈጥና ተነሥታ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሄደችና ስለዚህ ሰው በፍጹም ኀዘን በመሆን ወደ ፈጣሪዋ አመለከተች፡፡ በዚህ ጊዜ ጌታችን መጥቶ ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! ለዚህ ሰው ምሕረት አይገባውም፣ የምገድል የማድን የምቀስፍ ይቅር የምል አምላክ እኔ እያለሁ ፈጣሪውን ክዶ በሰይጣን ምክር ተማምኖአልና›› አላት፡፡ በዚህ ጊዜ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ጌታችንን እግሩ ሥር ተደፍታ ‹‹አንተ መዓትህ የራቀ ምህረትህ የበዛ ፈጣሪ ሆይ! ማርልኝ ሁሉ ይቻልሃልና…›› ስትል አጥብቃ ለመነችው፡፡ ሁሉን የፈጠረ ጌታችንም ‹‹ስለ አንቺ ፍቅር ምሬልሻለው›› አላት፡፡ ከዚህ በኋላ ማዕቀበ እግዚእን ጠርታ ‹‹ኃጢአትህን ይቅር ብሎሃል›› አለችው፡፡ ከዚህ በኋላ ከራስ ጸጉሩ እስከ እግር ጥፍሩ የተቀበረውን ዕፅ ሰውነቱን ፍቃ ስታወጣለት ደሙ እንደ ቦይ ውኃ ወረደ፤ በዚያው ነፍሱ ከሥጋው ተለይታ ከማኅበረ ሰማዕታት ጋር አንድ ሆነች፡፡ እግዚአብሔር አምላካችን ለቅድስት ክርስቶስ ሠምራ #ስድስት ክንፎችን ሰጥቷታል፡፡ በበዓለ ጥምቀት ወቅት ሙሴ፣ ኤልያስና መጥመወቁ ዮሐንስ ጌታ የተጠመቀበትን የዮርዳኖስን ውኃ አምጥተው ሙሴ የቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ቀኝ እጇን፣ ኤልያስ ግራ እጇን ይዘዋት ዮሐንስ ውኃውን በራሷዋ ላይ አፍስሶ አጥምቀዋታል፡፡ ከጌታችን ጥምቀት በኋላ እንደዚህ ዓይነት መንገድ የተጠመቀ ማንም የለም፡፡ እነርሱም ጓንጉት በምትባል ገዳም ውስጥ የገዳም አስተዳዳሪ እንደምትሆንና እጅግ ብዙ ተከታዮች እንደሚኖሯት ትንቢት ነግረዋት ወደ ሰማይ ዐርገዋል፡፡
በነገሯት ትንቢት መሠረትም ከብዙ ጊዜ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል በስሙ የተቀረጸ ጽላት አምጥቶ ሰጣትና በዚያች በጓንጉት ደሴት ውስጥ በእርሱ ስም ቤተ ክርስቲያን እንድታሠራ ነገራት፡፡ ‹‹እንዴት ይሆንልኛል?›› ባለችውም ጊዜ ‹‹እኒያ ያጠመቁሽ ቅዱሳን ከጥቂት ዓመታት በኋላ እመ ምኔት ትሆኛለሽ ያሉሽን ረሳሽውን? ያ ጊዜ እነሆ ዛሬ ደረሰ›› ብሎ ነገራትና አባ ይስሐቅ የሚባል መነኩሴ ላከላትና የእሷ ልጆች ሊሆኑ ከመጡ 600 መነኮሳት ጋር በሦስት ወር ውስጥ የቅዱስ ሚካኤልን ቤተክርስቲያን ሠርታለች፡፡ ብዙ ተከታይ መነኮሳትንም አፍርታለች፡፡ በዚህችም ጓንጉት ደሴት ቆማ ስትጸልይ እንደሁልጊዜው ጌታችን ተገልጦላት ሳለ ‹‹አዳምን በአርአያህና በአምሳልህ ለምን ፈጠርከው? በእንጨት መስቀልስ ላይ ለምን ተሰቀልክ? ስለ አዳምና ስለ ልጆቹ አይደለምን?›› አለቸው፡፡ ጌታችንም ‹‹አዎ ስለ አዳምና ልጆቹ ስል ነው የተሰቀልሁት›› አላት፡፡ እርሷም ‹‹እንግዲያውስ መሰቀልህ ስለ እነርሱ ከሆነ ከአቤል ጀምሮ እስከዛሬ የሞቱትን ከዛሬም በኋላ እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ የሚሞቱትን ማራቸው፣ ይቅርም በላቸው›› አለችው፡፡ ጌታችንም ‹‹ወዳጄ ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እስቲ አንቺ ራስሽ ፍረጂ›› በማለት በጲላጦስ ዘመን አይሁድ ያደረሱበትን እጅግ አሠቃቂ መከራዎችና የሞቱን ሁኔታ ሁሉ በዝርዝር ከነገራት በኋላ ‹‹እንግዲህ ይህን ውለታ ዘንግተው ከክፋት የማይመለሱትን፣ ለተንኮል የማያርፉትን ልምራቸው ወይስ ልኮንናቸው ይገባል? እስቲ ፍረጂ›› አላት፡፡ እንደልብ ጓደኛም ብዙ ከተወያዩ በኋላ መጨረሻ ላይ ቅድስት እናታችን ‹‹አቤቱ ፈጣሪዬ ፈቃድህስ ቢሆን የአዳም ልጆች ከሥቃይ ከኩነኔ ይድኑ ዘንድ ዲያብሎስን ይቅር ትለውና ትምረው ዘንድ እለምንሃለሁ፣ የኃጥእን መመለሱን እንጂ ጥፋቱን አትወድምና፡፡የምለምንህ ወድጄው አይደለም ነገር ግን እርሱ ከተማረ በአዳም ልጆች ላይ ሥቃይና ኩነኔ ሊኖር አይችልም ብዬ በመገመት ነው እንጂ›› አለችው፡፡ ይህንንም ባለችው ጊዜ ጌታችን በጥያቄዋ ተገርሞ ‹‹ሌሎች ካንቺ በፊት የነበሩ ካንቺም በኋላ የሚነሡ የማያስቡትን እጅግ የሚያስደንቅ ልመና ለመንሽኝ›› ብሎ ካደነቃት በኋላ ቅዱስ ሚካኤልን ጠርቶ ‹‹ሳጥናኤል እሺ ካላት ታወጣው ዘንድ ወደ ሲኦል ይዘሃት ሂድ›› ብሎ አዞታል፡፡ በእዚያም እንደደረሰች ለዲያቢሎስ ልታስታርቀው እንደመጣች ነገረችው፣ እርሱ ግን እንኳን ሊመለስላት ይቅርና እርሷንም እጇን ይዞ ወደ ሲኦል ወረወራት፡፡ በዚህ ጊዜ ይጠብቃት የነበረው መልአክ በእሳት ሰይፉ ዲያብሎስን በመቅጣት እርሷን መዞ ሲያወጣት በዚህ ጊዜ በቅዱስ ሚካኤልና በእርሷም ክንፍ ተጣብቀው ዐሥር ሺህ ነፍሳት ሊወጡ ችለዋል፡፡ እርሷም በዚህ እጅግ ተደስታ ወደ ፈጣሪዋ ሄዳ ‹‹አቤቱ ፍርድህ የቀና ምሕረትህ የበዛ ነው›› እያለች ለጌትነቱ ክብር ሰግዳለች፡፡
✤✣✤
በሌላም ጊዜ ሰይጣን የሚሸነፍባቸውን ሦስት ዋና ዋና መንገዶች ለክርስቶስ ሠምራ ነገሯታል፡፡ ከዕለታት በአንደኛው ቀን እናታችን ክርስቶስ ሠምራ ዕለተ ሞቷን እያሰበች በጣና ባሕር ውስጥ ቆማ ስታለቅስና ስትጸልይ ዲያብሎስ በሊቀ ጳጳሳት ተመስሎ እጅግ አስደናቂና ግሩም በሆነ አርዓያ ወደ እርሷ መጣ፡፡ እርሷም ልትሰግድለት ወደደች፣ ከኃዘኗ ያረጋጋት ዘንድ ከቅዱሳን አንዱ የመጣ መስሏት ነበርና፡፡ ነገር ግን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ፈጥኖ ደረሰና ‹‹ይህ ሰይጣን እንጂ ጳጳስ ወይም ከቅዱሳን አንዱ አይደለምና አትስገጂለት›› ብሎ ወደኋላዋ መለሳት፡፡
#ቅድስት_ክርስቶስ_ሠምራ
እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ የትውልድ ሀገሯ ሸዋ ቡልጋ አውራጃ ልዩ ስሟ ቅዱስ ጌየ ሲሆን እግዚአብሔርን ከሚፈሩ ደጋግ ወላጆቿ ከአባተቷ ቅዱስ ደረሳኒ ከእናቷ ከቅድስት ዕሌኒ በግንቦት 12 ቀን ተወለደች፡፡ እነርሱም ቅድስት ክርስቶስ ሠምራን ከወለዱ በኋላ በደም ግባቷና በጠባይዋ እየተደሰቱ የእግዚአብሔርን ሕግጋትና ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን በማስተማር ስላሳደጓት ከልጅነቷ ጀምራ በሥነ ምግባር፣ በሃይማኖት የታነጸች በመልኳም እጅግ ውብና ያማረች ሆነች፡፡ ባደገችም ጊዜ ለአቅመ ሔዋን ስትደርስ የንጉሥ ባለሟል ለሆነ ስሙ ሠምረ ጊዮርጊስ ለተባለ ደግ ሰው በሕግ አጋቧት፡፡ ከሕግ ባሏ ከሠምረ ጊዮርጊስም ዐሥራ ሁለት ልጆችን ወለደች፡፡ ከእነዚህም መካከል አስሩ ወንዶች ሁለቱ ሴቶች ነበሩ፡፡
እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ በዐፄ #ገብረ መስቀል ዘመነ መንግሥት የነበረች ኢትዮጵያዊት ጻድቅ ስለነበረች ንጉሠ ነገሥቱ ዐፄ ገብረ መስቀል በትዳሯ፣ በሥነ ምግሯና በሃይማኖቷ በሁለመናዋ የተመሰገነች መሆኗን ዝናዋን ስለሰማ ‹‹#በጸሎትሽ አስቢኝ›› በማለት ከአገልጋዮቹ ውስጥ እርሷን እንዲያገለግሏት፣ 174 አገልጋዮቸን ላከላት፡፡ ብዙ ፈረስና በቅሎ እንዲሁም ለነገሥታት ሚስቶች የሚገባ ከሐርና ከወርቅ የተሠራ ልብስና የወርቅ ጫማም ላከላት፡፡ ነገር ግን እሷ ይህን ሁሉ ክብር አልፈለገችም ይልቁንም ‹‹ለዓላማዬ እንቅፋትና ውዳሴ ከንቱ ይሆንብኛል እንደዚሁም ወርቁ ጌጡ ተሸጦ ለነዳያን ይመጸወታል ነገር ግን እነዚህን አገልጋዮች ምን አደርጋቸዋለው?›› እያለች ወደ እግዚአብሔር አመለከተች፡፡ ከጥቂት ቀናት በኋላ የመላእክት አለቃ ቅዱስ #ሚካኤል ፊቱ እንደ ፀሐይ እያበራ ሦስት ኅብስት በእጁ ይዞ መጥቶ ‹‹የእግዚአብሔር ባለሟል ክርስቶስ ሠምራ ሆይ! እነሆ ይህን #ኅብስት ተመገቢ እግዚአብሔር በቸርነቱ ብዛት ሰጥቶሻል›› አላት፡፡ እርሷም ፈጣሪዋን አመስግና ኅብስቱን ከመልአኩ እጅ ተቀብላ ተመገበች፣ መዓዛ ጣዕሙም ሰውነቷን አለመለመው፡፡ በዚህም የተነሳ እስከ ሦስት ቀን እህል ሳትበላ ውኃ ሳትጠጣ ቆየች ኃይለ መንፈስ ቅዱስ በሰውነቷ አድሮባታልና፡፡
ከዕለታት አንድ ቀን እንዲህ ሆነ፡- ከአገልጋዮቿ መካከል አንዷ ምግባሯ የከፋ ነበርና በጣም ስላበሳጨቻት በዚያች አገልጋይ አፍ ውስጥ የእሳት ትንታግ ጨመረችባት፡፡ ያም የእሳት ትንታግ እስከ ጉሮሮዋ ዘለቀና አገልጋይዋን ገደላት፡፡ በዚህ ጊዜ ብጽዕት ክርስቶስ ሠምራ ደንግጣ ወደ ሌላ ክፍል ገባችና ኃጢአቷን ለእግዚአብሔር እየተናዘዘች እጅግ በጣም አዝና ጥፋቷ እንደ ጸጸታትና እግዚአብሔር አምላክም በእጇ የሞተችውን አገልጋይዋን ከሥጋዋ አዋሕዶ ቢያሥነሳላት ያላትን ገንዘብና ሀብት ትታ ባላት ዘመኗ ሁሉ አገልጋዩ እንደምትሆን ብጽዓት (ስዕለት) አደረገች፡፡ እግዚአብሔርም ጸሎቷን ሰምቶ አገልጋይዋን ከሞት አሥነሳለት፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ‹‹ልመናዬን ቸል ያላለ ቸርነቱንም ከእኔ ከባሪያው ያላራቀ አምላክ ይክበር ይመስገን›› ብላ በታላቅ ምስጋና እግዚአብሔርን ካመሰገነች በኋላ አስቀድማ የገባችውን ቃል አስባ ልብሰ ምንኩስናዋን አዘጋጀች፡፡ ሕፃን ልጅዋንም ይዛ ወደ ደብረ ሊባኖስ ሄደች፡፡ ስትሄድም በልስላሴና በእንክብካቤ የኖረ እግሯ ከመንገዱ ብዛት ከእንቅፋቱም የተነሳ ፈለግ ሲያወጣ ሥጋውን እየቆረጠች ስትጥለው ደሟ መሬት ለመሬት እየፈሰሰ ደብረ ሊባኖስ ገዳም ደረሰችና አስቀድማ ያዘጋጀችውን ልብሰ ምንኩስናዋን ለብሳ ከሴቶች ገዳም ገባች፡፡ ይዛው የተሰደደችውን ሕፃን ግን ወንድ ስለሆነ ከደጅ ላይ አስቀምጣው ስለገባች ሕፃኑ አምርሮ ሲያለቅስ ከመነኮሳቱ አንዲቷ ሕፃኑ ሲያለቅስ ከሚያድር ብላ ወደ በአዓቷ ልታስገባው ስትል የመላእክት አለቃ ቅዱስ ሚካኤል ነጥቆ ወስዶ በገነት አስቀመጠው፡፡ ታኅሣሥ 29 ቀን ተወልዶ በ 3 ዓመቱ ታኅሣሥ 12 ቀን ብሔረ ብፁዓን ገባ፡፡
ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ቅዱስ ሚካኤል ካለችበት በዓት አውጥቶ በክንፉ ተሸክሞ ከጣና ደሴት አደረሳት፡፡ ከዚያም ሰውነቷ ተበሳስቶ የባሕር ዓሣ መመላለሻ እስከሚሆን ድረስ እንደ ተተከለ ዓምድ ሆና ሳትወጣ ባሕሩ ውስጥ ዐሥራ ሁለት ዓመት ቆማ ስትጸልይ ኖረች፡፡ ከዐሥራ ሁለት ዓመት በኋላም ጌታችን ተገልጦላት #ቃልኪዳን ሰጥቷታል፡፡ ከዚህ በኋላ ሕይወቷን በሙሉ በታላቅ ተጋድሎ ስታሳልፍ ጌታችንም ከቅድስት እናቱ ጋር ሆኖ በየጊዜው ይጎበኛት ነበር፡፡ ቅዱስ ሚካኤልንም የሁልጊዜ ጠባቂዋ አድጎ ሰጥቷታል፡፡ እናታችን ቅድስት ክርስቶስ ሠምራ ብሔረ ብፁዓን እየሄደች ከዚያ ከሚኖሩ ቅዱሳን ጋር እስከ ሰባት ቀን ድረስ ስትነጋገር ትቆይ ነበር፡፡
#ሄኖክና #ኤልያስ ወዳሉበት ወደ ብሔረ ሕያዋንም እየሄደች ትመለስ ነበር፡፡
#ቅዱስ_ቶማስ_ዘመርዓስ_
የመርዓስ ኤጵስ ቆጶስ የነበረው አባት አባ ቶማስ ክርስቶስን በማመን በጾም፣ በጸሎት፣ በሰጊድ፣ ቀንና ሌሊት በመትጋት ለድኆችና ለምስኪኖችም በመራራት ተጠምዶ የሚኖር ነበር። በዚህ ፅናቱ የክብር ባለቤት ጌታችን መርዓስ ለሚባል አገር ኤጲስ ቆጶስ ይሆን ዘንድ መንጋውንም ይጠብቅ ዘንድ መረጠው አባታችን ቶማስም ሐዋርያዊ ተልዕኮውን እየፈፀመ፣ ሕዝቡን እየመራ ሳለ ከሀዲ ዲዮቅልጥያኖስ በሱ ላይ፣ በአጠቃላይ ሕዝበ ክርስቲያኑ ላይም ተነሳባቸው፣ ክርስቲያኖችንም ያሰቃያቸው ጀመር በአንድ ወቅት ከመኳንንቶች አንዱ የነበረው፣ ቅዱስ ቶማስን ወደ እርሱ ያቀርቡት ዘንድ ጭፍሮቹን ላከ እነርሱም እየደበደቡ በምድር ላይ እየጎተቱ ወሰዱት ደሙም እንደ ውኃ ፈሰሰ ከዚህም በኋላ መኮንኑ ቅዱስ ቶማስን ለአማልክት ስገድ አለው ቅዱሱም እንዲህ ብሎ መለሰለት «እኔ ከሕያው እግዚአብሔር ልጅ ከጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ በቀር ለረከሱ ጣኦታት አልሰግድም ለረከሱ ጣዖታት የሚሰግድ ሁሉ የተረገመ ነውና» በዚህም ጊዜ መኮንንኑ በጣም ተቆጥቶ እጅግ የበዛ ስቃይን አሰቃየው የነዳጅ ድፍድፍን አፍልተው በላዩ በአፉና በአፍንጫው እስከመጨመርም ደረሱ ልባቸው እንደ ድንጋያ የፀና ስለ ነበር ቅዱስ ቶማስን ገድለው ቶሎ ማሣረፍ አልፈለጉም ይልቁንም የስቃዩን ዘመን አስረዘሙ እንጂ እርሱም ስለ ስህተታቸው ይዘልፋቸው ነበር፣ እንደ ማይመልስም ሲገባቸው በጨለማ ቦታ ጣሉት በየዓመቱም ወደ እርሱ እየሄዱ ከሕዋሳቱ አንድ፣ አንዱን ይቆርጡ ነበር፡፡
በዚህም ለሃያ ሁለት(፳፪) ዓመት ቆየ ሲቆይ ግን አፍንጫውን፣ ከንፈሮቹን፣ ጆሮዎቹን፣ እጆቹንና እግሮቹን ቆርጠው ነበር፤ በዚህም ምክንያት የአገሬው ሰው ሞቷል ብለው አስበው በየዓመቱ መታሰቢያ ያደርጉለት ነበር ይህ ለምን ሳይሞት ቢሉ ጊዜው ሲረዝም ቢሞት ነው እንጂ እስካሁንማ ይመጣ ነበር ብለው ስላሰቡ ነበር፤ ነገር ግን ከሕዋሳቶቹ አብዛኛው ክፍል ቆርጠው ቢጥሉትም አካሉ ግን ተቆራርጦ ሲጣል አንዲት ሴት አየችው፣ ይህችም ሴት በሌሊት ወደርሱ ተሠውራ በመሔድ ትመግበው ነበር፡፡
ጻድቅ ቈስጠንጢኖስም እስከነገሠና የቀናች የክርስቶስን ሃይማኖት ክብር እስከገለጥ ድረስ እንዲህ ሲሰቃይ ኖረ፡፡
#ቈስጠንጢኖስም በነገሠ ጊዜ ስለክርስቶስ በመታመን የታሠሩ እስረኞች ሁሉ እንዲፈቱ በማዘዙ ሁሉም ተፈቱ፡፡ ቅዱስ ቶማስ ግን የተጣለበት ቦታ፤ በሕይወት ያለም ስላልመሠላቸው አላወጡትም ነበር፤ ነገር ግን ይህን አዋጅ ትመግበው የነበረችው ሴት ሰምታ ነበርና ወደ ካህናቱ ዘንድ ሄዳ ስለ ቅዱስ ቶማስ ሃያ ሁለት ዓመት በዚያ ስለመኖሩ ነገረቻቸው ቦታውንም አመለከተቻቸው እነርሱም ባገኙት ጊዜ አንስተው ተሸከሙት እየዘመሩና እያመሰገኑም ወደ ቤተ ክርስቲያን አደረሱት በቤተ መቅደስ ፊት ለፊት በወንበሩ ላይ አስቀመጡት ምእመናንም ሁሉ ወደርሱ እየመጡ ከርሱ ይባረኩና የተቆረጡ ሕዋሳቱንም ይሳለሙ ነበር፡፡ ከቦታ ቦታ ይዘዋወር የነበረውም በቅርጫት ኹኖ በዘህያ ላይ ተጭኖ ነው፡፡
✤
ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ የከበሩ ፫፻፲፰ ኤጲስ ቆጶሳትን (ሠለስቱ ምዕት) የአንድነት ጕባኤን በኒቂያ አገር በሰበሰበ ጊዜ ይህ አባት (ቅዱስ ቶማስ) ከሠለስቱ ምዕት አንዱ ነበር፤ ወደ ኒቅያ ጕባኤ በቅርጫት ሁኖ በአህያ ተጭኖ እየሄደ መሆኑን አርዮሳውያን ሲሰሙ፤ ቶማስማ በጕባኤው ከተገኘ ተከራክሮ ይረታናል አንችለውም በማለት መንገድ ላይ ባደረበት ይዘውት ይጓዙት የነበሩትን አህዮች በጨለማ በሰይፍ መተዋቸዋል፤ ነገር ግን ሌሊት ሊነጋጋ ሲል ለመንገድ ሲነሱ ቶማስ በተዓምራት አግልጋይ ረድኡን የተቆረጡትን የአህያዎቹን አንገታቸውን ከሰውነታቸው አጋጥመው ይነሳሉ ብሎ ሲያዘው የአንዱን አህያ ከሌላኛው አህያ ቢያጋጥመውም ቅሉ አህዮቹ ሕይወት አግኝተው ጕባኤ ኒቅያ አድርሰውታል፤ በዚያም አርዮስን መልስ እስኪያጣ ድረስ በጽናት ሲከራከረውና መልስ ሲያሳጠው የጕባኤው ሊቀ መንበር ንጉሥ ቈስጠንጢኖስ እስኪደነቅ ድረስ በማየቱ ሃይመኖትስ የእነ ቶማስ ዘመርዓስ ነች ብሎ አጽንቶ ወስኗል፡፡ በጕባኤውም አርዮስን ተከራክረው ከረቱ በኋላ አውግዘው ለይተውታል፤ ከዚህ በኋላ መንፈስ ቅዱስ እንዳስተማራቸውና እንደመራቸው የሃይማኖትን ትምህርት በአንደበታቸው ተናገሩ፤ ሕግና ሥርዐትን ሥጋዊና፤ መንፈሳዊ ፍርድንም ሰሩ። ቅዱስ ቶማስ ወደ መንበረ ሢመቱ ከተመለሰ በኋላ ካህናቱና መንጋዎቹን ሁሉ ሰብስቦ አነበበላቸው እርሱንም እንዲያስተውሉት እንዲጠበቁትም በመጠበቅም እንዲጸኑ አዘዛቸው፡፡ ይህ አባት ለ፵ ዓመት ያህል በሢመቱ አገልግሎ በነሐሴ ፳፬ ቀን አርፋል፡
#አቡነ_ተክለሃይማኖት
አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቡልጋ ደብረ ጽላልሽ ወይም ዞረሬ ቅዱስ ሚካኤል ቤተክርስቲያን የሰበካ ክልል ከአባታቸው ከካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብና ከእናታቸው ቅድስት እግዚእ ኃረያ መጋቢት ፳፬ ቀን ተፀንሰው፤ በ፲፩፻፺፯ ዓ.ም ታኅሣሥ ፳፬ ቀን ተወለዱ፡፡ በተወለዱ በሦስት ቀናቸው ከእናታቸው እቅፍ ወርደው«አሐዱ አብ ቅዱስ፣አሐዱ ወልድ ቅዱስ፣ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ» ብለውሥላሴ ን አመስግነዋል፡፡ ወላጆቻቸውም ፍስሐ ጽዮን አሏቸው፡፡ ትርጓሜውም የጽዮን ተድላዋ ደስታዋ ማለት ነው፡፡
በወላጅ አባታቸው በካህኑ ቅዱስ ጸጋ ዘአብ ግብረ ዲቁናን ሥርዓተ ቤተክርስቲያንን ሲያጠኑ ቆይተው በአሥራ አምስት ዓመታቸው ከ እስክንድርያው ሊቀ ጳጳስ አቡነ ቄርሎስ /ጌርሎስ/ ዲቁናን ተቀብለዋል፡፡ በዚህም ቅድስት ቤተክርስቲያንን በወጣትነት ዕድሜያቸው ሲያገለግሉ ቆይተዋል፡፡
ከዕለታት በአንዱ ቀን ጻድቁ አቡነ ተክለ ሃይማኖት ከጓደኞቻቸው ጋር ወደ ዱር አደን ሄደው ሳለ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ተገልጾ ለኢትዮጵያ ውያን ክርስቲያኖች ሐዲስ ሐዋርያ አድርጎ መረጣቸው። ስማቸውንም «ተክለ ኃሃይማኖት» አለው፡፡ ትርጓሜውም የኃይማኖት ፍሬ ማለት ነው፡፡
አባታችንም ሐዋርያዊ ጉዟቸውን ሲጀምሩ /ገድለ ተክለ ሃይማኖት ምዕ ፳፰ ቁ ፪ - ፫/ ትሕትና በተሞላበትና በተሰበረ ልብ ወደ ፈጣሪያቸው ከለመኑ በኋላ በልዩ ልዩ የኢትዮጵያ ክፍለ ሀገራት ከኃጢአት ወደ ገቢረ ጽድቅ፣ ከክህደት ወደ ሃይማኖት መልሰዋል፡፡ በዚህም የተነሣ ለኢትዮጵያውያን ብርሃን ፀሐይ ተብለዋል፡፡
#ቅዱስ ጳውሎስ በዕብራውያን ክታቡ ስለ ቅዱሳን መንፈሳዊ ተጋድሎ ሲገልፅ:-
• «እነርሱ በእምነት መንግሥታትን ድል ነሱ» /ዕብ. ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ / እንዳለ አባታችን ቅዱስ ተክለ ሃይማኖትም በመንፈሳዊ ተጋድሎ እንዲሁም በትህትና በተአምራት አላዊ የነበረውን ንጉሥ ሞቶሎሚን ወደ ክርስትና መልሰዋል፡፡
• «ጽድቅን አደረጉ» እንዳለው አባታችን ወንጌልን በተጋድሎ ሕይወታቸው ተርጉመዋል፡፡
• «የአንበሶችን አፍ ዘጉ» ምዕ ፲፩ ቁ ፴፫ /ምዕ ፲፩ ቁ ፴፬ /እንዳለው አባታችንም የአውሬውን ፥ የዘንዶውን ራስ ቀጥቅጠዋል።
• «ከሰይፍ ስለት አመለጡ» እንዳለው አባታችንም ሞቶሎሚ ከወረወረው ጦር በተአምራት ድነዋል፡፡
• «ከድካማቸው በረቱ» እንዳለው አባታችንም ያለ ዕረፍት በብዙ ተጋድሎ በጾምና በስግደት በብዙ መከራ በርትተዋል፡፡
ይህን ሁሉ ገድልና ትሩፋት እየፈጸሙ ዕረፍታቸውም በደረሰ ጊዜ ደቀመዝሙሮቻቸውን «ልጆቼ ሆይ ሁሉም መነኩሴ መንግሥተ ሰማይ ይገባል ማለት አይደለም፤ ዓለምን በሚገባ የናቀ ብቻ ይገባል እንጂ መጀመሪያ የእግዚአብሔርን ✤✣✤ጽድቁን ብቻ ፈልጉ፤✤✣✤ ጾምና ጸሎትን አዘውትሩ፤ ✤✣✤እርስ በርሳችሁ ተዋደዱ፤ ትእዛዛቱንም ✤✣✤አጥብቃችሁ ጠብቁ እያሉ ይመክሯቸው ነበር. . .» በኋላም «ለዓለም ጨው ለራሴ አልጫ ሆንኩ፤ ለዓለም ብርሃን ለራሴ ጨለማ ሆንኩ፣ ከእውነተኛው ዳኛ ከጌታዬ ፊት ስቆም ምን እመልሳለሁ?» እያሉ በፍጹም ትህትና እና በልዩ መንፈሳዊ ተመስጦ ይጸልዩ ነበር፡፡
አባታችን በዳዊት ፀሎት ከነቢያት ምስጋና ሌሊቱን ሙሉ ይተጉ ነበር በያንዳንዱ መዝሙርም 10፣ 10 ስግደትን ይሰግዱ ነበር፡፡ በሕዳር 24 ቀን ቅዱስ ሚካኤል ወደ ላይ ነጠቃቸው (አወጣቸው) ከ24ቱ ካህናተ ሰማይ ጋር 25ኛ ካህን ሆነው የሥላሴን መንበረን “አሐዱ አብ ቅዱስ አሐዱ ወልድ ቅዱስ አሐዱ ውእቱ መንፈስ ቅዱስ” በማለት አጥነዋል ፡፡ በሐይቅ 10 ዓመት በደብረዳሞ 12 ዓመት ኖረዋል፡፡ አባታችን አቡነ ተክለሃይማኖት በ1267 ዓ.ም ደብረ ሊባኖስን በአት አድርገው ኖሩ፡፡ ለ22 ዓመት ቆመው በመፀለይ የአንድ እግራቸው አገዳ ተሠበረ ደቀ መዝሙሮቻቸው በጨርቅ ጠቅልለው ቀበሩት፡፡ በአንድ እግራቸው ለ7 ዓመት በፀሎት ቆሙ በጠቅላላው ለ29 ዓመት በፀሎት ከቆሙ በኋላ በ99 ዓመት ከ10 ወር ከ10 ቀን ነሐሴ 24 ቀን 1290 ዓ.ም አረፉ አባታችን ባረፉ 54 ዓመታቸው በ1354 ዓ.ም ለአባታችን ለአቡነ #እዝቅያስ ተገልጸው አጽማቸው ከደብረ አስቦ ወደ ደብረ ሊባኖስ ግንቦት 12 ቀን እንዲፈልስ አድርገዋል ፡፡
በዚህም መሠረት ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ለእኚህ ዕረፍታቸው በእግዚአብሔር ፊት ለከበረና ብዙ ክብር ለተሰጣቸው ለጻድቁ ተክለ ሃይማኖት በየዓመቱ በነሐሴ ፳፬ ቀን በዓለ ዕረፍታቸውን በታላቅ ድምቀት ታከብራለች፡፡ እኛንም ከጻድቁ ረድኤት በረከት ይክፈለን፡፡
የቀጨኔ ደብረ ሰላም መድኀኔዓለምና ደብረ ትጉሃን ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ፍኖተ ሕይወት ሰንበት ትምህርት ቤት
8h ·
#በደብራችን በቀጨኔ ደብረ ሰላም #መድኀኔዓለም ወደብረ ትጉሃን ቅዱስ #ገብርኤል ቤተክርስቲያን ከሚነግሡት ዓመታዊ ክብረ በዓላት መካከል አንዱ ነሐሴ ፳፬ ቀን የሚከብሩት የጻድቁ አባታችን አቡነ #ተክለ_ሃይማኖት፣
የቅድስት እናታችን #ክርስቶስሠምራ እና የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ በዓለ ንግሥ ነው(ታሪኩን ከታች ይመልከቱ) ፡፡
✤✣✤
እንኳን አደረሳቹ
ነሐሴ ፳፬(24) ቀን የሦስቱም ቅዱሳን በዓለ እረፍታቸው ሲሆን በእግዚአብሔርም ፈቃድ በደብራችን ታቦታተ ሕጉን በማውጣት መከበር የተጀመረው #በ፲፱፻፹፪(1982) ዓ.ም እንደሆነ አባቶቻችን ይናገራሉ፡፡አሁንም የአባቶቻችንን ፈለግ የተከተልን እኛ ከቅዱሳኑ ረድኤት በረከት ለማግኘት በየዓመቱ በድምቀት እናከብረዋለን፡፡
ታሪከ አቡነ #ተክለሃይማኖት ወቅድስት #ክርስቶስ ሠምራ እንዲሁም አርዮስን መልስ ለመስጠት በቅርጫርት ውስጥ ተጉዞ ለሄደው እና ከ 318 ሊቃውንት አንዱ ለሆንው የቅዱስ #ቶማስ ዘመርዓስ ታራክ ወሥርዓተ ማኀሌት ፡፡
✤✣✤
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
