ch
Feedback
M.O.R East Addis Ababa Branch

M.O.R East Addis Ababa Branch

前往频道在 Telegram

East Addis Ababa Small Tax Payer Branch Office is one of many branches of Ministry of Revenues at Addis Ababa. Which are responsible for collecting revenue from customs duties and domestic taxes.

显示更多

📈 Telegram 频道 M.O.R East Addis Ababa Branch 的分析概览

频道 M.O.R East Addis Ababa Branch (@moreastaa) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 24 017 名订阅者,在 政治 类别中位列第 2 481,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 386

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 24 017 名订阅者。

根据 06 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 489,过去 24 小时变化为 37,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 30.98%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.47% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 7 440 次浏览,首日通常累积 3 716 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 6

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
East Addis Ababa Small Tax Payer Branch Office is one of many branches of Ministry of Revenues at Addis Ababa. Which are responsible for collecting revenue from customs duties and domestic taxes.

凭借高频更新(最新数据采集于 07 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 政治 类别中的关键影响点。

24 017
订阅者
+3724 小时
+1777
+48930
帖子存档
TO EAST BRANCH.xlsx0.15 KB

ወድ  ግብር  ከፋዮቻችን ገቢዎች  ሚኒስቴር  በተያዘው በጀት ዓመት  የግብር  ከፋይ ምደባ( segementation) ማድረጉ የሚታወቅ ሲሆን ስም ዝርዝራችሁ ከዚህ በታች  የተጠቀሳችሁት ግብር ከፋዮች ከሀምሌ 1/2018 ዓ.ም ጀምሮ ታክስ የምትከፍሉትም ሆነ ማንኛውንም አገልግሎት የምታገኙት አዲስ በተከፈተው መካከለኛ ግ/ከ/ ቁጥር  3 ቅ/ጽ/ቤት መሆኑን አውቃችሁ ተገቢውን ዝግጅት እንድታደርጉ ስንል በአክብሮት እናሳውቃለን፡፡  መካከለኛ ግ/ ከ/ ቁጥር 3 ቅ/ጽ/ቤት አድራሻ የቀድሞ ግሎባል ሆቴል አጠገብ መሆኑን እናሳውቃለን Dear Taxpayers, The Ministry of Revenues has conducted taxpayer segmentation during the current fiscal year. Accordingly, taxpayers whose names appear on the list below are hereby informed that, effective Hamle 1, 2018 E.C. (July 8, 2026 G.C.), all tax payments and other tax-related services will be provided through the newly established Medium Taxpayers Branch Office No. 3. We respectfully notify you of this change and request that you make the necessary preparations. Please also be informed that the Medium Taxpayers Branch Office No. 3 is located near the former Global Hotel.

4th round.xlsx0.15 KB

የተሻሻለው የታክስ አስተዳደር አዋጅ በርካታ ለውጦችን እና አማራጭ አሰራሮችን የያዘ እንደሆነ ተረጋግጧል።የአዋጁን ሙሉ ማሻሻያ በሂደት የምናደርሳችሁ ይሆናል ። የፌደራል የታክስ አስተዳደር አዋጅ ቁጥር 983/2008ን ለማሻሻል የወጣው ማሻሻያ አዋጅ በርካታ መሠረታዊ ለውጦችንና አዳዲስ አሰራሮችን ይዞ ቀርቧል። ዋና ዋናዎቹ ለውጦች የሚከተሉት ናቸው፡- 1. አዳዲስ ትርጓሜዎችና የተቋም ስም ለውጥ መስማማት (Settlement)፡ የታክስ አለመግባባቶችን በውይይትና በስምምነት ለመፍታት የሚያስችል አዲስ አሰራር በትርጓሜ ደረጃ ተካቷል። የታክስ ማጭበርበር፡ ታክስን ለመሰወር የሚደረጉ እንደ ሐሰተኛ ደረሰኝ ማቅረብና ገቢን መደበቅ ያሉ ተግባራት በዝርዝር ተተርጉመዋል። 2. የታክስ አለመግባባቶችን በመስማማት የመፍታት ሥርዓት ይህ  አዋጁ ይዞት የመጣው ትልቁ ለውጥ ሲሆን፣ ክርክሮችን በፍርድ ቤት ወይም በይግባኝ ኮሚሽን ከመጨረስ ይልቅ በባለሥልጣኑና በታክስ ከፋዩ መካከል በሚደረግ ስምምነት እንዲቋጩ የሚያስችል ነው። የአስማሚ ሚና፡ የታክስ ባለሥልጣኑ ነጻና ገለልተኛ "አስማሚ" በመመደብ ሂደቱን ያመቻቻል። ሂደቱ፡ መስማማት የሚቻለው በታክስ ውሳኔ ላይ ቅሬታ ከቀረበ በኋላ ሲሆን፣ በዚህ ወቅት ለይግባኝ የተቀመጡ የጊዜ ገደቦች ታግደው ይቆያሉ። ውጤቱ፡ የሚደረሰው ስምምነት በጽሁፍ ሆኖ በሁለቱም ወገኖች ከተፈረመ አስገዳጅና ተፈጻሚነት ይኖረዋል። 3. በአዲስ ማስረጃ አቀራረብ ላይ የተጣለ ገደብ ታክስ ከፋዮች የታክስ ውሳኔ ከተሰጠ በኋላ በቅሬታ ወይም በይግባኝ ወቅት አዲስ ማስረጃ የማቅረብ መብታቸው ተገድቧል። አዲስ ማስረጃ ተቀባይነት ሊያገኝ የሚችለው ማስረጃው የታወቀው ከውሳኔ በኋላ ከሆነ ወይም አቅም በላይ በሆነ ምክንያት ካልቀረበ ብቻ ነው።

ወደ ቅርጫፍ ፅ/ቤታችን የተቀላቀላችሁ ክቡራን ግብር ከፋዮቻችን እንኳን ደኸና መጣች!

607 የሴግመንቴሽን ምደባ.xlsx0.40 KB

ከታች ስማችሁ የተዘረዘረው ወደ ቅርጫፋችን የተቀላቀላችሁ ውድ ግብር ከፋዮቻችን በገቢዎች ሚኒስቴር የሴግመንቴሽን ምደባ መሠረት፣ ከሐምሌ 1/2018 ጀምሮ አገልግሎትና ክፍያ የምትፈጽሙት ምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅ/ፅ/ቤት መሆኑን እየገለጽን ወደ ቅ/ጽ/ቤታችን በመምጣታችሁ እንኳን ደስ አላችሁ እንላለን ። • ብሔራዊ ባንክ (NBE) የኢ-ክፍያ ሂሳብ፡- 0100191040217 • ከባንክ ወደ ባንክ ማስተላለፊያ፡- ቁጥር.0100191040194. • የአካውንት ስም፡- Ministry Of Revenues east Addis Abeba Small Tax Payers Branch Office • ለተጨማሪ መረጃ፡- መገናኛ ለም ሆቴል አካባቢ በሚገኘው ኮሜት ህንፃ አንደኛ ፎቅ የታክስ ከፋዮች ምዝገባና አገልግሎት እንዲሁም ከዘፍመሽ ወደሾላ ገበያ መብራቱን ሳይደረስ ሲቲስኩዌር ህንጻ 5ኛ ፎቅ ትምህርትና መረጃ አቅርቦት ማንኛውም መረጃና ድጋፍ ማግኘት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን በተጨማሪም በስልክ ቁጥር 0116674695 መደወል እና ማብራሪያ ማግኘት እንደምትችሉ እንገልጻለን ። በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት!

1142_የኤሌክትሮኒክ_ደረሰኝ_ሥርዓት_አስተዳደር_መመሪያ_ቁጥር_1142_2018_260701_203727.pdf5.06 KB

የበጀት ዓመቱ የሰኔ ወር ክፍል ሶስትን የሞጁላር ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ ላሉ ግብር ከፋዮች ጋር ስልጠናና ውይይት ተካሄደ ……………… ሰኔ 24 /2018 //ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት // ቅ
+6
የበጀት ዓመቱ የሰኔ ወር ክፍል ሶስትን የሞጁላር ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ ላሉ ግብር ከፋዮች ጋር ስልጠናና ውይይት ተካሄደ ……………… ሰኔ 24 /2018 //ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት // ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ግብር ከፋዮች ታክስን በፈቃደኝነት እንዲከፍሉና ሀገራዊ ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ከሚያስችላቸው መንገዶች አንዱ ሞጁላር የተሰኘውን ስልጠና ለ90 ሰዓታት በመስጠት በታክስ ምንነትና አዋጅ ደንብ መመሪያና አሰራር ዙርያ ስልጠና እዲያገኙ ማድረግ ነው ፡፡ ይህንን ተከትሎ በዛሬው እለት የበጀት ዓመቱ የሰኔ ወር ክፍል ሶስትን የሞጁላር ስልጠናቸውን እያጠናቀቁ ላሉ ግብር ከፋዮች ጋር ስልጠናና ውይይት ተካሂዷል፡፡ ወ/ሮ የሺወርቅ ተጫኔ የታክስ ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት አስተባባሪ በሴምስተሩ መጨረሻ የሚሰጠውን የታክስ አስተዳደራዊ እና የወንጀል ቅጣቶች ስልጠና ሰጥቷል ፡፡ ከዚህም ጋር ተያይዞ የታክስ ትምህርትና መረጃ አቅርቦት የስራ ሂደት አስተባባዋ በስልጠናው ዙርያ ከግብር ከፋዮቹ ጋር ውይይት ያካሄዱ ሲሆን ተለነሱ ጥያቄዎችና አስተያቶች ምላሰሽ ሰጥተዋል ፡፡

5_የታክስ_አስተዳደራዊ_እና_የወንጀል_ቅጣቶች.pptx5.75 KB

በአዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ወደ መካከለኛ ቁ3 ለሚዛወሩ ሰራተኞች የስራ አቅጣጫ ተሰጠ .......... ሰኔ 20 / 2018 ዓ.ም (ም
+2
በአዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ወደ መካከለኛ ቁ3 ለሚዛወሩ ሰራተኞች የስራ አቅጣጫ ተሰጠ .......... ሰኔ 20 / 2018 ዓ.ም (ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት የገቢዎች ሚኒስቴር ግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን ተደራሽነት ለማስፋት እንዲሁም የግብር ከፋዮችን አደረጃጀት ለማስፋት ታስቦ አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ያደርጋል ። ይህንንም ተከትሎ ወ/ሮ ወርቅዓለም ተሾመ የቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ ከቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በአዱሱ ምደባ ወደ መካከለኛ ቁጥር 3 ግብር ከፋዮች ቅርጫፍ ጽ/ቤት የተመደቡ ሰራተኞችን የስራ አቅጣጫ ሰጥተዋል። ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በጀት ዓመቱን ጭምሮ እስካሁን ባሉት ዓመታት በስኬት መጓዙን በመግለፅ የዚህ ስኬት ምንጩ ጠንካራ አመራርና ሰራተኞች መኖራቸውእንደሆነ ተናግረው በአዱሱ ምደባ ከቅርጫፍ ጽ/ቤቱ የተዛወሩ ጠንካራ ሰራተኞች መሆናቸውን በመግለጽ እንደ ገቢዎች ሚኒስቴር የተቋሙን እቅድ ለማሳካትና ሀላፊነትን በመወጣት የቅርጫፍ ጽ/ቤቱ መልካም ስም እንደሚያስጠብቁ ጽኑ እምነት እንዳላቸው በመግለጽ አደራ ሰጥተዋል፡፡ በተጨማሪም በእጃቸው ያሉትን የቅርጫፉ ስራዎችን በተናበበ እና በተደራጀ አግባብ ላሉት ባለሙያዎችና ኋላፊዎች እንዲያስረክቡ አሳስበው መልካም የስራ ጊዜ ተመኝተዋል።

ለአዳዲስ ግብር ከፋዮ በመሰረታዊ የታክስ ህግ፣ መመሪያ እና ደንቦች ዙሪያ የግማሽ ቀን ስልጠና ተሰጠ፡፡ ........................... በገቢዎች ሚኒስቴር የምስራቅ አዲስ አበባ አነስተኛ ግብር ከፋዮች ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ዛሬ ሰኔ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በቅርብ ጊዜያት ውስጥ የታክስ ከፋይ መለያ ቁጥር ላወጡ ለአዳዲስ ግብር ከፋዮች በመሰረታዊ የታክስ ህግ፣ መመሪያ እና ደንቦች ዙሪያ የግማሽ ቀን ስልጠና ሰጥቷል፡፡ የስልጠናው ዋና ዓላማ አዳዲስ ግብር ከፋዮች መሰረታዊ የታክስ ህጉን እንዲረዱ በማድረግ ካላስፈላጊ ቅጣት ማዳን ፣ግብርን በመክፈል ሀገራዊ ሀላፊነትን እንዲወጡ ማሰቻል ነው ። ስልጠናውን የሰጡት የታክስ ከፋዮች ትምህርት ከፍተኛ ባለሙያ አቶ ተስፋየ ነጋሽ ሲሆኑ በስልጠናው ላይ ለተነሱ የተለያዩ ጥያቄዎች ሰፊ ማብራሪያ እና ምላሽ ሰጥተዋል ።

የአዲስ ቲን ስልጠና.pptx6.89 KB

photo content
+7

በመሠረታዊ የታክስና ጉምሩክ ህጎች ዙሪያ  ለሰለጠኑ የዩኒቨርሲቲ ተመራቂ ተማሪዎች እውቅና ተሰጠ። ሰኔ-18 ቀን 2018 ዓ.ም | አዲስ አበባ የገቢዎች ሚኒስቴር እና የኢትዮጵያ ጉምሩክ ኮሚሽን በመሠረታዊ የታክስና ጉምሩክ ህጎች ዙሪያ  ለሶስተኛ  ጊዜ ላሰለጠኗቸው የዩኒቨርሲቲ ተመራቂዎች የማጠቃለያና የእውቅና መርሐ-ግብር አካሂደዋል። በመድረኩ ላይ የተገኙት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ አይናለም ንጉሴ ፤  ተመራቂ ተማሪዎች የነገ የሕዝብ አገልጋዬች እንደመሆናቸው የቀሰሙትን እውቀት ተጠቅመው የታክስ እና የጉምሩክ ህጎች ተገዥነትን በማረጋገጥ ረገድ  መልካም ስነ-ምግባርን በመላበስ ግንባር  ቀደም አገር ወዳድ  አምባሳደር  በመሆን  አርአያ እንዲሆኑ አሳስበዋል። በጉምሩክ ኮሚሽን የጉምሩክ የህግ ተገዢነት ዘርፍ ም/ ኮሚሽነር አቶ  እዝዘው ጫኔ በበኩላቸው፣ ተመራቂዎች የሀገሪቱን የገቢ አሰባሰብ ስርዓት የሚጎዳውን ህገ-ወጥ ንግድ እና ኮንትሮባንድን በቁርጠኝነት የመከላከል ኃላፊነት እንዳለበት  ገልጸዋል። ምክትል ኮሚሽነሩ አክለውም ፤   የታክስና ጉምሩክ ህጎችን አክብረውና አስከብረው በታክስ አማካሪነት፣ በጉምሩክ አስተላላፊነት እና በፋይናንስ ዘርፍ በብቃት በመሰማራት የታክስ አምባሳደሮች መሆን  እንደሚችሉም  አመላክተዋል። በጉምሩክ ኮሚሽን የደንበኞች ትምህርትና ድጋፍ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኚ አሰፋ በበኩላቸው፤ ተመራቂ ተማሪዎች  የህግ ተገዢነትን ከማሳደግ እና የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ስርዓት ከማዘመን ረገድ ከፍተኛ ሚና  ሊጫወቱ  እንደሚገባ  አስምረውበታል ፡፡ በመርሐ-ግብሩ የታክስ ኦፕሬሽን ዘርፍ ሚኒስትር  ዲኤታ ወ/ሮ ያስሚን ወሀቢረቢ ፣ የኢዳታ ዘርፍ ሚኒስትር  ዲኤታ  አቶ ዳዊት ውብሸት ፣ የዩኒቨርስቲ ዲኖች፥ የአዲስ አበባ ገቢዎችና ጉምሩክ  ቅርንጫፍ  ጽ/ቤቶች ተወካዮች እና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል፡፡ በፕግራሙ ማጠቃለያ ላይ ስልጠናውን  ላጠናቀቁ ተማሪዎች ፣ ለአስተባባሪዎች፣ የዩኒቨርሲቲና ኮሌጅ ዲኖች የምስክር ወረቀት፤ እንዲሁም የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የክብር ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።