ar
Feedback
M.O.R East Addis Ababa Branch

M.O.R East Addis Ababa Branch

الذهاب إلى القناة على Telegram

East Addis Ababa Small Tax Payer Branch Office is one of many branches of Ministry of Revenues at Addis Ababa. Which are responsible for collecting revenue from customs duties and domestic taxes.

إظهار المزيد

📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام M.O.R East Addis Ababa Branch

تُعد قناة M.O.R East Addis Ababa Branch (@moreastaa) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 23 645 مشتركاً، محتلاً المرتبة 2 532 في فئة السياسة والمرتبة 1 414 في منطقة Ethiopia.

📊 مؤشرات الجمهور والحراك

منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 23 645 مشتركاً.

بحسب آخر البيانات بتاريخ 14 يونيو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 314، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 1، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.

  • حالة التحقق: غير موثّقة
  • معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 33.89‎%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.16‎% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
  • وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 8 012 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 3 584 مشاهدة.
  • التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 7.

📝 الوصف وسياسة المحتوى

يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
East Addis Ababa Small Tax Payer Branch Office is one of many branches of Ministry of Revenues at Addis Ababa. Which are responsible for collecting revenue from customs duties and domestic taxes.

بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 15 يونيو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة السياسة.

23 645
المشتركون
+124 ساعات
+1227 أيام
+31430 أيام
أرشيف المشاركات
part 3

ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ በተለያዩ ዙር ያስተማራቸውን የሞጁላር ሰልጣኞችን አስመረቀ ……………… ሰኔ 5/2018 //ምስራቅ አ/አ/አነ/ግ/ከ/ቅ/ጽ/ቤት// ወ/ሮ ወርቅዓለም ተሾመ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ ለሞጁላር ሰልጣኝ ተመራዎች እንኳን ደስ አላችሁ በማለት ፕሮገራሙን የከፈቱ ሲሆን በመልዕክታቸውም የገቢዎች ሚኒስቴር ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ ለግብር ከፋዮች የታክስ ሞጁሎችን በ13 ክፍል በማደራጀት ግብር ከፋዮችን በማሰልጠን በእውቀት ላይ የተመረኮዘ የግብር አከፋፈል ስርዓትና የህግ ተገዢነት እንዲጎለብት ከፍተኛ ጥረት አድርገዋል ብለዋል ፡፡ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱም ከ2014 ጀምሮ እስከ አሁን 2763 የሞጁላር ሰልጣኞችን ማስመረቁን በመግለጽ በዛሬው እለትም 595 ግብር ከፋዮችን ማስመረቅ መቻሉን ገልጸዋል ፡፡ ሚኒስቴር መስሪቤቱም ሆነ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ከተመራቂዎች የሚጠብቀው በተማሩት የታክስ ስልጠና ባገኙት እውቀት መሰረት ያለማንም አሰገዳጅነት ህጎችን መመሪያዎችን እንዲፈጽሙ እና ሀገራችን በራሷ ገቢ የራሷን ወጪ የመሸፈን አላማ ጉዞ እንዲሳካ በመሆኑ ግብር ከፋዮቹም ከተቋሙ ጐን እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፏል፡፡ ወ/ሮ የሺወርቅ ተጫነ የታክስ ከፋዮች ትምህርና መረጃ አቅርቦት የሥራ ሂደት ሞጁላር ስልጠና ወስደው ያጠናቀቁ ግብር ከፋዮች ቅድመ ስልጠና እና ድህረ ስልጠና ያላቸውን የሕግ ተገዥነት ደረጃ እና ለገቢ ያደረጉት አስተዋጽኦ በተመለከተ ዳሰሳዊ ጥናት ሰነድ ያቀረቡ ሲሆን በጥናቱም ሰልጣኞች በተለያዩ የታክስ ገቢ አይነቶች ላይ ከፍተኛ ለውጥ እንዳላቸውና የህግ ተገዥነታቸውን ማሻሻል መቻላቸውን በጥናታቸው አመላክተዋል፡፡ ፡ በእለቱም በቀረበው ሰነድ መነሻነት አቶ ብርሃኑ ሲሳይ በገቢዎች ሚኒስቴር የታክስ ጉዳዮች ትምህርት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር እና ወ/ሮ ወርቅዓለም ተሾመ የቅ/ጽ/ቤቱ ስራ አስኪያጅ በመሆን ከተመራቂ ሰልጣኞች ጋር ውይይት አካሄደዋል፡፡ ግብር ከፋዩም የሞጅላር ስልጠናው ለታክስ ሕግ ተገዥ ለመሆን እንዳስቻላቸውእና በታክስ ስርዓቱ የንግድ ሂደታቸውን ለማቀላጠፍ ያስቻላቸው መሆኑን በመጥቀስ የሞጁላር ስልጠናው እንዲጠናከር ያላቸውን ሐሳብ ሰጥተዋል፡፡ አቶ ብርሃኑ በዛሬው እለት የሞጁላር ሰልጣኝ ተመራቂዎችን እንኳን ደስ አላችሁ በማለት የሞጁላር ስልጠና የሚሰጥበት ዓላማ ግብር ከፋዩ መብትና ግዴታውን እንዲያውቅ ላላስፈላጊ ቅጣት እንዳይጋለጥ እንዲሁም የታክስ ሕግ ማስከበር ስርዓቱን ለማጠናከር ታስቦ የሚሰጥ ስልጠና መሆኑን በመጥቀስ ግብር ከፋዩም ይህንን አውቆ ግብሩን በወቅቱ እንዲከፍልና መብቱን እንዲያስጠብቅ አሳስበዋል ፡፡ በመጨረሻም ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተመራቂዎቹ እውቅናና ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ ……..

photo content

photo content
+9

photo content
+8

photo content
+2

photo content
+9

+1
PART 1

መመሪያ_ቁጥር_1104_2017_ይመለከታል_250904_081831_2.pdf2.62 MB

የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ VAT 1341-2016.pdf12.99 MB

+1
PART 2

አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ሰኔ 03 / 2018 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር) የ2019 በጀት ዓመት የታክስ
+4
አዲሱ የግብር ከፋዮች ምደባ (tax payers’ segmentation) ከሚቀጥለው በጀት ዓመት ጀምሮ ተግባራዊ ይደረጋል ሰኔ 03 / 2018 ዓ.ም (ገቢዎች ሚኒስቴር) የ2019 በጀት ዓመት የታክስ ከፋዮች የደረጃ ምደባ ኮሚቴ ያከናወናቸውን ተግባራት አስመልክቶ ለበላይ አመራሮች ሪፖርት አቅርቧል፡፡ በዚህ ወቅት የገቢዎች ሚኒስትር ወ/ሮ ዓይናለም ንጉሴ የምደባው ዓላማ ግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት እንዲያገኙ ለማድረግ፣ የሚኒስቴር መ/ቤቱን ተደራሽነት ለማስፋት እንዲሁም የግብር ከፋዮችን አደረጃጀት ለማስፋት ታስቦ ነው ብለዋል፡፡ ይህም የጋራ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ የጎላ ሚና እንደሚኖረው የገለጹት ሚኒስትሯ ለተግባራዊነቱም የሚመለከታቸው አካላት ኃላፊነታቸውን እንዲወጡ ጠይቀዋል፡፡ የታክስ ከፋዮች የደረጃ ምደባ ኮሚቴውን ሪፖርት ያቀረቡት አቶ ደረጄ ፋና ምደባው የተካሄደው ዓለምአቀፋዊ ተሞክሮዎችን መሠረት አድርጎ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም ለግብር ከፋዮች ተገቢውን አገልግሎት በመስጠት የሚሰበሰበውን ገቢም ለማሳደግ ጉልህ ሚና እንዳለውም አብራርተዋል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የገቢዎች ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታዎች እና የቅርንጫፍ ጽ/ቤት ሥራ አስኪያጆች ተሳትፈውበታል፡፡ በሽመልስ ሲሳይ ፎቶ፡- ክፍሌ ኣዳፍሬ

2nd round list.xlsx0.15 KB

photo content

የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ ሰኔ 02 / 2018 ዓ.ም ገቢዎች ሚኒስቴር የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደ
+2
የ2019 ረቂቅ በጀት ከ2.3 ትሪሊዮን ብር በላይ ሆኖ እንዲቀርብ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ወሰነ ሰኔ 02 / 2018 ዓ.ም ገቢዎች ሚኒስቴር የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳልፏል። ምክር ቤቱ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግሥት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቷል። የ2019 የፌዴራል መንግሥት በጀት የዐሥር ዓመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማት እና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችን እና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚ እና የፊሲካል ማዕቀፍን መሠረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማኅበራዊ እና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎች እና ዓላማዎች እንዲሁም በመንግሥት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግሥትን የፋይናንስ አቅም እና አስፈጻሚ መሥሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮ እና ኃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል። በዚሁ መሠረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግሥታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2 ትሪሊዮን 339 ቢሊዮን 268 ሚሊዮን 126 ሺህ 738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሦስት መቶ ሠላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺህ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት) ብር በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል። ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግሥት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምፅ መወሰኑን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አስታውቋል። ዘገባው የኢቢሲ ነው፡፡

photo content

ሠንጠረዥ “ሀ” ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ ምጣኔዎች
ሠንጠረዥ “ሀ” ከመቀጠር በሚገኝ ገቢ ላይ ተፈጻሚ የሚሆኑ ምጣኔዎች

photo content
+1

list of 200.xlsx0.18 KB