𝕖𝕕𝕦𝕔𝕒𝕥𝕚𝕠𝕟 ️️️𝕗𝕠𝕣 𝕒𝕝𝕝 📚
前往频道在 Telegram
እንኳን ወደ ⒶⓀ 𝕖𝕕𝕦𝕔𝕒𝕥𝕚𝕠𝕟 በሰላም መጡ! 👋 ለትምህርት ማህበረሰቡ እና ለተማሪዎች የተዘጋጀ ልዩ ቻናል! 📚 ጠቃሚ መጻሕፍትና ማስታወሻዎች ❓ የፈተናና የክለሳ ጥያቄዎች 📱 ትምህርታዊ አፕሊኬሽኖችና ቻናሎች ሁሉንም በአንድ ቦታ በቀላሉ ያግኙ! አሁኑኑ ይቀላቀሉን 👇 ⒶⓀ 𝕖𝕕𝕦𝕔𝕒𝕥𝕚𝕠𝕟
显示更多4 232
订阅者
无数据24 小时
+47 天
-6330 天
帖子存档
📢 ለድኅረ ምረቃ ትምህርት ፈላጊዎች በሙሉ
የአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የድኅረ-ምረቃ ትምህርት ቤት በ2019 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በተለያዩ የትምህርት መስኮች በመደበኛው እና በተከታታይ መርሃ ግብሮች በሁለተኛ (Master’s) እና በሦስተኛ (PhD) ድግሪ ፕሮግራሞች የመመዝገቢያ መስፈርቱን የሚያሟሉ ተማሪዎችን ተቀብሎ ማስተማር ይፈልጋል።
📅 የማመልከቻ ጊዜ፡ ከሐምሌ 09 ቀን 2018 ዓ.ም እስከ መስከረም 05 ቀን 2019 ዓ.ም
🔗 የማመልከቻ ድረ-ገጽ፡ www.aastu.edu.et/Application
📌 ማሳሰቢያ፡ ማንኛውም አመልካች በዩኒቨርሲቲው ድረ-ገጽ ላይ ለዚሁ ማመልከቻ ተብሎ በተዘጋጀው ሊንክ በመጠቀም በኦንላይን (Online) ብቻ መመዝገብ ይጠበቅበታል።
ቀጣይ 12ኛ ክፍል ለምትሆኑ ተማሪዎች ፤ ኢንትራንስ ላይ ከፍተኛ ውጤት የሚያገኙ ተማሪዎች (550+) የሚያመሳስላቸው ዋና ነገሮች
1. ካሁን ከክረምት ጀምሮ የሚጠኑበት ጊዜ
ማንኛውም ተማሪ ትንሽ ሰዓት እያጠና ኢንትራንስ ላይ እንደጠቀስነው አይነት ከፍተኛ ውጤት ሊያገኝ አይችልም፡፡ ምናልባት በትንሽ ወር ውስጥ ትልቅ ውጤት አመጣን የሚሉ ተማሪዎች ሰምታቹ ሊሆን ፤ እነሱ ከመጀመሪያም ሲያጠኑ የነበረ ሲሆን፡፡ Simply ፈተናው ሲደርስ የሚያጠኑበት Intensity ነው የጨመሩት፡፡
2. ከዚህ በፊት ያላቸው መሰረት(base)
ከ 9 - 11ኛ ክፍል ጥሩ መሰረት ያላቸው ተማሪዎች ፤ እነዚህን ክፍሎች እንደአዲስ ሳይሆን revise ነው የሚያደርጉት፡፡ ይህ ትልቅ ጊዜ ይቆጥላበቸው፡፡ እነዚህ ላይ ጥሩ መሰረት የሌለው ተማሪ ፤ ጥሩ ውጤት ለማግኘት ይበልጥ መልፋት ይኖርበታል፡፡
3. ጥያቄዎችን መስራት
ማንበብ ብቻውን በቂ አይደለም ፤ ጥያቄዎችን መስራት አለባቹ በተለይ የኢንትራንስ ፈተናዎችን፡፡ ጠቀሜታው
✅ ምንን ያህል እንዳወቃቹ ታዩበታላቹ
✅ ጥያቄ ስትሰሩ ፤ ይበልጥ እንድታስታውሱ ይረዳችኃል
✅ አጠያየቃቸው ተመሳሳይ ሆኖ ትንሽ ልዩነት ያላቸው ጥያቄዎች ታገኛላቹ
4. ትክክለኛ የሆነ የጥናት እቅድ ማውጣት
እቅድ የሚያስፈልገው በሚቀራቹ ጊዜ ፤ ስታነቡ ለአንዱ ምእራፍ የምትሰጡት ጊዜ balanced እንዲሆን ነው፡፡ ለአንዱ ከልክ ያለፈ ጊዜ ፤ ሌላኛው ትንሽ ጊዜ ብቻ እንዳትሰጡ ይረዳችኃል፡፡ እንደዚህ ስታደርጉ በሳምንት ምን ያህል ምእራፍ ማንበብ እንዳለባቹ ታቃላቹ
እቅድ ስታወጡ
✅ ከ 9 - 11 revise የምታደርጉበትን ጊዜ
✅ የት/ቤት ክፍል ውስጥ የምትማሩበትን
✅ የ12ኛ ክፍል የምታነቡበትን
✅ ጥያቄ የምትሰሩበትን
ያማከለ መሆን አለበት፡፡
—————————————-——————
እነዚህ 4ቱ ዋነኛ ምክንያት ናቸው፡፡ ከዚህ ውጪ ያሉት ሁለተኛ (secondary) ናቸው፡፡ አንዳንዴ የሆነ ያህል እውነት ይኖራቸው እና በጣም የተጋነነ ነገሮች ካያቹ ከ business ጋር የተገናኘ ነው፡፡
ከላይ ካልናቸው ውጪ ፤ ውጤታቹን በትልቁ የሚቀየር ነገር የለውም፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና አዲስ ማዕቀፍ አዘጋጅቷል።
ማዕቀፉ መምህራን በክረምት ስልጠና ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የሚሸጋገሩበት መሆኑ ተገልጿል።
ሚኒስቴሩ በቀን 06/11/2018 ዓ.ም ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች በጻፈው ደብዳቤ፣ ከአጠቃላይ ትምህርት ሥርዓተ ትምህርት ለውጥ ጋር ተያይዞ ከ2012 ዓ.ም ጀምሮ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ማስገባት መቋረጡን አስታውሷል፡፡
ይሁን እንጂ በቀጣይ በአዲሱ ሥርዓተ ትምህርት መሰረት በተዘጋጀ የስልጠና ማዕቀፍ፣ በክረምት የመምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና የሚሰጥ መሆኑን ገልጿል።
በ2018 ዓ.ም የክረምት ስልጠናውን ለመስጠት ስምንት አሰልጣኝ ዩኒቨርሲቲዎች መመረጣቸውን ሚኒስቴሩ አሳውቋል።
ለክረምት ስልጠናው የተመረጡ ዩኒቨርሲቲዎች፦
1. ኮተቤ የትምህርት ዩኒቨርሲቲ
2. ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
3. ሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ
4. መቐለ ዩኒቨርሲቲ
5. ጅማ ዩኒቨርሲቲ
6. ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ
7. ጎንደር ዩኒቨርሲቲ
8. አርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ
ተቋማት እና የስልጠናው አሰጣጥ አግባብነት ከትምህርት ሚኒስቴር እስከሚገለጽ ድረስ ከላይ ከተገለፁት ዩኒቨርሲቲዎች በስተቀር በክረምት መምህራን የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና መስጠት የማይቻል መሆኑን ሚኒስቴሩ አሳስቧል።
ከ2011 ዓ.ም በፊት ስልጠና ጀምረው ያላጠናቀቁ መምህራን ከዚህ በፊት በተሰጠው ውሳኔ መሰረት እንዲያጠናቅቁ እንዲደረግ በትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ ተፈርሞ ለሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች የተላከው ደብዳቤ ይገልጻል።
ረቂቅ መመሪያው COC ሳይፈተኑ ዲግሪ ለወሰዱ ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም ተመራቂዎች የተዘጋጀ ነው። - የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ም/ዋ/ዳይሬክተር
ከመስከረም 2ዐ1ዐ ዓ.ም እስከ 2015 ዓ.ም ባለው ጊዜ ውስጥ የመውጫ ፈተና ሳይፈተኑ የመጀመሪያ፣ ሁለተኛ እና ሦስተኛ ዲግሪ የያዙ ተመራቂዎች የመውጫ (COC) ፈተና እንዲፈተኑ የሚያደርግ ረቁቅ መመሪያ በትምህርት ሚኒስቴር ተዘጋጅቷል።
በረቂቅ ማሻሻያው ላይ የትምህርት ማኅበረሰቡ እና ባለድርሻ አካላት አስተያየት እንዲሰጡበት የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን መጠየቁ ይታወቃል።
COC ሳይፈተኑ ዲግሪ የወሰዱ ከ2010 እስከ 2015 ዓ.ም ተመራቂዎች ሲባል ረቂቅ መመሪያው መዘጋጀቱን የትምህርትና ስልጠና ባለሥልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ሽሻይ አማረ (ዶ/ር) ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡
ከዲፕሎማ ወደ ዲግሪ ትምህርት ለመቀጠል የሲኦሲ ማረጋገጫ መኖር አንዱ መሠረታዊ መስፈርት ቢሆንም፣ ይህ ሳይሟላ ቀርቶ ለማረጋገጥ የተቸገሩ በመኖራቸው፣ መፍትሔ ለማግኘት ሲባል ረቂቅ ማሻሻያው መዘጋጀቱን ገልፀዋል።
ባለሥልጣኑ መመርያውን ተፈጻሚ የሚያደርጉት ባለድርሻ አካላት በመሆናቸው የሚመለከታቸው በሙሉ በረቂቁ ላይ ያላቸውን ሃሳብና ማሻሻያ እስከ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም በተዘጋጀ ድረ-ገፅ አስተያየት እንዲሰጡ መጠየቁን ጠቁመዋል፡፡
ማሻሻያው በዋናነት ለዲግሪ መግቢያ መስፈርት የተቀመጠውን የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና ሳይወስዱ በቀጥታ በዲግሪ ተምረው የተመረቁትን ወይም በዲግሪ ለመማር ከተመዘገቡ በኋላ የደረጃ አራት የብቃት ማረጋገጫ ፈተና የወሰዱትን፣ በአገር ውስጥ በሚንቀሳቀሱ ማናቸውም የመንግሥት እና የግል የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ውስጥ ያለፉ ተመራቂዎችን በሙሉ እንደሚያጠቃልል በመመሪያው ተገልጿል።
👆👆👆👆👆
📚 ተማሪዎች ሆይ ለቀጣይ አመት አሁኑኑ ጥናት ጀምሩ መጽሀፍት ለማግኘት ከኬጂ እስከ 12ኛ ክፍል መጽሐፍ ከዚህ በላይ ተለቆላችኃል።
