ውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት
前往频道在 Telegram
“ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም” ቅዱስ ያሬድ ይኽ በደብረ ይባቤ ቅዱስ ያሬድ ቤተክርስቲያን የውሉደ ያሬድ ሰንበት ትምህርት ቤት የቴሌግራም አውታር ነው፡፡ የውሉደ ያሬድ ሰንበት ት/ቤት መንፈሳዊ ጽሑፎችን፣ ወቅታዊ ኹኔታዎችን የሚገልጹ መረጃዎችን እንዲኹም ማስታወቂያዎችን በዚኽ ገጽ ለተከታታዮቹ ያስተላልፋል፡፡ መልእክት ወይም አስተያየትና ጥቆማ ካሎት ⬇️⬇️
显示更多6 055
订阅者
无数据24 小时
+37 天
-1730 天
数据加载中...
吸引订阅者
八月 '26
八月 '260
在0个频道中
七月 '26
+86
在0个频道中
Get PRO
六月 '26
+67
在0个频道中
Get PRO
五月 '26
+80
在1个频道中
Get PRO
四月 '26
+66
在0个频道中
Get PRO
三月 '26
+53
在1个频道中
Get PRO
二月 '26
+51
在0个频道中
Get PRO
一月 '26
+103
在0个频道中
Get PRO
十二月 '25
+65
在1个频道中
Get PRO
十一月 '25
+63
在0个频道中
Get PRO
十月 '25
+75
在0个频道中
Get PRO
九月 '25
+86
在0个频道中
Get PRO
八月 '25
+105
在1个频道中
Get PRO
七月 '25
+75
在0个频道中
Get PRO
六月 '25
+62
在1个频道中
Get PRO
五月 '25
+118
在0个频道中
Get PRO
四月 '25
+101
在0个频道中
Get PRO
三月 '25
+80
在2个频道中
Get PRO
二月 '25
+80
在2个频道中
Get PRO
一月 '25
+106
在0个频道中
Get PRO
十二月 '24
+161
在0个频道中
Get PRO
十一月 '24
+103
在1个频道中
Get PRO
十月 '24
+102
在0个频道中
Get PRO
九月 '24
+155
在0个频道中
Get PRO
八月 '24
+219
在1个频道中
Get PRO
七月 '24
+214
在1个频道中
Get PRO
六月 '24
+257
在0个频道中
Get PRO
五月 '24
+236
在6个频道中
Get PRO
四月 '24
+213
在3个频道中
Get PRO
三月 '24
+237
在4个频道中
Get PRO
二月 '24
+225
在2个频道中
Get PRO
一月 '24
+219
在1个频道中
Get PRO
十二月 '23
+187
在2个频道中
Get PRO
十一月 '23
+136
在3个频道中
Get PRO
十月 '23
+111
在0个频道中
Get PRO
九月 '23
+88
在0个频道中
Get PRO
八月 '23
+88
在0个频道中
Get PRO
七月 '23
+92
在0个频道中
Get PRO
六月 '23
+117
在0个频道中
Get PRO
五月 '23
+132
在0个频道中
Get PRO
四月 '23
+89
在0个频道中
Get PRO
三月 '23
+86
在0个频道中
Get PRO
二月 '23
+103
在0个频道中
Get PRO
一月 '23
+129
在0个频道中
Get PRO
十二月 '22
+160
在0个频道中
Get PRO
十一月 '22
+84
在0个频道中
Get PRO
十月 '22
+51
在0个频道中
Get PRO
九月 '22
+107
在0个频道中
Get PRO
八月 '22
+81
在0个频道中
Get PRO
七月 '22
+75
在0个频道中
Get PRO
六月 '22
+61
在0个频道中
Get PRO
五月 '22
+81
在0个频道中
Get PRO
四月 '22
+69
在0个频道中
Get PRO
三月 '22
+71
在0个频道中
Get PRO
二月 '22
+21
在0个频道中
Get PRO
一月 '22
+67
在0个频道中
Get PRO
十二月 '21
+56
在0个频道中
Get PRO
十一月 '21
+67
在0个频道中
Get PRO
十月 '21
+49
在0个频道中
Get PRO
九月 '21
+89
在0个频道中
Get PRO
八月 '21
+65
在0个频道中
Get PRO
七月 '21
+82
在0个频道中
Get PRO
六月 '21
+100
在0个频道中
Get PRO
五月 '21
+68
在0个频道中
Get PRO
四月 '21
+83
在0个频道中
Get PRO
三月 '21
+107
在0个频道中
Get PRO
二月 '21
+59
在0个频道中
Get PRO
一月 '21
+564
在0个频道中
Get PRO
十二月 '20
+6 683
在0个频道中
| 日期 | 订阅者增长 | 提及 | 频道 | |
| 01 八月 | 0 |
频道帖子
✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿
የክርስቶስን አሳብ የተረዱ ጥቂቶች ናቸው፡፡ ከእርሱ የተማሩት ከእርሱ ጋር የተነጋገሩትና እርሱን ያደመጡት እንኳ የዚህን መልካም አስተማሪያቸውን አሳብ የሚቃረን የራሳቸው የሆነ አስተሳሰብ ነበራቸው፡፡
✨✨✨🌿
ጌታችን በአንድ ወቅት ወደ ሳምራውያን መንደር በገባ ጊዜ በዚያች በኃጢአተኞች ከተማ ውስጥ የነበሩ ሰዎች ሊቀበሉት አልወደዱም፡፡ በዚህ ጊዜ ከእርሱ ጋር ከነበሩት ሐዋርያት ሁለቱ ዮሐንስና ያዕቆብ “ጌታ ሆይ ኤልያስ ደግሞ እንዳደረገ እሳት ከሰማይ ወርዶ ያጥፋቸው እንል ዘንድ ትወዳለህን?” ብለውት ነበር። ጌታ ግን ከገሰጻቸው በኋላ
“ምን ዓይነት መንፈስ እንደሆነላችሁ አታውቁም፡፡ የሰው ልጅ የሰውን ነፍስ ሊያድን እንጂ ሊያጠፋ አልመጣም” ነበር ያላቸው:: ሉቃ 9፥52-56፡፡እነዚህ ሁለት ሐዋርያት ያስቡት የነበረው አሳብ መልካሙ አስተማሪያቸው በዚያች ከተማ ውስጥ ለእርሱ የተመረጡ እንዳሉና ሊጠፉ እንደማይገባቸው ያስብ ከነበረው አስተሳሰብ ጋር የማይስማማ አሳብ ነበር፡፡ ሐዋርያቱ እንዲህ በሳምራውያን ላይ ጥላቻ በልቦናቸው እንዲያድር ያደረጋቸው ከፈሪሳውያንና ከጻፎች የሰሙት ትምህርት ነው። ጌታ ግን አሳቡ ድንቅ ስለሆነ ሳምራውያንን ወዶአቸዋል አዝኖላቸዋል። ወደ እርሱም አቅርቦአቸዋል። ስለሆነም ለተከተሉት ሕዝብ ስለ መልካሙ ሳምራዊ ነግሮአቸዋል፡፡ ያቺ ኃጢአተኛዋን ሳምራዊት ሴት ወደ ጽድቅ ለመመለስም ረዥም መንገድ በእግሩ ተጉዞአል፡፡ በዚያች በሳምራውያን ከተማ ለሚኖሩት ሰዎችም አስተምሯል፡፡ ✨✨✨🌿 ስለ አሕዛብም ቢሆን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የራሱ የሆነ ድንቅ አሳብ ነበረው፡፡ አሕዛብ በአይሁድ ዘንድ የተጠሉ ቢሆንም እንኳ ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ከአሕዛብ ወገን ስለ ነበረው ስለ ሮማዊው የመቶ አለቃ እንዲህ በማለት መስክሮአል፡፡ “እውነት እላችኋለሁ በእስራኤል እንኳ እንዲህ ያለ ትልቅ እምነት አላገኘሁም፡፡” ማቴ 8፥10። በተጨማሪም ከአሕዛብ ወገን የነበረችውን የከነናዊቷን ሴት እምነትም በማወደስ ተናግሯል። ማቴ 15፥28። ከሰዎች ጋር በሚነጋገርበት ጊዜም ሌሎች የየራሳቸው የሆነ አሳብ ቢኖራቸውም እርሱ የራሱ የሆነና ከእነርሱ የተለየ ድንቅ አሳብ ነበረው፡፡ ያቺ በፈሪሳውያን ኃጢአት ተይዛ ወደ ጌታ የመጣች ሴት ፈሪሳውያን ከበዋት ከአሁን አሁን በድንጋይ ወግረን ልንገድላት ነው እያሉ በሚያሰቡበት ሰዓት የኢየሱስ ክርስቶስ አሳብ ከእነርሱ ፍጹም የተለየ ነበር፡፡ ስለሆነም “ከእናንተ ኃጢአት የሌለበት አስቀድሞ በድንጋይ ይውገራት” አላቸው፡፡ ዮሐ 8፥7። በዚህ ጊዜ ሁሉም ሹልክ እያሉ ሄዱ፡፡ እርሱም “እኔም አልፈርድብሽም ሂጂ፤ ከአሁንም ጀምሮ ደግመሽ ኃጢአት አትሥሪ አላት፡፡ ዮሐ 8፥11። ✨✨✨🌿 ይህ ጨካኝና ስለ ውጪው ብቻ የሚጨነቅ ዓለም እርሱን ትቶ የእርሱን ሥራ እየተመለከተ ሲደነቅ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሰውን ሁሉ ከሚወድ ልቦናው ጋር ብቻውን ነበር፡፡ ይህንንም ከሚከተለው ከሁለቱ ዓይነ ስውራንና ወደ ጌታ ከመጡት ሕፃናት ታሪክ በግልጽ መረዳት ይቻላል። አንድ ጊዜ ጌታ ከኢያሪኮ ሲወጣ ሁለት ዓይነ ሥውራን በመንገድ ዳር ተቀምጠው ይለምኑ ነበር፡፡ የሚያልፈው ኢየሱስ ክርስቶስ መሆኑን በሰሙ ጊዜም “ጌታ ሆይ የዳዊት ልጅ ማረን” ብለው ጮኹ፡፡ በዚህ ጊዜ ከምድራዊ አስተሳሰቡ ጋር ይጋፋ የነበረው ሕዝብ ጩኸታቸው የክብርን አምላክ የሚረብሸው መስሎ ስለታያቸው ዓይነ ሥውራኑ ዝም እንዲሉ ገሰጹአቸው:: ርኅራኄ የባሕርይ ገንዘቡ የሆነው ኢየሱስ ክርስቶስ ግን ጠራቸውና ዓይኖቻቸውን አበራላቸው፡፡ ማቴ 20፥29-34፡፡ ጩኸታቸውና ልመናቸው ሌሎችን ያበሳጫቸውን ያህል እርሱን አላስቆጨውም፡፡ በሌላ ጊዜም ሕፃናት ወደ እርሱ መጥተው በከበቡት ጊዜ የዚሁ ዓይነት ተመሳሳይ ሁኔታ ተፈጥሮአል፡፡ ደቀ መዛሙርቱ እርሱ የሚቆጣ ስለመሰላቸው ሕፃናቱን ገስጸዋቸዋል፡፡ ጌታ ግን “ሕፃናትን ተዉአቸው ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሉአቸው፡፡ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉት ናትና' አላቸው፡፡ ማቴ 19፥14፡፡ 📖የነፍስ አርነት 📝አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ 📝አያሌው ዘኢየሱስ እንደተረጎመው ✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿✨✨✨🌿🌿
| 2 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለታላቁ አባት ሰው ቢረሳ ቢረሳ ምግቡን አይረሳምና በእንተ (ስለ) #አባ አቢብ ብሎ በሚመገብ ጊዜ ስብሐት ብሎ ያሰበውን እምርልሃለሁ ብሎ ታላቅ ቃል ኪዳንን #መድኃኔዓለም ለሰጣቸው፤ የጌታችንን መከራ መስቀሉን በማሰብ ራሳቸውን ሰባት ጊዜ ለገደሉ ለታላቁና ክቡር ለሆኑ #አባ አቢብ ለተባሉት ለመስተጋድል #አባ ቡላ፣ #አክሚም ከሚባል አገር የመላእክት አምሳል ለሆነ #ለአባ እብሎኝ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአባ አቢብ ማኅበር ከሆኑ #ዐሥር ሺህ አርባ ሦስት ወንዶችና ሦስት መቶ ሰባት ሴቶች ሰማዕታትና #ከሰማዕቱ ከቅዱስ ዮልዮስ ከሥጋው ፍልሰትና ቤተ ክርስቲያኑ ከከበረችበት ዕለት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 308 |
| 3 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ከደቡብዊ_ግብጽ ከታችኛው ምድር አውራጃ ከንሒሳ ከተማ ለሆነ #ለቅዱስ_ለአባ_ኖብ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕፍቱ በዓል፣ #ለአባቶች ሊቃነ ጳጳሳት አርባ ሁለተኛ ለሆነ #ለእስክንድርያ_ሊቀ_ጳጳሳት #ለቅዱስ አባት #ለአባ_ስምዖን_ለዕረፍት በዓሉ መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን። በተጨማሪ በዚህች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከአንድ_መቶ_ዘጠና_ሽህ_ሰማንያ አራት #ከአባ_ኖብ_ማኅበር_ከሰማዕታት እና ከሌሎች ማኅበሮቻቸው ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 468 |
| 4 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለታላቋ_ሰማዕት ሰይጣንን በራሱ ጠጉር ይዛ ለደበደበችው በእግሮቿም ለረገጠችው #ለቅድስት_መሪና_ለዕረፍት_በዓል፣ #ከቀጰዶቅያ አገር ለሆነ በመስቀል ላይ ጌታችንን ከሞተ በኋላ የቀኝ ጎኑን ለወጋው #ለቅዱስ_ለንጊኖስ_ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚህች ቀን ከሚታሰበው፦ #ከአብጥልማዎስ ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 541 |
| 5 | ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
“ጸሎት ማለት ሰው ከልዑል እግዚአብሔር ጋር የሚነጋገርባት ነገር ናት” ፍ.ነገስት ፲ወ፬
✨ ሳምንታዊ የጸሎት መርሐ ግብር ✨
🗓 ዛሬ
🕕ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤታችን አዳራሽ
ሁላችኹም ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ እንድትቋደሱ ተጋብዛችኋል!
✨"ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም"
ቅዱስ ያሬድ✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨ | 634 |
| 6 | ✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯
ሐምሌ ፳፪ በዚህች ቀን ቅዱስ ዑራኤል ቅዳሴ ቤቱ የሚከበርበትና ለነቢዩ ዕዝራ ሱቱኤል የዕውቀትን ጽዋ ያጠጣበት ዕለት ነው፡፡
የከበረ ቅዱስ ዑራኤል ተረዳኢነቱ አይለየን
✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯✨🕯 | 568 |
| 7 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለሊቀ_መላእክት_ለቅዱስ_ዑራኤል #ለቅዱስ_ዕዝራ_ሱቱኤልየዕውቀት ፅዋ ላጠጣበት ፤ #ለቅዳሴ_ቤቱ_ዓመታዊ_በዓ ል፣ ለፋሲለደስ ልጅ #ለቅዱስ_መቃርስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል መታሰቢያ፣ #ለቅዱስ_ለውንትዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦# ከቅዱስ_መርካሎስ_ከመታሰቢያው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 553 |
| 8 | ✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
ሳምንታዊው የማክሰኞ ጉባኤ
🗓 ዛሬ
🕕ከ12:00 ሰዓት ጀምሮ በሰንበት ት/ቤታችን አዳራሽ
ሁላችኹም ከዚህ መልካም መዓድ ከምሽቱ 12:00 ጀምሮ እንድትቋደሱ ተጋብዛችኋል!
✨"ጽዮንን የሚወዳት አይደክምም"
ቅዱስ ያሬድ✨
✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨🌿✨ | 689 |
| 9 | ☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️☀️
"እናቴ ሆይ ነፍሴ በአንቺ ዘንድ ትክበር። ስለ ቸርነትሽ እናቴ ነሽ ፤ ስለ ንግሥትነትሽም እመቤቴ ነሽ ፤ ስለ ልጅሽ የመድኃኒት ቀንድ ሆይ አስቢኝ ፤ እንደ ወደቅሁ እቀር ዘንድ አትርሽኝ"
✨አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ✨
🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜🔱⚜ | 661 |
| 10 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለኢትዮጵያውያን_ጻድቃን ለአባታች ለከፋሌ ባሕር #ለአቡነ_ኤዎስጣቴዎስ_ለልደት_በዓል ለአባታች #ለአቡነ_በጸሎተ_ሚካኤል_ለዕረፍት በዐል፣ ደግ ለሆነ በጎ ምግባር ላለው ምፅዋት መስጠትም ለሚወድ መግሥቱን ትቶ ለመነነው ለአፄ ናዖድ የልጅ ልጅ ለቅድስት ለሮማነ ወርቅ ልጅ ለንጉሥ #ቅዱስ_ላእከ_ማርያም_ለዕረፍት በዐል፣ እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በጤና አደረሰን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 622 |
| 11 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን#ለእናታችን_ለእመቤታችን_ለቅድስት_ድንግል ማርያም ከተወለደች በኋላ #በሰማንያ_ቀን_ርግብ_ገላግልቶች_ጋር_ወደ #መቅደስ_ለተወሰደችበት_ቀን_መታሰቢያ_በዓልና ለታላቁና ለክቡር ለሆነ ለሠራዊት አለቃ #ለሰማዕቱ_ለቅዱስ_ቴዎድሮስ_ለዕረፍት_በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከታአኪጦስ፣ ከእስክንድርያው ሊቀ ጳጳሳት #ከቅዱስ_ጢሞቴዎስ_ከሙሴ ከመታሰቢያቸው፣ #ከሕፃኑ_ከቅዱስ_ቂርቆስ ከእናቱ ቅድስት ኢየሉጣ ጋር በሰማዕትነት ከአረፉ #ከአራት_መቶ_አራት_ሰማዕታት_ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 705 |
| 12 | 📣መልእክተ ብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን!
"ገባሬ ሣህል እግዚአብሔር፥ ወይፈትህ ለኩሉ ግፉዓን፦
እግዚአብሔር ይቅርታ አድራጊ ነው፤ ለተበደሉ ሁሉ ይፈርዳል።"
መዝሙር ፻፪፥፮
ከሁሉ በማስቀደም በሀገር ውስጥ እና በመላው ዓለም የምትኖሩ ኦርቶዶክሳውያን የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችንን ሐምሌ 19 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በከፍተኛ መንፈሳዊ ሥነ ሥርዓት ለሚከበረው፤ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተልኮ በእምነታቸው የጸኑትን ቅዱስ ቂርቆስንና ቅድስት ኢየሉጣን በመከራቸው መካከል እየተራዳ የእሳቱን ነበልባል እንደክረምት ውኃ ላቀዘቀዘበት፤ በእግዚአብሔር ቃል ኪዳን የታመኑትንም እስከ ሰማዕትነት ፍጻሜ ድረስ የሚያጸና መሆኑን ለምንዘክርበት ታላቅ በዓል እንኳን አደረሳችሁ ለማለት እንወዳለን።
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዘመነ ሐዋርያት ጀምሮ የወንጌልን ብርሃን በማብራት፣ የሰላምን መንገድ በማስተማር፣ ፍትሕን በማጽናት፣ የተጨነቁትንም በማጽናናት፣ ሕዝብንና ሀገርን እየደገፈች የኖረች ናት።
በዚህ ቅዱስ ተልእኮ ውስጥም መናንያን መነኮሳት እና መነኮሳይያት ዓለምንና ከዓለም የሚገኘውን ጊዜያዊ ክብር፣ ጥቅም፣ ምቾትና የመሳሰሉትን በፈቃዳቸው ትተው፤ በየገዳማቱ በበአታቸው በጾም፣ በጸሎት ተወስነው፤ ሕይወታቸውን በትሕትና ለእግዚአብሔር በመስጠት፤ ስለ ራሳቸው ብቻ ሳይሆን ስለ ሀገር፣ ስለ ሕዝብ፣ ስለ ሰላምና ስለ ዓለም ደኅንነት በመዓልትና በሌሊት የሚጸልዩ የምድራችን በረከቶች ናቸው።
መስቀልን በተሸከሙ፣ ጸሎትን መከታ ባደረጉ፣ ለፍጥረት ሁሉ ምሕረትን በሚለምኑ፣ ራሳቸውን ለመከላከልም ምንም ዓይነት ቁሳዊ ዝግጅት በሌላቸው በእነዚህ መናንያን ላይ እጅን ማንሣት በእግዚአብሔር ዘንድ የተከለከለ፣ በታሪክ ፊትም የሚያሳፍር ድርጊት ነው።
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን!
በደቡብ ወሎ ሀገረ ስብከት በቦረና ወረዳ በግዮን አባይ ገዳመ አስቄጥስ ቅድስት አርሴማ፣ አቡነ አረጋዊና ቅዱስ ቂርቆስ የአባቶችና የእናቶች አንድነት ገዳም ሐምሌ 15 ቀን 2018 ዓመተ ምሕረት በተፈጸመው ጥቃት የመናንያን መነኮሳይያት ሕይወት በግፍ መጥፋቱን፤ በርካቶች መቁሰላቸውን፤ በገዳሙና በንዋየ ቅድሳቱ ውድመት መድረሱን ከሀገረ ስብከቱ መግለጫ በከፍተኛ ሐዘን የሰማን ሲሆን፤ በተመሳሳይም በዚሁ ዕለት በሀድያና ስልጤ ሀገረ ስብከት የአምልኮ ሥፍራ በኃይል መፍረሱና በምእመናን ላይ ጥቃት መድረሱ የሚያሳዝንና በፍጹም ተቀባይነት የሌለው የተወገዘ ተግባር ነው።
በመሆኑም የጸሎት፣ የትምህርት፣ የሰላምና የመንፈሳዊ እሴት ማዕከል የሆኑትን ገዳማት መጠበቅ የአንድ ሃይማኖት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን፣ የሰው ልጅ ክብርን፣ የሕግ የበላይነትንና የሀገር ሰላምን የማስጠበቅ ሓላፊነት ያላቸው በየደረጃው የሚገኙ ባለሥልጣናትና የሕግ አስከባሪ አካላት ጭምር እንደመሆኑ አሰቃቂ ጥቃት የፈጸሙት ተጠያቂዎች ለፍትሕ እንዲቀርቡ፤ ሌሎች ገዳማትና አድባራት ደኅንነታቸው እንዲጠበቅልን፤ ለተጎዱትም ተገቢው ድጋፍ እንዲደረግልን ዛሬም አበክረን እንጠይቃለን ።
በመጨረሻም ሕዝበ ክርስቲያንና መላው ኢትዮጵያውያን የጥቃት ሰለባ ከሆኑት ወገኖች ጋር በመንፈሳዊም ሆነ በሰብአዊ ድጋፍ አብራችሁ እንድትቆሙ ከአደራ ጭምር እያሳሰብን፤ በጽድቅ የሚፈርደው እግዚአብሔር አምላካችን ለተበደሉት ፍትሕን፣ ለቆሰሉት ፈውስን፣ በግፍ ሕይወታቸውን ለተነጠቁት ዕረፍተ ነፍስን፣ ለቤተ ክርስቲያናችንና ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይስጥልን እያልን አባታዊ መልእክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን።
እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!!
አሜን።
አባ ማትያስ ቀዳማዊ
ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት
ሐምሌ 18 ቀን 2018 ዓ.ም.
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
© የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት | 722 |
| 13 | 没有文字... | 742 |
| 14 | ወርቅና ብር በእሳት ተፈትነው እንደሚጠሩ ቅዱሳን ሰማዕታትም በመከራ ውስጥ ተፈትነው እግዚአብሔርን አስደስተው ለእኛም የጽናት ምልክት ሆነው የክብር አክሊልን በመቀዳጀት ከገቡ መውጣት፣ ካገኙ ማጣት እና መከራ ወደ ሌለበት ዘለዓለማዊ ማረፊያቸው ይሄዳሉ፡፡
ቅዱሳን ሰማዕታት በመከራ ነፍስ ከመፈተን በመከራ ሥጋ መፈተንን መርጠው፣ ነፍሳቸውን በእሳተ ገሃነም ከመፈተን በምድራዊው ሰው ሠራሹ እሳት ውስጥ ሥጋቸውን ሳይሰቅቁ በመጨመር በመፈተን ዘለዓማዊ ዕረፍት ማግኘትን መርጠዋል፡፡
ሰው በባሕርዩ እንዲራባ በክፉ ግብር የሚራቡ አጋንንት እያደሩባቸው ዓላውያን ነገሥታት ቅዱሳን ሰማዕታት ላይ በጠላትነት እየተነሡ ያልፈፀሙት ክፉ ሥራ የለም፡፡ በሐምሌ ፲፱ ቀን የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነትን ያገኙት ልጅ እና እናት ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣም ስለ ንጽሕት ሃይማኖታቸው ለመመስከር ፈተናቸው የመጣውም ከዓላውያን ነገሥታት አንዱ በሆነው በእለ እስክንድሮስ ነው፡፡
ይህ ከሓዲ መኮንን ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስን ይዞ ‹‹ስምህ ማነው›› ብሎ በጠየቀው ጊዜ ‹‹ነቅዕ ዘእምዐዘቅት ንጸሕ ወእማይ ዘኢይማስን ክርስቲያን ስምየ፤ ከንጹሕ ዐዘቅትና ከማይለወጥ ከማይጠፋ ውኃ የተገኘ ስሜ ክርስቲያን ነው›› በማለት መልሶለታል፡፡
ሹሙ እለ እስክንድሮስ በቅዱስ ቂርቆስና በቅድስት ኢየሉጣ ብዛት ያላቸውን መከራ አድርሶም ስላልረካ ጭፍሮቹን በብረት ጋን ውስጥ ሰም፣ ጨው፣ ባሩድ፣ ሙጫ፣ የዶሮ ማር እና እርሳስ ብረትን በማስጨመር ሊያሠቃያቸው ፈለገ፡፡ ከጋኑ የሚወጣው ድምፅም እንደ ነጎድጓድ የሚሰማና ወላፈኑም እንደ ፀሐይ የሚያንጸባርቅ ነበር፡፡
ይህ የጋኑ ፍላት ግርማው እጅግ ያስፈራ ነበርና ቅድስት ኢየሉጣ ተሸበረች፡፡ ልጇ ቅዱስ ቂርቆስ ግን ይህን ፍርሃት ለማራቅ እግዚአብሔር ከእነርሱ በፊት በነበሩት ቅዱሳን በአናንያ፣ በአዛርያ እና በሚሳኤል፣ በሶስና እና በዳንኤል ሕይወት ሥራ ውስጥ የነበረውን የማዳን ችሎታ (ከሃሊነት) እያነሣ ሊያበረታት ሞከረ፡፡ ‹‹እናቴ ሆይ፥ ከሚያልፈው ዓለም ጭንቅና መከራ ለማምለጥ ስትዪ በማያልፈው ዘለዓለማዊ እሳት መቀጣት አይገባሽምና ጽኚ›› አላት፡፡ እንዲሁም ዓይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ ወደ እግዚአብሔር እጅግ ልብን የሚነካ ጸሎት አደረሰ፡፡
‹‹ባርያህ የሆነች እናቴ የሌለችበት ለእኔ ያዘጋጀሃት ርስት ውስጥ ከምገባ ከሕይወት መጽሐፍ ፋቀኝ፤ እርሻውን ልታቃጥል ፍሬውን ልትባርክ፣ ዕንጨቱን ቁረጡና አንድዱት፤ ቅጠሉን ጠብቁት፤ ልትል አይገባም፤ ጠላት ዲያብሎስ የአንተ የሆነውን ቅዱሳኑን ድል ነሳኋቸው ብሎ እንዳይመካና ከመንጋውም አንድ በግ ቀማሁ እንዳይል አቤቱ የኃይል መንፈስ ለእናቴ በመስጠት አበርታት›› በማለት ጸለየ ፡፡ የዚህ ሕፃን ሲሆን በመንግሥተ ሰማያት ለእናቱ አባት የሆነ ቅዱስ ጸሎት ከእግዚአብሔር ደርሶ እናቱን አጽንቶ ጭራሽ የብረት ጋኑን ውኃ በምንጭ ላይ በዝቶ እንደሚወርድ ጠል ሁኖ አሳያት፤ ወዲያውም ሁለቱንም ከብረት ጋን ውስጥ ጨመሯቸው፡፡
እሳቱ ዓርባ ክንድ ወደላይ ተመዝዞ ወጥቷል (ወተለዓለ ነበልባል መጠነ አርብዓ በእመት) ፣ የሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት አምላክም ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤልን ከሰማይ ልኮ በብርሃን በትር ቢመታው እንዳደረ ውርጭ ሆኗል፡፡ የብረት ጋኑም እሳት ጠፍቶ አንዳች ሳይጎዱ ምስክርነታቸውን ፈፀሙ፡፡ በዚህም አስቀድሞ ቅዱስ ዳዊት በመዝሙሩ የዘመረው ቃል ተፈፀመ፡፡ ይህም፡- ‹‹አኅለፍከነ ማዕከለ እሳት ወማይ፤ በእሳትና በውኃ መካከል አሳለፍኸን፡፡›› በቀደመ ግብሩ እሳት የነበረ በኋላ ግብሩ ውኃ ሆነ፡፡ (መዝ.፷፭፥፲፪)
ቃሉ የማይታበል ልዑል እግዚአብሔር አስቀድሞ በነቢየ ልዑል ቅዱስ ኢሳይያስ የተናገረውን ቃልም በሁለቱ ቅዱሳን ሰማዕታት ተፈፅሞ አገኘነው፡፡ ‹‹ወእመኒ ዐደውከ ማየ አነ: ሀሎኩ ምስሌከ: ወአፍላግኒ ኢያሰጥሙከ ወእመኒ ዐደውከ እሳተ ነበልባል ኢያውዕየከ፤ በውኃ ውስጥ ባለፍህ ጊዜ ከአንተ ጋር እሆናለሁ፤ በወንዞችም ውስጥ ባለፍህ ጊዜ አያሰጥሙህም፤ በእሳትም ውስጥ በሄድህ ጊዜ አትቃጠልም፤ ነበልባሉም አይፈጅህም፡፡›› (ኢሳ.፵፪፥፪)
እኛ እንደነ ቅዱስ ቂርቆስ እና ቅድስት ኢየሉጣ ከእሳት እና ከፈላ ውኃ ውስጥ ጨክኖ በመግባት በእምነት መውጣት የምንችልበት አቅምም ሆነ የጸሎት ኃይል ባይኖረንም በልባችን ጋን ውስጥ እየነደደ ለሀገራችን ኢትዮጵያም የተረፈው በፍቅርና በአንድነት እንዳንኖር ያስቸገረንን ክፉ እሳት አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ እንዲያጠፋልን መለመን ይገባል፡፡ ለዚህም የአምላካችን ልዑል እግዚአብሔር ቸርነት፣ የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት አይለየን!
ምንጭ ፡-
• መጽሐፍ ቅዱስ
• ድርሳነ ቅዱስ ገብርኤል ዘሐምሌ
• የመዝሙረ ዳዊት ትርጓሜ
• መጽሐፈ ስንክሳር
• መልክአ ሥላሴ
© ማኅበረ ቅዱሳን
✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐 | 1 037 |
| 15 | ✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐✨✨✨💐💐
‹‹በእሳትና በውኃ መኻከል አሳለፍኸን›› (መዝ.፷፭፥፲፪)
ሥራው ግሩም የሆነ አምላካችን እግዚአብሔር ማዳንም መግደልም የሚችል የባሕርይ አምላክ ነው፡፡ (መዝ.፷፭፥፫) በእርሱ የሚታመኑት ቅዱሳን ሰማዕታት የሚደርስባቸውን መከራና ፈተና ሁሉ በጽናት፣ በልበ ሙሉነት የሚያልፉት ለዚህ ነው፡፡
እሳት ለቅዱሳን ሰማዕታት ጌጣቸው ነው፡፡ በመልክአ ሥላሴ ‹‹የሰማይ ግምጃ ብርሃን ሸማኖች የሆናችሁ ሥላሴ ሆይ ልብሰ ምሕረታችሁ የሰማዕትነት ልብስን ይሁነኝ፤ የእስጢፋኖስ ልብስ ደንጊያ በእኔ ላይ የለምና፤ የሕፃኑ ቂርቆስ ጌጡ የሚሆን እሳትም በእኔ ላይ የለምና›› ብለን የምንጸልየውም ለዚህ ነው፡፡ (መልክአ ሥላሴ፡- ለአትያጺክሙ) | 666 |
| 16 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿
እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ለነበረው ለጌታችን ወንድም ለሚባለው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ያዕቆብ_ለዕረፍት በዓል፣ ከቁልዝም ከተማ ለሆነ በከሀዲው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለቅዱስ_አትናቴዎስ_ለዕረፍት_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በፍቅር አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከእንዱራናና_ከጦቢያ፣ #ከኤስድሮስ_ማኅበር_ከዘጠኝ_ሽህ ጭፍሮችና #ከመኰንኑ_ከእንድራኒቆስና ከሠራዊቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿 | 658 |
| 17 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿
እንኳን #ከሰባ_ሁለቱ_አርድእት አንዱ ለሆነው ለኢየሩሳሌም ኤጲስቆጶስ ለነበረው ለጌታችን ወንድም ለሚባለው #ለሐዋርያው_ለቅዱስ_ያዕቆብ_ለዕረፍት በዓል፣ ከቁልዝም ከተማ ለሆነ በከሀዲው በዲዮቅልጥያኖስ ዘመን ሰማዕትነት ለተቀበለ #ለቅዱስ_አትናቴዎስ_ለዕረፍት_በዓል እግዚአብሔር አምላክ በሰላምና በፍቅር አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከእንዱራናና_ከጦቢያ፣ #ከኤስድሮስ_ማኅበር_ከዘጠኝ_ሽህ ጭፍሮችና #ከመኰንኑ_ከእንድራኒቆስና ከሠራዊቱ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿 | 803 |
| 18 | ✨✨✨🍂✨🍂✨🍂
ኃጥእ በደለኛ ነህን? ተስፋ አትቁረጥ! ወደ ቤተክርስቲያን መጥተህም ንስሓ ግባ፡፡ ኃጢአት ሠርተሃልን? እግዚአብሔርን “በድያለሁ” በለው፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለመናዘዝ የሚጠይቅህ ድካምና ጥረት እንደ ምን ያለ ነው? “በድያለሁ [ይቅር በለኝ]” ለማለት የሚጠይቅህ ዓይነት የሕይወት መንገድ ወይም እንደ ምን ያለ መከራ ነው? “በድያለሁ” ብሎ አንዲት ቃል ለመናገር ክብደቱ ምኑ ላይ ነው? ምናልባት ኃጥእ ነኝ ብለህ ራስህን ባትጠራ፥ ዲያብሎስ በዚህ እንደማይነቅፍህ አስበህ ነውን?
✨✨🍂
በፍጹም! እንዲያውም ንስሓ ባትገባ ይህን ከዲያብሎስ የሚመጣ ነቀፋ እንደሚኖር ጠብቅ፡፡ የከሳሽ ግብሩ ንስሓ እንዳትገባ መከልከል በዚያ ንስሓ ባልገባህበት በደልም አንተን መውቀስ ነውና ንስሓ ባትገባ ይህን ጠብቅ፡፡ ስለዚህ ለቅጽበት ያህልስ እንኳን የማይተኛ ከሳሽ እንዳለህ ዐውቀህ ለምን እንዳይወቅስህ አትከለክለውም? ለምን በደልህን ተናዝዘሃት አታስወግዳትም?
✨✨🍂
ኃጢአት ሠርተሃልን? ወደ ቤተ ክርስቲያን ና፡፡ “በድያለሁ” ብለህ ለእግዚአብሔር ንገረው፡፡ እኔ ከዚህ ውጪ ከአንተ የምፈልገው ሌላ ምንም ነገር የለኝም፡፡ መጽሐፍ ሲናገር፡- “ትከብር ዘንድ አንተ አስቀድመህ ኃጢአትህን ተናገር” ይላል (ኢሳ.43፡26)፡፡
ስለዚህ ኃጢአትህን ታስወግዳት ዘንድ ተናዘዛት፡፡ ይህን ለማድረግ ድካም ጥረት አይጠይቅህም፡፡ አንደበተ ርቱዕ መኾን አያሻህም፡፡ ገንዘብ መክፈል አያስፈልግህም፡፡ ወይም እነዚህን የመሰሉ ሌሎች ነገሮች አያስፈልጉህም። አስቀድመህ በደልህን በሰቂለ ሕሊና በነቂሐ ልቡና ኾነህ አስባትና አንዲት ቃል ተናገር፡- “በድያለሁ” ብለህ ተናዘዛት፡፡
✨ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ "ንስሐና ምጽዋት"
📚ገጽ 28
📖በገብረ እግዚአብሔር ኪደ የተተረጎመ
✨✨✨🍂✨🍂✨🍂 | 818 |
| 19 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿
እንኳን #ለየዋሁ_ነቢይ_ለቅዱስ_ዮናስ_ከዓሣ_ዐንበሪ_ሆድ ውስጥ ለወጣበት ቀን መታሰቢያ በዓልና #ለቅድስት_አውፎምያ_ሰማዕትነት_ለተቀበለችበት ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ #ከቅዱሳን_ኤስድሮስና #ከሰማዕቱ_ቤዱል፣ #ከዘካርያስና_ከአውልያን_ከዐይነ_ፀሐይ ከመታሰቢያቸው #ከቅዱስ_ሰማዕት_ከዮስጦስም_ዐፅሙ_ከተገኘበት እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿 | 720 |
| 20 | 🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁
እንኳን #ለቅዱስ_አባት_ወንጌሉ_ዘወርቅ ለተባለ ልክ እንደ ገብረ ክርስቶስ በእናት አባቱ ቤት እንደ ነዳይ ሆኖ ለተጋደለ #ለአባ_ዮሐንስ_ለዕረፍት_በዐል በሰላም አደረሰን።
🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁🌿🍁 | 883 |
