217
المشتركون
-124 ساعات
لا توجد بيانات7 أيام
-1030 أيام
أرشيف المشاركات
አባ ገብረ ኪዳን ግርማ Said✨እመቤታችን ያለችበት ቤት ሁሉ ደስታ ይሞላዋል አጥተው የከፋቹው ሁሉ አግኝተው ደስ ይላቸዋል🤍
ለምን??የበረከት ምንጭ ነችና🤌💘
✨"ስለ ሌላው ሰው ከመፍረድህ በፊት፣ በእርሱ ጫማ ውስጥ ገብተህ ለመራመድ ሞክር። ያኔ መፍረድ ትተህ መጸለይ ትጀምራለህ።"🤍
✞ አባ ሙሴ ጸሊም 🤎ደህና እደሩልኝ አበባዎቼ💘
አቤቱ፥ ወደ አንተ እጠራለሁ፤ ዝም ብትለኝ ወደ ጓድጓድ እንደሚወርዱት እንዳልመስል፥ አንተ አምላኬ፥ ዝም አትበለኝ።
መዝ27:1
መልካም ቀን ✨🫶🏻ግንቦት 21 ደብረ ምጥማቅ✨የዛሬው ዕለት ከሠላሳ ሶስት የእመቤታችን በዓላት አንዱ ግንቦት 21 ቀን የሚከበረው የእመቤታችን በዓል ነው ። በግብጽ ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን የወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ጻድቃንን መልአክትን አስከትላ ለአምስት ቀን የታየችበት የተገለጸችበት ነው። በዚህ ዕለት እመቤታችን ከፀሐይ ሰባት እጅ አብርታ ከጉልላቱ ላይ በመንበር ብርሃን ተቀምጣ መላእክት ሊቃነ መላእክት ከበው ሲያመሰግኗት ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት እጅ ሲነሣት ታይታለች ። እስከ አምስት ቀንም ምእመናኑን አረማውያኑን አንድ ወገን አድርጋ ስትባርክ ሰንብታለች ከዚህም በኋላ ምእመናንም አረማውያንም በየዓመቱ እነዚህን ከግንቦት 21 እስከ ግንቦት 25 ለአምስት ዕለታት በደብረ ምጥማቅ ተሰብስበው የሚያከብሩ ሆነዋል።
እንኳን አደረሳችሁ🤍
እንኳን ለመናኙ ንጉሥ ቅዱስ አፄ ካሌብ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን✨
በአንድ ወቅት ዐመፀኛው የአይሁድ መሪ ፊንሐስ በሃገረ ናግራን የአሁኗ የመን ውስጥ የነበሩ ክርስቲያኖችን ክርስቶስን ካዱ በሚል ጨፈጨፋቸው
ከተማዋንም ለአርባ ቀናት በእሳት አነደዳት ዜናው በመላው ዓለም ሲሰማ በርካቶቹ ቢያዝኑም የተረፉትን ለመታደግ የሞከረ አልነበረም::
ቅዱስ አፄ ካሌብ ግን የሆነውን ሲሰማ ወደ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብቶ በግንባሩ ሰገደ: ወደ ፈጣሪም ጸለየ:- "ጌታዬ ሆይ! የክርስቲያኖችን ደም እመልስ ዘንድ እርዳኝ? እኔ በጦሬ ብዛት አልመካም: እኔ ተሸንፌ ክርስትና ከሚናቅ እዚሁ ግደለኝ" ብሎ በበርሃ ላሉ መነኮሳት እንዲጸልዩ ላከባቸው:
ጊዜ ሳያጠፋ በመርከብና በፈረስ : በበቅሎና በግመል ናግራን (የመን) ደረሰ:: ፊንሐስን ገድሎ ሠራዊቱንም ማርኮ ክርስቲያኖችን ነጻ አወጣ:: ደምና እንባቸውንም አበሰ:: አብያተ መቅደሶችን አንጾላቸው ወደ ኢትዮጵያ ተመለሰ::
ወዲያው እንደተመለሰ ወደ አክሱም ጽዮን ገብቶ
"ጌታየ ኢየሱስ ክርስቶስ ስላደረክልኝ የምሰጥህ ሰውነቴን እንጂ ሐብቴን አይደለም"ብሎ መንግስቱን ለልጁ ገብረ መስቀል አውርሶ ከዙፋኑ ወጣ:: የወርቅ አክሊሉን ወደ ኢየሩሳሌም ልኮ እርሱ በአባ ጰንጠሌዎን እጅ መንኩሶ መነነ::
በፎቶው ላይ የምታዩት አፄ ቅዱስ ካሌብ የመነነበት : አክሱም አካባቢ የሚገኝ የአባ ጰንጠሌዎን ገዳም ነውከዚሕች ዓለም ከአንዲት ረዋት (ኩባያ) : ከአንዲት ሰሌንና ከአንዲት ቀሚስ በቀር የወሰደው አልነበረም:: ከዚያም በበዓቱ ውስጥ በጾምና በጸሎት ተወስኖ አንድም ሰው ሳያይ በሰባ ዓመቱ (በ529 ዓ/ም) ዐርፏል:: ጌታችንም በሰማይ ክብርን አጐናጽፎታል:: ለቅዱስ አፄ ካሌብ የተለመነ አምላክ ለእኛም ይለመነን:: በጻድቁም ጸሎት ከመከራ ይሠውረን::🙏
በስተመጨረሻም እኔና እግዚአብሔር .......
ያኔ አለሁልሽ፤ከጎንሽ ነኝ፤ሁሌም እደግፍሻለው፤ደሞ ያንች ያልሆነ ቅብርጥስ...ምንትስትስ ሲሉ የነበሩት ሁሉ ዛሬ የሉም 🙂 ለምን ስለደከመኝ፤ስለሌለኝ፤ ችግር ስለገጠመኝ እንዲሁ ትናንት ያሉኝ የነገሩኝ ነገር ሁሉ ካንገት እንጂ ካንጀት ስላልነበረ ዛሬ ሁሉም ተውኝ።
ተስፋዬን ጥዬባቸው ነበር እግዚአብሔር ደግሞ ተስፋ ከርሱ ለእርሱ በእርሱ እንደሚጣል አስተማረኝ። እንዲሁ ተደግፌኣቸውም ነበር ነገር ግን የማይወድቀው እግዚአብሔርን የተደገፈ ሰው ብቻ እንደሆነ አስተማሩኝ ትናንት የካድኩት አምላክ ዛሬም ድረስ ያምነኛል ብቻ ተመስገን🙏🏻
ጽዮን ✨
Repost from N/a
✨I know እኮ ማንም ሰው ባይኖረኝ ገብርኤል እንዳለልኝ He knows my sadness behind my laugh እሱ ጋ ሄጄ ያለቀስኩትን ያህል ሰው ጋር ባለቅስ ጀመራት ደግሞ እንደምባል አውቃለሁ ጠንካራ ሰው አይደለሁም ግን ገብርኤል እንደሚረዳኝ ስለማውቅ ነው ጨንቆኝም የምስቀው ህመሜን ቁስሌን ድካሜን እያወቀ እንኳን መጣችልኝ እንጅ መጣችብኝ የማይለኝ የኔ ጠባቂ መልዐክ የልቤ ወዳጅ ተመስገንም ሲያንሰው ነው ለእኔ ገብርኤል🥹❤️🩹
Repost from ብሶት 𝐓𝐡𝐨𝐮𝐠𝐡𝐭'𝐬💭
"በጣም ዋጋ የሰጠናቸው ሰዎች ጥለውን ሲሄዱ ነው... በተቃራኒው ለእኛ ትልቅ ዋጋ የሰጡን ሰዎች አጠገባችን እንደነበሩ የሚገባን። 🙂
አንዳንዴ 'ሰው የለኝም' ብለን የምናዝነው፣ የፈለግናቸው ሰዎች ጥለውን ሲሄዱ ነው። ነገር ግን ማናስተውለው ነገር ቢኖር፤ ከልብ የሚወዱንና ዋጋ የሚሰጡን ሰዎች ሁሌም አጠገባችን እንዳሉ ነው። የኛ ያልሆኑትን ስናሳድድ እነሱ አልታዩንም እንጂ... የእነሱ ዋጋ የሚገባን ምናልባትም 'ከረፈደ' ይሆናል።"🥲👩🏽🦯
ዛሬ ቁጭ ብዬ የጻፍኳት ናት😍
"በአንተ ላይ ክፉ የሠራን ሰው ይቅር ለማለት ሲከብድህ፣ እግዚአብሔር አንተን ስንት ጊዜ ይቅር እንዳለህ አስብ። ያን ጊዜ የሰው በደል ከአንተ በደል ጋር ሲነጻጸር የባሕር ጠብታ ያህል ሆኖ ታገኘዋለህ።"🤍
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ✨መልካም ዕለተ-ሰኑይ🙏
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
