ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea
الذهاب إلى القناة على Telegram
የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)
إظهار المزيد2 935
المشتركون
-124 ساعات
+3307 أيام
+38330 أيام
أرشيف المشاركات
+9
በጥዋት ዜና እወጃችን የአፋብን ሽዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ዓፄ ዘርዓያዕቆብ ፩ኛ ኮር በነጎድጓድ ክ/ጦር በተካሄደው የአንጨቆረር ከተማ ጀብድ የምርኮ ዝርዝር ይፋ እንደሚከተለው አቅርበናል!!
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት ቀን 14/11/2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት ጠዋት በወጣው ዜና በሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ የአገዛዙ ጅምላ ተጋላቢ የሚሊሻ አባላት ላይ አመርቂ ድል መቀዳጀቱ ይታወሳል። አሁን ከሰዓት በደረሰን ተጨማሪ መረጃ መሠረት የተማረኩ አካላት እና የቁሳቁስ ዝርዝር መረጃ ይፋ ሆኗል።
የተማረኩ አካላት እና ቁሳቁሶች ዝርዝር
1ኛ.የተማረኩ የሚሊሻ ብዛት 5 አባላት
2ኛ.12 ክላሽኒኮቭ ጠመንጃዎች
3ኛ.4 ኤስ-ኬ-ኤስ (SKS): ጠመንጃ
4ኛ.1 መትረዬስ ክላሽ
5ኛ. ልዩ ልዩ የወገብ ትጥቅና ተተኳሾች ናቸው።
የኮሩና ክ/ጦሩ አመራሮች እንዳስታወቁት፣ በዚህ አውደ ውጊያ ላይ ለተሳተፉ አመራርና ሰራዊት አባላት ምስጋናቸውን በማቅረብ ይህና መሰል ስራዎችን ተጠናክረው በመቀጠል የድርጅታችን አፋብንን ጥሪ ባልተቀበሉ የአማራ ህዝብ ጠላቶች ላይ ሁሉ እርምጃው ተጠናክሮ መቀጠል አለበት ብለዋል።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግኑኝነት መምሪያ
በጉቶ ጊዳ ወረዳና ስቡ ስሬ ወረዳ የአንሻ ሰይድ ክ/ጦሮች የተናበበ መብረቃዊ ጥቃት በመፈፀም ድል ተቀዳጁ‼️
ሐምሌ 14ቀን 2018ዓ.ም
በአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ የሚንቀሳቀሱት
1 ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር
2 አበጀ ጥበቡ ነበልባል ክ/ጦር
3 አንገር ጉትን ክ/ጦርና
4 ታፈረ አለሙ ሳተናው ክ/ጦር
የአንሻ ሰይድ ዕዝ ምክትል ጦር አዛዥና የየክፍለ ጦሮች ጦር አዛዦች ጋር በመናበብ ደማቅ ወታደራዊ ገድልና የድል ታሪክ በመፃፋ ዛሬም በደመቀ ሁኔታ ቀጥለውበታል።
ላለፉት በርካታ ወራቶቺ በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳ ልጎ ቀበሌና በምስራቅ ወለጋ ዞን ስቡ ስሬ ወረዳ መርካቶ ቀበሌ ላይ ለበርካታ ወራቶች ካምፕ በማድረግ የአማራውን ማህበረሰብ በግፍ ሲጨፈጭፍ ፣ሲገል ፣ ሀብት ንብረቱን ሲዘርፍ እንዲሁም የሀይማኖት አባት ጨምሮ በአሰቃቂ ሁኔታ በመግደል የአማራ የጥላቻውን ጥግ ባደባባይ ሲያራምድ የቆየ፤በተጨማሪም ወደ ሁለቱም ከተሞች ማለትም በመርካቶ ከተማና በልጎ ከተማ ለገበያ ከገጠር የሚገቡ አማራዎች ላይ የሚገዙትን ነገር ሸምተው ሲመለሱ ኬላ ላይ በመጠበቅ ሀብት ንብረታቸውን በመቀማትና ፈሳሺ ነገሮችን ከዘይት ጀምሮ በማፍሰስ የተለያዩ የግፍ ድርጊቶቺን ሲፈፅም ቆይቷል።
ዛሬ ከንጋቱ 11:00 ሰዓት በምስራቅ ወለጋ ዞን ጉቶ ጊዳ ወረዳና ስቡ ስሬ ወረዳ ከኡኬ ኤርፖርት አየር ማረፊያ በ4 እና በ5 ኪሎ ሜትር ውስጥ የሚገኙት መርካቶ ከተማና ልጎ ከተማ ላይ ለወራቶች መሽጎ የነበረን የጥላት ጥምር ጦር በነዚህ ከተሞች ላይ ሰርጎ በመግባትና ምሽጎችን በመሰባበር 4ቱም ክፍለጦሮች የተናበበ የከተማ ሽምቅ ውጊያ በማድረግ ሁለቱንም ከተሞች በመቆጣጠር በጥላት ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅተዋል።
በመጨረሻም ውጊያው ከጠዋቱ 11:00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ቀኑ 5:00 ሰዓት ለስድስት ሰዓታት የተደረገ ሲሆን በየግዜው ወለጋ ምድር ላይ ታሪክን በጃቸው መፃፍ የለመዱት የአንሻ ሰይድ አናብስቶቺ በድል ተጠናቋል።
የጥላት ጥምር ጦሩም ሙትና ቁስለኛውን በማዝረክረክ ወደ ኡኬ ከተማ በመፈርጠጥ የፈሪ ደዱላውን በመድፍ፣በዙ23ና ሞርተር አማሮች የሚኖሩበትን ከተሞች እየደበደበ ይገኛል።
በዚህ ከባድ ጦርነት ጀብደኞች በምርኮ ያገኛቸው ቁሳቁሶች
👉15 የእግረኛ ጥምር ጦር አባላት
👉28 ክላሺ እኮብ
👉19 ኤፍዋን ቦምብ
👉24 ካዝናና 26 የደረትና የወገብ ትጥቅ
👉730 የብሬንና የክላሽ ተተኳሽ የተለያዩ ወታደራዊ ሻንጣዎች የተማረኩ ሲሆኑ የተገኙ ድሎቺን በፎቶና በቪድዮ የምናቀርብ ይሆናል።
ግፍ የወለደን:ግፈኞቺን የምንቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞች ነን!!!
©አፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ!
14/11/2018 ዓ.ም
+4
የምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የአጫጭር ስልጠናዎች እና የደንብ ልብስ የማልበስ ተሀድሶና ምርቃት አደረገ!!
ዘመናዊ ወታደር በመገንባቱ ረገድ ግንባር ቀደም በመሆን እየሰራ የሚገኘው (አፋብን) ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ ልዩ ዘመቻ መምሪያ የሰራዊቱን የግዳጅ አፈፃፅም አቅም የሚያሳድጉ አጫጭር ስልጠናዎችን ሲሰጥ ቆይቶ ትላንት ሐምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም በደማቅ ሁኔታ አስመርቋል።
የልዩ ዘመቻ መምሪያው አጫጭር ስልጠናዎቹን ከሰራዊቱ የደንብ ልብስ ተሀድሶ ጋር በማጣመር ያዘጋጀ ሲሆን፣ የምረቃ መርሃ ግብሩ በየደረጃው ያሉ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በድምቀት ተካሂዷል።
በእለቱ የተገኙት አመራሮች ለተመረቁት ሰራዊቶች የቀጣይ የግዳጅ አፈፃፀም መመሪያና የተለያዩ መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን፣ በስልጠናቸውና በግዳጅ ወቅት የላቀ አፈፃፀም ላሳዩ የሰራዊቱ አባላትም የዕውቅናና የሽልማት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት ተከናወኗል።
ይህ ስልጠናና የደንብ ልብስ ተሀድሶ ሰራዊቱ የተጣለበትን ህዝባዊ ኃላፊነት በላቀ ዝግጁነት፣ በፅናትና በብቃት ለመወጣት የሚያስችለውን አቅም በእጅጉ እንደሚያጎለብተው ተገልጿል ሲል የልዩ ዘመቻ መምሪያ ህዝብ ግንኙነት ክፍል መረጃውን አድርሷል።
ጀግንነትና አሸናፊነት ከርህሩህነት ጋር= አማራነት!
ይህንን ቻናላችንን አሁኑኑ ሰብስክራይ ላይክ (Like) እና ሼር (Share) በማድረግ አጋርነታችሁን አሳዩ፤ ! 💪ለሁሉም ያድርሱት። በትብብራችን ትግላችን ያሸንፋል!አብረን እንቁም
🔗 ሊንኩን ተጭነው ቤተሰብ ይሁኑ፡
የምኒልክ ዕዝ ወታደራዊና ሲቪል አመራሮች ከላስታ ወረዳ ማህበረሰብ ጋር ስትራቴጂካዊ ውይይት አካሄዱ!
በአፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ስር የሚገኙ ከፍተኛ ወታደራዊና የሲቪል መዋቅር አመራሮች ከላስታ ወረዳ ማህበረሰብ ጋር በትግሉ ሂደት፣ በወታደራዊ ስምሪትና በሲቪል አስተዳደር ቅንጅት ዙሪያ ሰፊ ውይይት አካሂደዋል።
መድረኩ የትግሉ አሁናዊ ደረጃ፣ የሕዝብና የሠራዊት ትስስር እንዲሁም የአገዛዙን <የምክክር መድረክ> ሴራ ማጋለጥን ጨምሮ በ5 ዋና ዋና አጀንዳዎች ላይ በጥልቀት በመምከር የቀጣይ ነፃነት ጉዞውን ስትራቴጂካዊ በሆነ መንገድ ለመምራት የሚያስችል መሠረት መጣሉ ታውቋል።
በዚሁ ታላቅ መድረክ ላይ የምኒልክ ዕዝ የአደረጃጀት ዘርፍ ኃላፊ፣ የዕዙ ዕቅድ ዝግጅትና ግምገማ መምሪያ ኃላፊዎች፣ የ303ኛ ኮር እና የ14ኛ ጥራሪ ክፍለ ጦር አመራሮች በግንባር ቀደምትነት ተገኝተዋል።
በተጨማሪም የሕዝብን ደጀንነትና የዕለት ተዕለት አስተዳደራዊ ሥራዎችን የሚመሩ የወረዳ፣ የንዑስ ወረዳና የቀበሌ የሲቪል መዋቅር ተወካዮች ከየአካባቢው ተወጣጥተው ተሳትፈዋል።
ስብሰባው በዕዙ ሥር ባሉ ወታደራዊና ሲቪል መዋቅሮች መካከል ያለውን የመረጃና የሥራ ቅንጅት ይበልጥ ለማጠናከር ያለመ ነው።
በውይይቱ የተዳሰሱ 5 ዋና ዋና አጀንዳዎች፦
1. የአማራ ትግል መነሻ፣ የደረሰበት ደረጃና መዳረሻ፦ ሕዝቡ ሕልውናውን ለማስከበር ወደ ትግል የገባበት አስገዳጅ ምክንያቶች፣ ትግሉ አሁን የደረሰበት የላቀ የጥንካሬ ደረጃና እየተመዘገቡ ያሉ ድሎች ተብራርተዋል።
እንዲሁም ትግሉ ዘላቂ ሰላም፣ እኩልነትና አስተማማኝ ደህንነት የሚያረጋግጥበት የመጨረሻ ግብ ተመላክቷል።
2. ወታደራዊና ሲቪል አደረጃጀትን ማጠናከር፦ የወረዳ፣ የንዑስ ወረዳና የቀበሌ የሲቪል አመራሮችን ሚና ከግንባር አዋጊዎች ጋር ማስተሳሰርና የዕቅድና ዝግጅት ሥራዎችን በተደራጀ መልኩ መምራት በሚቻልበት ስልት ላይ ውይይት ተደርጓል።
3. የሕዝብና የሠራዊት የማይበጠስ ትስስር፦ የፋኖ ሠራዊት የሕዝብ ልጅ በመሆኑ ያለ ሕዝብ ደጀንነት ትግሉ ግቡን ሊመታ እንደማይችል በመጠቆም፡ በሕዝቡና በሠራዊቱ መካከል ያለውን መተማመንና ትብብር ይበልጥ ማሳደግ እንደሚገባ ተገልጿል።
4. ትግሉን ከውስጥና ከውጭ ሴራዎች መጠበቅ፦ የትግሉን አቅጣጫ ለማስቀየር <ከአብይ አማሮች> እና ከሌሎች አካላት የሚሰነዘሩ የፖለቲካና የደህንነት ሴራዎችን በንቃት መከላከል እንደሚገባ ጥሪ ቀርቧል።
5. የአገዛዙን <የምክክር መድረክ> ማጋለጥ፦ አገዛዙ ሕዝቡን በድሮንና በከባድ መሣሪያ እየጨፈጨፈ ባረፈበት ወቅት በ«ምክክር መድረክ» ስም ያመጣው ሀሳብ ማደናገሪያና ሴራ መሆኑ ተብራርቷል።
አገዛዙ ሳይወገድ ምንም ዓይነት መፍትሔ ያለው ምክክር ሊኖር እንደማይችልና ትግሉ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በመድረኩ ማጠቃለያ ላይ ከተሳታፊዎች ለተነሱ በርካታ ጥያቄዎችና ስጋቶች በዕዙ ከፍተኛ አመራሮች ዝርዝርና አጥጋቢ ምላሽ ተሰጥቶባቸው ውይይቱ በስኬት ተጠናቅቋል።
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ጎርጎ ክላስተር የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ በታላቅ ድምቀት አካሄደ!!
ሐምሌ 14/2018 ዓ.ም
በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የክላስተር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። ቀን 13/11/2018 ዓ.ም በአፋብን የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተጉለትና ቡልጋ አውራጃ፣ አንኮበር ቀጠና ጎርጎ ክላስተር ያሰናዳው ይህ ጉባኤ፤ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የክላስተሩ ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት በታላቅ ወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል።
ጉባኤው የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችንና የህዝቡን ህልውና የሚያረጋግጡ ቁልፍ አጀንዳዎችን በጥልቀት የመከረ ሲሆን፣ በዋናነትም በሚከተሉት አራት አበይት ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡-
1ኛ.የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፡ የአጠቃላይ የክላስተሩንና የቀበሌዎችን የስራ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ አጠቃላይ ዳሰሳ ተደርጎበታል።
2ኛ.ጥልቅ ግምገማ፡ ያለፉትን ወታደራዊ፣ ድርጅታዊና ህዝባዊ ስራዎችን ጥንካሬንና ክፍተትን በመለየት አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል።
3ኛ. በወቅታዊ ጉዳዮችና በቀጣይ አቅጣጫዎች፡ የትግሉን መንፈስ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የህዝቡን ደህንነት የሚያረጋግጡ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል።
በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፤ የትግሉን ፈጣን ዕድገትና ጥንካሬ አጉልተው አሳይተዋል። ትግሉ በአጭር ጊዜ ውስጥ እየጎመራ ነው። ከሰፈርና ከቀበሌ አደረጃጀት ተሻግሮ፣ መላውን ህዝብ ያስተባበረ ታላቅ የአማራ ድርጅት መፍጠር መቻሉን ገልፀው ድላችንም ሩቅ አይመስልም ሲሉ ገልፀውታል። ህዝብን እንደ ህዝብ፣ ጦርን ደግሞ እንደ ጦር አደራጅቶ ዓመታዊ የክንውን ሒደትን በጉባዔ ደረጃ መገምገም መቻሉ የትግሉን ብስለትና የደረሰበትን ከፍተኛ የለውጥ ደረጃ የሚያሳይ ህያው ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል።
" ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"!
" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"!
የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
አይሰማም የአሳምነው ልጅ ነው አባቴ አባህ አገር ሽዋ መከረ አገር ጠነከረ ነው። በሰፊው እመጣበታለሁ እስከዛ ሸር
ሰበር የድል ዜና!!
ነጎድጓድ ክፍለጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ አስደናቂ ድል ተቀዳጀ!
ሀምሌ 14/11/2018 ዓ.ም
----------------------------------
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በወሰደው ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ ።
በአንጨቆረር ከተማ ዛሬ ሌሊት 11:00 የጀመረው አውደ ውጊያ የጀግኖቹ ወታደራዊ ወኔ ጨምሮ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ምት ሲያሳርፍ የቆየው ነጎድጓድ ክፍለጦር፣ በተካሄደው ወታደራዊ እርምጃ ታሪካዊና አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅቶ የአገዛዙ ሚሊሻና አድማ ብተና ማራገፊያ የነበረችውን አንጨቆረር ከተማን በተወሰደው መብረቃዊ የማጥቃት እርምጃ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል።
ክፍለጦሩ ወኔ በተሞላበት ስልታዊ ውጊያ የጠላትን ምሽግ በማፍረስ ፣ የጠላት ኃይልን በመበደምሰስ እና በመማረክ ግዛቱን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ የበላይነት መቀዳጀቱን ሲገልፅ የአገዛዙ ሀይል ለመመከት ቢሞክርም በተወሰደ ፈጣን የከተማ ውስጥ እርምጃ ሙት እና ቁስለኛ እንድሁም ምርኮኛ በማድረግ አዝረክርከነዋል እኛን መመከት አልቻለም ብለዋል።
የነጎድጓድ ክፍለጦር አባላት ላሳዩት የማይናወጥ ፅናት፣ የውጊያ ብቃት ከፍተኛ ምስጋናና አድናቆት በአዋጊወቻቸው የተቸራቸው ሲሆን ይህ ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ ቀጥሎ ጠላታችንን በየቦታው የመቅበር ስራ ይቀጥላል ብለዋል።
ይህ በነጎድጓድ ክፍለጦር የተመዘገበው ታላቅ ድል የሰራዊታችንን የማይበገር ፅናትና ከፍተኛ ብቃት አሁንም በግልፅ ያሳየበት አጋጣሚ ሆኗል። ጀግናው ሰራዊታችን የተጣለበትን ድርጅታዊና ህዝባዊ አደራ በላቀ ጀግንነትና ቁርጠኝነት መወጣቱን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል!
የቀሩ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን ይዘን እንመለሳለን።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
ሰበር የድል ዜና!!
ነጎድጓድ ክፍለጦር በአገዛዙ ሀይል ላይ በወሰደው እርምጃ አስደናቂ ድል ተቀዳጀ!
ሀምሌ 14/11/2018 ዓ.ም
----------------------------------
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር በወሰደው ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ ።
በአንጨቆረር ከተማ ዛሬ ሌሊት 11:00 የጀመረው አውደ ውጊያ የጀግኖቹ ወታደራዊ ወኔ ጨምሮ በጠላት ኃይል ላይ ከፍተኛ ምት ሲያሳርፍ የቆየው ነጎድጓድ ክፍለጦር፣ በተካሄደው ወታደራዊ እርምጃ ታሪካዊና አንፀባራቂ ድል ተቀዳጅቶ የአገዛዙ ሚሊሻና አድማ ብተና ማራገፊያ የነበረችውን አንጨቆረር ከተማን በተወሰደው መብረቃዊ የማጥቃት እርምጃ ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል።
ክፍለጦሩ ወኔ በተሞላበት ስልታዊ ውጊያ የጠላትን ምሽግ በማፍረስ ፣ የጠላት ኃይልን በመበደምሰስ እና በመማረክ ግዛቱን በመቆጣጠር ረገድ ከፍተኛ የበላይነት መቀዳጀቱን ሲገልፅ የአገዛዙ ሀይል ለመመከት ቢሞክርም በተወሰደ ፈጣን የከተማ ውስጥ እርምጃ ሙት እና ቁስለኛ እንድሁም ምርኮኛ በማድረግ አዝረክርከነዋል እኛን መመከት አልቻለም ብለዋል።
የነጎድጓድ ክፍለጦር አባላት ላሳዩት የማይናወጥ ፅናት፣ የውጊያ ብቃት ከፍተኛ ምስጋናና አድናቆት በአዋጊወቻቸው የተቸራቸው ሲሆን ይህ ፈጣን ስልታዊ የማጥቃት እርምጃ ቀጥሎ ጠላታችንን በየቦታው የመቅበር ስራ ይቀጥላል ብለዋል።
ይህ በነጎድጓድ ክፍለጦር የተመዘገበው ታላቅ ድል የሰራዊታችንን የማይበገር ፅናትና ከፍተኛ ብቃት አሁንም በግልፅ ያሳየበት አጋጣሚ ሆኗል። ጀግናው ሰራዊታችን የተጣለበትን ድርጅታዊና ህዝባዊ አደራ በላቀ ጀግንነትና ቁርጠኝነት መወጣቱን አሁንም አጠናክሮ ይቀጥላል!
የቀሩ ተጨማሪ ዝርዝር መረጃዎችን እንደደረሱን ይዘን እንመለሳለን።
ክብር ለትግሉ ሰማዕታት
ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን
ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ
የምን የማይታወቁ ኃይሎች?ይታወቃሉ እንጅ!
ሰሙን መጥራት ከፈራችሁ አኔ ልንገራችሁ።
የአፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘርዓ-ያዕቆብ 1ኛ ኮር ነጎድጓድ ክፍለ-ጦር የልዩ ኦፕሬሽን አባላት ናቸው።
+1
#ፋኖንና_የአማራ_ህዝብ_የከዳው ባንዳ መጨረሻ‼️
ማቻከል ወርዳ ላይ በተሰራ ኦፕሬሽን ከደ/ኤልያስ (ከቀስተ-ደመና ሻለቃ) ከድቶ ለብልጽግና ስላም አስከባሪ በመሆን ሲያገለግል የነበረ ከሃዲ በዚህ መልኩ እርምጃ ተወስዶበታል‼️
#የአማራ_ባንዳ_አለበት_እዳ‼️
13/11/2018 ዓ.ም
አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በምስራቅ አፍሪካ የውሃ ማማ ቀጠና የምትገኘው ዋበር ከተማ ወጣ ብሎ ከአረፋ ወንዝ እስከ አድባር፣ አልማና ፈረስቤት መገንጠያ ድረስ ከፍተኛ ተጋሃድሎ ሲፈፅም ውሏል!!
64ኛ ክ/ጦር ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም
~~~~~~
ወንዝ የማይበግረው አይበገሬው 64ኛ ክ/ጦር በደቡብ ወሎ በመከነ ሰላም፣ በአባይ ተፋሰስ ሸሎቃማ ቦታዎች በጎጃም በጃዊ ልዩ ስሙ ኩንቡር፣ በየቦቅላ፣ በቁይ፣ በደብረወረቅ፣ በደጀን ጉቢያ፣ በዋበረና በተለያዩ ቦታዎች በርካታ ተጋሃድሎዎችን ሲፈፅም የቆየና ዛሬም እንደ ትላንቱ እየፈፀመ ይገኛል።
በአብይ አህመድ ቀጭን ትዛዝ የተሰጣቸው ሌ/ጄነራል መሀመድ ተሰማ፣ ብ/ጀነራል አዲሱ መሀመድ፣ብ/ጄነራል መላኩ ገላነህ፣ ብ/ጄነራል ሶፍያን አህመድ የመሳሰሉት ያለ የሌለ መካናይዝድ ጦር በመያዝ ጎጃምን ለማውደም በተለያዩ ቦታዎች ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያርጉ ቢሆንም በአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር እና 54ኛ ክ/ጦሮች በተባበረ ክንድ በዋበር አስበውት የነበረ እቅዳቸውን በሙሉ የቁም ቅዠት ሆኖ ቀረቷል።
በፋሽቱ አብይ አህመድ ትዛዝ የተሰጣቸው ጀኔራሎችና ኮሎኔሎች ጎጃምን ለማውደም በርካታ መድፎችን፣ ዙ-23፣ BM ፣ ሞርተር፣ በቁጥር መግለፅ የማንችላቸው ድሽቃዎች፣ ብሬኖችና ስናይፕሮች የመሳሰሉት ከበባድ መሳሪያዎችን በመያዝ የም/አፍሪካ የውሃ ማማ የሆነውን ጮቄ ተራራን ለመያዝ ከድጎፂዮን ወደ ዋበር ጮቄ ተራራማና ደጋማ ቦታዎችን የተንቀሳቀሰ ቢሆንም ይህንን መርጃ ቀድሞ የደርሳቸው የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች 64ኛ ክ/ጦር ከ54ኛ ክ/ጦር ጋር በመቀናጀት የጮቄው ደጋማ ክፍል የሆነችው ዋበር ከተማን ሀምሌ 12/2018 ዓ.ም ለአገዛዙ ሳያስደፍሩ ውለዋል።
የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች በዋበር ከተማ መምጣታቸውን የሰመው የአገዛዙ ግሬሳ ሰራዊት ከድጎፂዮን ወደ ዋበር የመድፍና ከባድ መሳሪያ ቅንቡላዎች ሲያስወነጭፍ ውሏል። በሁለቱ ክፍለ ጦሮች ክንደ ብርቱ ሰራዊት ከፍተኛ ተጋሃድሎ ሲያደርጉ የዋሉት የጠላትን እቅድ በማክሸፍ፣ የጠላትን ዙ-23 የቡድን መሳሪያ በወገን ድሽቃና እና ሹተር አልሞ ተኮሾች ጀግኖች ከአገልግሎት ውጭ እንዲሆን በማድርግ የጠላት መካናይዝድ ጦር ቅስም በመስበር ባለበት ቦታ እንዲውል አድርገውታል።
የደጅ አዝማች በላይ ዘለቀ ልጆች ዋበር ከተማ ከፍተኛ ተጋድሎ ሲያደርጉ መዋላቸው የሰሙት የአብይ አህመድ ጀኔራሎች፣ ኮሎኔሎችና ግሬሳ ሰራዊታቸው ሀገር ስትደፈር፣ ስትወረር፣ ለሀገር ዳር ድንበር መጠበቂያ የሚሆነውን የቡድን መሳሪያ አስተዳድራዋለሁ በሚለው ህዝብ፣ በንፁሃን ላይ ሲያዝንቡት አምሽተው በአሉበት ቦታ አድፍጠዋል።
አዲስ ትውልድ፣ አዲስ ተስፋ፣ አዲስ አስተሳሰብ!!
ሀምሌ 13/2018 ዓ.ም
አፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 201ኛ ኮር 64ኛ ክ/ጦር ሕዝብ ግንኙነት
