ar
Feedback
ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

ፍኖተ- አማራ ሚዲያ (Finote- Amhara ) Midea

الذهاب إلى القناة على Telegram

የተመሠረተው የአማራን ሕዝብ ለማንቃት፣ ለማደራጀት እና ለማስተባበር ነው። የአማራ ሕዝብን ✅ ፖለቲካዊ ✅ ማህበራዊ ✅ ኢኮኖሚያዊ ታሪካዊ ጥያቄዎችን ለማሰማት እና የአማራን ሕዝብ በማንቃት ሰፊውን ሕዝብ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ይሰራል። ወደዱም ጠሉም የኃላ ታሪካችን በእኛ እጅ ይፃፋል። አማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ ( አፋብን)

إظهار المزيد
2 937
المشتركون
-324 ساعات
+3667 أيام
+38130 أيام
أرشيف المشاركات
እውነተኛ ህዝባዊ ምክክር ማለት እንዲህ ነው‼️ ትግላችን የህዝብ ፥ለህዝብ ነው የምንለው በበርካታ ማሳያዎችና መለኪያዎች ነው ።ከህዝባችን ተደብቀን ፣ከህዝባችን ጋር ሳንመክር የምንሰራው አንዳችም ነገር የለም ። የአብዮታችን ትግላችን ቁልፍ ጉዳይ የህልውና አደጋ ውስጥ የሆነውን ህዝባችን ከገጠመው አደጋና ከፈፅሞ መጥፋት መታደግ ነው ።ከዚያም ባሻገር ታላቁ ህዝባችን በወርድና ቁመቱ ልክ ፤ በነበረው፥ባለው አገራዊ አበርክቶ ልክ ትክክለኛ መሪዎች እንዲኖሩት እና ለሁሉም የሚበጅ ሰርአት- መንግስት ማወለድ ነው ። በመሆኑም በየትኛው ሁኔታ ውስጥ ሆነን ከህዝባችን ጋር ምክክር እናደርጋለን።የወገናችንን ጥቅሙን፣ፍላጎቱን እና ልባዊ መሻቱን ቁጭ ብለን እንጠይቃለን።በፍጥነትም ምላሽ እንሰጣለን። አዲሱ ትውልድ በአንድ እጁ ወደ ጠላት የሚተኩስ ፤በሌላኛው እጃችን ከህዝባችን ጋር እንመክራለን፣እናደራጃለን የወደፊቱን የትግል አቅጣጫችንን በጋራ እንተለማለን ። ህዝባዊ ምክክር ማለት ይኼው ነው። ክፋት ለማንም ፣በጎነት ለሁሉም! አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! Hailemichael Bayeh

ሰበር ዜና የጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር  አካል የሆነው ቴዎድሮስ ብርጌድ በወገራ ወረዳ ድል  ተቀናጀ።    የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ጎንደር ጠቅላይ ግዛት በላይ ዘለቀ ዕዝ  የዳግማዊ ቴዎድሮስ (5ኛ) ኮር  ግዙፋን  ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ቴዎድሮስ ብርጌድ አሀድ የሆኑት ራስ አሞራው  ውብነህ ሻለቃ ቁጥር አንድ  እና   አሳምነው  ሻለቃ  በጥምረት  ባደረጉት ከባድ አውደ ውጊያ ጠላትን በዝረራ ሸኝተውታል ። የቴዎድሮስ ብርጌድ መሰረት የትግል ጀማሪ የሆኑት  ሁለቱ ሻለቆች ትናንት  ሀምሌ 10/2018 ዓ/ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከ ምሽቱ 2፡30  በወገራ ወረዳ ትርጎስጌ እና ዳባት አቦ ቀበሌዎች  ለመግደልና ለመዝረፍ የመጣውን  ሆድ አደር ሀይል  የሚገባውን በቀይ ጥይት ሰጥተውታል ።እንደ ተከበበና መውጣት እንደማይችል የተረዳው  የአብይ አህመድ ወንበር አስጠባቂ ሀይል የድረሱልኝ ጥሪ  ባስተላለፈው  መሰረት ተጨማሪ ሀይል ከአምባጊወርጊስ ፣ገደብየ እና  ዳባት ከተሞች አምጥቶ ለጊዜው ሀይሉን ከሙሉ ድምሰሳ ቢያተርፍም  መታደግ ያልቻላቸው አራት አጥቦ አይለብሴ ሚኒሻን ጨምሮ  11 የመከላከያ አባላቱን  በሞት   8ቱን ደግሞ  በቁስል አጥቷል ከቆሰሉት መካከል  ጌታቸው ውቤ  የተባለ ማህበረሰቡን ሲያሰቃይ የነበረ  የሚኒሻ መሪም ይገኝበታል አሁን ላይ  ቁስለኞች ጎንደር ሆስፒታል  ለህክምና መግባታቸው ተረጋግጧል  ። ግዙፋ  ጎንደሬ በጋሻው ክፍለ ጦር ትናንትና በጎንደር ዙሪያ ዳዋ እና አምቦበር እንዲሁም በወገራ ወረዳ ትርጎስጌ እና ዳባት አቦ ቀበሌዎች አሰፍስፎ  የመጣውን የብርሃኑ ጁላን ምስለኔ ሰራዊት  በሚገባ መክቶ  ጭቃ ላይ ሲያንከባለል የዋለ አሳማ አስመስሎ መልሶታል  ።               ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን  !!! አርበኛ  ታድሎ ደሴ (ካስትሮ ) የጎንደሬ በጋሻው ክ/ጦር ህ/ግን /ኃላፊ                 ሀምሌ 11/2018 ዓ/ም

አንገር ጉትን ክ/ጦር በአገዛዙ ጦር ላይ በደፈጣ ጥቃት ድል መቀዳጀቱ ሲገለፅ፤በጉቶ ጊዳ ወረዳ ሜጢ ቀበሌ ለይ በአንድ ሆድ አደር ካድሬ ላይ የማያዳግም እርምጃ ተወሰደበት!!! የአፋብን ወለጋ/ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ አንገር ጉትን ክ/ጦር አካል የሆነው የድቾ መብረቅ ሻለቃ1 በጥላት ሃይል ላይ አንፀባራቂ ድል ተቀዳጀ። ሐምሌ13ቀን 2018ዓ.ም ከጠዋቱ 2:00 ሰዓት መነሻውን በምስራቅ ወለጋ ዞን ጊዳ አያና ወረዳ አንዶዴ ቀበሌ ልዩ ቦታዋ "ዶሮ በራ" ከምትባል ቦታ በመነሳት ወደ ዲቾ ተራራ ለደፈጣ እቅስቃሴ እያደረገ ባለበት ሁኔታ የድቾ መብረቅ ሻለቃ1 ቀድሞ ቦታውን በመያዝ የጥላትን ሃይል ሙትና ቁስለኛ ማድረግ ተቺሏል። ፨በጥላት ላይ የደረሰበት ጉዳት ሁለት የመከላከያ ሃይል ተበታትነው እግሬ አውጪኚ ብለው ሲሮጡ እጅ ከፈንጂ ከነሙሉ ትጥቃቸው ሲያዙ የደረሰበትን ምት መቋቋም ሲያቅተው ቁስለኛውን ይዞ ወደኋላ እዲመለስ ተገዷል። በሌላኛው ጌጤ ግርማ መብረቅ ክ/ጦር የኦፕሬሺን ስራ በመስራት የጥላት የመረጃ መረብ በመበጣጠስ ላይ ይገኛል።ክ/ጦሩ በምስራቅ ወለጋ ጉቶ ጊዳ ወረዳ ሜጢ ቀበሌ ላይ የአገዛዙ መረጃ የነበረ ተከፋይን ዘመን ወርቁ በሚባል ባንዳ ላይ እርምጃ መውሰዱን አስታውቋል። ግለሰቡ በተደጋጋሚ በክ/ጦሩ ማስጠንቀቂያና ምክር ቢሰጠውም ባለመስማቱ በብሶት ሻለቃ የቅኚት ቡድን አማካኚነት ዘልቆ በመግባት እስከወዳኛው ሊሰናበት እንደቻለ የክፍለጦሩ ሪፖርተር ከግንባር በላከው መረጃ አመላክቷል። በተጨማሪም የአገዛዙ ተላላኪ ተከፋይ ካድሬ ላይ እድህ አይነት የማያዳግም እርምጃዎቺ ተጠናክረው ስለሚቀጥሉ ሌሎች  ተላላኪዎቺ ከዘመን ወርቁና ከጌታቸው መንግስቱ ተማሩ። ግፍ የወለደን: ግፈኞቺን የምቀጣ የአንሻ ሰይድ ወድሞቺ ነን!!! አፋብን ወለጋ /ቢዛሞ አንሻ ሰይድ ዕዝ ህ/ግንኙነት መምሪያ

አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር 31ኛ ክፍለጦር በዳውንት ወረዳ ታላቅ ጀብዱ ተቀዳጁ! የክፍለጦሯ ቃኝ ባደረገችው የደፈጣ ውጊያ የአገዛዙን ሰራዊት 09 ቀበሌ ጉደር በተባለ ቦታ ላይ ጥምር ሰራዊቱ በርካታ ሙትና ቁስለኛ ሲደረግ፤ ሌሊቱን የዳውንት ወረዳ ጤና ጣቢያ አልጋዎች በአገዛዙ ቁስለኛና ሙት ሰራዊት ተጨናንቀው ያደረ ሲሆን ጠዋት ላይ በሁለት ባስ ከፍተኛ ቁስለኞቹ ተጭነው ወደ ደሴ ሆስፒታል ተወስደዋል። የአማራን ህዝብ ሊጨፈጭፍ ወደ አማራ ክልል በብአዴን ፊትአውራሪነት የገባው የአገዛዙ ጥምር ሰራዊት በ31ኛ ክፍለጦር አናብስት ፋኖዎች ወደ ሲዖል ተሸኝቷል። በመጨረሻም የጓዶቻቸውን አስከሬን ለማውጣት ሲገትቱ የነበሩ የጠላት የሰራዊት በአልሞ ተኳሽ ፋኖዎች ቅንድብ ቅንድባቸውን ተብለው ሙት ተደርገዋል። መዳረሻውን ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ሕዝብ የሕልውና ተጋድሎ ይቀጥላል ሲል መረጃውን የ106ኛ ኮር ሚዲያና ኮሚኒኬሽን መምሪያ አድርሷል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 106ኛ ኮር ሚድያና ኮሙኒኬሽን ሀምሌ 13/11/2018 ዓ/ም

ከትጥቅ ትግሉ ባሻገር ጎን ለጎን ህዝባዊ መድረኮች ተጠናክረው ቀጥለዋል። የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ (አፋብን) ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ 303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር በተቆጣጠራቸው ቦታወች ከውጊያ ጎን ለጎን ህዝባዊ መድረኮችን በማካሄድ የህዝቡን እና የፋኖን የተቀናጀ  ትስስር በመፍጠር አንድነትን ማጠናከርና የተጋረጠበትን የአማራ የህልውና ታጋድሎ በጥልቀት በመወያየት የነቃ ተሳቶፎን እያሳዬ ይገኛል። ህዝባዊ መድረኮቹ ፋኖ በተቆጣጠራቸው  በተለያዩ ጊዚያዊ የሲቪል መዋቅር ወረዳዎች መቄት ወረዳ ፣ላስታ ወረዳ እና ቡግና ወረዳ የሲቪል መዋቅር ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም የክፍለጦር እና የኮር አመራሮችን ስምሪት በመስጠት ጠንከር ያለ ህዝባዊ መድረኮች ተካሒደዋል። ህዝባዊ መድረኮቹ የህዝቡን የነቃ ተሳትፎ ያካተተ ሲሆን ላስታ ወረዳ 04 ሳርዝና ቀበሌ ፣መቄት ወረዳ 09 ቂላ ቀበሌ እና ቡግና ወረዳ 05 ቅደስ ሃርቤ ቀበሌ ላይ ለተከታታይ ቀናት የህዝብና የሰራዊቱን አሁናዊ የአማራን ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ እንዲቀጥል የህዝቡና የሰራዊቱ የጋራ ጥምረት አስፈላጊ እንደሆነ በኮሩ እና በክፍለ ጦሩ ትምህርት ተሰጥቷል ። ውይይቶቹ በአምስት ዋናዋና ነጥቦች ያተኮረ ነው። 1' የአማራ ፋኖ መነሻወች እና አሁን ያለበት ደረጃ 2' የህልውና ትግሉን ጫፍ ለማድረስ ከህዝቡ ምን ይጠበቃል 3' የህዝብ አስተዳደር ተግባርና ሃላፊነት 4' የህዝብ እና የፋኖ አንድነትና አብሮ ከመስራት አኳያ 5' ከአገዛዙ ስቦ በማስከዳት ሂደት ለሚመጡ የአገዛዙ ወታደሮች እንክብካቤ ከመስጠትና ተደጋግፎና ተባብሮ ከመስራት አኳያ በሚል ህዝባዊ ውይይቶች ተካሂደዋል ሲል የ303ኛ ግዙፉ አሳምነው ኮር ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን  መምሪያ መረጃውን አድርሷል። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልውና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል። ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን !! አፋብን ወሎ ቤተ-አማራ ምኒልክ ዕዝ ሚዲያና ኮሚዩኒኬሽን መምሪያ! ሐምሌ13/11/2018 ዓ 'ም

ከጠላት ዕቅድ በተቃራኒ አጸፋዊ ምላሽ የሰጠው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር የባሶሊበን ወረዳ ኮርክ ከተማን በመቆጣጠር ወታደራዊ ድል አስመዝግቧል። ሐምሌ13/2018 ዓ.ም ~~~~~~~ የ206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር ከሌሊቱ 11:00 ኮርክ ከተማ በመሸገውን የአገዛዙን ኃይል ላይ እርምጃ በመውሰድ ከ35 በላይ አድማ ብተና ፣15 ሚኒሻ ፣አንድ ሻለቃ አዛዥ፣ሁለት ሻምበል መሪዎችን በመደምሰስ ከተማውን ሙሉ ለሙሉ ተቆጣጥሯል። በፈጣን ማጥቃት የጠላትን ምሽግ የሰበረው 34ኛ ክ/ጦር 5 ክላሽ፣ ጥይት፣ ወታደራዊ ቦርሳና ልዩ ልዩ ቁሳቁስ የማረከ ሲሆን ከየጁቤ ከተማ ተነስቶ ድጋፍ ለመስጠት በሁለት FSR መኪና ተጭኖ በተንቀሳቀው የመከላከያ ኃይል ላይ በተደረገ ተጨማሪ ጥቃት ሻምበል አዛጆችን ጨምሮ የሰራዊት አባላት ሙሉ  ተደምስሰው ተሽከርካሪው ከጥቅም ውጭ ሁኗል። የጁቤ ሆስፒታል በቁስለኞች ተሞልቶ መደበኛ አገልግሎት አቁሟል። ከጠላት እቅድ በተቃራኒ አጸፋዊ ምላሽ የሰጠው 206ኛ ኮር 34ኛ ክ/ጦር የታቀደ አንጸባራቂ ድል በማስመዝገብ የጠላትን ወታደራዊ ኃይል አርግፎታል። በተመሳሳይ 24ኛ ክ/ጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ ከደጋሰኝን፣ ደብረ ማርቆስ እና ረቡዕ ገበያ ተሰባስቦ  ሜካናይዝድ ድጋፍ ካለው የጠላት ኃይል ጋር ትንቅንቅ እያደረገ ሲሆን በጠላት ላይ ከፍተኛ ጉዳት ደርሷል ። ውጊያው እጅ በእጅ እንደቀጠለ ነው። አዲስ ትውልድ! አዲስ አስተሳሰብ ! አዲስ ተስፋ! የአፋብን ቴዎድሮስ ዕዝ 206ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት

የነፃነት ንድፍ፦ የጉዞው እሳትና የፅናት ዋጋ!! ​የአማራ ልጅ ፋኖ በአራቱም ማዕዘን ተነስቷል። ያንን አማራ ጠል የሆነ አረመኔያዊ ሥርዓት ከምድር ገፅ ለማጥፋትና የህዝቡን ክብር ለመመለስ ሌት ተቀን የሚከፍለው መስዋዕትነት የጀግንነት ጥግ፣ የታሪክም አሻራ ነው። በዚህ የታሪክ አጋጣሚ ውስጥ ተገኝቼ የዚህ ትውልድ አካል መሆኔ ሁልጊዜም ኩራት ይሰማኛል። ​ነገር ግን ታሪክ ሁሌም ቀና አይደለም፤ አማራ በመሆኔ ብቻ በገዛ ወገኖቼ፣ በሆዳም አማራዎች መገፋቴ እጅጉን ያመኛል። ዛሬም ድረስ በነዚሁ ጥቅመኞች እየተሳደድኩ ብኖርም፣ ተስፋ ግን አልቆረጥኩም። ምክንያቱም ዛሬ በሸዋ ጠቅላይ ግዛት በአሳምነው ዕዝ ውስጥ የህዝብ አስተዳደር አርበኛ የሆነውን የወንድሜን የኤፍሬም ባዬን እና የጓዶቹ የትግል ጉዞ ስመለከት፣ የነፃነት ፈር ቀዳጅነቱን ሳስተውል፣ የቆሰለው ልቤ እንደ እሳት ይሞቃል፤ ብርታትም ይሰማኛል። ​የፋኖ ትልቁ ፈተናው ጠላትን መጋፈጥ ብቻ አይደለም፤ ያንን አቀበትና ቁልቁለት፣ ያንን ተራራና ገደል እየወጡ መውረዱም ጭምር ነው። እንዲህ ባለው መከራ ውስጥ አልፎ፣ በዱር በገደሉ እየተዋደቀ ነው ፋኖ የአማራን ህዝብ ነፃ ለማውጣት እየታገለ ያለው። የምወድህና የማክብርህ አርበኛ ኤፍሬም ባዬ ወንድሜ ሆይ፣ እጅጉን ክበርልኝ! ​በዚሁ አጋጣሚ፣ በየጎጡ ተሸሽጋችሁ ጎንደርን ከጎጃም፣ ጎጃምን ከወሎ፣ ወሎን ከሸዋ ለመነጣጠልና ህዝቡን ለመከፋፈል የምትሞክሩ ሆዳም አስመሳዮች ሆይ ይህ መልእክት (ቪዲዮ) ለእናንተ ይድረሳችሁ። አንዳንዴ በሆዳችሁ ያደራችሁ እውነተኛ ጀግኖችን በመሳደብና ስም በማጥፋት ለተሰማራችሁ ሁሉ ይህ የታሪክ ትዝብት ነው። እውነታው ግን አንዱና ግልጽ ነው፦ የአማራ ልጅ ፋኖ እናንተንም እኛንም፣ መላውን ህዝብ ነፃ ለማውጣት ነው ዛሬ በየጫካው ውድ ህይወቱን እየገበረ ያለው! #Dave #Amhara

በዙ_23 የተመታው የ3ዓመት ታዳጊ የዐምሐራ ሕዝብ እንዲጠፋ ከተፈረደበት ዓመታትን አስቆጥሯል። ዐምሐራ ሆኖ መወለድ ወንጀል ከሆነ እና ስርዓት ከተዘረጋ ፣ሕገመንግሥት ከተቀረፀ መቶ አመታትን አስቆጥሯ
በዙ_23 የተመታው የ3ዓመት ታዳጊ    የዐምሐራ ሕዝብ እንዲጠፋ ከተፈረደበት ዓመታትን አስቆጥሯል።  ዐምሐራ ሆኖ መወለድ ወንጀል ከሆነ እና ስርዓት ከተዘረጋ ፣ሕገመንግሥት ከተቀረፀ መቶ አመታትን አስቆጥሯል። በተለይ የአብይ አህመድ ስርዓት የዐምሐራን ሕዝብ እሳት እያዘነበበት ነው። ይህ የሚታየው ሕፃን የሶስት አመት ህፃን ነው ። በምስራቅ ጎጃም ዞን ማቻከል ወረዳ    ቅዳምን(ድንጋይ በር )  ላይ ከዋዳን በተተኮሰ ዙ_23  የተመታ ህፃን ነው።    የዐምሐራ ሆኖ ስለተገኘ ብቻ ከቤቱ ደጅ ሳጫዎች በአብይ አህመድ ጨፍ*ፊ ሰራዊት  የተመታ ሕፃን ነው። የዐምሐራ ሕዝብ አገሩ ወዴት ነው? አዲስ ትውልድ፣ አዲስ አስሳሰብ፣አዲስ ተስፋ! የቴዎድሮስ ዕዝ  ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ      ሐምሌ 13/2018ዓ.ም

የምረቃት ዜና!! የአማራ ፋኖ ብሔራዊ ንቅናቄ  ወሎ ቤተ አማራ ምኒልክ ዕዝ 102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት  ሰልጣኞችን በደማቅ ሁኔታ አስመረቀ። ሀምሌ 12/2018 ዓ/ም የ102ኛ ኮር አመራር በተገኘበት  ለተከታታይ  ሁለት ወር በወንጀልና በፍትሀ ብሔር ህግ የሰለጠኑ የህግና ስነ-ስርዓት ባለሙያዎችን ለመጀመሪያ ጊዜ በብቃት አስመረቀ። የ102ኛ ኮር  ከዚህ በፊት በሁሉም ክፍለጦሮች ብቁ የሆኑ የህግና ስነ-ስርዓት ባለሙያዎችን በመመደብ በሰራዊታችንና በህዝባችን ያሉ የፍትህ ጥያቄዎችን በመፍታትና የጀርባ አጥንት በመሆን ተስፋ የተጣለበት መሆኑ ይታወቃል። በአገዛዙ የብልፅግና ካድሬዎች አማካኝነት የአማራን ህዝብ የህግና ስነ-ስርዓት አገልግሎት እንዳያገኝ በማድረግ የተለያየ የፖለቲካ ስያሜ በመስጠትና የአለማቀፍ መርህ በመጣስ ህግና ስነ-ስርዓትን ለፖለቲካ ፍጆታ በማዋል በተለያዩ አካባቢዎች የፍትህ እጦት እዲፈጠር ተደርጓል ። በመሆኑም የ102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት አገልግሎት  ከወታደራዊ ግዳጅ ጎን ለጎን በተቆጣጠራቸው አካባቢዎች ከሰራዊታችን አልፎ ለአማራ ህዝብ የፍትህ አገልግሎት  አቅም በፈቀደ መልኩ እየሰጠ ይገኛል ሲል የ102ኛ ኮር የህግ መምሪያ ሀላፊ አርበኛ አበበ በላይ ገልጿል። ችግሩን በበዘላቂነት ለመቅረፍ ተከታታይ የህግና ስነ-ስርዓት ስልሰጠናዎች እንደሚቀጥሉ የመምሪያ ሀላፊው  ገልፀዋል ። አርበኛ አበበ  አያይዘው እንደገለፁት ከሆነ ከማንም ጋር ሰላም መፍጠር የማይፈልገው አገዛዙ በመላው ሀገሪቱ የተራዘመ  የጦርነት አዙሪት በመለኮስ በአማራ፣ በትግራይ፣ በኦሮሚያ፣በቤንሻንጉልና በአፋር ክልል ህግና ስነ-ስርዓት እንዳይከበር በማድረግ በዜጎች ላይ ከፍተኛ በደል ተፈፅሟል በማለት ተናግረዋል። በመጨረሻም የ102ኛ ኮር የህግና ስነ-ስርዓት ሰልጣኞች በታማኝነትና በልበ ሙሉነት  በየትኛዉም አስቸጋሪ የግዜና የቦታ ሁኔታ ቢሆን ከራሳችን በፊት ለወጣንለት አላማና  የሙያ መስክ ቅድሚያ እንሰጥአለን ሲሉ የዕለቱ ተመራቂዎች ቃለ-ምህላ ፈፅመዋል ። መዳረሻው ድልና ነፃነት የሆነው የአማራ ህዝብ የህልዉና ተጋድሎ ተጠናክሮ ይቀጥላል! "ክብር ለትግሉ ሰማዕታት" ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን! የአፋብን ወሎ(ቤተ-አማራ) ምኒልክ ዕዝ የ102ኛ ኮር ህዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም

ሰበር ዜና❗❗ በአቶ ተስፋዬ ጌታቸው ላይ ነጓድጓድ ክ/ጦር እርምጃ መወሰዱን ገለጸ !! ​ሀምሌ 13 ቀን 2018 ዓ.ም. ደብረብርሃን ​አፋብን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ አፄ ዘረያዕቆብ ኮር ነጎድጓድ ክ/ጦር ታላቅ ጀብድ መፈፀሙ ተሰማ። ቅዱስ የሆነውን የፋኖን ትግል ከድቶ በተለያዬ ቦታ ፋኖን በማስከበብ እንቅስቃሴዎች ውስጥ ተሳታፊ በመሆን በህብረተሰቡ ሰላምና ደህንነት ላይ ስጋት ለነበረው ለአቶ ተስፋዬ ጌታቸው አገዛዙ የባሶናወረና ሰላም እና ደህንነት ሀላፊ አድርጎ የሾመው ቢሆንም ፣ በነጓድጓድ ክ/ጦር የውስጥ ስፔሻሊስቶቹ በደ/ብረብርሃን ከተማ እርምጃ ተወስዶበታል ። ​ በግለሰቡ ላይ በተደረገው የቅርብ ክትትል እና በተሰበሰበው የደህንነት መረጃ መሰረት፣ እርምጃው የተወሰደው ዛሬ ጠዋት በተካሄደ ልዩ ኦፕሬሽን ነው። አቶ ተስፋዬ ጌታቸው ከፋኖ ተቋም በመክዳት የአገዛዙን ሹመት ተቀብሎ በአማራ ህዝብና ፋኖ ላይ የዘመተ እና ያስገደለ ከሀዲ መሆኑ ይታወቃል።ቀደም ሲል ከሌሎች ከሀድዎች ጋር በመሆን በአገዛዙ ሚዲያ ድርጅታችን አፋብንን እና የአማራን ህዝብ ሲዘልፍ የነበረው ተስፋዬ በአማራ ህዝብ ትግል ላይ ሻጥር መስራት እና ደም መርገጥ የማይቻል መሆኑን መቀጣጫ በማድረግ የአገዛዙን ሁሉ የከተማ ዙሪያ ምሽግ ዘልቀው በመግባት በምሀል ደ/ብርሃን አደባባይ እርምጃ ተወስዶበታል። የተወሰደውን እርምጃ ተከተሎ በደ/ብርሃን ከተማ በአመራሮችና ከሀድዎች ቤት ውጥረቱ ነግሷል። "የአማራን ህዝብ ህልውና ለማስከበርና ለማረጋገጥ የሚደረገው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል" ሲሉ አልሞ ገዳይ ጀግኖች ገልጸዋል። ክብር ለትግሉ ሰማዕታት ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን ሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ

201ኛ ኮር 54ክፍለጦር የመዝገቡ ዋለልኝ ሻለቃ እና109ኛ ኮር 99ኛ ክፍለጦር ኢንጅነር ክበር ተመስገን ሻለቃ ጮቄው ላይ ጠላትን በልኩ እያናገሩት ነው። ከስናን ወረዳ ወደ ጮቄው የሚንቀሳቀሰውን ጠላት206ኛ ኮር 24ኛ ክፍለጦር ስናን አባጅሜ ሻለቃ እጅ በእጅ በቦብ እያጨማለቁት ነው። በርካታ ጀኔራሎች እና ኮረኔሎችን አሰልፍ ከደንበጫ ወደ ገሊላ እና ከድጎ ፅዮን ወደ አልማ የሚንቀሳቀሰው ሀይል እና ከስናን ወረዳ ወደ መስታይት የሚንቀሳቀሰው ጠላት ሰባዊና ቁሳዊ ኪሳራን እያስተናገደ ነው ። ከዙ-23 እሰከ መድፍ እና ድሮን ቢያሰልፍም ጠላት ሬሳውን በየጫካው እያጠባጠበ ነው። በእውር ድብር የሚተኩሰው ከባድ መሳሪያም ንፁሃንን እየጨፈጨፈ ቀጥሏል። የዐምሓራ ሕዝብ በዚህ አረመኔ* ስርዓት ዋጋ እየቀፈለ ነው። የአለም አቀፍ ማህበረሰብ እየጠፋ ላለውን ሕዝብ ትኩረት ሊሰጠው ይገባል። ውጊያዎች በሁሉም ቀጠና እንደቀጠሉ ናቸው። አዲስ ትውልድ፣አዲስ አስተሳሰብ ፣አዲስ ተስፋ! ቴዎድሮስ ዕዝ ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ ሐምሌ13/2018ዓ.ም

የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ በደረፎ ክላስተር የመጀመሪያውን ጠቅላላ ጉባኤ በታላቅ ድምቀት አካሄደ!!              ሐምሌ 13/2018 ዓ.ም በአማራ ህዝብ የህልውና ትግል ታሪክ ውስጥ አዲስ ምዕራፍ የሚከፍት የክላስተር ጠቅላላ ጉባኤ ተካሄደ። በአፋብን  የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ተጉለት አውራጃ፣ አንኮበር ቀጠና በደረፎ ክላስተር ያሰናዳው ይህ ጉባኤ፤ የዕዙ ከፍተኛ አመራሮች እና የክላስተሩ ስራ አስፈፃሚዎች በተገኙበት በታላቅ ወታደራዊና ድርጅታዊ ስነ-ስርዓት ተካሂዷል። ጉባኤው የወደፊት የትግል አቅጣጫዎችንና የህዝቡን ህልውና የሚያረጋግጡ ቁልፍ አጀንዳዎችን በጥልቀት የመከረ ሲሆን፣ በዋናነትም በሚከተሉት አራት አበይት ነጥቦች ላይ ትኩረቱን አድርጓል፡- 1ኛ.የአፈጻጸም ሪፖርት ማቅረብ፡ የአጠቃላይ የክላስተሩንና የቀበሌዎችን የስራ እንቅስቃሴ የሚያሳይ ዝርዝር ሪፖርት ቀርቦ አጠቃላይ ዳሰሳ ተደርጎበታል። 2ኛ.ጥልቅ ግምገማ፡ ያለፉትን ወታደራዊ፣ ድርጅታዊና ህዝባዊ ስራዎችን ጥንካሬንና ክፍተትን በመለየት አጠቃላይ ግምገማ ተካሂዷል። 3ኛ.ወቅታዊ ሁኔታዎችና የአደረጃጀት ማሻሻያ፡ አሁን ባለው የትግል እንቅስቃሴ፣ ወቅታዊ ሀገራዊ ሁኔታዎች እና ድርጅታዊ አደረጃጀቶችን የበለጠ ለማጠናከር በሚያስችሉ ማሻሻያዎች ላይ ሰፊ ውይይት ተደርጓል። 3ኛ.ቀጣይ አቅጣጫዎች፡ የትግሉን መንፈስ ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግሩና የህዝቡን ደህንነት የሚያረጋግጡ የወደፊት ስትራቴጂካዊ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል። በጉባኤው ማጠቃለያ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች በሰጡት አስተያየት፤ የትግሉን ፈጣን ዕድገትና ጥንካሬ አጉልተው አሳይተዋል። ትግሉ በሶስት ዓመታት አጭር ጊዜ ውስጥ ከሰፈርና ከቀበሌ አደረጃጀት ተሻግሮ፣ መላውን ህዝብ ያስተባበረ ታላቅ የአማራ ድርጅት መፍጠር መቻሉን ገልጸዋል። ህዝብን እንደ ህዝብ፣ ጦርን ደግሞ እንደ ጦር አደራጅቶ ዓመታዊ የክንውን ሒደትን በምክር ቤት ደረጃ መገምገም መቻሉ የትግሉን ብስለትና የደረሰበትን ከፍተኛ የለውጥ ደረጃ የሚያሳይ ህያው ማረጋገጫ መሆኑን አስምረውበታል። " ክብር ለትግሉ ሰማዕታት"! " ህልውናችን በተባበረ ክንዳችን"! የሸዋ ጠቅላይ ግዛት አሳምነው ዕዝ ህዝብ ግንኙነት መምሪያ!!