MESOB_Initiative (MI)
الذهاب إلى القناة على Telegram
🌈 Mesob Initiative : An Ethiopian queer arts and advocacy collective using media, literature, and creative expression to advance LGBTQ+ rights and visibility.✊✨ 🕊 PEACE AND FREEDOM FOR ALL! 🌍 YOUR Voice , OUR Freedom! 🏳️
إظهار المزيد406
المشتركون
-124 ساعات
+1167 أيام
+14030 أيام
جاري تحميل البيانات...
القنوات المماثلة
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
سحابة العلامات
لا توجد بيانات
هل تواجه مشاكل؟ يرجى تحديث الصفحة أو الاتصال بمدير الدعم الخاص بنا.
الإشارات الواردة والصادرة
---
---
---
---
---
---
جذب المشتركين
يونيو '26
يونيو '26
+166
في 1 قنوات
مايو '26
+19
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+31
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+34
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+20
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+28
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+19
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+23
في 1 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+31
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+51
في 2 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+60
في 1 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+56
في 2 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+81
في 1 قنوات
Get PRO
مايو '25
+148
في 2 قنوات
Get PRO
أبريل '250
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+121
في 1 قنوات
Get PRO
فبراير '250
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '250
في 2 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+56
في 0 قنوات
| التاريخ | نمو المشتركين | الإشارات | القنوات | |
| 17 يونيو | +3 | |||
| 16 يونيو | +3 | |||
| 15 يونيو | +1 | |||
| 14 يونيو | +2 | |||
| 13 يونيو | +5 | |||
| 12 يونيو | +6 | |||
| 11 يونيو | +10 | |||
| 10 يونيو | +109 | |||
| 09 يونيو | +2 | |||
| 08 يونيو | +2 | |||
| 07 يونيو | 0 | |||
| 06 يونيو | +2 | |||
| 05 يونيو | +1 | |||
| 04 يونيو | +1 | |||
| 03 يونيو | +1 | |||
| 02 يونيو | +7 | |||
| 01 يونيو | +11 |
منشورات القناة
"አኩኩሉው ፍቅሬ"
ምዕራፍ ሁለት ፦ ክፍል አንድ
ፀሀይዋ ከነ ዘር ማንዘሯ የወጣች ይመስላል ፣ አናቴ ላይ ወታ በቃጠሎ እየጨፈረችብኝ ነው «የማያውቁት ሀገር አይናፍቅም» ብዬ ሊዮራን ትቼ መሄዴ ልቤን ቅር ቢያሰኘውም መንገዴን ወደ ፅናት አዙሬ እየተጓዝኩ ነው።
ስልኬን በእጄ እንደያዝኩት ይነዝረኝ ጀመር ፣ ፅኑ እየደወለች ነው
"ሄሎ ፅኑዬ"
"ወዬ አቢጉ ቆየሽ እኮ"
"ይቅርታ የተከበሩ እየመጣው ነው ደርሻለው"
"እሺ ቶሎ በያ"
"ይኸው ደርሻለው በራፋ ጋር ነኝ ፣ የቱ ጋር ነሽ"
"በራፉ ጋር ስትደርሺ አይሻለሁ"
"ደርሻለሁ ብዬ መዋሸት እንኳን አልቻልኩምኮ" አልኳት እየሳኩ
"ሲጀምር ውሸት እንደማልወድ እያወቅሽ ለምን ትዋሺኛለሽ" ድምጿ ሲቀየርብኝ ታወቀኝ ፣ ውሸትን አምርራ ነው ምትጠላው በርግጥ እኔም ውሸት አልወድም ግን ብዙ ጊዜ አርፋጅ ስለሆነኩ እዚ ደርሻለሁ እያልኩ መዋሸቱን ተላምጄዋለሁ
"እሺ በቃ አትኮሳተሪ ፣ ማርያምን አሁን በራፉ ጋር ነኝ"
"ምንድ ነው የለበሽው?"
"ነጭ ቲሸርት በቡኒ ሸሚዝ እና ሰማያዊ ጂንስ ሱሪ"
"አየሁሽ አዎ ፣ ከፊት ለፊትሽ ቀይ Swift መኪና አትታይሽም?"
"ትታየኛለች"
"በቃ አስፓልቱን ተሻግረሽ ወደ መኪናዋ ነይ"
በመኪና እንዳልገጭ ብዬ ግራ ቀኜን አይቼ አስፓልቱን በጥድፊያ ተሻግሬ ወደተባልኩት መኪና አቀናው ፣ መኪናዋ ጋር ስደርስ ፅኑ ከውስጥ ወርዳ ለረጅም አመት ሳይገናኙ እንደቆዩ እህትማማቾች ተቃቅፈን ሰላም ተባባልን ፤ እውነት ለመናገር ገና ሳቅፋት ነው ልቤ እርግት ብሎ ሰላሙን ያገኘው በቃ እቅፏ ማላውቀውን እረፍት ሰቶኝ ነበር እንደዛው ብንቀር ምኞቴም ነበር ግን መላቀቃችን ግድ ሆነና ተላቀቅን
"አንቺ አርፋጅ" አለችኝ እየፈገገች
"አርፋጅ መሆኔን እኮ ባለፈው ስናወራ ነግሬሻለሁ"
"ደሞኮ አታፍሪም ታወሪያለሻ" አለችኝ አይን አይኔን እያየች
"እውነታው እኮ ነው ባይሆን አንቺን የመሰለች ቆንጆ ብቻሽን ስላስጠበኩሽ ይቅርታ"
"ምንም አይደለም ለቅጣት ግን ተዘጋጂ"
"ንግስት ሆይ ሺ ቅጣት ቢቀጡኝ ለመቀጣት ዝግጁ ነኝ" አልኳት ፈገግ እያልኩ ፣ በውስጤ ግን ምናለበት ቅጣቱ ፊት ለፊቴ እራቁትሽን ቁሚ ወይ ከንፈሬን ሳሚኝ በሆነ ብዬ እየተመኘው ነው
"ባንዳፍ ፣ ነይ ግቢ አሁን በዚ በፀሀይ አንቃጠል" ብላኝ ወደ መኪናዋ ጠቆመችኝ
እኔም በመገረም "ያንቺ መኪና ነው እንዴ!?" ብዬ ጠየኳት
"አዎ"
"ኦው እና ባለፈው ያለአቅሜ ነዋ ካልከፈልኩ ብዬ ስታገል የነበረው"
እየሳቀች "እኔ ግን አልከፋኝም ይኸው በዛ ምክንያት ድጋሜ ልጋብዝሽ ተገናኘን"አለችኝ
"እኔ ግን ባንገባበዝም አንቺን ሁሌም ባገኝሽ ደስ ይለኛል"
"እኔስ መች ጠልቼው" ብላኝ ወደ መኪናዋ ገባን
ከፅኑ ጋር ኢነርጂያችን በጣም ተስማምቷል ፣ ምን እንደነካኝ ባላውቅም ከሷ ጋር በጣም ግልፅ እየሆንኩ ነው ፣ ሳሽኮረምማት እራሱ በነፃነት ነው በእርግጥ እሷም ትሽኮረመምልኝና መልሳ ታሽኮረምመኛለች ፤ በመሀላችን አንዳች ልዩ ነገር እየተፈጠረ እንዳለም እየተሰማኝ ነው። ውስጤ ሌዝቢያን እንደሆነች እየነገረኝ ሲሆን ተግባሯ ፣ አነጋገሯ እና አስተያየቷ ደግሞ እየመሰከሩልኝ ነው ።
"እና ቆይ ደግሞ ባለመኪና ሆነሽ ስለምን ታክሲ መጠቀምን መረጥሽ?"
"ሰሞኑን የመንዳት ሙድ ላይ አልነበርኩም ፣ አንዳንዴ መንዳት ያስጠላኛል" አለችኝ እየተንዘፈዘፈች እና እየተንገሸገሸች ፤ ለጉራ አልነበረም ያለችኝ እውነትም መንዳት ያስጠላት ትመስላለች
"አቤት አቤት ልዩነታችንን አየሽልኝ አ ፣ አንቺ መንዳት ያስጠላሻል እኔ ደግሞ ብነዳ ብዬ ሁሌ እመኛለሁ" አልኳት ከንፈሬን እየመጠጥኩ ፣ እውነት ለመናገር ወደፊት የምወዳትን ላንድክሩዘሬን እንደምነዳ ስለማውቅ አሁን ላይ ብዙም አልጓጓም ግን መኪና በጣም ነው ምወደው
"እና ምን ችግር አለው ትነጃለሻ" አለችኝ ትከሻዋን እየሰበቀች
"በደስታ ነዋ" አልኳት እኔም እየሳኩ
"በቃ ከሰሞኑ አንድ ቀን አለማምድሻለሁ ከዛን እኔ ሲደብረኝ አንቺ ትነጂልኛለሽ"
"መንጃ ፍቃዱስ?"
"ውስጥ ውስጡን አንቺ አስፓልት አስፓልቱን እኔ" ብላኝ ተሳሳቅን
"የት ነው ግን ምንሄደው" ጠየኳት
"ምነው እንዳላግድሽ ፈራሽ እንዴ"
"አንቺን በመሰለች ቆንጆ መታገድኮ መመረቅ ነው ፣ እንደውም ካገድሽኝ የቅም ቅም አያቶቼ ምርቃት ለኔ እንደሰራ ነው ምቆጥረው" ስላት ከትከት ብላ ሳቀች
"አቤት አቤት ምላሳም! እኔ እንደውም ሳስበው የቅም ቅም አያቶችሽን ምላስ በሙሉ የወሰድሽው ነው ሚመስለኝ"
"ቆንጆ ቆንጆዎችን በቃላቶቼ ለማስደሰት እና ለመሳም ከሆነ አይደብረኝም"
"እና እኔስ አይደርሰኝም" አለችኝ አይኔን እያየች ፣ አስተያየቷ የሆነ ነገር ከፊቴ ምታነብ ይመስላል
"ላንቺማ ምላሴን ብቻ ሳይሆን ልቤንም ነው ምሰጥሽ" ብዬ ስመልስላት ሁለታችንም በዝምታ ተዋጥን ፤ እኔ እንኳን ዝም ያልኩት ከአፌ አምልጦኝ በወጣው ቃል ነው ፣ አፍ አውጥቼ ልሳምሽ ማለት እኮ ነው የቀረኝ እሷስ ግን ለምን ዝም አለች!? አስደብሬያት ይሆን? ልጠይቃት ወይስ ዝም ልበል እያልኩ ከራሴ ጋር ስጣላ "ተጫወቺ እንጂ" ብላኝ መኪናውን በአንድ እጇ እየነዳች በሌላኛው እጇ እጆቼን ያዘቻቸው ፤ የምይዝ የምጨብጠው ነበር የጠፋኝ ልቤ እኔን ጥላ በአፌ የወጣችም መሰለኝ
ይቀጥላል...
ለታሪኩ አዲስ ከሆናቹ ምዕራፍ አንድን ማንበብ እንዳትረሱ! አመሰግናለሁ 🙏
✍ አቢጌል ነኝ
| 2 | #ምልስት
These are the days I saw him... the man I will never date!
ለመጀመሪያ ጊዜ ያየውት ከጽንኤል ጋር ሻይ ቡና ብለን ስንወጣ ነበር. I thought we had a moment when we stared at each other. ሲያየኝ ድንገጥ ያለ ይመስላል እኔም ሳየው ብደነግጥም ላላማስነቃት ሞክሪያለው ኮፍያ አድርጎ ነበር የሆነ ሰማያዊ ነገር ያለበት የስፖርት ጃኬት አድርጎ ነበር ጽኒ" wow" እንዳለ አስታውሳለሁ ያው መልሶ ቢክደውም የሆነ ሳየው የተሰማኝ ነገር ነበር።
በሳምንቱ ጽንኤል ስለ ልጁ ረስቷል እኔ ግን አልረሳውም ነበር የሆነ ሰው መንገድ ላይ ከማረከኝ ከአዕምሮዬ አይጠፋም ሴሰኝነት ይሁን አይሁን አላቅም ምክንያቱም ካየዋቸው እና ከተመቹኝ ጋር ስለ ሩካቤ አስቤ አላቅም, but what if we had something real with someone I admire and am passionate about? የሚል ጥማት እንጂ ስለዚ ያየውትን እና ውስጤ የገባን ሰው አልረሳም ለነገሩ ሰው ጭራሽ አልረሳም ስምም እንደዛው አሁን ሳረጅ እንደሰነፍኩት አይደለም ልቤ እነሱ ጋራ የለም ለዛ ይሆናል እኔነቴ ከጠፋ ቆይቻለሁ።
ይህን ሰው ሁለተኛ ጊዜ ያየውት ቀኑን አላስታሳውስም ወይ ምን አድርጌ ከየት እየተመለስኩ እንደነበር አላቅም 81 ባጃጅ ውስጥ ተቿክዬ ገባው መሽቶ ነበር ጠጋ ብዬ ሌላ ሰው እስኪገባ ስጠብቅ በተቀመጥኩበት ባጃጅ በኩል አንድ ሰው አለፈ ጠረኑ ደስ ይላል ወዲያው አወኩት እሱ ነበር ከላይ ወይንጠጅ የሚመስል ሹራብ ለብሷል ከታች ነጭ ስስራይፕ ያለው ሱሩ(የሱፉ ሱሪ) አድርጓል እጁን ኪሱ ከቶ እየሄደ ነበር ስፓርኛ አቋም አለው ቸስቱም ደስ ይላል፥ በልብስ ውስጥ ሲታይ።
ሶስተኛ ጊዜ ሳየው ከሀዋሳ እየተመለስኩ ነበር ታንቶስቲና አከባቢ እንደደረስን ሰው ለማውረድ ሲቆም ከመኪናው በስተግራ በኩል ቁልቁል ሲወርድ ተመለከትኩት የለበሰውን ልብስ አላስታሳውስም።
አራተኛ ጊዜ ያየውት አቦስቶ ነው ዛሬ ለብሶ የነበረውን ጥቁር ጃኬት አድርጓል ጥቁር ሱሪ በቦታው ላይ ውርውር እንል ከነበርን ሁሉ ዘንጦ የሚታየው እሱ ነው ያምር ነበር ባየውት ቁጥር ለአለባበሱ ትኩረት የሚሰጥ እንደሆነ ተረድቻለው። He must, because he is pretty, and pretty guys must ራሳቸውን ማሳመር ።
ዛሬ ሳየው መሽቶ ነበር እሱ መሆኑን አላወኩም ለአንድ ጓደኛዬ ወደ እሱ ጠቁሜ ይኸውልህ ይሃ በጣም ቆንጆ ነው አቋሙ ብትል ደስ ይላል ቀረብ ስል እና ትንሽ ዘወር ሲል እሱ ነው ጥቁር ጃኬት በፈዛዛ ጎመኔ ካኪ ሱሪ አድርጓል He just looks pretty. I didn't even see his face at first, but his energy pulled me toward him. I don't need to see someone's face to feel attracted; sometimes I just feel attracted to them even if I am walking behind them. I don't know what this means, but when I see him, I get sad and happy at the same time.
ለጓጀኛዬም ከዚ በፊት ስለነገርኩት ላስታውሰው ሞከርኩ እሱ ጭራሽ ረስቷል ሰው ይረሳል እኔ ግን አልረሳም ባጃጅ እየጠበቀ ወዲ ወዲያ ይላል ብቻዬን ብሆን እስኪሳፈር ቆሜ ባየውት ከጓደኞቼ ስለይ የለም ሄዷል።
የማላገኘው ሰው ነው። አሁን ባለውበት ሰዓት ፍቅረኛ እንደማያስፈልገኝ አስረግጬ አቃለሁ ግን I can't stop wanting someone's companionship, such a deep connection and intimacy that one gets from a friend and a lover. What I want in all this admiration of young men is not sex or something lustful; it's something different. I want to feel welcomed in a pretty young man's arms with love. I want to feel that I can also be as astonishing as they are to me. I want to feel wanted, desired, and loved, and for them to want my company as much as I want theirs.
Those people whom I am attracted to are, or might be, out of my league in the context of sexuality, but that is not necessarily the case. I think I have a belief that says I am not good enough for such people who are pretty, sexy, and beautiful.
I truly wish to have coffee with this man. Whenever I see him, he is always alone. He seems ጭምት and introverted, ሰው የማይረዳው ይመስለኛል. When I see him, I think he is cool, wise, content, and unhurried. But that contentment is not necessarily about his surroundings. He might not even love the way he is living iko, but his core seems still. My inner self is not content or at rest. I want to share what he has inside with what I have inside.
@2015 | የተፃፈ
ሻሸመኔ
#ሰላምእናነፃነትለሁሉም
#የእናንተድምፅየሁላችንነፃነት
#የማይረሱ
@mesobinitiative | 132 |
| 3 | ከዚ በፊት እዚህ Page ላይ ስለቀው የቆየሁት "አኩኩሉው ፍቅሬ" የተሰኘው የሳፎ(የሌዝቢያን) ተከታታይ የፍቅር ታሪክ ምዕራፍ ሁለት ከእሮብ አጀምሮ ይለቀቃል ፤ ይሄንን ድንቅ የፍቅር ታሪክ በኩራት ወራችን ላይ ለማንበብ ዝግጁ ናችሁ!?😊
እስከዛ ድረስ ያላነበባችሁት ምዕራፍ አንድ ፣ ክፍል አንድን ከላይ አታች ስላረኩላቹ አንብቡት 🙏 ወይም እዚሁ ቻናል ላይ "አኩኩሉው ፍቅሬ" ብላቹ Search ብታረጉት ሁሉንም ክፍል ታገኙታላቹ(6 ክፍል ነው ያለው) 😊
መልካም ንባብ
መልካም የኩራት ወር 🌈
#ሰላምእናነፃነትለሁሉም | 182 |
| 4 | እስኪ አድነኝ ሁነኝ ረዴት
ከጠፋውበት ከተደበኩበት
ፈልገህ
አግኝተህ
አባብለህ
አስታመህ
ሰው አድርገኝ ፍቅርን መግበህ
#ሰላምእናነፃነትለሁሉም
#የእናንተድምፅየሁላችንነፃነት | 211 |
| 5 | እራስን መውደድ ብልህነት ነው!!
ወረቀት ሲመረት ነጭ ነው ፣ ሲፃፍበት የተፃፈበትን ቀለም ይይዛል ፤ ወረቀት ምንም ብንፅፍበት ወረቀትነቱን አይተውም ይልቁንስ ባዶ ወረቀት ከመሆን አልፎ እውቀትን ያዝላል ፤ ነገር ግን ወረቀት ስራውን እና እራሱን ጥሎ ቢቃጠል ወይ ቢቀደድ ዋጋውን ያጣል ፣ ጥቅም የለውም እንደውም አመድ ወይ ቁርጥራጭ ቆሻሻ ሆኖ አከባቢያችንን እንዳያበላሽ ከቆሻሻ ጋር ይጣላል።(አንቺ ሴት ምንድ ነው ምትዘላብጂው እንዳትሉኝ!? 😁)
ምን ልላቹ ፈልጌ ነው!? 😊
እራሳችሁን ስትወዱ እና በተዘጋጀላቹ ቦታ ስትገኙ ልክ እንደዚ ወረቀት እራሳችሁንም ሌሎችንም ትጠቅማላቹ ‟አይ እምቢየው አሻፈረኝ” ካላቹ ግን ተቃጥላቹ እና ስሜታቹ ተሰባብሮ የማይሆን መንገድ ላይ እራሳችሁን ታገኛላቹ!! ስለሆነም እራሳችሁን ውደዱ ፣ ቦታችሁን አትሳቱ ፤ እራስን መውደድ Selfish መሆን ሳይሆን ብልህነት ነው ፤ አስታውሱ እናንተ ከሌላቹ የለፋችሁለት እና እራሳችሁን ያጣቹለት ነገርም የለም ፣ ሁሉም ይጠፋል!!😊
በሉ በቃ ከመሸ አላዝጋችሁም ደህና እደሩልኝ 🙏
#ሰላምእናነፃነትለሁሉም | 228 |
| 6 | በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት፡ ይህ ትክክለኛ ቅርስ ነው እንጂ ከውጭ የመጣ አይደለም
ክፍል አምስት፡ በኮንሶ ባህል ውስጥ የነበሩት "ሳጎዳ (Sagoda)"
በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን በተመለከተ፣ እንግዳ የሆኑ ታሪኮችን መፈለግ አያስፈልግም። ይልቁንም፣ የዕለት ተዕለት ሕይወት እውነተኛ አካል በሆኑ የባህል ክፍሎች ላይ ትኩረት እናደርጋለን። አሁን ወደ ደቡብ ክልሎች ወደምትገኘው ኮንሶ እንሂድ። በ1960ዎቹ አካባቢ፣ ተመራማሪው ክሪስቶፈር ሮቢን ሃልፓይክ (Christopher Robin Hallpike) ያደረጉት ጥናት "ሳጎዳ" የሚል ስም የነበረው የሚታወቅ ሦስተኛ-ሥርዓተ-ፆታ ሚና ላይ ግልጽ እይታ ይሰጠናል።
"ሳጎዳ" እነማን ነበሩ?
ሃልፓይክ እንዳብራሩት፣ ኮንሶዎች "ሴትነት የሚታይባቸው ወንዶች" የሚል ትርጉም ያላቸው በርካታ ቃላት ነበሯቸው፣ እና "ሳጎዳ" ከእነዚህ ውስጥ አንዱ ነበር። ይህ ደግሞ ፈጽሞ ያላገቡ ወንዶችን፣ በአካልም ሆነ ከማኅበረሰቡ ከሚጠበቀው የወንድነት ሚና አኳያ ደካማ ተብለው የሚታዩ ወንዶችን፣ እና አንዳንድ ጊዜ ቀሚስ ይለብሱ የነበሩ ወንዶችን ያካትታል። ሃልፓይክ ከጋሆ መንደር የመጣ፣ ብዙውን ጊዜ ከሴቶች ሥራ ጋር የተያያዘ የሆነውን ቆዳ የማድበስበስ ሥራ የሚሠራ፣ እንዲሁም ለስላሳ፣ ከሴት ልጅ ጋር የሚመሳሰል ድምፅና ምግባር የነበረው ሰው መኖሩን ገልጿል።
"ሳጎዳ" የተወሰኑ ጾታዊ ባህሪያት ጋርም ይያያዙ ነበር። ሃልፓይክ አንዳንድ "ሳጎዳዎች" በአንድ ዓይነት የፍቅር ግንኙነት ውስጥ የተገዥ (Passive) ሚና ይወስዱ እንደነበር ተመልክቷል። እርሳቸው የሰበሰቧቸው መግለጫዎች እውነተኛ እንደነበሩና በማኅበረሰቡ ውስጥ በሰፊው የታወቀውን እንደሚያንፀባርቁ ያምኑ ነበር። እንደነዚህ ያሉት ባህሪያት በ"ሳጎዳ" ብቻ የተገደቡ እንዳልነበሩ ያምናል፤ ምንም እንኳ አብዛኞቹ የኮንሶ ወንዶች ስለ ጾታ በግልጽ ማውራት ቢርቁም፣ አንዳንድ ወንዶች እርስ በእርስ በአንድ ዓይነት የፍቅር ግንኙነት ውስጥ ይሳተፉ ነበር። አልፎ አልፎ፣ "ሳጎዳ" ነው ተብሎ የሚታሰበውን ሰው ወደ እርሻ ጎትቶ ስለማጥቃት ከባድ ቀልዶች ይሰሙ ነበር። እነዚህ ቀልዶች ሁሉም ሰው "ሳጎዳ" ምን ማለት እንደሆነ፣ አምነውትም ይሁን አልፈለጉም፣ እንደሚያውቁ ያሳያሉ።
ለምን ጠፉ?
ስለ አሽቲሜ፣ ኡራኒን እና ዋንደርወራድ ከተማርኩት አንፃር ስመለከት፣ "ሳጎዳ" ቀስ በቀስ የጠፉት በተደባለቀ ማኅበራዊና ባህላዊ ምክንያቶች እንደሆነ እገምታለሁ። ከጊዜ ወደ ጊዜ፣ የኮንሶ ሕዝቦች ወንዶች በጣም ጥብቅ በሆኑ መንገዶች እንዲመሩ መጠበቅ እንደጀመሩ አስባለሁ። ገር ወይም ሴትነት የሚታይባቸው ወንዶች "ልዩ" ተብለው መታየት ጀመሩ፤ በግልጽ መኖርም ለእነርሱ አስቸጋሪ ሆነ። በተመሳሳይ ጊዜ፣ አዳዲስ ትውልዶች ከሃይማኖት እና ጠባብ የሆነ የወንድና የሴት ሚናዎችን ከሚያበረታቱ የመንግሥት ሕጎች ግፊት ገጠማቸው። ቤተሰቦች "ሳጎዳዎችን" እንዲያገቡና "መደበኛ" የሚባሉ ሥራዎችን እንዲይዙ ያበረታቱ ነበር፤ በዚህም በማኅበረሰቡ ውስጥ የመታየት ዕድላቸው እየቀነሰ ሄደ።
መጥፋታቸው ማንነታቸው የተሳሳተ ወይም ከተፈጥሮ ውጭ ስለሆነ አይደለም። ይልቁንም ማኅበረሰቡና ባህሉ ጥብቅ የሆኑትን ደንቦች ከማያሟሉ ሰዎች ጋር ምንም ቦታ በማይሰጥ መልኩ ቀስ በቀስ በመቀየሩ ነው።
ልናስታውሰው የሚገባ ቅርስ
የ"ሳጎዳ" ታሪክ በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ጥልቅ ሥሮች እንዳሉት ያሳየናል። እነዚህ ወንዶች የማኅበረሰባቸው አካል ነበሩ፤ ማኅበረሰቡ በአንድ ወቅት የተገነዘባቸው፣ ሁልጊዜም ሙሉ በሙሉ ባይቀበልም እንኳ፣ የራሳቸው ሚናዎች፣ ግንኙነቶች እና የአኗኗር መንገዶች ነበሩ። "ሳጎዳ"ን ማስታወስ በሥርዓተ-ፆታና በማንነት ላይ ያሉ ልዩነቶች አዲስ ወይም ከውጭ የመጡ እንዳልሆኑ ያስታውሰናል፤ እነርሱ የእውነተኛ ባህላችን አካል ናቸው።
Gloria Victor
June 2026 | 252 |
| 7 | አንዳንድ ቀን በራሳችሁ ማንነት መለወጥ ገርሟችሁ አያውቅም? ጣልነው የምትሉት ማንነት ይኖራችሁ ይሆናል? ግን የምንፀፀትበት ነው? ወይስ ማደጋችንን የምጋውቅበት ነው? የሚለው እንደየሰዉ ይለያያል። ግን ልንረሳ የማይገባን ነገር ቢኖር ትላንት ያለፈ ፣ ነገ ደግሞ የማይጨበጥ መሆኑና ዛሬ ላይ ያለው እኛ የተሻለ ግንዛቤ ያለው፣ ከትላንቱ የተሻለ እውቀት ያለው፣ የበለጠ ኃላፊነት መቀበል የሚችል ሰው እንደሆነ ነው። ዛሬ ላይ ቆመን በጥበብ ከተናገርን ትላንት ይሻላል ማለት አንችልም!!!
ዛሬን መኖር ነፃነት ነው!
መልካም ከሰዓት!
#ሰላም_እና_ነፃነት_ለሁሉም
#የእናንተድምፅየሁላችንነፃነት | 187 |
| 8 | MESOB THURSDAY CONFESSION
Content Warning: Suicide, self-harm, homophobia, mental health struggles.
#Submittedanonymously.
I have a confession.
I tried to kill myself so many times, but I couldn't do it, and I don't know why.
There was a time when my dad owned a gun. I put it inside my mouth. I could taste the cold metal on my tongue. I was going to shoot myself and get it over with. Make everything end.
But I didn't.
I always thought of myself as cursed, a mistake, an abomination. I hated myself.
I could handle physical pain, but this was different. This pain lived inside me. I couldn't see it I could only feel it. It felt like drowning in darkness with no light.
I couldn't accept myself. I kept asking, "Why me? Why am I like this?" I never found an answer.
So I wanted it all to end.
I tried many ways to kill myself. I tried jumping off a cliff. I tried drowning. Nothing worked.
Then one day, I had a sleepover at a friend's house. We ate dinner, got drunk, and went to bed.
In the middle of the night, I woke up and saw him sleeping.
I don't know what I was thinking, but I kissed him.
It felt good.
I kept kissing him and cuddling with him until he woke up. He saw me lying on his chest, got shocked, and pushed me away.
The next morning, he looked at me with disgust and said:
"You cuddled with me last night. That's so gross. I've never even cuddled with girls like that."
I started having panic attacks.
I told myself what society had always told me: that I was a sin, a mistake, cursed.
And once again, I wanted to die.
I got my dad's gun, closed my eyes, put it in my mouth, and pulled the trigger.
Nothing happened.
I had forgotten to take the safety off.
I dropped the gun. I was shaking.
For the first time, I asked myself a different question:
"What if I stop trying to kill myself and start listening to myself?"
So I stopped.
I started trying to understand myself.
I started listening to myself.
I'm okay now, but I'm still trying.
Trying not to lose myself.
፦ Anonymous
If you are struggling with thoughts of suicide or self-harm, please reach out to someone you trust or a mental health professional. You do not have to face it alone.።።።
Even if Mesob doesn't provide professional mental health we can listen and talk. Feel free fo DM.
#peaceandfreedomforall
#yourvoiceourfreedom
#MesobThursdayConfession
#MentalHealthMatters #YouAreNotAlone #SurvivorStory #SelfAcceptance#HealingJourney | 320 |
| 9 | በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት፡ ይህ ትክክለኛ ቅርስ ነው እንጂ ከውጭ የመጣ አይደለም
ክፍል አራት፡ ዋንደርወራድ (Wandarwarad)—በአማራ ማኅበረሰብ የሥርዓተ-ፆታ ተለዋዋጭነት
ይህ ጽሑፍ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ከኢትዮጵያ ባህል ውጭ የሆነ ነው የሚለውን የተሳሳተ አመለካከት የሚፈታተን የጽሑፎች ተከታታይ ክፍል ነው። በምዕራብ ስለነበሩት "አሽቲሜ" እና በሐረር ስለነበሩት "ኡራኒን" ካደረግነው ዳሰሳ በኋላ፣ አሁን ደግሞ ወደ አማራ ክልል እንዞራለን። ታሪካዊ መረጃዎች እንደሚያሳዩት የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ለኢትዮጵያ እንግዳ አልነበረም፤ ይልቁንም በዚያን ጊዜ የማኅበረሰቡ ተፈጥሯዊና አስፈላጊ አካል ነበር። ከአምሳ ዓመት በፊት የተደረገ አንድ ጥናት በአማራ ተራራማ መንደሮች ውስጥ በቀላሉ "ወንድ" ወይም "ሴት" ብቻ ሊባል የማይችል ማንነት መኖሩን አስመዝግቧል። እነርሱም "ዋንደርወራድ" የሚል የራሳቸው ስም ነበራቸው፤ ይህም የሥርዓተ-ፆታ ተለዋዋጭነት የተፈጥሮ እና የመንደር ሕይወት አካል እንደነበረ ያሳያል።
"ዋንደርወራድ" እነማን ነበሩ?
በ1950ዎቹ ውስጥ፣ ተመራማሪው ሳይመን ሜሲንግ (Simon Messing) በአማራ መንደሮች ውስጥ በመወለድ ወንድ ሆነው የተመደቡ ቢሆንም፣ ከባህላዊው የወንድነት ሚናዎች በእጅጉ የተለዩ ሚናዎችንና ባህሪያትን የተከተሉ ግለሰቦችን መዝግቧል። እነርሱም "ዋንደርወራድ" ተብለው ይጠሩ ነበር—ይህ ቃል በከተሞች የማይታወቅ ቢሆንም በአካባቢው ተቀባይነት ነበረው። እነዚህ ግለሰቦች ብዙውን ጊዜ ልቅ ያለ ልብስ ይለብሱ ነበር፣ በለስላሳ ይናገሩ ነበር፣ እና እንደ ምግብ ማብሰል ወይም እንጨት መሰብሰብ ባሉ ሥራዎች ይሳተፉ ነበር። በጣም አስፈላጊው ነገር፣ ልዩነታቸው እንደ ተቃውሞ ወይም ግጭት አይታይም ነበር፤ ይልቁንም በቀላሉ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር።
ከሴቶች ጋር ጠንካራ ትስስር ፈጥረው ነበር፤ ወንዶች ብዙውን ጊዜ ራሳቸውን ቢያርቁም፣ በጋራ ማኅበራዊ ዝግጅቶች ላይ ሙሉ በሙሉ ይሳተፉ ነበር። ማንነታቸው ዘመናዊ የሆኑ እንደ "(Gay)" ወይም "የሥርዓተ-ፆታ ሽግግር ያደረጉ (Transgender)" ባሉ ቃላት ሳይሆን፣ በመንደሩ ሕይወት የተገለጸ፣ ተፈጥሯዊ አካል ነበር።
የማንነት መጥፋት
"ዋንደርወራድ" የጠፉበትን ምክንያት ለመረዳት ስሞክር፣ በአንድ ምክንያት ብቻ እንዳልሆነ ግልጽ ሆነ። ይልቁንም ህልውናቸውን ቀስ በቀስ እንዲደበዝዝ እና በመጨረሻም ከሰዎች ትዝታ እንዲጠፉ ያደረጉ የተቀናጁ ምክንያቶች ነበሩ።
· የሃይማኖት ተጽዕኖ: ቀደም ሲል፣ የመንደር ሕይወት ሰዎች በሥነ-ምግባር እስከተመሩ ድረስ በሥርዓተ-ፆታ ሚናዎች ላይ የተወሰነ ተለዋዋጭነት ይፈቅድ ነበር። ነገር ግን የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እየጠነከረች ስትመጣ፣ "ወንድ" እና "ሴት" ተብለው በሚታሰቡት መካከል ግልጽ ድንበሮች እንዲኖሩ አጥብቃ በመጠየቋ፣ አካባቢው ይበልጥ ግፊት የበዛበት እና ለተለየ ሰው ተቀባይነቱ የቀነሰ ሆነ። ብዙውን ጊዜ ቀጥተኛ ቅጣት ባይኖርም፣ ከመደበኛው ጋር የማይጣጣሙ ሰዎች በማኅበረሰቡ ውስጥ ያላቸው ቦታ ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጠበበ እንደሄደ ተሰማቸው።
· የቤተሰብ እና የአካባቢ ማኅበረሰብ ጫና: ከእነዚህ ግለሰቦች መካከል ብዙዎቹ ከዘመዶቻቸው እፍረት ወይም ጫና ገጥሟቸዋል፤ እንዲያገቡ ተገፋፍተዋል፤ ወይም ከሕዝብ ሕይወት እንዲርቁ ተበረታተዋል። ይህ ደግሞ በዝምታ እንዲኖሩ አስገድዷቸዋል፤ በዚህም ታሪኮቻቸውንና ልምዶቻቸውን ለወደፊት ትውልዶች የማስተላለፍ ዕድል ቀንሷል።
· ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ለውጦች፡ በመጨረሻም፣ ማኅበራዊና ፖለቲካዊ ለውጦች "ዋንደርወራድ" ላይ ተጽዕኖ አሳድረዋል። ማዕከላዊ መንግሥት እየጠነከረ ሲሄድና መንደሮች ከከተሞች ጋር እየተገናኙ ሲሄዱ፣ የመንደሩ ሕይወት መለወጥ ጀመረ። "ወንድ" እና "ሴት" ብቻ የሚለው አዲስ አስተሳሰብ ከአገር ውስጥ ልማዶች የበለጠ አስፈላጊ እየሆነ በመጣ ምክንያት፣ ከዚያ የተለዩ የሥርዓተ-ፆታ ማንነቶች ቀስ በቀስ ጠፉ።
በደቡብ ለነበሩት አሽቲሜ፣ በሐረር ለነበሩት ኡራኒን፣ እና ለ"ዋንደርወራድ" የደረሰውን ስንመለከት፣ የተለመደ ንድፍ ይወጣል፡- የሃይማኖት፣ የቤተሰብ እና የማኅበራዊ-ፖለቲካዊ ለውጥ ጥምር ግፊቶች ከሕዝብ ሕይወትና ከትዝታ እንዲጠፉ አድርጓቸዋል—ማንነታቸው "ከተፈጥሮ ውጭ" ስለነበር ሳይሆን፣ ማኅበረሰቡ ለልዩነት የነበረው ተቀባይነት ስለቀነሰ ነው።
ልናውቀው የሚገባ ቅርስ
ስለ "ዋንደርወራድ" ታሪክ ሳስብ፣ እነርሱ ከውጭ የመጡ ሳይሆኑ የመንደር ሕይወት አስፈላጊ አካል እንደነበሩ ያረጋግጣል። ህልውናቸው በኢትዮጵያ ውስጥ ሥርዓተ-ፆታ ተለዋዋጭና ተስማሚ እንደነበረ፣ በዕለት ተዕለት ተግባራትና ግንኙነቶች ውስጥ በዝምታ የተሸመነ እንደነበር ያሳያል።
ይህንን መረዳት የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ከውጭ የመጣ ወይም የገባ ሐሳብ ነው የሚለውን አመለካከት ለመቀበል አስቸጋሪ ያደርገዋል። በተቃራኒው፣ የአገር ውስጥ ባህል አካል ነበር፤ ሰዎች ራሳቸውን የሚገልጹበትንና የሚኖሩበትን መንገድ የውጭ ተጽዕኖዎች ለማጥበብ ከመሞከራቸው ከረጅም ጊዜ በፊት የነበረ ነው። ታሪካቸው የኢትዮጵያ ያለፈው ዘመን እኛ ከምንገምተው በላይ ክፍትና ውስብስብ እንደነበረ ያስታውሰናል፤ ይህንን ልዩነት ማወቅ ደግሞ ታሪካችንን ለመረዳት ወሳኝ ነው።
Gloria Victor
June 2026 | 346 |
| 10 | እና በቃ ማንም ኑዛዜ የለውም🤭🙄
@MesobConfessBot
አናቆርፍደው እንጂ🤭
#ስላምእናነፃነትለሁሉም
#የእናንተድምፅየሁላችንነፃነት | 348 |
| 11 | ምዕራፍ አንድ
እኔ እና ሜሮን
2010ዓ.ም (እውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሰረተ)
በህይወቴ እንኳን ለሌላ ለራሴ እንኳ ለወንድ ያለኝን ስሜት ደግሜ ተናግሬ አላቅም ፆታዊ ፍላጎቴን ማወቅ ከጀመርኩ ወዲህ ያለኝ ነገር በሙሉ ለወንድ ነው ለሴት ትልቅ ክብርና ፍቅር ያለኝ ቢሆንም በፃታዊ መንገድ ለማሰብ አቅሙ ኖሮኝም አያውቅም ለምን እኔም አላቅም…..ይህ አመት እኔ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ከመጣ በኋላ ጊቢ የተባለ መካነ አዕምሮ የገባውበት ነበር ብዙም ምጠብቀው ነገር ስለሌለ የተሰጠኝን ነገር በፀጋ ተቀብዬ አስፓልት ሆነ ኮብልስቶን የሌለበት ካለውበት ከተማ እጅግ የሚርቅ ጠረፍ ድንበር ገብቻለው መንገዱ አዛ ነው አድካሚ ነው የአካባቢው ሙቀት አንደኛ ነው ቢሆንም ግን ለእኔ ምንም ነበር ሁሉ መቻል ስንፈለግ እንችለዋለን።
ጊቢ ከገባው በርካታ ጊዜያት በኋላ በርካታ ሰዎችን በአንድ ጊዜ ለመተዋቅ ጊዜ አልፈጀብኝም ተጫዋችነቴ እና ተግባቢነቴ እንኳን ፍሬሽ የሲኒየር ሲኒየር ነበር ያስመሰለኝ ቤተ ክርስቲያን ላይ ክላስ ላይ እንዲው ከመላው የጊቢው ሰው ጋር ተዋወኩ(እንደ ጋደኞቼ ከሆነ ጊቢ ውስጥ 5ሺ ሰው ቢኖር 3ሺውን ያውቃል ይላሉ) ሜሮን ቤተ ክርስቲያን ላይ ከተዋወካቸው ሰዎች አንደኛዋ ናት ሲበዛ ለሰው ፍቅር ያላት የዋህና ትሁት ንፁህ ሴት ናት በእድሜ ታላቄም ብትሆን ልጅነት አለባት ነገር ግን ሰው ስትወድ ከልቧ ነው፡፡
አንድ ቀን ማታ ስለፍቅር እየተወራ በነበረበት የመፅሐፍ ቅዱስ ጥናት ጊዜ በእኛ ቡድን ስር ያሉት ራሳቸውን እየደበቁ አንዳንድ ነገር ገልጠው ተናገሩ እኔ ምናገረው ምንም ነገር አልነበረም ብቻ ልጅ ሳለው እወዳት ስለነበረች የእቃቃ ሚስቴ አወራው ..ፍቅር እጅግ ጥልቅና ኃያል ነገር ነው መኃልየ መኋልዬ ፍቅርን ሲገልፀው፦
“በልብህ እንዳለ፣ በክንድህም እንደምትይዘው ማኅተም አስቀምጠኝ፤ ፍቅር እንደ ሞት የበረታች፣ ቅናቷም(ጥልቅ ስሜት) እንደ መቃብር(ሲኦል) ጨካኝ ነትና፤እንደሚንቦገቦግ እሳት፣እንደ ኀይለኛም ነበልባል ትነዳለች፡፡የውሃ ብዛት ፍቅርን ሊያጠፋ አይችልም፣ ፈሳሾችም አያሰጥሟትም.”
በዚ ክፍል ለበርካታ ሰዓታት ስንመካከር ቆይተን ወደ ጊቢ ገባን እኔና ሜሪ እንደ ለመድነው ቀደም ቀደም እያልን እያወራን እንሄዳለን ሜሪ ለኔ የአንድ አመት ሲኒየሬ ናት ቢሆንም እንደ ጓደኛ ቀለል ያለችም ናት አንድ ነገር ሂንት ነግራችኋት ሙሉ ነገሩን ካልሰማች አትፋታችሁም አወራቸው ስለነበረች የልጅነት ሚስቴ እየጠየቀችኝ ወደ ጊቢ አመራን እኔም የመጣው ይምጣ መናገር አለብኝ ስሜቴን ስል ላወራት እንደ ምፈልግ ነገርኳት፡፡
ሁሉንም ተሰናብተን በላውንቹ ፊት ጨለም ካለው ስፍራ ተቀመጥን..ምን ተብሎ ነው ሚጀመረው ግራ ገባኝ መናገር እንደጀመርኩ ማልቀስ ጀመርኩ አሁን ስስቅ የነበርኩት ልጅ በአንዴ እንባ በእንባ ንፍጥ በንፍጥ ሆንኩኝ ለስሜቴ ይሄን ያህል ቅርብ ነበርኩ ለረጀም ጊዜያት ማንንም ሳላወራ የታፈነው ብቸኝነቴን የዛን ቀን ማታ አፈረጥኩት…ለወንድ ልጅ ስሜት እንዳለኝም ነገርኳት ጊቢ ከገባው አይቼ ማላቀው የወንድ ልጅ እርቃን ገላ በየቀኑ ዶርሜ ፊት ራቁታቸውን ሻወር የሚወስዱ ወንዶች ሰለም ነስተውኛል ማታ በህልሜ ሁሉ ድንገት ብቅ እያሉ ያስጨንኩኝ ጀምረዋል ዶርም ውስጥ ወንድ ለወንድ አይተፋፋር የተባለ ይመስል መለመላቸውን ፓንት ሲቀይሩ አንዴ ቂውን ቁውን ሳይ ድንግጥ እላለው ነገር ግን የዶርሙን እንኳ ለመከላከል ችያለው ማንም እኔ ስኖር እንደዛ እንዲቀይሩ እንደማልፈለግ በግልጥ ነው የተናገርኩት ሁሉም ስለሚወዱኝና ሲለሚያከብሩኝ ታዘዙልኝ ፡፡
ሜሪ የምነግራት ነገር ፈፅሞ ሰምታ የማታቀው እንግዳ ነገር እንደሆነ ተረዳው ለማን ምን መናገር እንዳለብን ማውቅ ትልቅ ብልሃት ነው ምክንያቱም እናንተ አውርታችሁ ቀለል ሊላችሁ ይችላል ይሃ ሰው ግን ምንም ማድረግ በለመቻሉ የሚሰማውን ስቃይ መረዳት አንችልም ፡፡አብራኝ ማልቀስ ጀመረች coming out እንደዚ መሆኑን መቼ አወኩ ስናለቅስ ድምፃችን ሁሉ ይሰማ ነበር ብቻ ኃይሏን አሰባስባ ‹‹ እሺ አባ ኪያ አድርገህ ታቃለህ..›› ስትል እንባ ባነቀው ድምፅ ጠየቀችኝ ‹‹ በየሱስ ስም ሞቻለው እንዴ ይሃን የማደርገው….›› እውነት ነው አሁን ላይ ከዚ ቃሌ የተነሳ ሞቻለው ከወንድ ጋር ወሲብ ማድረግ ያነፃፀርኩት ከሞት ጋር ነበር ይህም ከተጨመረብኝ አስተሳሰብ የተነሳ እንደሆነ መለስ ብዬ ሳስበው እገረማው ምን ያህል ማህረሰቡ ሆነ ያመናቸው ያከበርናቸው ሰዎች ራሳችንን እንድንጠላ የማድረግ አቅም እንዳቸው እረዳለሁ፡፡
ብዙም አልቆየንም አለቀስን በምትችለው መንገድ ከዚ ነገር መውጣት እንድችል ልትረዳኝ ቃል ገባችልኝ የዋህነቷ ሻወር ውጪ እንድወስድ ሁላ ሃሳብ አቅርባልኝ ነበር፡፡ አንዳልፈተን ቤት ውጪ ልትከራይልኝ ሁሉ ነበር ምንም እንኳ 2011 የአመቱ መጨረሻ ላይ በዚ ነገር አሳንሳ እንደምታየኝ እስከምረዳ ድረስ ጥሩ ወዳጅነት አሳይታኛለች ምንም እንኳ ባልጠላት ለሷ መንገሬን እፀፀትበታለው ክፉ ሆና አይደለም ነገር ግን መፍትሄ የሌለውን ነገር መፍትሄ ለመፈለግ የማትወጣው ጉድ ውስጥ ስለጨመርኳት በራሴ እናደዳለው …የዛን ቀን ማታ እኔ ወደ ዶርም እፎይ ብዬ ስገባ ሰዎች እንደነገሩኝ ስታለቅስ እንዳመሸች እና ቤተ ክርስቲያን ላይ አብሯት የሚያገለግለውን በተለምዶ DAD የምንለውን ሰው ጠርታ ነገሩን ነገረችው ልንገረው ስትለኝ እሺታዬን ገልጬ ስለሆነ በፍቃዴ ነው ከዛ ቀስ በቀስ እያለ በህይወቴ ያማልረሳው ጠባሳ ጥሎ ለመሄድ በቃ 2011 የአመቱ መጨረሻ ላይ 10-15 የሚደርሱ የቤተ ክርስቲያን የወጣቶች ህብረት መሪዎቸ እና አንዳንድ ሰዎች ስለ እኔ ለማወቅ በቅተዋል፡፡ከዚ ቀደም ብሎ ባለው 2010 ክረምት ቤት መታ ለቤተሰቤ ካልተናገርኩ ብላ አስደንግጣኝ ነበር፡፡
እሷ መታ ለእናቴ እንደ ምትናገር ስለነገረችኝ ሳልወድ በግዴ ለቤተሰቤም HALF COMING OUT ለማድረግ ተገድጄ ነበር እነሱ ባደረሱብኝ ነገር ከትምህርት ገባታ ሁሉ አቋርጬ ሁሉ ለመሄድ እስከመወሰን ደርሼ ነበር ነገር ግን ይሃ አልሆነም እነሱ ተመርቀው ሲወጡ የተሰበረውን ልቤን ደብቄ ጠንካራ መስዬ ለመኖር ሞክሪያለው ጓደኞቼ ለእነሱ ነግሬ ለነሱ ያልተናገርኩት ነገር ምን እንደሆነ እስከዛሬ ባለማወቃቸው ነገሩ ሲነሳ ጥፋቱ የእኔ እንደሆነ ይወቅሱኛል ልክ ናቸው ጥፋቱ የእኔ ነው ፡፡
#ስላምእናነፃነትለሁሉም
ገጠመኝ (2014) የተወሰደ
#የእናንተድንፅ የእኛ ነፃነት
ገጠመኛችሁን በዚ👇 በኩል መልዕክት መላክ ትችላላችሁ!
@MesobConfessBot | 344 |
| 12 | لا يوجد نص... | 297 |
| 13 | በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት፡ ይህ ትክክለኛ ቅርስ ነው እንጂ ከውጭ የመጣ አይደለም
ክፍል ሦስት፡ በሐረር ከተማ የነበሩት ኡራኒን (Uranin)—የሥርዓተ-ፆታ ገደብ ያልነበረበት ጊዜ
የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት በአፍሪካ ላይ ከውጭ የተጫነ ጽንሰ-ሐሳብ ሳይሆን፣ የባህላችንና የታሪካችን እውነተኛ ክፍል መሆኑን ለማረጋገጥ ባደረግነው ጥረት፣ የታሪካዊቷ የሐረር ከተማ "ኡራኒን" (Uranin) ይህንን ሐሳብ የሚደግፍ ሌላ ጥልቅና ጠቃሚ ትዝታ ይሰጣሉ። በአንድ ወቅት የወንድና የሴት ባህላዊ ሚናዎችን በመቃወም የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን የሚቀበል ክፍት አስተሳሰብ ያለው ማኅበረሰብ እንደነበርን ያረጋግጣሉ።
ይህ ቡድን የታሪካዊቷ ሐረር ከተማ ነዋሪ ነበር። የጀርመን ተመራማሪ ፍሬድሪክ ቢበር (Friedrich Bieber) በ1900ዎቹ መጀመሪያ ላይ ስለ እነርሱ መዝግቧል፤ ባህላዊውን የወንድነት መመዘኛ የማያሟሉ ወንዶችን ለመግለጽ "ኡራኒዝም" የሚለውን ቃል ተጠቅሟል—ይህም ማንነቱ ከመጥፋቱ በፊት ነበር። ይህም በሐረሪ ማኅበረሰብ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ተለዋዋጭነት (Gender Flexibility) የመጀመሪያው የአገር ውስጥ አካል እንጂ ከውጭ የመጣ አስተሳሰብ እንዳልሆነ ግልጽ ማስረጃ ነው።
"ኡራኒን" እነማን ነበሩ?
ቢበር በሐረር ከተማ ውስጥ የነበሩ፣ ሰፊው ማኅበረሰብ ከ"ባህላዊ የወንድነት" የተለየ አድርጎ የሚቆጥራቸውን ባህሪያት የተከተሉ ወንዶች መኖራቸውን መዝግቧል፤ እነዚህ ልዩነቶች የሚከተሉትን ያካትታሉ፡-
አንዳንድ "ኡራኒን" የሴቶችን ልብስ መልበሳቸው እና ባህላዊ የሴት ተግባራትን መፈጸማቸው።
ሌሎች ደግሞ ለስላሳ ምግባር የነበራቸው እና ከባህላዊው የሴትነት አነጋገር ጋር የሚቀራረብ አነጋገር ያላቸው ነበሩ።
ምንም እንኳ የሐረሪ ማኅበረሰብ በይፋ "ሦስተኛ ሥርዓተ-ፆታ" የሚል ስያሜ እንደሰጣቸው የሚያረጋግጥ የአገር ውስጥ መረጃ ባይኖርም፣ ህልውናቸው በሐረር ውስጥ የታወቀና የተለመደ ነበር።
የሚገርመው፣ መኖራቸው በአጠቃላይ በመቃወም አልተስተናገደም ነበር። ይልቁንም፣ የሚጠበቅባቸውን ሚና እስከተወጡ ድረስ፣ የማኅበራዊ አደረጃጀቱ መደበኛ አካል ተደርገው ይታዩ ነበር። ይህ ዓይነቱ ተቀባይነት—ምንም እንኳ ውስን ቢሆንም—በኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ከሚቀርቡት ዘመናዊ ክርክሮች የበለጠ ተለዋዋጭና ክፍት የሆነ የአገር ውስጥ ታሪክ እንደነበረ ያሳያል።
ለምን ጠፉ?
የ"ኡራኒን" መጥፋት መንስኤነት ሐረሪ ማኅበረሰብን በድጋሚ የቀየሩ ተያያዥ ለውጦች ስብስብ ነው፡-
የሃይማኖታዊ ጥብቅነት መጨመር፡ ሐረር የኢስላም ዋነኛ ማዕከል እንደመሆኗ፣ ቀስ በቀስ ወደ ጥብቅ ሃይማኖታዊ አስተሳሰቦች የመቀየር ሂደት ታየባት። የሃይማኖት ማሻሻያ እንቅስቃሴዎች ጥብቅ ሁለት-ሥርዓተ-ፆታ ስርዓት (ወንድ/ሴት) በመዘርጋት እና የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን የማይቀበሉ ከባድ የሥነ-ምግባር ደንቦችን በመፍጠር ቁልፍ ሚና ተጫውተዋል። ማንኛውም ከባህላዊው ሁለትዮሽ ስርዓት ውጪ የሆነ የሥርዓተ-ፆታ መገለጫ "ነውርና ክልከላ" እንዲሁም "የውጭ" ወይም "እንግዳ" ተብሎ መሰየም ጀመረ። ይህ ግፊት ቀስ በቀስ የ"ኡራኒን" መጥፋት ምክንያት ሆነ።
የአውሮፓ ተጽዕኖ እና የሕግ ወንጀለኛነት፡ ሌላው ዋና ችግር በ20ኛው ክፍለ ዘመን የተስፋፋው የአውሮፓ ተጽዕኖ ሲሆን፣ አንድ ዓይነት የፍቅር ዝንባሌ ያላቸውን ድርጊቶች ሕገ-ወጥ የሚያደርጉ ሕጎችን ይዞ መጣ። ምንም እንኳ "ኡራኒን" የአገር ውስጥ ማኅበረሰብ አካል ቢሆኑም፣ እነዚህ የውጭ አስተሳሰቦች "ከመደበኛው የወጡ" በማለት አጠቁዋቸው። እነዚህ ተጽዕኖዎች ቀደም ሲል የነበረውን የሥርዓተ-ፆታ ተለዋዋጭነት አጠፉት፤ ማኅበረሰቡን ወደ ጥብቅ ሁለት-ሥርዓተ-ፆታ ሞዴል (ወንድና ሴት ብቻ) እንዲገባ አስገደዱት፤ ይህም ከዚህ ጥብቅ፣ ከውጭ ከመጣ የሥርዓተ-ፆታ ማዕቀፍ ጋር የማይጣጣም ማንኛውንም ባህሪ ማግለልና ወንጀል ማድረግ አስከተለ።
የቤተሰብ ፍርሃት እና ማዕከላዊ ቁጥጥር፡ ከላይ በተጠቀሱት ምክንያቶች፣ የሐረሪ ቤተሰቦች ማኅበራዊ ውግዘትን በመፍራት እነዚህን ልማዶች ማስቆም ጀመሩ። ይህ የሆነው ደግሞ ማዕከላዊ መንግሥት የአገር ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን የሚገድብ አንድ ወጥ የሆነ ባህል ለማስፈጸም እየሞከረ በነበረበት ጊዜ ነበር።
ይህ ቡድን በአገር ውስጥ የጽሑፍ መዝገቦች ውስጥ ፈጽሞ ስላልተመዘገበ፣ ሰዎች ቀስ በቀስ ረሱት። ዛሬ፣ ቢበር የጻፋቸው ማስታወሻዎች ብቻ ህልውናቸውን የሚያስታውሱን አልፎ አልፎ የሚገኙ ምንጮች ሆነው ቀርተዋል።
"ኡራኒን"ን እንደ ትግል ማስታወስ
የ"ኡራኒን" ትዝታን መልሶ ማምጣት የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ለአፍሪካ እንግዳ ነው የሚለውን ሐሳብ የሚዋጋ አዲስ መንገድ ነው። ጥብቅና የማያዳግሙ አስተሳሰቦች ከመጫናቸው በፊት ለልዩነት የበለጠ ክፍትና ተቀባይ እንደነበርን ያረጋግጣል።
ቢበር ስለ "ኡራኒን" መመዝገቡ በሐረር ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት የአገር ውስጥ ታሪክ የመጀመሪያ ክፍል እንጂ ከውጭ የመጣ ሐሳብ ወይም ማኅበራዊ ስህተት እንዳልሆነ ያረጋግጣል። ይህም በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት በኃይል እንዴት እንደተለወጠ ያለውን እውነተኛ ጥልቀት ለመረዳት ትዝታቸውን መልሶ ማምጣት ወሳኝ ያደርገዋል።
Gloria Victor
June 2026 | 482 |
| 14 | لا يوجد نص... | 439 |
| 15 | ካማሱትራ
ክፍል 7
አለቃው
ሁሌ የስራ ሺፍታችን ሲያልቅ ሁላችንም ለመታጠብ እንገባለን ጥቁር ፣ ጠይም ፣ ቢጫ ፣ ቡኒ ፣ ነጭ የማይታይ የሰውነት ቆዳ አይነት የለም ሁለት አመት ሆኖኛል እዚ ሀገር ከመጣው የጉልበት ስራ ሀገራችን አልሰራም ስል የኖርኩት ሰው ሁሉ የሆነ የበታች አድርጎ እንዳያየኝ ነው : የሚናቅ ስራ የለም እያሉ "አስተናጋጅ ብትሆንስ" ይሉሃል ወይ ደግሞ "ሊስትሮ ብትሰራስ" እያሉ የሆነ ጉድለት ያላቸው እንደሆነ ይመሰክሩልሃል በነሱ ቤት ሊያነቃቁህ መሆኑ ነው እኮ እናት አባት ራሳቸው ልታዋርደኝ ይሉሃል በተለይ የማስተርስ ምሩቅ ሆነህ ሰው ሁሉ የቡና መጠጫ ያደርግሃል ብቻ በስደት ሀገር የሚደብር ነገር የለም ስራ ስራ ነው አቧራ መስለን እንውልና ፏ ብለን ማታ እንወጣለን
የሆነ ቀን ድክም ብሎኝ ሰዎቹ ሁሉ ሲገቡ እረፍት ለማድረግ ከፎቁ ሰገነት ላይ ወጣውና ቁጭ አልኩ ፀሐይ ሊተኛ አይኑን እንዳሸ ልጅ ቀላልታለች ሀገሬ የነበረው ግባት ነው ለውጥ የለውም : አለም ሁሉ ሀገራችን ነው ቢባል ውሸት አይደለም በውበቷ ተደምሜ ስፈዝ 12:30 ሆኖ ነበር ብድግ አልኩና ወደ ሻወር ገባው ረጭ ብሏል ደስ ይላል እንደዚ ሲሆን የፈለኩትን ያህል ጊዜ መውሰድ እችላለሁ
አወላለኩና እርቃኔን ሆኜ ከላዬ የሞቀ ውሃው እንዲመታኝ አደረኩ በጠራራ ፀሐይ የደከመው ሰውነቴ በሙቀቱ እንደሚታሽ ሰው ድካሜን ሲያስወጣው ታወቀኝ ሌላ ሰው ሲገባ ራሱ አላወኩም ነበር ድንገት ለሳሙናዬ ዞር ስል አየውት ፣ የተወጠረ ደበልበል ያለ ቀይ ቂጡን ወደ እኔ አዙሮ ኦየታጠበ ነው ጀምስ ይባላል ከየት እንደሆነ አላቅም ግን supervisor ነው ሁሌ ቂጡን ሳይ ሻፍዳለው ድንገት ዞር ሲል አይን ለአይን ተገጫጨን
"Hello Dev" አለኝ በፈረንጅኛ ቅላፄው ለአመሉ
"Hello James " አልኩና ሳሙናውን ይዤ ዞርኩ ከጭኖቼ መሃል ብልቴ ሲነቃቃ እየታወቀኝ ነበር ወንድ ልጅ መብዳት ደስ ይለኛል የሆነ ነፍሴን የሚያረካ ዜማ አለው ሀገሬ ግብረሰዶማዊ ሊሉኝ ይችላሉ ግን ከቁብ አልቆጥራቸውም ወንድ ውስጤ ነው። ስሜቴ በሴት ገላ ሲታቀፍ ቢያድር ፍንክች አይልም አሁንም ድንገት ዞር ስል ፊቱን ወደእኔ አድርጎ እየታጠበ ነበር ያልተገረዘ ቁላውን ሲያሻሽ አየውት : ያልተገረዘ ቁላ ያየውት እዚ ሀገር ነው የበለጠ ይቀነዝርብኛል እንደዛ አይነት ጌይ ሳገኝ ራሴን መቋቋም አልቻልኩም ከፊቴ ሲገተር ፊቴን አዞርኩ ጀምስ ግን እያየኝ ነበር ወደ እኔ እየተራመደ መቶ ትከሻዬን ነካ አደረገኝ
አንገቴን ብቻ መለስ አድርግ ግንባሬን ወደላይ በማድረግ ድንጋጤ በሚታይበት መልክ ምን ልርዳህ የሚል ምላሽ አሳየው ድንጋጤ ነበር እሱም ላይ
"It is okay" አለኝ ምን ለማለት እንደፈለገ አውቂያለሁ ግን ዝም አልኩ በቀስታ ተጠጋኝ እና ሳመኝ ተሳምኩለት አንዴ የሰመረ መስመር ሳገኝ ውስጤ ያለውን አውሬ ለቀኩት እና ተቆጣጠርኩት ዝቅ አደረኩና አፉን በቁላዬ መብዳት ጀመርኩ ጎሮሮው ድረስ ትኩስ ጀላዬን ሳስገባ ነጭ ፊቱ ቲማቲም እየመሰለ በደስታ አስጠባውት
ወደ ግድግዳው አዙሬ ትከሻውን መሳም ጀመርኩ በእጆቼ የቁጡን ቀዳዳ በጣቶቼ ማጫወት ጀመርኩ በደስታ ማቃሰት ጀመረ በርከክ አልኩና ደንደን ባሉው ወፍራም ቂጡ ስንጥቅ መሃል ምላሴን አስገብቼ በምላሴ እበዳው ጀመረ የበለጠ ማቃሰት ጀመረ ጣቴን እያስገባው ፊንገር አደርገው ጀመረ መልሼ በምላሴ በዳውት ተነሳውና ወደ ላይ አየሳምኩት ወጣው ቁመቱ የተወሰነ ከእኔ ይረዝም ነበረ እና ወገቡን በእጆቼ ወደታች በእግሮች እግሩን ሰፋ አደሩኩ እና ጣቶቼን አፉ ውስጥ ጨመርኳቸው የተገተረ ቁላዬን ቂጡ ውስጥ ጨመርኩት ሰተት ብሎ ገባ በቀስታ የተወሰነ ገፋ ወጣ አደረኩና ፍጥነቴን እየለዋወጥኩ በዳውት መጮህ ሲፉልግ አፉን እፍን አደረኩትና አነኩት የበለጠ መውረግረግ ጀመርን ሽንጡን በመዳፌ ጨብጬ በፍጥነት እበዳው ጀመረ ክፉሉ ውስጥ የሚሰማው ድምፅ የእኔ ታፋ ወፍራም ቂጡን ሲገጭ የሚፈጠረው ድምፅ ነበር
"Yeah baby ... yeah my lord...fuck me fuck me..." መቀባጠር ጨመረ እኔም ይህ ጩኸት የበለጠ ያረካኛል ስራዬን በቅጡ እንደሰራው ያሳውቀኛል በብልቱ በኩል ፈሳሹ ሲፈስ የበለጠ ማቃሰት ጀመረ ቂጡ ጥብቅ ሲል ታወቀኝ እኔም ቁላይን ሳብ አድረጌ አወጣውት እና በቀኝ እጄ ይዤ ጀርባው ላይ ረጨውበት
ባለከለከ ድምፅ ተቃቀፉን እና የተወሰነ ተሳሳምን ...ታጠብን ምንም እንዳልተፈጠረ ልብሴን ለባብሼ ወደ አንድ ክፍል መኝታ ቤቴ አቀናው
#ይቀጥላል ....
ካማሱትራ ሾጥ ሲያደርገኝ እና ከሰማዋቸው ህይወት ተሞክሮዎች በመነሳት የማፃፉ ናቸው።
#ሰላም እና #ነፃነት ለሁሉም | 442 |
| 16 | https://substack.com/@robinjoab/note/p-200678625?r=4utnvb | 390 |
| 17 | የተሻለ አጋር መሆን የሚቻልባቸው መንገዶች፦
ደህንነታቸውን ይጠይቁ - “እንዴት ነህ/ነሽ/ኖት?” የሚል ቀላል ጥያቄ ትልቅ ትርጉም አለው። በዚህ ወር ለኩዊር ጓደኛዎ የአጋርነት መልእክት ይላኩ።
የግል ሚስጥራቸውን ይጠብቁ - የሰዎችን ማንነት፣ ፎቶዎችን፣ ስሞችን ወይም ታሪኮችን አያጋሩ።
ያዳምጡ - ስላለፉበት ተሞክሮ የሚነገርዎትን ይመኑ፡፡ ማዳመጥ በራሱ አጋርነት ነው።
በራስዎ ይማሩ- ኩዊር ጓደኛዎ ሁሉንም ነገር እንዲያሳውቅዎ ከመጠበቅ ይልቅ በራስዎ እውቀት ለማግኘት ይሞከሩ፡፡
የኩዊር ጥላቻን (ሆሞፎቢያን) ይቃወሙ - የራስዎን ደህንነት አደጋ ውስጥ በማይጥል መልኩ የቅርብ በሚሏቸው ሰዎች አካባቢ ያሉ ጎጂ የሆኑ ንግግሮችን፣ ቀልዶችን ወይም የተሳሳቱ መረጃዎችን ሲሰሙ ልክ አለመሆኑን ይናገሩ፡፡
ተግባራዊ ድጋፍ ያድርጉ - በዕድሎች፣ በግብአቶች፣ በትስስር (ኔትወርክ) ወይም በቀላሉ አብሮ በመሆን እና ጊዜ በማሳለፍ ኩዊር ጓደኛ ወይም ቤተሰብዎን ይደግፉ፡፡
ለኩዊር ድርጅቶች ድጋፍ ያድርጉ - የሕግ እገዛ፣ የአስቸኳይ ጊዜ ድጋፍ እና የማህበረሰብ ፕሮግራሞች የአጋሮችን እገዛ ይፈልጋሉ። የገንዘብና የአይነት ድጋፍ በማድረግ እንዲሁም ድምጽ በመሆን የኩዊር ድርጅቶች ለማህበረሰቡ እንዲደርሱ የበኩልዎን ያድርጉ፡፡ ይህ ድጋፍ ከኩራት ወር በኋላም መቀጠሉን ያረጋግጡ፡፡ | 369 |
| 18 | መልካም የኩራት ወር!
ኩዊር መሆን በወንጀል ከሚያስቀጣባቸው ሀገራት አንዷ በሆነችው ኢትዮጵያ እንደመሆናችን ይህ ወር ለየት ያለ ትርጉም አለው፡፡ እንደኢትዮጵያ ባሉ ሀገራት አጋርነት በይፋ ድጋፍ ከመስጠት ወይም የፕሮፋይል ምስልን በቀስተ ደመና ቀለም ከማሸብረቅም በላይ ነው፡፡ ከዚህ ይልቅ ኩዊር የሆንን ብቸኛ እንዳንሆን እና ደህንነት እንዲሰማን የሚያደርጉ ቀላል እና ቀጣይነት ያላቸው ድርጊቶች ትልቅ ሚና አላቸው፡፡በዚህ የኩራት ወር በዙሪያችን የሚገኙ አጋሮቻችን አጋርነታቸውን በምን መልኩ መግለፅ እንደሚችሉ ለማሳየት ኩዊር ኢትዮጵያ መልእክት ይዛ መጥታለች፡፡ | 347 |
| 19 | በኢትዮጵያ ውስጥ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት፡ ይህ ትክክለኛ ቅርስ ነው እንጂ ከውጭ የመጣ አይደለም
ክፍል ሁለት፡ የአሽቲሜ ታሪክ — የኢትዮጵያ የጠፋው የሥርዓተ-ፆታ ማንነት
የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት ለአፍሪካ አዲስ አለመሆኑን፣ ይልቁንም የረዥም ጊዜ ታሪካችን አካል እንደነበር ለማሳየት፣ አሁን ሙሉ በሙሉ የተረሱት አሽቲሜዎች ጥልቅና ውብ የሆነ ትዝታ ይሰጣሉ። በአንድ ወቅት የተለያዩ የወንድነት እና የሴትነት አኗኗሮችን የምናከብር እውነተኛ ሕዝብ እንደነበርን ያስታውሰናል።
አሽቲሜዎች በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ የሚገኘው የማሌ ማኅበረሰብ አባላት ነበሩ። የሰብአዊ ሳይንስ ተመራማሪ ዶናልድ ደንሃም በ1970ዎቹ ውስጥ የነበራቸውን ህልውና መዝግቧል። እርሳቸውም ከተለመደው የወንድ/ሴት ምድቦች የወጣ፣ የመጀመሪያ አፍሪካዊ ምሳሌ እንደነበሩ አስፍረዋል።
ዶናልድ ደንሃም በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ያለውን የማሌ ሕዝብ ያጠኑ ቁልፍ ተመራማሪ ናቸው። ሥራቸው በጣም አስፈላጊ ነው ምክንያቱም ይህ ማንነት ሊጠፋ ሲል መዝግቦ ስለነበር ነው።
ስለ አሽቲሜ ያደረጉት ጥናት በማሌ ማኅበረሰብ ውስጥ ስላለው ማኅበራዊ ለውጥ እና ሥልጣን ካደረጉት ሰፋ ያለ ጥናት የተወሰደ ነው። ስለዚያ አካባቢ ካሳተሟቸው ቁልፍ መጻሕፍት መካከል፡-
Work and Power in Maale, Ethiopia (በማሌ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ ሥራ እና ሥልጣን)
Southern Marches of Imperial Ethiopia: Essays in History and Social Anthropology (የንጉሣዊቷ ኢትዮጵያ ደቡባዊ ድንበሮች፡ በታሪክና በሰብአዊ ማኅበራዊ ሳይንስ ዙሪያ ያሉ ጽሑፎች)
ደንሃም የአሽቲሜን ታሪክ ከመመዝገብ ባሻገር፣ መጥፋታቸውን በኢትዮጵያ እየተከናወኑ ካሉ ትላልቅ ለውጦች ጋር ያገናኘ ጥልቅ ትንተናም ሰጥተዋል።
በቀላል አነጋገር፣ የደንሃም ሥራ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት በአፍሪካ "የውጭ" አስተሳሰብ እንዳልነበረ የሚያሳይ ጠንካራ ማስረጃ ነው። በደቡብ ኢትዮጵያ ውስጥ ትክክለኛ፣ የአገር ውስጥ ቅርጽ ነበረው፤ ነገር ግን በውጫዊ ኃይሎች ምክንያት ጠፋ።
አሽቲሜዎች እነማን ነበሩ?
አሽቲሜዎች ባዮሎጂያዊ ወንድ የሆኑ፣ ነገር ግን በማኅበረሰባቸው ውስጥ የሴትነት ማንነትን የወሰዱ ሰዎች ነበሩ። ይህ ማንነት ሙሉ በሙሉ ተቀባይነት ያገኘ ነበር፤ ሰዎችም እንደ "ልዩ ሁኔታ" ወይም "ስህተት" አያዩአቸውም ነበር። ይልቁንም፣ የማሌ ሕዝብ ማኅበራዊና ሃይማኖታዊ ወጎች አካል ነበሩ።
ከባህላዊ የወንዶች ሥራዎች፣ እንደ መዋጋት፣ ከብቶችን መጠበቅ ወይም ከባድ የእርሻ ሥራ ከመሳሰሉት ነፃ ነበሩ። ይልቁንም ባህላዊ የሴቶችን ሚናዎች መረጡ እንደ ምግብ ማብሰል፣ ልጆችን መንከባከብ እና አረጋውያንን መጠበቅ።
እንዲሁም ከቅዱስ ንጉሣቸው (ኬቲ) ጋር በተያያዘ የሃይማኖትና የመንፈሳዊ መዋቅር አካል ነበሩ። በንጉሡ ግቢ ውስጥ ልዩ ቦታ የነበራቸው ሲሆን፣ በአካላዊው ዓለም እና በመንፈሳዊው ዓለም መካከል እንደ አገናኝ ሆነው ያገለግሉ ነበር።
ደንሃም አሽቲሜዎችን እንደ ዘመናዊው የአውሮፓ ምድቦች—ለምሳሌ "አንድ ዓይነት የፍቅር ዝንባሌ"—ውስጥ ማስገባት እንደሌለብን በግልጽ አስቀምጧል። ምክንያቱም ማንነታቸው በዋነኝነት የተመሠረተው በሥርዓተ-ፆታቸውና በመንፈሳዊ ሚናቸው ላይ እንጂ በጾታዊ ባህሪያቸው ላይ አይደለም።
የአሽቲሜ ማንነት እንዴት ጠፋ?
የአሽቲሜ ማንነት በ1900ዎቹ ውስጥ በኢትዮጵያ ውስጥ አዲስ በሆኑ ትላልቅ ለውጦች ምክንያት ቀስ በቀስ እየጠፋ መጣ፡-
የፖለቲካ ለውጥ እና የንጉሡ ስልጣን መዳከም፡ እነዚህ ለውጦች የጀመሩት በ1890ዎቹ ንጉሥ ምኒልክ ዳግማዊ የማሌን አካባቢ በኃይል ሲቆጣጠሩ ነው። ይህ እርምጃ አሽቲሜዎችን ይጠብቅ የነበረውን የንጉሥ ኬቲን ነጻነት አጠፋ። ዓመታት እያለፉ ሲሄዱ፣ ንጉሡ እውነተኛ ሥልጣን የሌለው ሃይማኖታዊ ምልክት ብቻ ሆኑ።
የአዲስ ኢኮኖሚ መለኪያዎች፡ እንደ ግብር መክፈል እና ለደሞዝ መሥራት ያሉ አዳዲስ የኢኮኖሚ ሕጎች ማኅበረሰቡ የወንዶችን ሚና የሚመለከትበትን መንገድ ሙሉ በሙሉ ለወጠው። ቀደም ሲል ወንድ መሆን ማለት በእርሻ ላይ በጋራ መሥራት እና ከብቶችን መንከባከብ ነበር። የወንድነት አዲስ መለኪያ ግን የሚያገኘው በገንዘብ መጠን ሆነ። አሽቲሜዎች የእርሻ ሥራ ወይም አዲሱን የሚከፈልበትን ሥራ ስላልሠሩ፣ ሰዎች በድንገት "ምርታማ ያልሆኑ" በማለት መጥራት ጀመሩ—ይህም አዲስ፣ አሉታዊ ቃል ነበር።
የሃይማኖት ተጽዕኖ እና የሥርዓተ-ፆታ ደንብ መጣስ፡ የኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን እና ክርስቲያን ሚስዮናውያን የሥርዓተ-ፆታ ደንቦችን በመለወጥ ረገድ አስተዋፅዖ አደረጉ። የቤተ ክርስቲያን መሪዎች አሽቲሜዎችን መወገድ ያለበት "የድሮ የአረማዊነት አስተሳሰብ" አድርገው ተመለከቱ። ክርስትና ጥብቅ "ወንድ ወይም ሴት" የሚል ደንብ አመጣ። ይህ ደግሞ ለማንኛውም የተለየ የሥርዓተ-ፆታ መገለጫ ሰዎች አለመቀበልና ማሸማቀቅ እንዲጨምር አደረገ፤ በዚህም አሽቲሜዎች የማኅበረሰባቸውን ተቀባይነት አጡ።
የወንጀል ሕግ ተጽዕኖ፡ ለአሽቲሜዎች የመጨረሻው ትልቅ ችግር የሆነው ኢትዮጵያ አንድ ዓይነት የፍቅር ዝንባሌ ያላቸውን ድርጊቶች ወንጀል የሚያስቀጣ ሕግ ካወጣች በኋላ ነው። ምንም እንኳ የአሽቲሜዎች ማንነት በጾታዊ ሕይወታቸው ባይገለጽም፣ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነታቸው ለእፍረትና ለሕግ ችግር ቀላል ዒላማ አደረጋቸው። ይህ አዲስ ሕግ የቀሩት አሽቲሜዎች በባህላዊ ወንዶች መንገድ እንዲኖሩ፣ ባይፈልጉም እንኳ፣ አስገደዳቸው።
አሽቲሜዎችን እንደ ትግል ማስታወስ
የአሽቲሜ መጥፋት ማሌ ዘመናዊ የኢትዮጵያ ግዛት አካል ለመሆን የከፈለው ዋጋ ነበር። እነርሱ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነት የአገር ውስጥ ባህል እንደነበር የሚያሳዩ ጠንካራ ማስረጃዎች ናቸው፤ መጥፋታቸው ደግሞ "የምዕራባውያን አስተሳሰቦች" እንዴት እነዚህን የቆዩ ማንነቶች እንዳጠፉ ያሳያል። የደንሃም ጥናት የሚነግረን እነዚህ የውጭ አስተሳሰቦች፣ በመንግሥት ተቀባይነት ያገኙት፣ የሥርዓተ-ፆታ ልዩነትን ይጠብቅ የነበረውን የድሮ ሥርዓት እንደሰበሩ፣ የተለያየ ማንነትን እንዳጠፉ እና የተለየውን ሰው የማይቀበል ማኅበረሰብ እንደፈጠሩ ነው።
አሽቲሜዎችን ዛሬ ማስታወስ ማንነትና ሥርዓተ-ፆታ ኃያል ገዥዎች ጥብቅ ወሰኖችን እንድንቀበል ከማስገደዳቸው በፊት እዚህ አካባቢ በጣም ክፍት እና ተለዋዋጭ እንደነበሩ ያሳየናል። ይህም ልዩነት ከውጭ የመጣ አይደለም፤ ይልቁንም እውነተኛ የኛ ቅርስ መሆኑን ያረጋግጣል።
Gloria Victor
June 2026 | 362 |
| 20 | https://open.substack.com/pub/robinjoab/p/q-and-a-gays-in-ethiopia-2?utm_source=share&utm_medium=android&r=4utnvb | 318 |
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
