👳🏽ባለዕዳው
الذهاب إلى القناة على Telegram
ሁሉም ስለእኛ ነው ። መሆን ስለምፈልገው ፣ እንድትሆኑ ስለምፈልገው እና መሆን ስላለብን!
إظهار المزيد3 764
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
-77 أيام
-3230 أيام
أرشيف المشاركات
3 764
ሰው ሲደሰት ማየት የሚያመነጨው እርካታ እንዴት ያለ ውብ ነው በአላህ ።
ሀቢቢ ﷺ ከሰው ሁሉ ምርጡ ማነው ተብለው ተጠየቁና በመጨረሻም " ሰዎችን ከክፋቱ የጠበቀ " አሉ ። ለሰዎች ደስታ ሰበብ የሆነስ ምን ይሆን ደረጃው ?
-አለምን ከሞላው የኔነት ጭጋግ እንራቅ
-ካልጠቀመኝ ምናገባኝ ከሚል አስጠሊ እሳቤ እንሽሽ
- ለሰዎች በጎ መዋል ..ሰዎችን ማስደሰት የትርፍ ጊዜ ተግባር እስኪመስል ህይወት ተጨማላልቃለችና እሳቤያችንን እናፅዳ ።
ህይወትን የአመታት ትግል አናድርገው በአላህ ... በቃ ሰው ሄዶ ሄዶ ሰው ነው ! አስደስቱ ተደሰቱ ኑሩ ተኗኗሩ ።
ደስታችሁን በሌሎች ውብ ሰዎች ደስታ ስር ፈልጉ🤍
3 764
አንዳንዱ በሚሰራት ትንሽ ስራ ለቤተሰቡ የሚችለውን እያረገ የተረጋጋና ሰላማዊ ህይወት ይመራል .... ከፊሉ በየቀኑ ብዙ ሺዎችን እያዘዋወረ የቤተሰብነትን ጣዕም ትቶ የተቻኮለ ሀያት ይኖራል ።
ልክ እንዲሁ አንዳንዱ ከእጦቱም በተጨማሪ የሰዎችን ጓዳ እያየ መብቃቃትም ደስታም አጥቶ ይኖራል ... ከፊሉ አላህ ሀብት ሰጥቶት በአግባቡ እየተጠቀመ ተረጋግቶ በደስታ ይኖራል ።
ደስታና መረጋጋት በገንዘብ መጠን የሚወሰኑ ሳይሆኑ ሁሉም ለህይወት ባለው ፍልስፍና የሚገሩ ናቸው ።
ዱንያ ለናንተ ምንድናት ? እሱ ነው ዋናው ነገር ።
3 764
ዜናው
" -የዋጋ ግሽበቱ በዚ በዚ ፐርሰንት ጨምሯል
- በዚ በዚ አካባቢ ድርቅ ተከስቶ በመቶ ሺ የሚቆጠሩ ህዝቦች ረሀብ ተደቅኖባቸዋል
- ይህን ያክል ሰዎች ባልታወቁ ታጣቂዎች ተገድለው እንዲህ የሚሆኑት ታግተዋል
-እዚ እዚህ አካባቢ ለአመታት የቀጠለው ጦርነት ተባብሷል "
ህዝቡ
"- በእግሬ ሄጄ የታክሲውን ለቤተሰቤ ዳቦ ልግዛበት ?
- በየት በኩል ሄጄ ቤተሰቤን ከርሀብ ልታደግ
- ልጆቼን እንዴት ላስተምር
መንግስት
" -ግብር ጨምሩ
- ጦቢያ ለአለም አርዓያ የሚሆን እድገት አስመዝግባለች
- ጦቢያ ለነዋሪዎቿ ምቹና ለቱሪስቶች ተመራጭ ሆናለች
- ቢሊየን መድበን የሆነ ጫካ እናለማለን "
ኧረ መንግስትና ኑሮ - መንግስትና ህዝቡ አልስማማ አሉኮ .... ዱባይ እየኖሩ ነው እንዴ የሚመሩን😭
3 764
የምትጓጉለት ነገ " ድካም ፣ አለመቻል እና መገደብ'ን " የያዘ ነው ። አሁንን ለመኖር እንጣር ... ሲደክመን እንረፍ ስንሰበር ስብራታችንን እየሰነጠቅን መታመማችንን አቁመን ወደመፍትሄ እንሩጥ ።
በሉ ዛሬን እንኑር🤍
3 764
በጣም ዛልና ?
ሰዎች ተስፋ እየቆረጡ አንገታቸውን ለገመድ እየሰጡ ነው .... ወጣቶች ብዙ አልመው እርምጃ ለመጀመር ሲያስቡ ተተብትበው እየወደቁ ነው ። ውስጡም ውጪውም ለውድቀት የሚጣራ አልፎም የሚጠልፍ ጩኸት ሆኖባቸው ደክሟቸዋል ። አቃጆች አቅደው አቅደው ማህበረሰቡን በማያልቅ አስከፊ አዙሪት ነክረውት ተስፋውን በየዙሩ በየከፍታና ዝቅታው እያሳሱት ነው ..... ግን ይሁን ግድ የለም ።
ከአቃጆችም በላይ አቃጁ አላህ አለ አብሽሩ .... ሴራዎቻቸው ሁሉ ፈርሰው የተሻለ ነገር ይመጣል። ብቻ ታገሉ አትድከሙ....ነፍሳችሁን አበርቷት አላህ አለ.... ነገ አለ በሏት ። አብሽሩማ የልፋታችሁ ውጤት ህመም እንኳ ቢሆን አላህ ጋር ሚዛን አለው .... ጊዜው እስኪመጣ ግን ታገሱ በምትችሉት ሁሉ ታገሉ .... ጊዜው ቀርቧል ኢንሻአላህ ።
3 764
ለመኖር ስል እየነካካው ያለኋቸው ርዕሶች ሁላ ከመኖር ሲያርቁኝ ነው የማስተውለው ። አማኝ ለመሆን ስጥር ከጌታዬ መራቅ ለምን ይሰማኛል ? ለማወቅ ስጥር የውሸት ትርክት የማጎር አይነት ስሜት....ለመጠንከር ስሞክር ድካም... ለምን ?
ጊዜያቶች ባለፉ ቁጥር እቺ አለም የውሸት ሹራብ እየደረበች ...የእውነትን ብርሀን እያደበዘዘች ...የመኖርን ጣዕም እያጎመዘዘች ነው ።
እቺ አለም እንደነበረችው አይደለችም...መሆን እንዳለባትም አይደለችም ። ከዘመናት በፊት የተቀየሰ አዲስ መንገድ ሳይኖር አይቀርም ። ይህ መንገድ ሁሉን ነገር አሳጥቶናል ...እምነታችንን ፣ ህይወታችንን ፣ እኛነታችንን ሁሉ ነጥቆናል ። አማኝነትን በራስ ወዳድነትና በተጨቃጫቂነት ለውጦብናል...ህይወታችንን ለሌሎች በማቀበል ስለሌሎች የሚገበር ተራ የጊዜያት ጥርቅም አድርጎብናል...እኛነታችንን ለማናውቀው እና ፍፁም ደስታችንን ለሚመጠው ሌላ ነገር አሳልፎ ሰጥቶብናል ።
ይህ ሌላ ነገር ግን ምንድነው ? እየኖርን ያለነው ምንድነው ? ምን እየተፈጠረ ነው ግን?
ብቻ መኖር ያለብን ህይወት አለ ....ያን ህይወት ፈልገን ማግኘት አለብን ።
3 764
ሁለት ወፎች በአንድ ሽቦ አጥር ውስጥ ታስረዋል ... ወፎቹ በተጣሉ ቁጥር አሳሪው ላባቸውን ይነቅላል ። በዛ ቅፅበት መጣላታቸውን ትተው ያጉረመርማሉ ...ከጥቂት ጊዜ በኋላ ወደጥላቸው ይመለሳሉ አሳርያቸውም ላባቸውን መንቀል ይቀጥላል ።
ከረጅም ጊዜ በኋላ የማሰሪያውን በር ከፈተላቸው ግን ... ግን አልበረሩም አላመለጡም ... አዎ ክንፍ አልነበራቸውም ።
እኚህ ወፎች እኛው ነን ... እኛው ሙስሊሞች !
ሀቢቢﷺ እንዲህ ቅጡ የጠፋውን ኡማቸውን ቢያዩ እንዴት ያማቸው ይሆን ... የማንም መጫወቻ ሆኖ እርስ በርሱ ለመቶ አመታት ሲታገል የከረመውን ኡማ ቢያዩ ምን ያህል ያማቸው ይሆን ? ጠላቶቻቸው ለመቶ አመታት የሚዘልቅ ሴራ አሲረው ኢስላምን ያፈራርሳሉ የነሱ ኡመት እርስ በርስ ይፋተጋል ... ያለአላማ የርስ በርስ ትግል ራሱንና ዲኑን ያደክማል ።
3 764
በቁሙ የጊዜ ክምር ማንነቱን በከንቱነት ወዳለመኖር እንዲሄድ የፈቀደው ትውልድ ከምን ጊዜውም በላይ ለእምነቱ ተቆርቋሪ ሆኗል ¡
ሁላችንም አንድ ቁስል ተሸክመናል ..... አለመኖር። ይህን ቁስል የምናስተናግድበት ሂክማውም ...የመኖር አቅሙም የለንም ምክንያቱም አለመኖራችንን ለመርሳት ሄደን የተጠለልንበት ጥላ "ዲን" ነው ።
የእምነታችንን መሠረቶች ሁሉ ከማመን በዘለለ ወደነፍሳችን አላስገባንም .... አምልኮ የምንለው ሁሉ አድካሚ ድርጊት ሆኖብን የጊዜ ክምራችንን ሁሉ በባዶነት ውስጥ እየፈረካከስን እየሞላን ነን ።
ነፍሳችንን አለማችንን የምንዋጋበት አንድ ተራ መሣሪያ የሌለን ጦረኛ ነን .... ሀሳባችንን አስገዝተን ያለ አንድ መሣሪያ ከተመሣሣዬ "የሀሳብ ባርነት" ውስጥ ካለ አካል ጋር እየተዋጋን አለመኖራችንን ...ባርነታችንን የዘነጋን ።
እያልኖርን ያለነውን ዲን ሽሽት ዲን ስር የተጠለልን ... መገዛት ጠንቶን ተገዢ በሚያስመስል ርዕስ ውስጥ የምንርመሰመስ አመፀኞች ። ሌት ተቀን ሰዎችን አተልቀን አላህን አሳንሰን በ አመፅ ባህር ውስጥ የምንዋኝ ግና በእምነታችን ፍፁማዊ ለመምሰል ሌላ የማስመሰል ትግል የምንታገል ወዳቂዎች ።
በጌታችን ትዕዛዝ ውስጥ መኖር ጠንቶን የአለመኖርን መራራ ፅዋ እየቀመስን አለመታዘዛችንን ሽሽት ወደዲኑ ተሸጉጠን ለመርሳት የምንጥር እፍረት የለሾች ።
ማነን ? ቆይ ማነን ?
ቁርጭራጭ የህክምና ፅሁፎችን አንብበን ሀኪም የሆንን ? የሆነ ቦታ ስለግንባታ አንብበን ኢንጂነር የሆንን ? እስቲ ማነው በቁርጥራጭ ንባብ ዶክተር የሚጋፈጠው ? ማነው በሶስት ቀን ፖድካስት እራሱን አዋቂ አርጎ ኢንጂነር የሚከራከረው ?
እስልምናና አስተምህሮቱ ከህክምና ያነሰ ቦታ ነው ያላቸው ? የእስልምና አስተምህሮት ከኢንጂነሪንግ ያነሰ ቦታ ነው ያለው ? ምነው ዲናችን ላይ ሲሆን ደረታችን አበጠ ? የኪታብ ስም የማያነበው ሁሉ ምንው አዋቂ ነኝ ብሎ ቁጭ አለ !
" ያወከውን አስተላልፍ " የሚል ሀዲስ ስላለ ነው ? እሺ ልክ ነው ግን መች አወቅን ?ለእያንዳንዱ መረጃ ወደ ሰርች ባር የሚሮጥ ሁሉ ዲን ላይ ቃዲ ይመስል ሲያከፍር ሲያሰልም ... ለዲኑ ሲታገል ሲሳደ* ይውላል ።
ኧረ ምን አይነት እፍረት የለሽ ትውልድ ነን በአላህ ።
3 764
አሁን ረጅጅም ፅሁፍ ልለቅ ነው ወይ ደግሞ አጭር ። ወይ ወቀሳ ነው ወይ ሌላ ነገር ነው .... ለማን እንደምፅፍ አላቅም ለራሴ ...ለናንተ ? እንጃ ብቻ
3 764
©️©️©️
ቁድወቱና ፊል ኢብቲሳመህ
ስለ ዉዱ ነብያችንﷺ ሌሊት አብዛኞቻችን እንሰማለን እንዲህ ሲባል...
"ረሱል ﷺ ለሊት እግራቸው እስኪሰነጠቅ ድርስ ይቆሙ ነበር... ኡመቴም እያሉ ያለቅሱ ነበር።"
በዚህ መንገድ ግን አስበነው እናውቃለን? እንደዚያ ሌሊቱን በእንባ ሚያሳልፉት ነብይﷺ ፤ ቀኑን በፈገግታ እንጂ አይታዩም ነበር።
ጀሪር ኢብኑ ዓብዲላህ እንዲህ ይላል...
"በሕይወቴ አንድም ቀን አላለፈም የኔው ነብዬ ﷺ ሲያዩኝ ፈገግ ያሉ ቢሆን እንጂ"
በፈገግታቸው ነው ከሰው ሁሉ ልብ የገቡት።
በፈገግታቸው ነው ያነባን አይን ያበሱት
በፈገግታቸው ነው የሰሃባን ተስፋ ያለመለሙት
ፈገግታቸው አንድ የጥሪ መንገድም ነበር።
ፈገግታቸው የመሃባ መንገድም ነበር።
ፈገግታቸው ብዙ ብዙ ነገር ሆኖ አልፏል።
ለዚያም ነው በኛ ዉስጥም ሱና ሊሆን የቻለው
ፈገግ እንበል ፣ የሰዎችን ሕይወት በፈገግታችን እናድሰው የቁድዋችን የተፈቃሪያችን ነብይ ﷺ መንገድ ነዉና
ሰሉ ዓለል ሀቢብ
3 764
ሀቢቡና ﷺ እጅግ ጠንካራውና ልስልሱ ፍጡር ነበሩ ።
ምድርን ከረገጡ ባለምሉዕ ስብዕና ግለሰቦች ቁንጮው ናቸው ። በነሱ መላክ ከተደረማመሰው የክህደት ተራራ ዘወር ብለን አኗኗራቸውን ብቻ ብናይ ..... ነብይ ከመሆናቸው በፊት ያለውን ረጅም ዘመናቸውን ብንቃኝ ታሪካቸው እጅግ ውብ ነው ።
ሰው የመሆን ስርዓት የሚቀዳባቸው ... ሰው ሆኖ መኖር የሚኮረጅባቸው ሰው ሆነው የኖሩ መኖርን አሳምረው አለምን ያበሩ እጅግ ውቡ ሰው!
ሀቢቡና ﷺ ነብይ ከመሆናቸው በፊትም ሆነ በኋላ ለፍጡር ሁሉ ሞዴል የሚሆኑ ... ለኡማቸው ኮቴያቸውን መከተል አስገዳጅ የሆኑ ድንቁ ስብዕና ናቸው ።
እነሱ የስርዓት መለኪያ...የመኖር መስታወት ናቸው ። ለእያንዳንዱ የመኖር ቅያሳችን ትክክለኛ መንገዱ መምረጫችን ... ከጠፋንበት የበታችነት በረሀ የመውጫ ኮንፓሳችን ናቸው ።
አደበ ቢስነት ... ንቀት ... ጨቅጫቃነት...አርቆ አለመመልከት... ትላልቅ ነገር አለማሰብ ... የመኗኗር ስርዓት አለማወቅና ሌሎች መጥፎ ባህሪዎች ሁሉ ከአለሙ ብርሀን ፍፁም ተቃራኒ የሆኑ ነገራቶች ናቸው ።
አዎ ሁላችን በጎ ከሚመስለን ባህሪያችን ጋር ከሀቢባችን ፍፁም ተቃራኒ ፍጥረት ነን ። ለዲኑ የምንቆረቆርበትና ዲኑን ለመጠበቅ የምንሞክርበት መንገድ ሁሉ የነሱ ተቃራኒውና አስቀያሚው ማንነት ነው ።
ሰው እንሁን ! ሰውነት ላይ ክፋት የለም ... ሰው እንሁን ! ሰውነት ላይ ጭካኔ የለም ...ሰው እንሁን ! ሰውነት ላይ በጎነት እንጂ የለም ።
በመንገዳቸው አኑሮ ይግደለና 🙌
3 764
የሆነ ፅሁፍ አይቼ አረካኝ😄
" በፍፁም ጩኸትና ጭቅጭቅ tolerate ማድረግ አልችልም ለዚያ ወይ ተረጋግታችሁ አውሩኝ ወይንም ምንም አታውሩኝ" ይላል...
ልክ የሆነ ሰው ሊጨቃጠቅ ድምፁን ከፍ ባረገበት ቅፅበት
- ህይወት ያስጠላኛል
- ጓደኛዬ ስለሆነ ይቆጨኛል
- ስለተዋወኩት ራሴን እወቅሳለው
- ውስጤ ሲፈረካከስ ይሰማኛል
እና ይደክማኛል
ስለዚህ ምንም ብትል ብዙ ሀሳብ ውስጥ ስለምገባ አልሰማህም ......በሰላም አውርተን እንፍታው pls 😭
3 764
"አንዱን አልሞላንም ኻሊቁ ካዘዘን
ጨለማው ላይ ቀረን እንዳሻው ተጉዘን
አንድ ያረጉት ኡማን ቅርንጫፍ አሲዘን
መጠለል ያምረናል ዋርካውን ገዝግዘን "
በሶሪያና ሊባኖስ ወታደሮች መሀል የተደረገውን ንግግር እያየሁኝ ውስጤ ተላወሰ ። ስለጋራ ጠላታቸው እያወሩ እርስ በርስ ዱዓ እየተደራረጉ የሚያሳይ ቪዲዮ ነበር ። ሀቢቡና ሙሀመድ ﷺ ለአመታት ጥረው ግረው የገነቡትን ሁሉ አፍርሰን ... ዘርግተው ካስቀመጡት መንገድ አፈንግጠን ድንበራችንን "ሙስሊም መሆን" ከሚል መስፈርት አውጥተን ካርታ ላይ በተሳለ መስመር አርገን አሁን ካለንበት ደርሰናል ። ከኢስላም ወንድማማችነት ርቀን በብሄር ቦለቲካ ተጠልፈን የኢስላምት ተልዕኮ ረስተናል ።
በመስመር የተሰማመረውን ሀገርና አህጉር አንድ ስለማድረግና ስለማሳደግ ከኩፋሮች ጋር እየመከርን እየጣርን ስለኢስላም ሲሆን ግን ረሱል የተከሉትን የአንድነት ዋርካ መገዝገዝ ላይ እንጠመዳለን ።
እንደው አላህ የምር ባሮቹ ያድርገን ... የመልዕክተኛውን መንገድ አጥብቀን ይዘን ዲኑን ከሚነስሩት የሰራዊቶቹ አንድ አካል ያድርገን ። ለሱ ፍላጎት የምንኖር ...የምንሞት ያድርገን ።
3 764
ስለፈለግነው ብቻ አሳክተን የኛ ማረግ የምንችል የሚመስለንን ነገር.....ስላልፈለግን ብቻ ከኛ አርቀን ሰላም መሆን የምንችል የሚመስለንን ነገር አላህ ያርቅልን ። የምንጎዳው ባመንበት ልክ ነውና !
ሰላም ለልባቹ❤️🩹
3 764
ጨረቃዋን ተመልከት ሙሉ ፊቷን ከነሙሉ ፈገግታዋ ወደምድር ወዳቅጣጨችው..... የተዘሩ ከዋክብቶችን ...ንፋስ ያንገላታቸው ረጃጅም ዛፎችን....ምድርን አጥብቀው የያዙ ብርቱ ተራሮችን ሁሉ ተመልከት ....እነሱም ይመለከቱሀልና ።
በል ራስህን ተመልከት.... አካላቶችህን ገምግም እጅና እግርህን .... ደረትና ትከሻህን ... ሁሉን ተመልከት ። እኚህ ነገሮች እንኳ አንተን አይደሉም .... እኚህ አካላቶች እንኳ ላንተ ህያውነት ያገለገሉ ፈራሽ ፍጥረቶች እንጂ ሌላ አይደሉም .... አካላቶችህ እንኳ ባንተ ላይ ምስክር የሚሆኑ ስጋዎች እንጂ ሌላ አይደሉም ።
ተረጋጋማ .... ቀስ ብለህ ፊትህን እይማ ብቻህን ነህኮ ! አካላቶችህ በራሱ እዚው ቀሪ ፈራሾች ናቸውኮ.... ታድያ ለምን ራስህን ትበድላለህ ? ለማን ብለህ ህያው አንተነትህን ከጥልቁ ገሀነም ትሰዳለህ ? ላንተ ያለ አላህ ማን አለህ ? ለማን ብለህ አላህን ትተዋለህ ?
ዙርያህን እይማ ብቻህን ነህኮ🙂
