ar
Feedback
ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻‍♂️

ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻‍♂️

الذهاب إلى القناة على Telegram

እኔ ምናቤ ውስጥ የተፈጠረብኝን አልያም አንብቤ የወደድኩትን አሰፍራለሁ። . . . ለማንኛውም ሀሳብ ወይም አስተያየት inbox:- @Beck1me

إظهار المزيد
1 096
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+37 أيام
+430 أيام
أرشيف المشاركات
የባከነ ጊዜ! “በአንድ በሚፈስ ወንዝ ውስጥ ከአንድ ጊዜ በላይ ማቋረጥ አትችልም” ይባላል፡፡ እውነት ነው! ይህ አባባል ሲተነተን፣ አሁን በእግሮችህ ተራምደህ የገባህበት ወንዝ አልፏል፡፡ ስትገባበት የነበረው ውኃ ቀጥሎ ለሚፈስሰው ውኃ ስፍራውን ለቆ በመሄዱ ምክንያት ተመልሰህ ብታቋርጥ ሌላ ውኃ ነው የምታገኘው፡፡ ወንዙ አንድ ነው፣ ውኃው ግን የተለያ ነው፡፡ ፍሰቱ ተመሳሳይ ነው፣ ወንዙ ይዞት የሚመጣው ነገር ግን የተለያየ ነው፡፡ የአፈሳሰሱ ሂደት ያው ነው፣ የፈሰሰው የውኃው አካል ግን ሌላ ነው፡፡ የጊዜያችንም ጉዳይ እንደዚሁ ነው፡፡ ⏱️ የሰዓታት፡- ነግቶ እስኪመሽ የሚመጡትና የሚሄዱት ሰዓታት በተመሳሳይ ስም ይጠራሉ፣ ይዘውት የሚመጡትና ይዘውት የሚሄዱት ምርጫ ግን የተለያየ ነው፡፡ ⏱️ የቀናት፡- ከሰኞ እስከ እሁድ ያሉን ቀናት በስም ተመሳሳይ ናቸው፣ ይዘው መጥተው የሚያሳልፉት እድል ግን ልዩ ልዩ ነው፡፡ ⏱️ የወራት፡- በየሰላሳ ቀናት የሚቀያየሩት ወራቶች መምጣትና መሄድ አንድ አይነት ነው፣ እነሱም ቢሆኑ ደግሞ የማይገኝ እድልን ይዘው መጥተው ጥርግ ብለው ይሄሉ፡፡ ጊዜ እንዲህ ነው! ሲመጣና ሲሄድ ያለው “አንድ አይነትነት” ያታልላል፡፡ የምንባንነው በወቅቱ ማድረግ የምንችለውን ነገር ማድረግ የማንችልበት ቀን ከመጣና ኋላ ከቀረን በኋላ ነው፡፡ ዶክተር እዮብ ማሞ

ከሁሉም ነገር ተመችቷቹ አትደርሱም ትንፋሽ አጥሯቹ ጉልበት ክዷቹ ደክሟቹ ተዝለፍልፋቹ ነው የምትደርሱት እንዲሁ የምንደርስበት ነገር የለም ልማር ቢሉት ያው ነው ላስተምር ቢሉት ያው ነው ልመንን ቢሉት ያው ነው ቢያገቡም ያው ነው ቢነግዱም ያው ነው ምንድነው ተራራ ያልሆነ ነገር??? የሰው ህይወቱ በዚህች ምድር ላይ ብርቱ ሰልፍ ነው፣. . . ሰልፍ ውጊያ ነው፣ ከአጋንንት እና ከዚህ አለም አኗኗር ጋር ይዋጋል የሰው ልጅ፣ ስለዚህ ያንን አውቀን የምንኖረው ነው አባ ገ/ኪዳን

private ነገር ይኑርህ. . . እንደምታስበው ሁሉም ሰው ባንተ ነገር ደስተኛ የሆነ አይምሰልህ. . . ላንተ ተኝቶ የማያድር ብዙ ሰው አለ. . . እና ለምን ብለህ ነው ሁሉንም ነገርህን ምታሳየው man. . . በR/ship'ም እንደዛ ነው እስቲ ዝም ብለህ tiktok or ሌላ social media ላይ ድሮ ሲያስቀኑን የነበሩ couples አሁን የት እንዳሉ ተመልከት. . . ለምን ይመስልካል?? የሰው አይን ከምታስበው በላይ አደገኛ ነው . . . ድጋሚ ማንንም ሰው እንዳታምን አድርጎክ ነው ሚጎዳክ. . . ምንም ነገር ስትጀምሩ ፈጣሪን አስቀድሙ እርሱ  አሳምሮ ይሰጣቹሀል። ዝም ብለህ ስራ. . . ማንም የማይገምተው ሰው ሁን. . . ያኔ ካንተ በላይ አሸናፊ አይኖርም

አንዳንድ ጊዜ ሰው ብቻውን የሚቀርበት ቀን አለ ብቻውን የሚቀርበት ቀን ማለት ነው ምንም. . . አንተን እኔ ሞቼም አልተውህም ያለህ ሰው ሁሉ ምንም. . . የሰው ልጅ የልፋቱን ዋጋ እግዚአብሔርን ካደረገ ሰው ምንም ይንሳው በሰላም ይኖራል በዚህ አለም ከባዱ ነገር ልብን ሰላም ማድረግ ነው ከሰው ጋር በሰላም ለመኖር መቼም ዋሽቶም ቀጥፎም አስመስሎም ይ'ኖራል፣ ልብን ሰላም ለማድረግ ግን ዋሽቶም ቀጥፎም አስመስሎም ማረግ አይቻልም. . . ልብን ሰላም ለማድረግ እግዚአብሔርን ዋጋ ማድረግ ነው አባ ገ/ኪዳን

🌿✨ መልካም አዲስ ዓመት! ✨🌿 አዲሱ ዓመት የሰላም፣ የጤና፣ የደስታ፣ የፍቅርና የበረከት ዓመት ይሁንልን። ያለፈው ዓመት ያስተማረንን ትምህርት ይዘን፣ አዲሱን ዓመት በተስፋ፣ በእምነትና በአዲስ ●ጉልበት እንቀበል። ●ምኞታችሁ ይሳካ፣ ●ስኬታችሁ ይበዛ፣ ●ፍቅራችሁ ይጠና፣ ●ቤታችሁ በሰላም ይሞላ፣ እያንዳንዱ ቀንም ከቀድሞው የተሻለ ይሁን። እንኳን ለ2019 ዓ.ም. አዲስ ዓመት በሰላምና በጤና አደረሳችሁ! 🎉

Follow, share, comment and engage yargu🙌🏾 that's alot of help. Let's challenge the limits of humanity!!!😮‍💨 https://vt.tiktok.com/ZSqUtqAMM/

"እወድሀለው" ብላኝ በረጅሙ ተነፈሰች. . . አተነፋፈሷ ዜማ ነበረው ዘወትር ሊሰሙት እንደሚናፍቁት አይነት አንዳንዴ ምን የሙዚቃ  መሳርያ ትወዳለህ ሲሉኝ የእሷ ትንፋሽ ማለት ይቃጣኛል. . . እነዛ እንቧይ የሚያክሉ እይኖቿን አይኔ ላይ ተክላ "ዝም አልክ እኮ እ. . ." ስትለኝ "እኔም" ብዬ አንገቴን ደፋው ከዛች እለት ጀምሮ "እኔም" ተተርጉማ ሌላ መልክ ያዘች የመውደዴ ጥግ ተለካበት. . . ተመዘነበት ወደቅሁ. . . አንዳንዴ በዚህች ቃል ተረግሜ ነው የፍቅር አድባር የሸሸኝ እላለሁ. . .

"እወድሀለው" ብላኝ በረጅሙ ተነፈሰች. . . አተነፋፈሷ ዜማ ነበረው ዘወትር ሊሰሙት እንደሚናፍቁት አይነት አንዳንዴ ምን የሙዚቃ  መሳርያ ትወዳለህ ሲሉኝ የእሷ ትንፋሽ ማለት ይቃጣኛል. . . እነዛ እንቧይ የሚያክሉ እይኖቿን አይኔ ላይ ተክላ "ዝም አልክ እኮ እ. . . " ስትለኝ "እኔም" ብዬ አንገቴን ደፋው ከዛች እለት ጀምሮ "እኔም" ተተርጉማ ሌላ መልክ ያዘች የመውደዴ ጥግ ተለካበት. . . ተመዘነበት ወደቅሁ. . . አንዳንዴ በዚህች ቃል ተረግሜ ነው የፍቅር አድባር የሸሸኝ እላለሁ. . .

ስኬትህ ጭንቅላትህ ላይ አይውጣ ውድቀትህም ልብህ ውስጥ ዘልቆ አይግባ . . . ሲሳካልህ ተናነስ፣ ስትወድቅ ቀና በል 🖤🙌🏼

ግጥም የምትወዱ እና ለጥበብ ግድ የሚላቹህ ሁሉ የኔ page follow በማድረግ ከበረከቱ ተቋደሱ። https://vm.tiktok.com/ZN8YCKWy1/

ግጥም የምትወዱ እና ለጥበብ ግድ የሚላቹህ ሁሉ የኔ page follow በማድረግ ከበረከቱ ተቋደሱ። https://vm.tiktok.com/ZN8YCKWy1/

አንድ መፅሐፍ ላይ ያነበብኩት በጣም ስለ ተመቸኝ ለእናንተ ላካፍላችሁ ወደድኩ! ብረት ጽኑ ነው እሳት ያሸንፈዋል፤ እሳት ብርቱ ነው ውሃ ያሸንፈዋል፤ ውሃ ብርቱ ነው ደመና ይሸከመዋል፤ ደመና ኃያል ነው ንፋስ ይበትነዋል፤ ንፋስ ብርቱ ነው መሬት ይገድበዋል፤ መሬት ጽኑ ነው የአዳም ልጅ ያሸንፈዋል፤ የአዳም ልጅ ብርቱ ነው ሀዘን ያሸንፈዋል፤ ኃዘን ጽኑ ነው ጠጅ(መጠጥ )ያሸንፈዋል፤ ጠጅ ብርቱ ነው እንቅልፍ ያሸንፈዋ፤ እንቅልፍ ብርቱ ነው ሞት ያሸንፈዋል፤ የዚህ ሁሉ ነገር ማጠቃለያው ምን እደሆነ ታውቃላችሁ. . .? ነገርግን ሁሉንም ሴት ታሸንፈዋለች ብሎ ነው ሀሳቡ የሚደመድመው፡፡ አያችሁ አባቶች ተመራምረው በህይወት ልምዳቸው ቀምረው የደረሱበት አንድ ሀቅ የዚህ አለም የመጨረሻዋ አሸናፊ ሴት መሆኑዋን ነው። በሴት የማይሸነፍ ምንም ነገር የለም ሞትም ጭምር. . . በታሪክ ሞትን ያሸነፈው ክርስቶስ ብቻ እንደሆነ ነው የማውቀው፡፡ ታድያ ሴት ሞትን እንዴት አድርጋ ታሸንፈዋለች ብዬ አያቴን ጠይቄ ነበር. . . "ሞት የሚሸነፍበት ብቸኛው ዘዴ መውለድ ነው ልጅ በመውለድ ሞትን ታሸንፈዋለች. . . ጨካኙ ሞት እሷን ገደልኩ ሲል እሷ የወለደቻቸው ሌላ ሶስት እና አራት ልጆች ይጠብቁታል፡፡ ስራ አብዝታበት ታሰቃየዋለች. . .፡፡"

« በሰው ሕመም ራስን ማጽናናት ቁስል ላይ ጨው እንደመነስነስ ነው "የባሰም አለ" እያሉ መኖር ራስን ማታለል እንጂ ራስን ማፅናናት አይሆንም ሕመም በሌሎች ሕመም አይለካም ቁስልም የሌሎችን ቁስል በማየት አይድንም » አደራችሁን ለማፅናናት በሚል ምክንያት የባሰም አለ አትበሉ የሚብሰው ያ ሰው ያለበት ወቅታዊ ችግር ነው 🎀🥀

Repost from The Dev
Get $175 in free AI API credits from AgentRouter Supported models: > OpenAI GPT 5.6 SOL > Claude Opus 4.8 > Claude Opus 5 lin
Get $175 in free AI API credits from AgentRouter Supported models: > OpenAI GPT 5.6 SOL > Claude Opus 4.8 > Claude Opus 5 link https://agentrouter.org/register?aff=8d6L > sign up With a GitHub account (least 1 year old) > Generate your API key > Check your balance in Wallet Credit and non withdraw money it used developers and builder. https://t.me/+9qX11QsL6IQ1NGQ0 https://t.me/+9qX11QsL6IQ1NGQ0

አፈሳ ሰው በመልኩ ይኖር መስሎሽ በቁንጅናሽ ከመኮፈስ እድልሽን ተጠቀሚ ነይ እፈሺኝ ሳልታፈስ::
ተሻለ ቸርነት

በቀኝ ይሁን በግራ ወይም በጀርባ እና በሆዴ በየቱም አቅጣጫ ብተኛ እንቅልፍ እኔን ከድቶኛል። የከዳኝ እሱ ብቻ አይደለም ሁሉም በክህደቱ መርዞኛል። ሰዎች ከቤቴ ሊለቃቅሙ ይመጣሉ፤ ጓዳዬ ባዶ በሆነ ግዜ በመጡበት በር ይመለሳሉ። እናም በባዶ ወንበሬ ላይ ተቀምጠው የነበሩ ሰዎችን አስታውሳለሁ። አዎን ቡና ከቀዘቀዘ ወዲያ ጥፍጥናው  እሬት ነው። የግቢዬ አበባዎች እንደኔ ተረስተው ደረቅ ቅጠል ያንጠባጥባሉ፤ አየሩ ይበርዳል ፤ሰማይ ጥቁር ደመና ቋጥሯል። ማስተዋል በቂ ነው ጎዳናው በጠቅላላ ለሁሉም ነገሮች ፍላጎታቸውን አጥተዋል። -ቡናው ቢመረኝ የምውጠው አማራጭ ስላጣው ነው። እንደቀዳውት ስለረሳውት ፈቃዴ መዘንጋቴ ስለሆነ. . . -የውስጤን እሳት ለማብረድ የለኮስኩት ሲጋራ አልቋልና ጣቶቼን ለበለባቸው። በደንብ ልቃጠል! የጀመርኩት እሳት ነው የሚጨርሰኝ. . . -ሁሌም ከዛሬ ጀምሮ እቀየራለሁ የእውነት እለወጣለሁ የሚል መሃላዬ ቀዝቃዛ ጸጸት በጭኔ ስር ይሰዳል። ይበለኝ! ስለራሴ እያወራው እራሴን የረሳው እኔ ነኝ. . .።

በቀኝ ይሁን በግራ ወይም በጀርባ እና በሆዴ በየቱም አቅጣጫ ብተኛ እንቅልፍ እኔን ከድቶኛል። የከዳኝ እሱ ብቻ አይደለም ሁሉም በክህደቱ መርዞኛል። ሰዎች ከቤቴ ሊለቃቅሙ ይመጣሉ፤ ጓዳዬ ባዶ በሆነ ግዜ በመጡበት በር ይመለሳሉ። እናም በባዶ ወንበሬ ላይ ተቀምጠው የነበሩ ሰዎችን አስታውሳለሁ። አዎን ቡና ከቀዘቀዘ ወዲያ ጥፍጥናው  እሬት ነው። የግቢዬ አበባዎች እንደኔ ተረስተው ደረቅ ቅጠል ያንጠባጥባሉ፤ አየሩ ይበርዳል ፤ሰማይ ጥቁር ደመና ቋጥሯል። ማስተዋል በቂ ነው ጎዳናው በጠቅላላ ለሁሉም ነገሮች ፍላጎታቸውን አጥተዋል። -ቡናው ቢመረኝ የምውጠው አማራጭ ስላጣው ነው። እንደቀዳውት ስለረሳውት ፈቃዴ መዘንጋቴ ስለሆነ. . . -የውስጤን እሳት ለማብረድ የለኮስኩት ሲጋራ አልቋልና ጣቶቼን ለበለባቸው። በደንብ ልቃጠል! የጀመርኩት እሳት ነው የሚጨርሰኝ. . . -ሁሌም ከዛሬ ጀምሮ እቀየራለሁ የእውነት እለወጣለሁ የሚል መሃላዬ ቀዝቃዛ ጸጸት በጭኔ ስር ይሰዳል። ይበለኝ! ስለራሴ እያወራው እራሴን የረሳው እኔ ነኝ. . .።

በሕይወት ውስጥ ብቸኛው ችግርህ፣ አንድ ነገር ሊሆን በሚገባው መንገድ ሊሆን አልቻለም ብለህ ማሰብህ ነው፡፡ አንድ ነገር ሊሆን ይገባዋል ብለህ ባሰብከው መንገድ ካልሆነ፣ ምናልባት ያ ነገር የሆነ ሰው በሚፈልገው መንገድ ሆኖ ያ ሰው ተደስቶበት ሊሆን ይችላል፡፡ ብዙ ሰዎች በአንድ ላይ “በፈጣሪ እናምናለን” ይላሉ፤ ስለዚህ ምናልባት ያ ነገር በእነርሱ መንገድ ሆኖ ይሆናል፡፡ በመሰረታዊነት ሁሉም ነገር አንተ ሊሆን ይገባዋል በምትለው መንገድ አይሆንም፡፡ እስቲ አንተ የምታስብበትን መንገድ ተመልከት ፤ ከሁለት አመት በፊት የምታስበውና ዛሬ የምታስበው ተመሳሳይ ነው? አይደለም፡፡ ስለዚህ ምናልባት ከሁለት አመት በፊት ትፈልጋቸው የነበሩት እነዚያ ነገሮች ባለመሆናቸው ደስተኛ ነህ፡፡ ነገር ግን ያንን ለማስተዋል ሁለት አመታት ፈጅቶብሃል፡፡ አስፈላጊው ነገር የሕይወት ተሞክሮህ ምን  ያህል ጥልቅና አስደሳች መሆኑ ላይ ነው፡፡ የሕይወት ኬሚስትሪ

ወጣት ሳለህ እራስህ ማን እንደሆንክ መመርመር አለብ!!! ለምን አዘንኩ? ለምን ተጎዳሁ? ለምን ከፋኝ? ለምን ደስታቢስ ሆንኩ? ለምን ልቤ ተሰበረ? የእነኝህን ነገሮች መንስኤ እራስህ ተመራምረህ ማግኘት አለብህ:: በማንም በምንም ላይ ጥገኛ ሳትሆን ለዚህ ደግሞ የግድ ልዩ ትኩረት ለራስህ  መስጠት አለብህ:: ግንሳ እኛ ችግሮቻችንን ማምለጥ እንጂ ማወቅ (መረዳት) አንፈልግም:: ችግሮቻችንን መሸሽ እንጂ መቆጨት አንችልም ለዛም ነው ችግሮቻችንን  ለሚያብራሩልን ወይም ስሜታችንን ለሚጋሩን ነገሮች ትኩረት የምንሰጠው::

አንዳንድ💭 . . አንዳንድ መተዉ መተዉ ብቻ አይደለም ዉስጡ እንደገና  መፈለግም አለበት. . . አንዳንድ መሄድ መሄድ ብቻም አይደለም የሄዱበትን ዞሮ ደጋግሞ ማየትንም ይጨምራል. . . አንዳንድ ናፍቆት የማይብራራ ቅኔ ነዉ. . . አንዳንድ ቦታ ቦታ ብቻ አይደለም እልፍ ትዝታዎችን ተሸክሟል. . . አንዳንድ መረጋጋት ዉስጥ የማይታይ ማዕበል አለ. . . አንዳንድ ሰዎች ትናንት ብቻ አይደሉም በሌሉበት ነገም ሕያዉ ናቸው. . . አንዳንዴ ከጊዜ ጋር ታግለዉ ከመረሳት የሚረሱ ሰዎች. . .