ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
前往频道在 Telegram
እኔ ምናቤ ውስጥ የተፈጠረብኝን አልያም አንብቤ የወደድኩትን አሰፍራለሁ። . . . ለማንኛውም ሀሳብ ወይም አስተያየት inbox:- @Beck1me
显示更多1 097
订阅者
无数据24 小时
-57 天
-1030 天
帖子存档
1 097
Repost from ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
እሳት ወይ አበባ... 🌸
ለአመታት አብራኝ ኖራ የተለየችኝ ያህል ምሬት ተሰማኝ፡፡እያንዳንዷን እርምጃ ስራመድ ደግሜ የማላገኛት መሆኔ እየታወሰኝ አዘንኩ፡፡የሆነ ነገሬ እሷ ጋር ቀርቷል፡፡ባዶ ሆኛለሁ፡፡መጠጥ አብዝቼ መጠጣቴ ጠቅሞኝ እንጂ ከአጠገቧ ለመራቅ ድፍረቱም አይኖረኝም ነበር፡፡አይ ሰው ሃሃሃሃሃ ሳቅኩኝ፡፡ከእንግዲህ እኔ ጋ የቀረው ሳቋ ብቻ ነው፡፡
አስፓልቱን ጨርሼ ወደ ሰፈሬ የሚያስገባውን ኮብልስቶን ይዤ በጨለማው እየተደናበርኩ ወደ ፊት ቀጠልኩ፡፡በቃ አላገኛትም ቲሽ! ተበሳጨሁ፡፡ለምን ሰማኀት?ለምን በአንዴ ወድጃት ቀረሁ?ለምን ስልካችንን እንዳንለዋወጥ ህግ ስታወጣ ተስማማሁ?ለምን አብራኝ እንድትቆይ ለመጠየቅ ድፍረቱን አጣሁ?ለምን ዞሬ ሳላያት አቅፌ ሳልሰናበታት ተለየኀት?
በድን ሰውነቴን እየጎተትኩ ከፍራሼ ላይ ወጣሁ፡፡በማየው ነገር ሁሉ እየታየችኝ ስቸገር መብራት አጠፋሁ፡፡ሃሃሃሃሃሃ ደሞ በሳቋ መጣች፡፡ኦ ሳምራዊት ጣዕመ እስከመቼ ዙሪያየን ከበሽኝ ትቆይ ይሆን?
ወደተለማመድኩት ድህነት ተመልሼ በቀን ሶስቴ ሽሮየን እያንዶከዶኩ ኪስ በማያሞቅ ደሞዝ የመንግስት ባሪያ ሆኜ መስራቴን ቀጥያለሁ፡፡ያቺ አንድ ቀን በህይወቴ ብቅ ብላ ሌላ አለም ያሳየችኝ ልጅ የለችም፡፡እሷን ካገኘሁ በኀላ የምኖረው የመጨረሻው የድህነት አዘግጥ ውስጥ መሆኑ ታየኝ፡፡እንዴት ከዚህ አዙሪት መውጣት እንዳለብኝ አላውቅም፡፡ግን የግድ መለወጥ እንደ ሰው መኖር አለብኝ፡፡
ሳምንት አለፈኝ ግን አልረሳኀትም፡፡ሳቋ ዘወትር በጆሮየ ያቃጭላል፡፡አንዳንድ ሰው ባጋጣሚ በህይወትህ ይከሰትና ጨለማ የነበረውን ህይወትህን በብርሃን ወገግ አድርጎት ይሄዳል፡፡ችግሩ ብቻህን ስትቀር የጨለማው ብርታት ማየሉ ነው፡፡
ሁለት ሳምንት አለፈኝ፡፡ውስጤ ተስላ ስለቀረች በየደቂቃው አስባታለሁ፡፡ድምጿ ቅርብ ፈገግታዋ አጠገቤ ያለ ይመስለኛል..
ሶስተኛው ሳምንት አለፈ፡፡በጣም ናፍቃኛለች፡፡እድሌን መጠቀም አቅቶኝ የገፋኀት ራሴው ነኝ፡፡በጣም ከፍቶኛል፡፡ደግሜ ማግኘት የማልችለውን ነገር አሳይታኝ ሂይወቴ ጣእም የሌለው እንዲሆን አድርጋኛለች፡፡ስለዚህም እረፍት ማድረግና ወደ ቀደመው አቋሜ መመለስ አለብኝ፡፡የሚያዛልቀኝ የተጋባሁት ድህነቴ ነው፡፡
በወሩ የአንድ ሳምንት እረፍት ሞልቼ ከስራ ወጣሁ፡፡ሳምንቱን ለማሳለፍ ገዳም ለመሄድ ነው ያሰብኩት፡፡አንድ ሁለት ቅያሪ ልብሶች ይዤ ከመስሪያ ቤቴ ወደ አውቶብስ ተራ ለመሄድ ታክሲ ስጠብቅ
"ኧረ ስለ ሴት ልጅ አምላክ ሃሃሃሃሃሃሃ"
የተሰማኝን ስሜት በቃላት መግለጽ ይከብዳል፡፡ራሷ ናት ሳምራዊት!!ቦርሳየን እያንጀላጀልኩ ስሮጥ መኪናዋ ጋር ደረስኩ፡፡ከመኪናዋ ወጣች አቀፍኳት!!ወደ ራሴ አስጠግቼ በሀይል አጥብቄ አቀፍኳት፡፡
"ከአንተ ማምለጥ አይቻልም፡፡በጣም ነበርኮ የናፈቅከኝ"አይኖቿ ረጠቡ፡፡
"ለምን ዞረህ እንኳን ሳታየኝ ሄድክ?የጠላኸኝ የተጸየፍከኝ ነበር የመሰለኝ፡፡ ያፈርክብኝ እንደ እብድ የቆጠርከኝ ነበር የመሰለኝ"
"ትእዛዝሽን መጣስ ከበደኝ፡፡ደግመሽ ልታገኝኝ ያልፈለግሽ መሰለኝ እንጂ እኔማ እየከፋኝ ነበር የሄድኩት"
ደረቴን እየቀጠቀጠች አነባች፡፡አልተከላከልኩም ተደበደብኩላት፡፡እጆቼን ይዛ እየመራች መኪናዋ ውስጥ ገባን፡፡ወዳሻት ነዳችው፡፡ከሷ ጋር ሆኜ ለምን ወደ ሞት አትወስደኝ ከመሄድ አልመለስም፡፡
ቀዳማዊ ዮሓቶኤል!!
1 097
Repost from ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
እሳት ወይ አበባ 🌸
ይቅር ብቻ አንናገርም...
እኔና አንቺ አንወያይም...
ለውይይት አልታደልንም...
እንዲያው ዝም እንጂ ዝም...ዝም
አበባ አንሆን ወይም እሳት...
ተጠምደን በምኞት ቅጣት...
ዕድሜአችንን እንደማጥናት...
እሳት አንሆን ወይ አበባ...
በሕቅ-እንቅ ስስንባባ...
ባከነች ልጅነታችን እየቃተትን ስናነባ።
1 097
ደስታህ ግን ጠፍቶ ሊቀር የሚችል ነገር አይደለም ጊዜያዊ በሆነ ከፈን ሊጋረድ ብቻ ነው የሚችለው።
እናም በህይወት እስካለህ ድረስ ያንን ከፈን ልትገልጠው እድሉ አለህ።ያለምንም መሸማቀቅ እና ፍርሃት የሰማዩን መንበር በሙሉ አይንህ ማየት እስከቻልክ ድረስ፣ ውስጥህ ሙሉ በሙሉ ንፁህ እስከሆነ ድረስ እመነኝ ፒተር. . . . እዚህ ሁሉ ችግርም ውስጥ ሆነህ ደስታን ማግኘት ትችላለህ።
አና ፍራንክ1 097
የእድሜ ልክ ምክሬ ይህ ነው፦
በህይወት ሳሉ ወላጆቻችሁ የሚሏችሁን አድምጡና ተግብሩ። አለበለዝያ ሞት ከለየን ወዲያ "ምነው ያሉኝን ባደረኩ ኖሮ" "ምነው ያን አለመሌን በቀየርኩ ኖሮ!" የሚል የጸጸት ሰይጣን ያንገላታናል። ይህም አዚም እስከ ሞት ድረስ አይተወንም። ፍቅረኛ ማጣት የአንድ ሰው ጉድለት ነው፤ ጓደኛ ማጣት የእምነት ጉድለት ነው፤ ግን አባትና እና እናትን ማጣት ሙሉ እራስን ማጣት ነው። ምክንያቱም ሁሉም ነገር ዋጋ አለው ወላጆቻችን ግን ሁሉም ነገር ናቸው።
የሰማይ ጥያቄ በምድር ይተገበራል። ከወላጆቻችን ጋር ያለን ግንኙነት ረጅም ይመስለናል። ስንወድቅ ሲያነሱን፣ ሲርበን ሲያበሉን፣ አልብሰውን በኛ መልበስ ሲደሰቱ፣ አቅፈው ደግፈው ሲያሳድጉን እረጅም አመታት ይመስለናል። ግን ተሸውደናል። ስናጣቸው ምንያህል አጭር ጊዜ እንደነበረች እናስተውላለን። በጣም ተራ የሆኑ ነገሮችን አድርጉ ብለውን አናደርግም ብለን መለገማችን አሳፋሪና አሳማሚ ጸጸት ይለቅብናል። ቆንጠጥ ካልኩ ይቅርታ ግን ይህ እውነት ነው!!!።1 097
ብቸኛ ሰው ነህ፤ በትክክልም ብቸኛ ሰው!። የምትወደውን ዘፈን ማንም አልሰማውም፤ ያነበብከውን መፅሐፍ ማንም አላነበበውም። ቆንጆ ነው ብለህ በምታስበው ቀልድ ማንም አይስቅም። ትዝታዎች አሉህ ነገር ግን እነሱ ልክ እንደ ዋሻ ዘመን ገንዘብ ይመስላሉ፤ ዛሬ ዋጋ ቢስና የማይጠቅሙ ናቸው። ምንም እንኳን ለአንተ ጠቃሚ ቢሆንም ለሌሎች ምናቸውም ነው። የድሮ ጓደኞችህ ተራ በተራ ተለይተህዋል ቦታዎች እና ፍላጎቶችህ በጠቅላላ ተቀይረዋል።
አንተ ምርጥ የጉዞ ባለቤት ነህ። አንተ ማለት ሰይፍ ሰሪ ነህ። አንተ ጥሩ የሆንክበትን ነገር ማንም አይፈልገውም፤ በበጎ አይቀበለውም። ምንም እንኳን በአቀባበልህ አንተ የተሻልክ ብትሆንም ቀረቤታህን አያስተናግዱትም። እና አንዳንዴ እንደ ሰው መቼ ይሆን ወደ ንቃተ ህሊና የምመለሰው? ብለህ ታስባለህ፤ የድሮውን ውበት መቼ ይሆን የምትመልሰው???፤ መቼ ነው እንደገና አስፈላጊ የምትሆነው?፤ ያ መቼም አይሆንም!። በስተመጨረሻ ወደ ጨለማው ወንዝ ትሄዳለህ፡፡ ስንቶች ቀድመውህ ተሻግረው ላይመለሱ የገቡበት ወንዝ። ወደ ማዶ ትሻገራለህ ከዛ ሁሉም ይረሳሃል።
አህመድ ካሊድ ታውፊቅ1 097
ብቸኛ ሰው ነህ፤ በትክክልም ብቸኛ ሰው!። የምትወደውን ዘፈን ማንም አልሰማውም፤ ያነበብከውን መፅሐፍ ማንም አላነበበውም። ቆንጆ ነው ብለህ በምታስበው ቀልድ ማንም አይስቅም። ትዝታዎች አሉህ ነገር ግን እነሱ ልክ እንደ ዋሻ ዘመን ገንዘብ ይመስላሉ፤ ዛሬ ዋጋ ቢስና የማይጠቅሙ ናቸው። ምንም እንኳን ለአንተ ጠቃሚ ቢሆንም ለሌሎች ምናቸውም ነው። የድሮ ጓደኞችህ ተራ በተራ ተለይተህዋል ቦታዎች እና ፍላጎቶችህ በጠቅላላ ተቀይረዋል።
አንተ ምርጥ የጉዞ ባለቤት ነህ። አንተ ማለት ሰይፍ ሰሪ ነህ። አንተ ጥሩ የሆንክበትን ነገር ማንም አይፈልገውም፤ በበጎ አይቀበለውም። ምንም እንኳን በአቀባበልህ አንተ የተሻልክ ብትሆንም ቀረቤታህን አያስተናግዱትም። እና አንዳንዴ እንደ ሰው መቼ ይሆን ወደ ንቃተ ህሊና የምመለሰው? ብለህ ታስባለህ፤ የድሮውን ውበት መቼ ይሆን የምትመልሰው???፤ መቼ ነው እንደገና አስፈላጊ የምትሆነው?፤ ያ መቼም አይሆንም!። በስተመጨረሻ ወደ ጨለማው ወንዝ ትሄዳለህ፡፡ ስንቶች ቀድመውህ ተሻግረው ላይመለሱ የገቡበት ወንዝ። ወደ ማዶ ትሻገራለህ ከዛ ሁሉም ይረሳሃል።
አህመድ ካሊድ ታውፊቅ1 097
ብዙ ጊዜ ማንነት ወይም እኔነት የምንለውን በቃላት መግለፅ አይቻልም። ለዛም ነው እኔ ማን ነኝ ወይም ምንነቴ ምንድነው ብለን ራሳችንን ስንጠይቅ ትክክለኛ መልስ የማናገኘው።
. . .ነገር ግን አሁን ባለንበት የህልም አለም ውስጥ የነበሩ ሁሉንም ልማዶቻችንን ስንገድል በእውነተኛው ማንነታችን መንቃት እና እኔነታችንን ወደ መገንዘብ ደረጃ እንደርሳለን። ራሳችንን በቁሳቁስ ከመለካት አልፈን አዲስ ሰው እንሆናለን ምክንያቱም በህልማችን ስንሞት ከእንቅልፋችን እንነቃለን።
1 097
“እኔ በብቸኝነት ውስጥ ያደግኩ ሰው ነኝ፤ ያለእሱ ምግብና ውሃ እንደሌለኝ ሌላ ሰው ነበርኩ። ብቸኝነት የሌለበት እያንዳንዱ ቀን ድክመቴ ነው። በብቸኝነቴ አልተመካሁም ነገር ግን መደገፊያዬ ነው። በዛ ጨለማ ክፍል ውስጥ ለእኔ እንደ ፀሀይ ብርሃን ነበር. . . ”
🗣 ቻርለስ ቡኮውስኪ1 097
Repost from ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
ጊዜ የሁሉ ነገር ፈዋሽም፣ የሁሉ ነገር አፍራሽም ነው። ዛሬ በጉልበቱ የሚመካውን ነገ ያደክመዋል፤ ዛሬ የሚያለቅሰውን ነገ ያፅናናዋል። የሰው ልጅ በህይወቱ ምንም ያህል ቢያቅድና ቢጥር፣ ከመጣበት አፈር ወደ አፈር መመለሱ የማይቀር የተፈጥሮ ህግ ነው።
ስለዚህ በዚች አጭር የህይወት ዘመናችን ሰውን ከመጥላት፣ ከማሳነስና ቂም ከመያዝ ይልቅ፤ በምንችለው አቅም ፍቅርን መስጠትን እንለማመድ። ምክንያቱም በመጨረሻው ሰዓት ይዘነው የምንሄደው ያካበትነውን ሀብት ሳይሆን፣ በሰዎች ልብ ውስጥ የተውነውን በጎ ትዝታ ብቻ ነው።
📕ፍቅር እስከ መቃብር
1 097
💭
.
.
መናገር እየፈለግን ዝም የውስጣችንን ስቃይ እና መቃጠል ማሳየት እንፈልጋለን ግን ምንም ማድረግ አይቻልም. . .
ብዙዎቻችን በዝምታ እየተሰቃየን ነው!!!1 097
ከልቤ. . . ከነፍሴ. . . ከእኔነቴ ውስጥ እሷነቷን ለማክሰም ያልወጣሁት ተራራ ያልወረድኩት ዳገት የለም ጭራሹኑ እንደ ወይን እያደር እየጎላች ትመጣላች. . . ስሟ ሲነሳ እንደ አዲስ ማፍቀር ያገረሽብኛል ልክ እንደ በፊት እንዳገኘዋት ቀን ልቤ መምታት አንደበቴ መተሳሰር ይጀምራል. . . ደውዬ ደንነቷን መጠየቅ፣ ቁጥብ ሳቋን መኮምኮም የምረኛል. . . ግን አልችልም ዛሬ ትናት አደለም ሁለተኛ እድል አይሰጥም እሷን አይመልስልኝም. . . በነበር ባህር ውስጥ ከመ'ነከር ውጪ
1 097
ጓደኛ ነበረችኝ. . . አሳሳቋ የሚናፈቅ፣ ነገዬን በብሩህ ቀለም የሳለችልኝ. . . ጓደኛ ነበረችኝ. . . ነበረችኝ እንደማለት ደባሪ ቃል የለም. . . ለምን??? ነበረኝ ማለት አሁን አለመኖሩን ያሳያላ. . .፣ እንደማንደርስበት የሰማይ ክዋክብት መራቁን ያሳያላ ይህ ደግሞ ጀምበር እክታዘቀዘቅ እየጠበቁ ከሚሊዮኖች ኮኮብ ውስጥ መኖሯን እያሰቡ ሰላም ማለት ነው. . . ማን ያቃል ነገ??? ምናልባት ዛሬ ከኮከቦች ውስጥ አንዱ እሆን ይሆናል. . .
1 097
Repost from ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
ልባችሁን፦ክብደት፣ሸክም፣ጫና፣መታፈን፣ጭንቀት፣ድካም ከሚያሰሟችሁ ሁኔታዎች ውስጥ በግዜ ውጡ።እየቆየ ሲሄድ እንደምስጥ ውስጣችሁን በልቶ ያፈርሳችል ማንነታችሁን ታጣላቹ ሰላም የማይሰጣቹ ቁስል ነገር እኔኮ እንዲ አልነበረኩም እስክትሉ ድረስ የምትወዱት እናንተን አጥፍቶ የተጨማደደ ማንነት ውስጥ ይከታችኋል።እንደዚ አይነት ስሜት የሚፈጥርባችሁን ነገሮች ከልባችሁ አርቁ።
1 097
የፍቅር ጥያቄውን በጨዋ ደንብ አቀረበላት። እዝን አለች።
አለች፦
“ታውቃለህ እንዴት እንደማከብርህ። ያንተን ያህል የምቀርበው ሰውም የለኝም። ከአንተ በላይ ምቾቴን የሚሰጠኝ ሰው የለም። የነፍሴ ሰው ነህ። የልቤ ሰው ነህ። ግን ይህንንም ታውቃለህ። የእናቴ ልጅ ማለት ነህ። በሁለታችን መሃል ሌላ ነገር ግን፣ የኃጢያት ያህል ነው።”
“እሺ” አላት
“ትረዳኛለህ አደል?”
“ደግነቱ. . . እኔም አንቺም ሁላችንም እንሞታለን። ሁለመናችን አፈር ይለብሳል። አፈር።” ተፍለቀለቀ።
1 097
"አንዳንድ ጊዜ ብዙም ማህበራዊ መስተጋብር የሌላቸው፣ ከሰው መሀል ወጥተው ዳር የሚይዙ ሰዎች ማህበራዊ ኑሮ የሚጠሉ አይደለም፤ ከዚህ ይልቅ የውሸት ድራማን፣ ድድብናንና አስመሳይነትን መቋቋም ስለሚከብዳቸው ነው።"
Osho
1 097
Repost from ኖህቶኤል ከመጻሕፍት ገፅ📚
…ሰው የሆንኩት ሰው ምን እንደሆነ ሳላውቅ ነው። የሰው ልጅ አሁንም ቢሆን ራሱን ፍለጋ ላይ ነው። ድመት መሆን ግን ራስን መሆንን አይጠይቅም። ድመት ሲፈጠር ያው ድመት ሆኖ ነው የተፈጠረው። ሰው ግን ሙሉ ሰው ሆኖ አይፈጠርም። ሙሉ ሰው ለመሆን
ወደ መጣበት እስኪመለስ ድረስ ይታትራል። ይህም ሆኖ ሙሉ ሰው ሆኖ የተቀበረ የለም። ድመት ወደዚህ ምድር ሲመጣ ግን ሙሉ ድመት ሆኖ ነው የሚመጣው፡፡ ሲሄድም ሙሉ ድመትነቱን ጠብቆ ነው። የሰው ልጅ እንደ ሰው መጥቶ እንደ እንስሳ ኖሮ ወደመጣበት
ሊመለስ ይችላል። እንዲያውም የብዙ ሰው እጣ ፈንታ ሰው ሆኖ መጥቶ እንደ እንስሳ ታይቶ ማለፍ ሆኗል!።
የኦጋዴን ድመቶች ገጽ 147
1 097
Repost from ዘ ተ ሐ ር ያ ን 🧘🏻♂️
♻️ውድ ኦሾ፦
እባኮትን ባጭሩ ማንነትዎን አስረዱን?!
ስለራስዎ ያለዎትን አጠቃላይ እይታ ይስጡን? አንዳንዶች አጭበርባሪ ነህ ይሉሀል? ለዚህ ምን ትላለህ??
ኦሾ፦"እኔ መስታወት ብቻ ነኝ...
አጭበርባሪ ሲያየኝ የአጭበርባሪውን ምስል ያያል። ሁሉም በተመልካቹ ላይ የተመሰረተ ነው።
እኔ እስከሚገባኝ ድረስ እራሴን መገለጽ አልችልም። እኔ አቧራ የሌለኝ ባዶ መስታወት ነኝ።
ጥረቴ ሁሉ ሰዎች ማሰላሰልን እንድማሩ ማድረግ ነው። ማሰላሰል ማለት ማህበረሰቡ፣ ሃይማኖት እና የትምህርት ስርዓቱ በመስታወት ላይ የሚጥሉትን አቧራ የማስወገድ ጥበብ ነው።
ማሰላሰል ማለት ከአንተ ጋር ያልተወለዱትን ነገሮች በሙሉ ማስወገድ እና ወደ ተወለድክበት ወደ መጀመሪያ ንፁህነት ማምጣት ማለት ነው።
ዳግመኛ መወለድ ማለት ነው።
ዳግም ከተወለድክ በኋላ መስታወት ትሆናለህ።
እግዚአብሔርን በውስጤ የሚያዩ ሰዎች አሉ፣ አንዳንዶች እንደ አጭበርባር አድርገው ይመለከቱኛል፣ አንዳንዶች ደግሞ እንደ ዝንጀሮ ያዩኛል፣አንዳንዶቹ ደግሞ እንደ አህያ...
ይህ ደግሞ የእነርሱ ጉዳይ ነው።
በመስታወት ውስጥ የሚንፀባረቀው ፊታቸው ነው እኔን አይተው የሚሰጡኝ ትርጉም እራሳቸውን እንጂ እኔን አይገልጸኝም።"
🖤"OSHO"
1 097
💭
.
"ወደዚች ምድር የመጣንበት አንዳች ምክንያት አለ ወይም ልናሳካው የሚገባ የሆነ ተልእኮ አለን። ይህን እንዲሆን ደግሞ ያልተገደበ አቅም ተሰጦናል ውስጣችን ከምናስበው በላይ ታላቅ መለኮታዊ ሀይል አለ እንኳን ለኛ ቀርቶ ለአለም የሚተርፍ ታላቅ አቅም አለን።"
እናም. . . ህይወታችንን ለመለወጥ መጀመሪያ ውስጣችን ያለውን አቅም እና ተሰጥኦ እንመርምር እና እንወቅ፤ የምንኖርለት አላማ እና ራዕይ ይኑረን፤ ይህንን ራዕይ ለማሳካት የሚያስችል ታላቅ አቅም እንዳለን በፍፁም ፍቅር እንመን፤ በሙሉ አቅማችን አላማችንን ለማሳካት በፅናት እንትጋ።"
አይመስላችሁም???🤔
1 097
ሁላችንም እየጠበቅን ነው። አንዳንዶች ከህይወታቸው የሄደውን እስኪመለስ እየጠበቁ ነው፤ ሌሎች ደግሞ የህይወታቸውን ለውጥ እየጠበቁ ነው።
በወደቀ ሰው ላይ የሌላ ሰው ተስፋ አለ፤ በወደቀ ቤተሰብ ሌላ አዲስ ህይወት አለ፤ በወደቀ ሀገር ግን ከየት ይሸሻል? ሞትን አረፍን ስንል መቃብራችን በልማት ይነሳል! ለቦታ ይዘት አጽማችን በአንድ ይማገዳል። ታድያ ለመዳን ጊዜ ያስፈልጋል ተብሎ ነበር ግን ያ ጊዜ እስከሚደርስ እድሜያችን አለፈ ወይስ ሞትን ሞተናል???
የምንጠብቀው ለምን አይመጣም??? እንጃ ብቻ ተስፋችን ቅዠት ብቻ ነው እንቅልፍ የሚነሳ የአዕምሮ ጭንቀት!።
"We don’t even ask happiness, just a little less pain."
-Charles Bukowski1 097
ግዑዝኤል -16/09/18
፠
የዛሬ ዝምታዬ የተወለደው ከትናንት ልፍለፋዬ ማህፀን ውስጥ ነው ።
የፊት ሸፍጥ የጀመርኩት ሁሉን የሚያወራ መልኬን ያዩ ስሜታዊነቴን ሁሉ ደካማነት ሲያረጉት ነው ።
የኔ ያልኳቸው ፊት የወረዱኝን እንባዎች እረግማቸዋለሁ ።
ማቅረብ በሚል ህልውና በሌለው ሞኝነት ታጅላ ብዙ ታወራ የነበረ ምላሴን እገስፃለሁ።
አንድ ስሜት ለማስወጣት የወጣኝ ቃል በሪኣክሽናቸው አሳቦ መቶ ስሜቶችን ጠርቶብኛል።
" ደክሞኛል '' ስል የሚቀለኝ ይመስለኝ ነበር ።
ለካ ለሰው ያወሩት ሁሉ አይቀልም !።
አይናቸውን ሳይ ( ዝምታቸውን ስሰማ ) ነፍሴ ላይ ዱካክ ይለቅብኛል ።
" አስደብረህኛል " ስለው
'' አናደሽኛል" ስላት...
መነፋረቅ የቀረው ማለቃቀሴን ሳራምድ...
አይኔ እንባ ቋጥሮ ሲቀላ...
ሰውነቴ መንቀጥቀጥ ሲጀምር...
መንተባተብና ብዙ ማውራት ሳመጣ...
እያንዳንዱ እንቅስቃሴዬ ጠልፎ የሚጥል መሰናክል ነበር~ ገደል የሚጥል ተዳፋት !::
፨
ዛሬ እኔ ከነገርኩት ዉጭ ማንም ስለኔ ምንም አያውቅም።
በስለት የተዘረገፈ ሆዴን ይዤ ፈገግ ማለትን እችልበታለሁ ፡፡
መቅደላ አፋፍ ቆሜ፣ ሽጉጥ አፌ ውስጥ ደግኜ
'' ጥይት ይጠጣል ? ወይስ ይጎረሳል ነው ሚባል ?? "
እያልኩ መቀለዷን አወቅባታለሁ።
ልውደድህ አልውደድህ ፣ ልጥላህ አልጥላህ እስካልነገርኩህ መቼም አይገባህም :: በቀኝ ልንፈስ በግራ ማንም የሚያውቅ የለም። ሁሌም የምፈልገውን ብቻ ባደርግም still ምን እንደምፈልግ ማንም አያውቅም !።
፧፧
ይህ ማንነት ወዳጆቼ በፍቅር ስም ሸፍነው ፤ ጠላቶቼ በንቀት ስም ጠቅለው የሰጡኝ ስጦታ ነው ። እናም ልጠብቀው የመስቀሌ እዳ አለብኝ!።
“I used to think my life was a tragedy, but now I realize, it’s a comedy.” 🤪 – Joker[ ]
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
