Ethiopian Public Service University
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام Ethiopian Public Service University
تُعد قناة Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 12 736 مشتركاً، محتلاً المرتبة 15 736 في فئة التعليم والمرتبة 2 645 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 12 736 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 13 يوليو, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 112، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 2، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 34.81%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 15.93% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 434 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 029 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 30.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 14 يوليو, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التعليم.
12 736
المشتركون
+224 ساعات
+217 أيام
+11230 أيام
أرشيف المشاركات
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
የውል ስምምነቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የመንግሰት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ለመፈጸም እና ለማስፈጸም በሚያስችል አደረጃጀት የሰው ኃይል ብቃትና ምዘና ሥርዓትን በተፈለገው መንገድ ለማራመድ ታስቦ የተካሄደ ሲሆን፣ በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተፈጸመ መሆኑ ታውቋል፡፡
የፊርማ ስነ-ስርዓቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት፣ የመንግሰትን አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መሥራት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸው፣ “በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው ሪፎርም ዓላማ፣ ከተለመደው ኋላቀር አሠራር ሙሉ በሙሉ ተላቀን፣ ዘመኑ በሚጠይቀው የዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ፣ ዜጎች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ፈጣንና ተገቢ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራርን በመዘርጋት እርካታን ማምጣት ነው፡፡” ብለዋል።
ሚኒስትር መስሪያ ቤቱን ወክለው ፊርማቸውን ያኖሩት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ለማ ጉዲሳ (ዶ/ር) ሲሆኑ፣ በስነስርአቱ ላይ እንደተናገሩት፣ “የኒቨርሲቲው የተጣለበት ኃላፊነት የትውልድ አደራ በመሆኑ፣ የሚጠበቅበትን ሚና ለመወጣት ብርቱ ጥረት ያደርጋል፡፡” ብለዋል፡፡
Visit our website: https://www.epsu.edu.et/user
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
PR call: 0945746405
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፋይናነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት Validation ወርክሾፕ አካሄደ፤
በኢፐሰዩ የፋይናነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ (College of Finance & Economics) በዩኒቨርሲቲው አዲስ ምእራፍ ተልእኮ መሰረት፣ በመጀመሪያ ዲግሪ ሊሰጡ ለታቀዱት አራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ሲያካሄድ የቆዬውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ተከትሎ፣ ታህሳስ 24 ቀን 2018 በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ኢንስቲትዩት ስልጠና ክፍሎች Validation ወርክሾፕ አካሄደ፡፡
በወርክሾፑ ላይ የኮኖሚክስ የትምህርት ክፍል የካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ፣ የህዝብ ፋይናንስ አስተዳደር እና አካውንቲንግ የካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ፣ የታክስ እና ከስተምስ አስተዳደር ካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ እና የፕሮኪዩርመንት እና ንብረት አስተዳደር ካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ ከየትምህርት ክፍሉ ለተውጣጡ መምህራን እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ለመጡ የየዘርፉ ባለሙያዎች የዳሰሳ ጥናት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡
የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ተስፋዬ ጩፋና (ዶ/ር) በወርክ ሾፑ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት፣ “የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ የተካሄደው፣ ዩኒቨርሲቲያችን ወደ ተግባር ዩኒቨርሲቲነት የሚያደርገውን ሽግግር መሰረት አድርጎ በመሆኑ፣ ሪፖርቱን ሰምታችሁ የግምገማ አስተያየታችሁን እንድትሰጡ እየጋበዝኩ፣ የምትሰጡት ሀሳብ እና አስተያየት፣ እዚህ ተምረው የሚወጡ ተመራቂዎች ያለምንም ተጨማሪ ስልጠና በቀጥታ ወደ ተግባር የሚሰማሩ መሆኑን ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል” በማለት ተሳታፊዎቹ በንቃት እንዲሳተፉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡
ወርክሾፑ ለአራቱም የትምህርት ክፍሎች ሪፖርት አቀራረብ እንዲመች ሆኖ፣ በተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሶች የተካሄ ሲሆን፣ የአካዳሚክ ዘርፍ ምክትል ፕሬዘዳንቱ ለማ ጉዲሳ (ዶ/ር) የታክስ እና ከስተምስ አስተዳደር (Tax & Customs administration) ካሪኩለም ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት አዳምጠው ሀሳብ እና አስተያየታቸውን አካፍለዋል፡፡
ከጠዋቱ 2፡30 ሰዐት ጀምሮ ለግማሽ ቀን የተካሄደው ወርክሾፕ፣ ጥናቱን አጠቃሎ ለማጽደቅ በሚያስችል ሁኔታ ግምገማ ተደርጎበት፣ ሀሳብ እና አስተያየት ተሰጥቶበት ከቀኑ 6፡30 ሰዐት ሲሆን ተጠናቋል፡፡
Visit our website: https://www.epsu.edu.et/user
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
PR call: 0945746405
Dear EPSU Family,
We have received several inquiries regarding the registration process for the recently advertised vacant position. Please be informed that registration is being conducted at the Federal Civil Service Commission, located near Dembel City Center, along the Meskel Adebabayi–Bole Road.
For your convenience, you may access the location and directions via Google Maps using the link provided in this post.
https://maps.app.goo.gl/2soXkAYdY4RDSZRY6
+2
Dear Ethiopian Public Service University Family,
Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public sector? Here is an exciting opportunity to join us and contribute to our mission of modernizing and strengthening the larger Ethiopian public service.
Don’t miss the chance to grow with us and make a meaningful impact! We also encourage you to share this opportunity with friends who might be interested. For full details on the position, criteria, and requirements, please see the attached job vacancy.
+1
Dear Ethiopian Public Service University Family,
Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public sector? Here is an exciting opportunity to join us and contribute to our mission of modernizing and strengthening the larger Ethiopian public service.
Don’t miss the chance to grow with us and make a meaningful impact! We also encourage you to share this opportunity with friends who might be interested. For full details on the position, criteria, and requirements, please see the attached job vacancy.
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
#ethiopianpublicserviceuniversity
PR call: 0945746405
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት ጋር የCBE በእጀ አገልግሎት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዩጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት ጋር ለመምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ያለማስያዣ የብድር አገልግሎት ማስገኘት የሚችል CBE በእጀ የተባለ የስምምነት ሰነድ ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡
የስምምነት ሰነዱን በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኩል ፕሬዚዳንቱ ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት በኩል የዲስትሪክቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሊያ ተስፋዬ ፈርመዋል፡፡ ስምምነቱ፣ የዩኒቨርሲቲውን መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች CBE በእጀ የድጅታል አነስተኛ ብድር እና ቁጠባ አገልግሎት /DMSL/ ተጠቃሚ ማድረግን ዓላማ ያደረገ መሆኑ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገልጿል፡፡
የፊርማ መርሐ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ እስካሁን ባለው አሰራር ባንኮች የብድር አገልግሎት የሚሰጡት ማስያዣ ማቅረብ ለሚችል ባለሀብት እና እራሳቸው ለሚያስተዳድሯቸው ሰራተኞቻቸው ብቻ እንደነበረ አስታውሰው፣ “ዛሬ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የምንፈራረመው ስምምነት፣ ባንኩ ተደራሽነቱን ወደ ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል እያሰፋ ለመሆኑ እንደማሳያ የሚወሰድ ነው፤ ከዚህም አልፎ ዜጎች ለባንኩ የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ተግባር ነው” ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመገናኛ ዲስትሪክት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሊያ ተስፋዬ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለላፉት 83 ዓመታት ሀገራችንን በፋይናንስ ዘርፍ እያገለገለ እና የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን እየደገፈ የተሻገረ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን አውስተው፣ “ባንካችን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀብት እንደመሆኑ መጠን፣ የደንበኞቻችንን የረጅም ጊዜ ጥያቄ መሰረት በማድረግ ለሁሉም ደንበኞቻችን የብድር አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተመቻቸውን CBE በእጀ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ስናቀርብ ታላቅ ደስታ ይሰማናል” ብለዋል፡፡
ከዚህ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲው መምህራን እና ሰራተኞች ባንኩ የሚሰጣቸውን የአጭርና የረጅም ጊዜ የብድር አገልግሎቶች አስመልክተው ላቀረቧቸው ጥያቄዎች የባንኩ ሙያተኞች ማብራሪያ እና ገለጻ ሰጥተው የፊርማ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
#ethiopianpublicserviceuniversity
PR call: 0945746405
በኢፐሰዩ የከተማ ጥናት ኮሌጅ የመጀሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹን የዳሰሳ ጥናት አጸደቀ፡፡
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ጥናት ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው የአዲስ ምእራፍ ተክእኮ መሰረት ሲያካሂዳቸው የነበሩትን እና ግምገማ የተደረገባቸውን ስድስት የትምህርት ፕሮግራሞችን የዳሰሳ ጥናት ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ/ም በኮሌጁ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አጸደቀ፡፡
በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን ደጉ በቀለ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ ዩኒቨርሲቲው በጀመረው የአዲስ ምእራፍ ጉዞ ቀደም ሲል ያልነበሩ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞችን ለማስጀመር ሰፊ ስራ ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰው፣ “ዛሬ በኮሌጅ ደረጃ የምናጸድቃቸው ስድስት የትምህርት ፕሮግራሞች የዳሰሳ ጥናቶች ፣ በተለያዩ ደረጃዎች ግምገማ ተካሂዶባቸው እና በተቀመጠው መለኪያ መሰረት አልፈው የመጡ ናቸው” ብለዋል፡፡
ኮሌጁ ያጸደቃቸው የትምህርት ፕሮግራ የዳሰሳ ጥናቶች የከተማ ፕላንና ዲዛይን ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የከተማ መሬት ሥራ አመራርና እንፎርሜሽን ስስተም ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የንብረት ግመታ ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የከተማ ምህንድስና ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የቅየሳ ምህንድስና ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት እና የእንቫይሮንሜንታል ሳይንስ ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት የሚሉት ናቸው፡፡፡
በእለቱ የዳሰሳ ጥናቶቹን ከማጽደቅ በተጨማሪ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ደጉ በቀለ ከትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና ከሌሎች የኮሌጅ ኃላፊዎች ጋር ከትምህርት ሚኒስቴር በመጣው ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ /KPI ላይ ተፈራርመዋል፡፡
Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb
Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram
#ethiopianpublicserviceuniversity
PR call: 0945746405
በኢፐሰዩ የተማሪዎች ተሰጥኦ መለያ እና ማልሚያ ማንዋል ተገመገመ፤
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ ባካሄደው የአንደኛ መንፈቅ አመት ስብሰባ፣ “የኢፐሰዩ የተማሪ ተሰጥኦ እና ማልማት ማኑዋል (EPSU Student Talent & Development Manual)” ተብሎ በተዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡
የውይይት መርሐ ግብሩን የመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በመክፈቻው እንደተናገሩት፣ “አንድ ዩኒቨርሲቲ ዋና ተግባሩ ተማሪዎቹን ወደ መዳረሻቸው እንዲሄዱ መደገፍ ነው፤ መዳረሻቸው ደግሞ የንድፈሀሳብ ትምህርት ብቻ ላይሆን ይችላል፤ ስለዚህ፣ ከንድፈ ሀሳብ ትምህርት ባለፈ ስነምግባራቸውን እየመራን፣ እምቅ ችሎታቸውን እንዲያወጡ እየረዳን፣ ተሰጥኦዋቸውን እንዲለዩ እያስቻልን እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ክህሎት እያለማን መሄድ እንድንችል Talent Development and essential soft skill በሚል ይህንን አደረጃጀት ፈጥረን፣ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡” በማለት ስለሚቀርበው ረቂቅ ማንዋል የካውንስሉ አባላት የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ አድርገዋል፡፡
ከዚያም የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ዲን አብዱ ሙሀመድ (ዶ/ር) የተዘጋጀውን ረቂቅ ማንዋል ለካውንስሉ አባላት ሲያቀርቡ፣ የተማሪዎችን ተሰጥኦ (talent) ለይቶ በማውጣት ጥቅም ላይ እንዲውል የማድረግ ስራ፣ በአንድ ሰው ወይም በአንድ የስራ ክፍል ብቻ የሚሰራ ስራ እንዳልሆነ እና ተማሪዎቹ ከዲግሪ ባሻገር ምን ይዘው ይውጡ የሚለው የዩኒቨርሲቲያችን ዋና የትኩረት ማእከል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም፣ “ሁላችንም የተለያየ ተሰጥኦ (talent) አለን፤ ያንን ተሰጥኦ ለተማሪዎቻችን በማካፈል ያላቸው እምቅ ችሎታ ተፈልቅቆ እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅብናል፤ ተሰጥኦ በመምረጥ ብቻ የምናመጣው አይደለም፤ ከመምረጥ ባሻገር የማያቋርጥ ክትትል እና እንክብካቤ በማድረግ የምናሳካው ጉዳይ ነው፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ አስከትለውም በረቂቅ ማንዋሉ የተዘረዘሩ ዋና ዋና ተግባራትን እና የአፈጻጸም አቅጣጫዎችን አቅርበዋል፡፡
በመቀጠልም ተሰብሳቢዎቹ በቀረበው ረቂቅ ማንዋል ላይ ሀሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል፤ ከሰጡት ሀሳብ እና አስተያየቶች መካከል፣ በፕሮግራሙ የኤክስቴንሽን እና የቅዳሜ እና እሁድ ተማሪዎች ቢካተቱበት መልካም ነው፤ ተሰጥኦ ያላቸው የአካዳሚክ እና የአስተዳደር ሰራተኞችም ቢሳተፉበት አይከፋም፤ ለማሰላሰል እና ሀሳብ ለማመንጨት ምቹ የሆኑ ማእዘኖች ቢዘጋጁ መልካም ነው፤ የሚሉ ይገኙበታል፡፡
በማጠቃለያውም የቀረቡት ሀሳብ እና አስተያቶች ተካተውበት ረቂቅ ማኑዋሉ እንደሚጸድቅ ፕሬዘዳንቱ ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ገልጸው ውይይቱ አብቅቷል፡፡
ኢፐሰዩ ባካሄደው የካውንስል ስብሰባ የ1ኛ መንፈቅ አመት ሪፖርቱን አጸደቀ፤
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ ለግማሽ ቀን ባካሄደው የካውንስል ስብሰባ፣ በአንደኛ መንፈቅ አመት በተሰሩ መደበኛ ተግባራት፣ በሪፎርም ስራዎች እና ቁልፍ የውጤት አመላካች አፈጻጸም መለኪያዎች መሰረት በተከናወኑ ተግባራት ላይ የቀረበውን ሪፖርት ገምግሞ አጸደቀ፡፡
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ዛሬ ለካውንስሉ የሚቀርበው የአንደኛ መንፈቅ አመት ሪፖርት፣ ከአብዛኛው የካውንስል አባል ጋር በተለያዩ የኮሚቴ ስብሰባዎች፣ የጋራ መድረኮች እና በሪፎርም ቡድን ውይይቶች ንግግር ሲደረግበት የቆዬ መሆኑን ጠቅሰው፣ “የዩኒቨርሲቲው ማናጅመንት አፈጻጸማችንን ገምግሞ፣ የትኛው ላይ ጥሩ እንደሰራን፣ የትኛው ላይ ተጠናክረን መቀጠል እንዳለብን እና ቀጣዩ የትኩረት አቅጣጫችን የቱ መሆን እንዳለበት ለይቷል፤ ከዛሬው ውይይታችን የሚጠበቀው ሪፖርቱን ገምግሞ ማጽደቅ እና ለቀጣይ ምን እንስራ? በሚለው ላይ ካውንስሉ ሀሳብ እና አስተያየት እንዲሰጥበት ነው፡፡” በማለት ስብሰባውን ከፍተዋል፡፡
ከመክፈቻው በኋላ የፕሬዘዳንት ጽ/ቤት ኃላፊው አብርሃም ሐጎስ (ዶ/ር) የአፈጻጸም ሪፖርቱን አቅርበዋል፤ ሪፖርቱ፣ መሰረታዊ መረጃዎች፣ በእቅዱ መሰረት በ14 ግቦች የተቀመጡ ዋና ዋና ተግባራት፣ ቁልፍ የውጤት አመላካች አፈጻጸም፣ በመንፈቅ አመቱ እንደ ውጤት የሚታዩ ተግባራት እና በቀጣዩ መንፈቅ አመት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራት በሚል ተደራጅቶ የቀረበ መሆኑን፣ ከሪፖርቱ አቀራረብ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡
በመቀጠልም ከተሰብሳቢዎቹ ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ በፕሬዘዳንቱ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡ በመጨረም ፕሬዘዳንቱ ውይይቱን ሲያጠቃልሉ፣ “ማኔጅመንቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ፣ በዛሬው ውይይት ያገኘናቸውን ግብአቶች እና በቀጣይ ከመላው ሰራተኛ ጋር በሚደረገው ውይይት የምናገኘውን ሀሳብ እና አስተያየት አዳምረን፣ ለቀጣዩ ስድስት ወር አፈጻጸም ተገቢ የሆነ የእቅድ ማሻሻያ እናደርጋለን” ብለዋል፡፡
