ch
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

前往频道在 Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

显示更多

📈 Telegram 频道 Ethiopian Public Service University 的分析概览

频道 Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 12 732 名订阅者,在 教育 类别中位列第 15 748,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 643

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 12 732 名订阅者。

根据 12 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 112,过去 24 小时变化为 6,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 未认证
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 34.77%。内容发布后 24 小时内通常能获得 16.09% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 428 次浏览,首日通常累积 2 049 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 27

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

凭借高频更新(最新数据采集于 13 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。

12 732
订阅者
+624 小时
+237
+11230
帖子存档
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር ጋር ታህሳስ 23 ቀን 2018 ዓ.ም የመግባቢያ ስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ የውል ስምምነቱ ሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እና የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረውን የመንግሰት አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ለመፈጸም እና ለማስፈጸም በሚያስችል አደረጃጀት የሰው ኃይል ብቃትና ምዘና ሥርዓትን በተፈለገው መንገድ ለማራመድ ታስቦ የተካሄደ ሲሆን፣ በሚኒስትር መስሪያ ቤቱ የመሰብሰቢያ አዳራሽ የተፈጸመ መሆኑ ታውቋል፡፡ የፊርማ ስነ-ስርዓቱን አስመልክቶ መልዕክት ያስተላለፉት የከተማና መሠረተ-ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትር ክብርት ወ/ሮ ጫልቱ ሳኒ እንደተናገሩት፣ የመንግሰትን አገልግሎት እና አስተዳደር ሪፎርም ውጤታማ ለማድረግ ከባለድርሻ አካላት ጋር ተቀናጅቶ መሥራት ፋይዳው የጎላ መሆኑን ገልጸው፣ “በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው ሪፎርም ዓላማ፣ ከተለመደው ኋላቀር አሠራር ሙሉ በሙሉ ተላቀን፣ ዘመኑ በሚጠይቀው የዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ፣ ዜጎች ለሚያነሷቸው ጥያቄዎች ፈጣንና ተገቢ ምላሽ መስጠት የሚያስችል አሰራርን በመዘርጋት እርካታን ማምጣት ነው፡፡” ብለዋል። ሚኒስትር መስሪያ ቤቱን ወክለው ፊርማቸውን ያኖሩት ክቡር ሚኒስትር ዴኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር)፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲን በመወከል የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዘዳንት ለማ ጉዲሳ (ዶ/ር) ሲሆኑ፣ በስነስርአቱ ላይ እንደተናገሩት፣ “የኒቨርሲቲው የተጣለበት ኃላፊነት የትውልድ አደራ በመሆኑ፣ የሚጠበቅበትን ሚና ለመወጣት ብርቱ ጥረት ያደርጋል፡፡” ብለዋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/user Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፋይናነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት Validation ወርክሾፕ አካሄደ፤ በኢፐሰዩ የፋይናነስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ (College of Finance & Economics) በዩኒቨርሲቲው አዲስ ምእራፍ ተልእኮ መሰረት፣ በመጀመሪያ ዲግሪ ሊሰጡ ለታቀዱት አራት የትምህርት መርሃ ግብሮች ሲያካሄድ የቆዬውን የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት ተከትሎ፣ ታህሳስ 24 ቀን 2018 በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ኢንስቲትዩት ስልጠና ክፍሎች Validation ወርክሾፕ አካሄደ፡፡ በወርክሾፑ ላይ የኮኖሚክስ የትምህርት ክፍል የካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ፣ የህዝብ ፋይናንስ አስተዳደር እና አካውንቲንግ የካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ፣ የታክስ እና ከስተምስ አስተዳደር ካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ እና የፕሮኪዩርመንት እና ንብረት አስተዳደር ካሪኩለም ጥናት ኮሚቴ ከየትምህርት ክፍሉ ለተውጣጡ መምህራን እና ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ለመጡ የየዘርፉ ባለሙያዎች የዳሰሳ ጥናት ሪፖርታቸውን አቅርበዋል፡፡ የኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል ኃላፊ የሆኑት ተስፋዬ ጩፋና (ዶ/ር) በወርክ ሾፑ ላይ ተገኝተው እንደተናገሩት፣ “የፍላጎት ዳሰሳ ጥናቱ የተካሄደው፣ ዩኒቨርሲቲያችን ወደ ተግባር ዩኒቨርሲቲነት የሚያደርገውን ሽግግር መሰረት አድርጎ በመሆኑ፣ ሪፖርቱን ሰምታችሁ የግምገማ አስተያየታችሁን እንድትሰጡ እየጋበዝኩ፣ የምትሰጡት ሀሳብ እና አስተያየት፣ እዚህ ተምረው የሚወጡ ተመራቂዎች ያለምንም ተጨማሪ ስልጠና በቀጥታ ወደ ተግባር የሚሰማሩ መሆኑን ታሳቢ ያደረገ መሆን ይኖርበታል” በማለት ተሳታፊዎቹ በንቃት እንዲሳተፉ ማሳሰቢያ ሰጥተዋል፡፡ ወርክሾፑ ለአራቱም የትምህርት ክፍሎች ሪፖርት አቀራረብ እንዲመች ሆኖ፣ በተለያዩ የመሰብሰቢያ አዳራሶች የተካሄ ሲሆን፣ የአካዳሚክ ዘርፍ ምክትል ፕሬዘዳንቱ ለማ ጉዲሳ (ዶ/ር) የታክስ እና ከስተምስ አስተዳደር (Tax & Customs administration) ካሪኩለም ኮሚቴ ያቀረበውን ሪፖርት አዳምጠው ሀሳብ እና አስተያየታቸውን አካፍለዋል፡፡ ከጠዋቱ 2፡30 ሰዐት ጀምሮ ለግማሽ ቀን የተካሄደው ወርክሾፕ፣ ጥናቱን አጠቃሎ ለማጽደቅ በሚያስችል ሁኔታ ግምገማ ተደርጎበት፣ ሀሳብ እና አስተያየት ተሰጥቶበት ከቀኑ 6፡30 ሰዐት ሲሆን ተጠናቋል፡፡ Visit our website: https://www.epsu.edu.et/user Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram PR call: 0945746405

Dear EPSU Family, We have received several inquiries regarding the registration process for the recently advertised vacant position. Please be informed that registration is being conducted at the Federal Civil Service Commission, located near Dembel City Center, along the Meskel Adebabayi–Bole Road. For your convenience, you may access the location and directions via Google Maps using the link provided in this post. https://maps.app.goo.gl/2soXkAYdY4RDSZRY6

Dear Ethiopian Public Service University Family, Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public s
+2
Dear Ethiopian Public Service University Family, Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public sector? Here is an exciting opportunity to join us and contribute to our mission of modernizing and strengthening the larger Ethiopian public service. Don’t miss the chance to grow with us and make a meaningful impact! We also encourage you to share this opportunity with friends who might be interested. For full details on the position, criteria, and requirements, please see the attached job vacancy.

Dear Ethiopian Public Service University Family, Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public s
+1
Dear Ethiopian Public Service University Family, Do you aspire to be part of a team shaping the future of Ethiopia’s public sector? Here is an exciting opportunity to join us and contribute to our mission of modernizing and strengthening the larger Ethiopian public service. Don’t miss the chance to grow with us and make a meaningful impact! We also encourage you to share this opportunity with friends who might be interested. For full details on the position, criteria, and requirements, please see the attached job vacancy. Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram #ethiopianpublicserviceuniversity PR call: 0945746405

የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት ጋር የCBE በእጀ አገልግሎት የስምምነት ሰነድ ተፈራረመ፡፡ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ከኢትዩጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት ጋር ለመምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች ያለማስያዣ የብድር አገልግሎት ማስገኘት የሚችል CBE በእጀ የተባለ የስምምነት ሰነድ ታህሳስ 22 ቀን 2018 ዓ.ም ተፈራረመ፡፡ የስምምነት ሰነዱን በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በኩል ፕሬዚዳንቱ ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር)፣ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መገናኛ ዲስትሪክት በኩል የዲስትሪክቱ ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሊያ ተስፋዬ ፈርመዋል፡፡ ስምምነቱ፣ የዩኒቨርሲቲውን መምህራን እና የአስተዳደር ሰራተኞች CBE በእጀ የድጅታል አነስተኛ ብድር እና ቁጠባ አገልግሎት /DMSL/ ተጠቃሚ ማድረግን ዓላማ ያደረገ መሆኑ በመርሐ ግብሩ ላይ ተገልጿል፡፡ የፊርማ መርሐ ግብሩን በንግግር የከፈቱት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ እስካሁን ባለው አሰራር ባንኮች የብድር አገልግሎት የሚሰጡት ማስያዣ ማቅረብ ለሚችል ባለሀብት እና እራሳቸው ለሚያስተዳድሯቸው ሰራተኞቻቸው ብቻ እንደነበረ አስታውሰው፣ “ዛሬ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር የምንፈራረመው ስምምነት፣ ባንኩ ተደራሽነቱን ወደ ዝቅተኛው የማህበረሰብ ክፍል እያሰፋ ለመሆኑ እንደማሳያ የሚወሰድ ነው፤ ከዚህም አልፎ ዜጎች ለባንኩ የባለቤትነት ስሜት እንዲሰማቸው የሚያደርግ ተግባር ነው” ብለዋል፡፡ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የመገናኛ ዲስትሪክት ዋና ዳይሬክተር የሆኑት ወ/ሮ ሊያ ተስፋዬ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ለላፉት 83 ዓመታት ሀገራችንን በፋይናንስ ዘርፍ እያገለገለ እና የተለያዩ ሜጋ ፕሮጀክቶችን እየደገፈ የተሻገረ ግዙፍ የፋይናንስ ተቋም መሆኑን አውስተው፣ “ባንካችን የሁሉም ኢትዮጵያዊ ሀብት እንደመሆኑ መጠን፣ የደንበኞቻችንን የረጅም ጊዜ ጥያቄ መሰረት በማድረግ ለሁሉም ደንበኞቻችን የብድር አገልግሎት ተደራሽ ለማድረግ የተመቻቸውን CBE በእጀ የብድር እና የቁጠባ አገልግሎት ለዩኒቨርሲቲው ማህበረሰብ ስናቀርብ ታላቅ ደስታ ይሰማናል” ብለዋል፡፡ ከዚህ በመቀጠልም የዩኒቨርሲቲው መምህራን እና ሰራተኞች ባንኩ የሚሰጣቸውን የአጭርና የረጅም ጊዜ የብድር አገልግሎቶች አስመልክተው ላቀረቧቸው ጥያቄዎች የባንኩ ሙያተኞች ማብራሪያ እና ገለጻ ሰጥተው የፊርማ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram #ethiopianpublicserviceuniversity PR call: 0945746405

በኢፐሰዩ የከተማ ጥናት ኮሌጅ የመጀሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞቹን የዳሰሳ ጥናት አጸደቀ፡፡ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የከተማ ጥናት ኮሌጅ ዩኒቨርሲቲው በተሰጠው የአዲስ ምእራፍ ተክእኮ መሰረት ሲያካሂዳቸው የነበሩትን እና ግምገማ የተደረገባቸውን ስድስት የትምህርት ፕሮግራሞችን የዳሰሳ ጥናት ታህሳስ 21 ቀን 2018 ዓ/ም በኮሌጁ የመሰብሰቢያ አዳራሽ አጸደቀ፡፡ በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን ደጉ በቀለ (ዶ/ር) እንደተናገሩት፣ ዩኒቨርሲቲው በጀመረው የአዲስ ምእራፍ ጉዞ ቀደም ሲል ያልነበሩ የመጀመሪያ ዲግሪ ፕሮግራሞችን ለማስጀመር ሰፊ ስራ ሲያከናውን መቆየቱን ጠቅሰው፣ “ዛሬ በኮሌጅ ደረጃ የምናጸድቃቸው ስድስት የትምህርት ፕሮግራሞች የዳሰሳ ጥናቶች ፣ በተለያዩ ደረጃዎች ግምገማ ተካሂዶባቸው እና በተቀመጠው መለኪያ መሰረት አልፈው የመጡ ናቸው” ብለዋል፡፡ ኮሌጁ ያጸደቃቸው የትምህርት ፕሮግራ የዳሰሳ ጥናቶች የከተማ ፕላንና ዲዛይን ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የከተማ መሬት ሥራ አመራርና እንፎርሜሽን ስስተም ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የንብረት ግመታ ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የከተማ ምህንድስና ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት፣ የቅየሳ ምህንድስና ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት እና የእንቫይሮንሜንታል ሳይንስ ፕሮግራም ዳሰሳ ጥናት የሚሉት ናቸው፡፡፡ በእለቱ የዳሰሳ ጥናቶቹን ከማጽደቅ በተጨማሪ የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ደጉ በቀለ ከትምህርት ክፍል ኃላፊዎችና ከሌሎች የኮሌጅ ኃላፊዎች ጋር ከትምህርት ሚኒስቴር በመጣው ቁልፍ የአፈጻጸም መለኪያ /KPI ላይ ተፈራርመዋል፡፡ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram #ethiopianpublicserviceuniversity PR call: 0945746405

በኢፐሰዩ የተማሪዎች ተሰጥኦ መለያ እና ማልሚያ ማንዋል ተገመገመ፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ ባካሄደው የአንደኛ መንፈቅ አመት ስብሰባ፣ “የኢፐሰዩ የተማሪ ተሰጥኦ እና ማልማት ማኑዋል (EPSU Student Talent & Development Manual)” ተብሎ በተዘጋጀው ረቂቅ ሰነድ ላይ ውይይት አካሄደ፡፡ የውይይት መርሐ ግብሩን የመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በመክፈቻው እንደተናገሩት፣ “አንድ ዩኒቨርሲቲ ዋና ተግባሩ ተማሪዎቹን ወደ መዳረሻቸው እንዲሄዱ መደገፍ ነው፤ መዳረሻቸው ደግሞ የንድፈሀሳብ ትምህርት ብቻ ላይሆን ይችላል፤ ስለዚህ፣ ከንድፈ ሀሳብ ትምህርት ባለፈ ስነምግባራቸውን እየመራን፣ እምቅ ችሎታቸውን እንዲያወጡ እየረዳን፣ ተሰጥኦዋቸውን እንዲለዩ እያስቻልን እና ወቅቱ የሚጠይቀውን ክህሎት እያለማን መሄድ እንድንችል Talent Development and essential soft skill በሚል ይህንን አደረጃጀት ፈጥረን፣ በርካታ ስራዎች ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡” በማለት ስለሚቀርበው ረቂቅ ማንዋል የካውንስሉ አባላት የጋራ ግንዛቤ እንዲይዙ አድርገዋል፡፡ ከዚያም የተማሪዎች አገልግሎት ምክትል ዲን አብዱ ሙሀመድ (ዶ/ር) የተዘጋጀውን ረቂቅ ማንዋል ለካውንስሉ አባላት ሲያቀርቡ፣ የተማሪዎችን ተሰጥኦ (talent) ለይቶ በማውጣት ጥቅም ላይ እንዲውል የማድረግ ስራ፣ በአንድ ሰው ወይም በአንድ የስራ ክፍል ብቻ የሚሰራ ስራ እንዳልሆነ እና ተማሪዎቹ ከዲግሪ ባሻገር ምን ይዘው ይውጡ የሚለው የዩኒቨርሲቲያችን ዋና የትኩረት ማእከል መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በመቀጠልም፣ “ሁላችንም የተለያየ ተሰጥኦ (talent) አለን፤ ያንን ተሰጥኦ ለተማሪዎቻችን በማካፈል ያላቸው እምቅ ችሎታ ተፈልቅቆ እንዲወጣ ማድረግ ይጠበቅብናል፤ ተሰጥኦ በመምረጥ ብቻ የምናመጣው አይደለም፤ ከመምረጥ ባሻገር የማያቋርጥ ክትትል እና እንክብካቤ በማድረግ የምናሳካው ጉዳይ ነው፡፡” በማለት ተናግረዋል፡፡ አስከትለውም በረቂቅ ማንዋሉ የተዘረዘሩ ዋና ዋና ተግባራትን እና የአፈጻጸም አቅጣጫዎችን አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም ተሰብሳቢዎቹ በቀረበው ረቂቅ ማንዋል ላይ ሀሳብ እና አስተያየት ሰጥተዋል፤ ከሰጡት ሀሳብ እና አስተያየቶች መካከል፣ በፕሮግራሙ የኤክስቴንሽን እና የቅዳሜ እና እሁድ ተማሪዎች ቢካተቱበት መልካም ነው፤ ተሰጥኦ ያላቸው የአካዳሚክ እና የአስተዳደር ሰራተኞችም ቢሳተፉበት አይከፋም፤ ለማሰላሰል እና ሀሳብ ለማመንጨት ምቹ የሆኑ ማእዘኖች ቢዘጋጁ መልካም ነው፤ የሚሉ ይገኙበታል፡፡ በማጠቃለያውም የቀረቡት ሀሳብ እና አስተያቶች ተካተውበት ረቂቅ ማኑዋሉ እንደሚጸድቅ ፕሬዘዳንቱ ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ገልጸው ውይይቱ አብቅቷል፡፡

ኢፐሰዩ ባካሄደው የካውንስል ስብሰባ የ1ኛ መንፈቅ አመት ሪፖርቱን አጸደቀ፤ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ታህሳስ 20 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ ለግማሽ ቀን ባካሄደው የካውንስል ስብሰባ፣ በአንደኛ መንፈቅ አመት በተሰሩ መደበኛ ተግባራት፣ በሪፎርም ስራዎች እና ቁልፍ የውጤት አመላካች አፈጻጸም መለኪያዎች መሰረት በተከናወኑ ተግባራት ላይ የቀረበውን ሪፖርት ገምግሞ አጸደቀ፡፡ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዘዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) በመክፈቻ ንግግራቸው፣ ዛሬ ለካውንስሉ የሚቀርበው የአንደኛ መንፈቅ አመት ሪፖርት፣ ከአብዛኛው የካውንስል አባል ጋር በተለያዩ የኮሚቴ ስብሰባዎች፣ የጋራ መድረኮች እና በሪፎርም ቡድን ውይይቶች ንግግር ሲደረግበት የቆዬ መሆኑን ጠቅሰው፣ “የዩኒቨርሲቲው ማናጅመንት አፈጻጸማችንን ገምግሞ፣ የትኛው ላይ ጥሩ እንደሰራን፣ የትኛው ላይ ተጠናክረን መቀጠል እንዳለብን እና ቀጣዩ የትኩረት አቅጣጫችን የቱ መሆን እንዳለበት ለይቷል፤ ከዛሬው ውይይታችን የሚጠበቀው ሪፖርቱን ገምግሞ ማጽደቅ እና ለቀጣይ ምን እንስራ? በሚለው ላይ ካውንስሉ ሀሳብ እና አስተያየት እንዲሰጥበት ነው፡፡” በማለት ስብሰባውን ከፍተዋል፡፡ ከመክፈቻው በኋላ የፕሬዘዳንት ጽ/ቤት ኃላፊው አብርሃም ሐጎስ (ዶ/ር) የአፈጻጸም ሪፖርቱን አቅርበዋል፤ ሪፖርቱ፣ መሰረታዊ መረጃዎች፣ በእቅዱ መሰረት በ14 ግቦች የተቀመጡ ዋና ዋና ተግባራት፣ ቁልፍ የውጤት አመላካች አፈጻጸም፣ በመንፈቅ አመቱ እንደ ውጤት የሚታዩ ተግባራት እና በቀጣዩ መንፈቅ አመት ትኩረት ሊደረግባቸው የሚገቡ ተግባራት በሚል ተደራጅቶ የቀረበ መሆኑን፣ ከሪፖርቱ አቀራረብ ለመገንዘብ ተችሏል፡፡ በመቀጠልም ከተሰብሳቢዎቹ ጥያቄና አስተያየት ቀርቦ በፕሬዘዳንቱ ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፡፡ በመጨረም ፕሬዘዳንቱ ውይይቱን ሲያጠቃልሉ፣ “ማኔጅመንቱ ያስቀመጠውን አቅጣጫ፣ በዛሬው ውይይት ያገኘናቸውን ግብአቶች እና በቀጣይ ከመላው ሰራተኛ ጋር በሚደረገው ውይይት የምናገኘውን ሀሳብ እና አስተያየት አዳምረን፣ ለቀጣዩ ስድስት ወር አፈጻጸም ተገቢ የሆነ የእቅድ ማሻሻያ እናደርጋለን” ብለዋል፡፡

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት