University of Gondar (UoG)
前往频道在 Telegram
University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.
显示更多📈 Telegram 频道 University of Gondar (UoG) 的分析概览
频道 University of Gondar (UoG) (@uofgondar) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 13 191 名订阅者,在 教育 类别中位列第 15 389,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 568 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 13 191 名订阅者。
根据 20 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 187,过去 24 小时变化为 3,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 15.88%。内容发布后 24 小时内通常能获得 9.98% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 095 次浏览,首日通常累积 1 317 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 10。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“University of Gondar is one of a pioneer public higher education institution with commendable achievements in teaching, research and community services.”
凭借高频更新(最新数据采集于 21 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 教育 类别中的关键影响点。
13 191
订阅者
+324 小时
+157 天
+18730 天
帖子存档
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለአመራሮቹ ያዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና ቀጥሎ ውሏል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ተቋማዊ ሽግግር፣ ለስትራቴጂካዊ አስተዳደር እና ለአካዳሚክ ፈጠራ የሚበቃ የላቀ አመራር” በሚል መሪ ቃል ለከፍተኛ፣ ለመካከለኛ እና ለመሰረታዊ አመራሮቹ ያዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና ዛሬም ሰኔ 14/2018 ዓ.ም በታወር 59 ህንፃ ዘርአያቆብ አዳራሽ ቀጥሎ ውሏል።
በዛሬው ዕለት በተሰጠው ስልጠና ላይ የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (AFLEX) ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ሰፊ ገለጻና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
አቶ ዛዲግ በስልጠናው ወቅት በሀገራዊ፣ ተቋማዊ እና ግለሰባዊ ህልሞች ዙሪያ ሰፊ ትንተና የሰጡ ሲሆን፣ በተለይም እንደ ሀገር ሊኖር ስለሚገባው የጋራ ህልም ከተለያዩ የዓለም ሀገራት ተሞክሮና ከምሁራን እይታ አንጻር ያለውን ታሪካዊ ሂደት በዝርዝር አቅርበዋል።
በተጨማሪም እንደ ዘርፉ ምሁርነታቸው ዩኒቨርሲቲውና አመራሮቹ ሊከተሏቸው የሚገቡ ጠቃሚ ምክረ ሀሳቦችን አካፍለዋል።
አሰልጣኙ ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ በገለጻቸው ላይ እንዳሳሰቡት፣ የአንድ ተቋም ሽግግርና ስኬት ሊረጋገጥ የሚችለው አመራሩ ግለሰባዊና ተቋማዊ ግቦቹን ከሀገራዊ ታላቅ ህልም ጋር ማሰናሰል ሲቻል እንደሆነ አመላክተዋል።
ይህ እጅግ አሳታፊ የነበረው ስልጠና የቀረበውን ገለጻ ተከትሎ ከተሳታፊዎች በርካታ ጥያቄዎችና አስተያየቶች የተነሱበት ሲሆን፣ በአሰልጣኙ አቶ ዛዲግ አብርሃ በኩል ማብራሪያና ምላሽ ተሰጥቶባቸዋል።
ይህ ለአመራሮች የተዘጋጀው የአቅም ግንባታ ስልጠና ነገ ሰኔ 15/2018 ዓ.ም ቀጥሎ እንደሚውል ከቦታው ያገኘነው መረጃ ያመላክታል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙዩኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሰኔ 14/2018 ዓ/ም
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሥራ ዕድልና ፈጠራ ልማት ማዕከል (CEED) ለ2018 ዓ.ም ዕጩ ምሩቃን በሥራ ተነሳሽነትና ዝግጁነት ዙሪያ ሥልጠና በመስጠት ላይ ነው፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሥራ ዕድልና ፈጠራ ልማት ማዕከል (CEED) ለ2018 ዓ.ም ዕጩ ምሩቃን ስልጠናውን ከሰኔ 13-14/2018 ዓ.ም በሁሉም የዩኒቨርሲቲው ግቢዎች የሰጠ ሲሆን በዛሬው ዕለት ሰኔ 14/2018 ዓ.ም ፍፃሜውን ያገኛል።
የሥራ ዕድልና ፈጠራ ልማት ማዕከል አስተባባሪ የሆኑት ዶ/ር ገብሬ ሙሉዓለም ስልጠናውን አስመልክተው እንደተናገሩት “ይህ የምሩቃን ሥልጠና በዓላማ-መር ሕይወት (Purpose-Driven Life)፣ ራስን ማወቅና ግላዊ ክህሎትን ማሳደግ ፣ በሥራ ዝግጁነት ክህሎት (Employability Skills) እና በሥራ ፈጣሪነት (Entrepreneurship) ዙሪያ ላይ ያተኮረ መሆኑን አስረድተዋል፡፡
ዶ/ር ገብሬ አክለውም “ይህ ሥልጠና ተማሪዎቻችን ከተለመደው የአካዳሚክ ዕውቀት ባሻገር ወደ ሥራው ዓለም ሲቀላቀሉ ተወዳዳሪና ስኬታማ እንዲሆኑ የሚያስችል ትልቅ ድልድይ ነው" ሲሉ ገልፀዋል።
ምሩቃን ወደፊት በቅጥር ላይ ብቻ ሳይወሰኑ በሥራ ፈጣሪነት አስተሳሰብ የታነጹና በሀገር ኢኮኖሚ የራሳቸውን አወንታዊ አሻራ የሚያሳርፉ መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ሥልጠናውን የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር በተሰጠው የዋና አሰልጣኞች ሥልጠና (Master Trainers) የሰለጠኑ 38 አሰልጣኝ መምህራን እየመሩት ይገኛል።
የሥልጠናው ይዘትና ዝግጅት ከተማሪዎቹ ፍላጎት ጋር እጅግ በጣም የተናበበ በመሆኑ ተማሪዎች ከተመረቁ በኋላ የሚገጥሟቸውን ተግዳሮቶች አስቀድመው እንዲረዱና በራስ መተማመን እንዲገነቡ ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ያነጋገርናቸው አስልጣኞች ገልፀዋል፡፡
በሥልጠናው ላይ የተሳተፉ ዕጩ ምሩቃን በሰጡት አስተያየት ሥልጠናው በተለይ በተግባር ላይ የተመሰረቱ እንቅስቃሴዎች (የበዙበት በመሆኑ ክህሎታችን በተጨባጭ ለመፈተሽ እንደረዳንና ወደ ሥራው ዓለም ለመግባት ትልቅ ስንቅና መነሳሳት ፈጥሮብናል፤ ወደፊትም ይህ አይነቱ ሥልጠና በተቋሙ ተጠናክሮ መቀጠል አለበት” በማለት ገልፀዋል፡፡
የገበያውን ዓለም መሠረት ያደረገው ይህ ሥልጠና ዛሬ ሰኔ 14/2018 ዓ.ም በስኬት ከተጠናቀቀ በኋላ፣ ምሩቃኑ ሰኔ 16/2018 ዓ.ም “ከትምህርት ወደ ሥራ ዓለም” በሚል መሪ ቃል የአሠሪ ድርጅቶችና አምራች ኢንዱስትሪዎች በሚሳተፉበትና በልዩ ሁኔታ በተቋሙ በድምቀት በሚከበረው ዓመታዊ የሥራ ትስስር መድረክ ላይ በንቃት እንዲሳተፉ ዶ/ር ገብሬ ጥሪያቸውን አቅረበዋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን.
የዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሰኔ 14/2018 ዓ.ም.
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ከነርቸር ፕሮጀክት (NURTURE Project) ጋር በመተባበር ባዘጋጀው የተመራቂ ተማሪዎች የፋይናል ፕሮጀክት የውድድር መድረክ (Graduate Final Project - Competition Challenge) ላይ እንዲገኙ ጋብዞዎታል!
የዕለቱ ዋና ዋና ሁነቶች፦
የፈጠራ ስራዎች ኤግዚቢሽን፦ የወደፊት ዲጂታል መፍትሄዎችን እና የቴክኖሎጂ ውጤቶችን ይመለከታሉ፤ ለተቋምዎ የሚሆኑ አዋጭ የዲጂታል መፍትሄዎችንም ይመርጣሉ።
የሽልማት ሥነ-ስርዓት፦ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለሚወጡ አሸናፊዎች የገንዘብ ሽልማት (15,000 ETB፣ 10,000 ETB እና 7,000 ETB) እንዲሁም የእውቅና ሰርተፍኬት ይበረከታል።
የትስስር መድረክ (Networking)፦ ከተመራቂ ወጣቶችና ከኢንዱስትሪ ባለሙያዎች ጋር ትስስር የሚፈጠርበት ምቹ አጋጣሚ እንደሚሆንም ይታመናል።
ሁነቱ የሚካሄድበት ቀን እና ቦታ፦
ቦታ፦ ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ፣ PG አዳራሽ (College of Informatics PG Hall)
ቀን፦ ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም. (June 24, 2026)
ሰዓት፦ ጠዋት 2:30
የነገዎቹን የቴክኖሎጂ መሪዎች በአካል በመገኘት እንዲያበረታቱ እና ለተቋምዎ የሚሆኑ አዳዲስ የፈጠራ ሀሳቦችን እንዲያበረታቱ በአክብሮት ተጋብዘዋል!
Graduate Final Project – Competition Challenge
The College of Informatics, in collaboration with the NURTURE Project, cordially invites you to the Graduate Final Project Competition Challenge. Join us to support our graduating students and discover cutting-edge digital solutions tailored for your institution!
Key Highlights of the Event
👉Innovation Exhibition: Explore future-ready digital solutions and technological advancements. A prime opportunity to scout viable digital products for your organization.
👉 Award Ceremony: Celebrating excellence with attractive cash prizes for top performers—1st Place (15,000 ETB), 2nd Place (10,000 ETB), and 3rd Place (7,000 ETB)—along with Certificates of Achievement.
🤝 Industry-Academia Linkage: A dynamic networking platform to connect talent with potential industries and sector experts.
Event Details@
👉 Venue: College of Informatics, PG Hall
👉 Date: June 24, 2026
👉 Time: 2:30 Local Time (8:30 AM)
Be there to empower tomorrow's tech leaders in person and explore innovative breakthroughs ready for institutional adoption. Your presence is highly valued!
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለቅድመ ምረቃ እጩ ተመራቂዎች ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና ተጠናቀቀ
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሰኔ 4 -12/2018 ዓ.ም ሲሰጥ የቆየው የቅድመ ምረቃ እጩ ተመራቂዎች የመውጫ ፈተና ዛሬ ተጠናቋል።
ከሰኔ 4 ጀምሮ ሲሰጥ የቆየው የመውጫ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ አካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ካሳሁን ተገኘ የምስጋና መልዕክት አስተላልፈዋል፡፡
የመውጫ ፈተናው ያለምንም ችግር መጠናቀቁን ያስታወቁት ምክትል ፕሬዝዳንቱ የፈተና ግብረ ሀይሉን ጨምሮ የፀጥታ ዘርፍ አባላት፣ በየደረጃው የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው የስራ ሀላፊዎች፣ መምህራን እንዲሁም የአይ.ሲ.ቲ ዳይሬክቶሬት ሰራተኞች ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽዎ አመስግነዋል።
በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ማራኪ ግቢ የፈተና ማዕከል ሀላፊ የሆኑት አቶ ጋዲሳ ወንዶ በበኩላቸው፤ በዩኒቨርሲቲው የፈተናው ሂደት በስኬት እንዲጠናቀቅ ከመጀመሪያ ቀን አንስቶ ለተፈተኛ ተማሪዎች በቂ ገለፃ በመስጠት እና ከአመራሩ ጋር በቅርበት በመነጋገር ያለፉትን ሰባት የፈተና ቀናት ካለምንም የዲሲፒሊን ችግር ፈተናውን በሰላም ማጠናቀቅ መቻሉን ተናግረዋል።
በመጨረሻም በዩኒቨርሲቲው በነበራቸው ቆይታ ከአቀባበል ጀምሮ ለተደረገላቸው መልካም መስተንግዶ ምስጋናቸውን አቅርበው፤ በፈተናው ወቅት የበኩላቸውን ድርሻ የተወጡ አካላትን አመስግነዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መርሃ ግብር መሰረት በዩኒቨርሲቲው ከሰኔ 4 -12/2018 ዓ.ም በተሰጠው ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከ6759 በላይ እጩ ተመራቂዎች በዩኒቨርሲቲው ሦስት ግቢዎች (ማራኪ፣ ቴዎድሮስና ፋሲል) የመውጫ ፈተናውን ወስደዋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነት እና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈፃሚ
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
በጎንደር ዩኒቨርሲቲ የሕክምና ቁሳቁስ ድጋፍ ተበረከተ።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅና ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል አገልግሎት የሚውል 60 ሚሊዮን ብር የተገዛ ዘመናዊ የቀዶ ጥገና ህክምና ማይክሮስኮፕ ሰኔ 12/2018 ዓ.ም '''ሪች አናዘር'' ከተሰኘ በጎ አድራጎት ድርጅት በስጦታ ተበርክቷል።
የማይክሮስኮፑ ድጋፍ በሆስፒታሉ የሕክምና፣ የምርመራና የምርምር አገልግሎቶችን ለማጠናከር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት የተገለጸ ሲሆን መሣሪያው በተለይ በኒሮ ሰርጀሪ።
በፓቶሎጂ፣ በላቦራቶሪ ምርመራዎች እና በተለያዩ የሕክምና ምርምር ሥራዎች ላይ ትክክለኛና ፈጣን ውጤት ለማግኘት እንደሚያግዝ ተጠቁሟል።
በስጦታ ማስረከቢያ ሥነ-ሥርዓቱ ላይ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ እና የሆስፒታሉ ኃላፊዎች በተገኙበት የበጎ አድራጎት ድርጅቱ ለዩኒቨርሲቲው እና ለማህበረሰቡ እያደረገ ላለው ድጋፍ ምስጋና ቀርቧል።
የሆስፒታሉ አመራሮች እንደገለጹት፣ የተበረከተው ዘመናዊ ማይክሮስኮፕ የምርመራ አገልግሎቶችን ጥራት ከፍ ከማድረጉም በላይ ለተማሪዎች፣ ለመምህራንና ለተመራማሪዎች ተግባራዊ የስልጠናና የምርምር ሥራዎችን ለማጠናከር ከፍተኛ እገዛ ያደርጋል።
ይህ ድጋፍ በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታል የሕክምና አገልግሎትን ለማዘመንና ለማሻሻል እየተደረጉ ካሉ ጥረቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ ለታካሚዎች የተሻለ እና ተደራሽ የሕክምና አገልግሎት ለማቅረብ ያግዛል ተብሏል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀት እንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
የተቋምን ታሪክ መሰነድ ተቋሙ የመጣበትን መንገድ ለመረዳትና ጠንካራ ጎኑን ለማሳደግ እንዲሁም ሊስተካከል የሚገባውን ለይቶ ለማረም በአጠቃላይ ተቋማዊ እድገትን ለማረጋገጥ አይነተኛ ሚና አለው::
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
በተለይም ተቋሙን ሊደግፉ የሚችሉ አካላት ስለተቋሙ የተሟላ መረጃና ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማስቻሉም በተጨማሪ በየተቋማቱ በኃላፊነትም ሆነ በሁሉም የአገልግሎት ዘርፎች ለትውልድ አሻራቸውን እያኖሩ ያሉ ባለታሪኮችን እንደየ ተሳትፏቸው የሚያነሳ በመሆኑ በማስተማሪያ ሰነድነት የመዋል አቅምም አለው።
ከዚያም ባሻገር የተቋማትን እና የማኅበረሰቡን አበርክቶ በአግባቡ በማደራጀት ተገቢውን ክብርና ትኩረት እንዲያገኙ በማሳለጥ ለሀገር ግንባታ ከፍ ያለ አስተዋጽዖ ይኖረዋል፡፡
ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ለዚህ ማሳያ የሚሆንና ልምድ ሊወሰድበት የሚችል ታሪክ ተቋሙን ማዕከል ባደረገ መንገድ “የትውልድ አሻራ” በሚል ርዕስ መጽሐፍ አሰናድቷል፡፡
ይህን ተሞክሮ ሊያሰፋ የሚችል ዝግጅት ሰኔ 15 ቀን 2018 ዓ.ም. ከቀኑ በ 8፡00 ሰዓት በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዲሱ ፕሬዚዳንት ጽ/ቤት ሕንጻ 6ኛ ፎቅ ላይ መጽሐፉን በማስመረቅ ይካሄዳል፡፡
ስለሆነም በዚህ ደማቅ ዝግጅት ትሳተፉ ዘንድ ሁላችሁም ተጋብዛችኋል፡፡
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀትእንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሰኔ 12/2018 ዓ/ም
"የአንድ ሀገር ወይም ተቋም ስኬትና ውድቀት የሚወሰነው በተፈጥሮ ሀብት መኖር ሳይሆን በተቋማት ጥራትና ጥንካሬ እንዲሁም በመሪዎች ስልታዊ እይታ ነው" — ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ተቋማዊ ሽግግር፣ ለስትራቴጂካዊ አስተዳደር እና ለአካዳሚክ ፈጠራ የሚበቃ የላቀ አመራር” በሚል መሪ ቃል ለከፍተኛ፣ ለመካከለኛ እና ለመሰረታዊ አመራር ያዘጋጀውን የሶስት ቀናት ስልጠና መስጠት ጀምሯል።
ከሰኔ 12/2018 ዓ.ም ጀምሮ በዘርአያቆብ አዳራሽ (ታወር 59 ህንፃ ) እየተሰጠ በሚገኘው በዚህ ስልጠና ላይ የዩኒቨርሲቲው ሥራ አስፈጻሚዎች፣ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ የትምህርት ክፍል ኃላፊዎች፣ ፕሮፌሰሮችና አስተባባሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ። በተጨማሪም ከጎንደር ከተማ አስተዳደር እና ከደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የተጋበዙ የሥራ ኃላፊዎችና እንግዶች በፕሮግራሙ ላይ ታድመዋል።
ስልጠናውን እየሰጡ ያሉት የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (AFLEX) ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ ናቸው።
የመድረኩን መከፈቻ ንግግር ያደረጉት የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር አሥራት ዓፀደወይን፣ የአንድ ሀገር ወይም ተቋም ስኬትና ውድቀት የሚወሰነው በተፈጥሮ ሀብት መኖር ሳይሆን በተቋማት ጥራትና ጥንካሬ (Institutional Quality) እንዲሁም በመሪዎች ስልታዊ እይታ (Strategic Governance) መሆኑን በተለያዩ ዋቢ መጻሕፍት አስደግፈው አብራርተዋል።
የጎንደር ዩኒቨርሲቲ የነገ የሀገር መሪዎችንና ከፍተኛ ምሁራንን የሚያፈራ ተቋም በመሆኑ ይህንን እውነት ወደ ተግባር የመቀየር ቀዳሚ ኃላፊነት እንዳለበት ፕሬዚደንቱ አስገንዝበዋል።
አክለውም "እውነተኛ ተቋማዊ ሽግግር (Institutional Transformation) ለማምጣት መዋቅርና አሰራርን መቀየር ብቻ አይበቃም፤ ከሁሉ አስቀድሞ የአመራሩን የአስተሳሰብ አድማስ (Mindset) ማደስና ማሳደግ ግድ ይላል" በማለት የዩኒቨርሲቲውን ራዕይ አብራርተዋል።
ይህ ስልጠና አመራሩ ቀጣይ ስራዎቹን በላቀ እይታ፣ በአዲስ ስትራቴጂካዊ መነቃቃትና በሙሉ ጉልበት ለመምራት ትልቅ የእውቀትና የክህሎት አቅም እንደሚፈጥር ሙሉ እምነታቸውን የገለጹት ዶ/ር አሥራት፤ ሰልጣኞች ስልጠናውን በንቃት በመከታተል ከሀገራዊ ተጨባጭ ሁኔታዎች ጋር ያገናዘበ ውጤታማ ውይይት እንዲያደርጉ አሳስበዋል።
ፕሬዚዳንቱ ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ ለዩኒቨርሲቲው ላሳዩት ልዩ አጋርነትና ወንድማዊ እገዛ በራሳቸውና በተቋሙ ስም ከልብ የመነጨ ምስጋና አቅርበዋል።
የአፍሪካ አመራር ልህቀት አካዳሚ (AFLEX) ፕሬዚደንት ክቡር አቶ ዛዲግ አብርሃ በአመራርነትና ተያያዥ ርዕሰ-ጉዳዮች ላይ ያተኮረውን ይሄንን ስልጠና መስጠት የጀመሩ ሲሆን፣ መርሃ ግብሩ በቀጣዮቹ ሁለት ቀናትም በተከታታይ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ታውቋል።
፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨
ለልህቀትእንተጋለን!
የህዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ስራ አስፈፃሚ
ሰኔ 12/2018 ዓ/ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
