ar
Feedback
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

الذهاب إلى القناة على Telegram

በኢ.ኦ.ተ.ቤ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። በግቢ ጉባኤያችን የሚከናወኑ ተግባራት፣ መረጃዎችንና መልእክቶችን ለውድ አባላቶቹ ያደርሳል። Instagram: https://www.instagram.com/unitygebigubae TikTok: https://www.tiktok.com/@unitygebigubae

إظهار المزيد
2 145
المشتركون
+324 ساعات
+57 أيام
+2030 أيام

جاري تحميل البيانات...

جذب المشتركين
أغسطس '26
أغسطس '26
+2
في 0 قنوات
يوليو '26
+70
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '26
+40
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '26
+64
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '26
+44
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '26
+196
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '26
+68
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '26
+53
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '25
+59
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '25
+94
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '25
+130
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '25
+17
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '25
+14
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '25
+16
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '25
+30
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '25
+29
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '25
+42
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '25
+103
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '25
+47
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '25
+85
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '24
+112
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '24
+216
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '24
+125
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '24
+46
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '24
+38
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '24
+20
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '24
+42
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '24
+34
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '24
+47
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '24
+75
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '24
+60
في 1 قنوات
Get PRO
يناير '24
+85
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '23
+105
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '23
+41
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '23
+35
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '23
+15
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '23
+15
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '23
+20
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '23
+26
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '23
+28
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '23
+22
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '23
+30
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '23
+44
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '23
+12
في 0 قنوات
Get PRO
ديسمبر '22
+20
في 0 قنوات
Get PRO
نوفمبر '22
+29
في 0 قنوات
Get PRO
أكتوبر '22
+33
في 0 قنوات
Get PRO
سبتمبر '22
+9
في 0 قنوات
Get PRO
أغسطس '22
+19
في 0 قنوات
Get PRO
يوليو '22
+8
في 0 قنوات
Get PRO
يونيو '22
+14
في 0 قنوات
Get PRO
مايو '22
+16
في 0 قنوات
Get PRO
أبريل '22
+4
في 0 قنوات
Get PRO
مارس '22
+14
في 0 قنوات
Get PRO
فبراير '22
+6
في 0 قنوات
Get PRO
يناير '22
+328
في 0 قنوات
التاريخ
نمو المشتركين
الإشارات
القنوات
01 أغسطس+2
منشورات القناة
"ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡አለው፥እኔም፡በመጨረሻው፡ቀን፡ አስነሣዋለኹ።ሥጋዬ፡እውነተኛ፡መብል፡ደሜም፡እውነተኛ፡መጠጥ፡ነውና።ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡በእኔ፡ይኖራል፡እኔም፡
"ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡የዘለዓለም፡ሕይወት፡አለው፥እኔም፡በመጨረሻው፡ቀን፡ አስነሣዋለኹ።ሥጋዬ፡እውነተኛ፡መብል፡ደሜም፡እውነተኛ፡መጠጥ፡ነውና።ሥጋዬን፡የሚበላ፡ደሜንም፡የሚጠጣ፡በእኔ፡ይኖራል፡እኔም፡በርሱ፡እኖራለኹ።" የዮሐንስ ወንጌል 6፥ 54-56 የሕይወት ቀን - በኅብረት ቅዱስ ቁርባን እንቀበል ነሐሴ ፰፤ ፳፻፲፰ (8/2018) ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

2
"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ማቴ 26፥41 ወርኃዊ የመሐረነ አብ ጸሎት 🤲 የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በግቢ ጉባኤያችን በወሩ የመጨረሻ
"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ማቴ 26፥41 ወርኃዊ የመሐረነ አብ ጸሎት 🤲 የእግዚአብሔር  ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በግቢ ጉባኤያችን በወሩ የመጨረሻ አርብ የመሐረነ አብ ጸሎት እንደምናደርስ ይታወቃል። ስለሆነም የፊታችን አርብ ሐምሌ 24/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 - 11፡00 በመገኘት ስለ ሀገራችን ፣ ስለ ሃይማኖታችን ፣ ስለ ማኅበራችን በኅብረት እንጸልይ ስትል ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። ለበለጠ መረጃ፦ 0912947576 0970038330 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
412
3
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦ ❝ሃሌ ሉያ የእግዚአብሔር ቤት ሆይ ተቀደሺ ኃይልንም ልበሺ እነሆ በኃይሉ የሚያበራልሽ ንጉሥሽ መጥቶአልና! ይህችን ቤት አብ አስቀድሞ አነጻት ይህችን ቤት ወልድ አነጻት ይህችን ቤት መንፈስ ቅዱስ ፈጸማት❞ ምልጣን ዘሰኔ 21 ✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያዊ ቤተክርስቲያን ምሥረታን ለግቢ ጉባዔያችን ደግሞ የ2018 ዓ.ም የሥራ አስፈጻሚዎች ልዩ የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ሐምሌ 25 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0912947576 0970038330 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
501
4
✤ ቅዱስ #ቂርቆስ እድሜው የሦስት ዓመት ሳለ እናቱ ቅድስት እየሉጣ ከሮሜ ወደ ሌላ ሃገር ሸሽታ ይዛው ሄደች በዚያም የሸሸችውን መኮንኑን አገኘችው። የሚያውቋትም ሰዎች ሸሽታ እንደመጣች ስለተረዱ ለመኮንኑ ነገር ሰሩባት። መኮንኑም ቅድስት አየሉጣን አስጠራትና ስለ አምልኮ ጠየቃት። ቅድስት ኢየሉጣም መኮንን ሆይ፡ እድሜው ሦስት አመት የሆነው ሕፃን አለ አማልክቶችህን ማምለክ መልካም እንደሆነ ወይም እንዳልሆነ ያስረዳን ዘንድ እርሱን ጠይቅ አለችው። መኮንኑም ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስም ወደ አለበት ጭፍራውን ልኮ ወደ እርሱ አስመጣው ሕፃኑንም ፊቱ ብሩህና ደስተኛ እንደሆነ አየውና አንተ ደስተኛ ሕፃን ሆይ እንዴት ነህ አለው። ሕጻን ቅዱስ ቂርቆስም መለሰለት እንዲህም አለው። አዎ እኔ በጣም ደስተኛ ነኝ ደስታየም ተጠብቆልኛል ላንተ ግን ኀዘንና ለቅሶ ጥርስ ማፋጨትም ነው፤ መጽሐፍ ቅዱስም ለዝንጉዎች ተድላ ደስታ የላቸውም ብሏልና አለው። እግዚአብሔር አምላክ ኃይልንና ንግግርን ሰጥቶታልና በዚያ ለተሰበሰቡት ሰዎች እስኪደነግጡ ድረስ ብዙ ተናገረ። ሕፃን ቅዱስ ቂርቆስም ንጉሱን መኳንንቱንና ጣዖታቱን ረገማቸው ከብርታቱም የተነሳ አደነቁ። መኮንኑም በአፈረ ጊዜ በየአይነቱ በሆነ ስቃይ፡ ታላላቆች አንኳ የማይችሉትን ታላቅ አስጨናቂ የሆነ ስቃይን አሰቃየው። እናቱ ቅድስት እየሉጣንምከእርሱ ጋር እንደ እርሱ በጣሙን አሰቃያት። እግዚአሔብሔር ግን ያለ ምንም ጉዳት ያነሳቸው ነበር። ብዙዎች አህዛብም ይህን አይተው አደነቁ ክብር ይግባውና በጌታችን በመድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አምላክነት አምነው በሰማእትነት ሞቱ የሰማእትነትንም አክሊል ተቀበሉ። በሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ላይም የመንፈስ ቅዱስ ጸጋ አደረበት። ታላላቅ ድንቅ ተአምራቶችንም ያደርግ ነበር። ብዙዎች በሽተኞችንም ያድናቸው ይፈውሳቸው ነበር ። ይህንን ያየ መኮንን በታላቅ የነሃስ ጋን ውስጥ ውሃ ጨምረው በእሳት ያፈሉት ዘንድ አዘዘ። የፍላቱም ድምጽ እንደ ክረምት ነጎድጓድ ሆነ ድምጹም በጣም ያስተጋባ ነበር። ይህን ያየችና የሰማች እናት ቅድስት እየሉጣም ፍርሃትና የሃይማኖት ጉድለት ታየባት። ሕፃኑ ቅዱስ ቂርቆስ ግን እናቱ ቅድስት እየሉጣን ሁኔታዋን አይቶ ወደ አምላኩ እግዚአብሔር ጸለየ። ያን ጊዜ ልዑል እግዚአብሔር ልቧን ወደ ሰማይ አሳርጎ ለቅዱሳን ሰማዕታት የተዘጋጁ የብርሃን ማደሪያዎችን አሳያት። ቅድስት እየሉጣም እንደገና በሃይማኖቷ ጸናች። እግዚአብሔር አምላኳንም አመሰገነችው። ልጇን ሕፃኑን ቅዱስ ቂርቆስንም ልጄ ሆይ አንተ ከእንግዲህ አባቴ ነህ እኔም ልጅህ ነኝ አለችው። ቅድስት እየሉጣም ለልጇ ያች የተወለድክባት እለት ቀኗ የተባረከችና የተቀደሰች ናት አለችው። የመኳንንቱ ጭፍሮችም እሳት ወደ አለበት ጋኖች ውስጥ ቅዱስ ቂርቆስንና እናቱን ቅድስት እየሉጣን በጨመሯቸው ጊዜ የውሃው ፍላት ወደያውኑንቀዘቀዘ። ከእግዚአብሔር የታዘዘ የመላእክት አለቃ ቅዱስ ገብርኤል ከሰማይ ወርዶ የእሳቱን ኃይል አቀዝቅዞታልና። ይህን ያየ መኮንን ሥጋቸው ተቆራርጦ እስከሚወድቅ ድረስ በመቃጥን ውስጥ አድርገው አንዲጎትቷቸው አዘዘ። ከእግዚአብሔርም የታዘዘ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል አዳናቸው። መኮንኑም በታላቅ ስቃይ ያሰቃያቸው ዘንድ አስቦ እስኪመክር ድረስ በወህኒ ቤት ዘጋባቸው። በዚህን ጊዜ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስን አረጋጋው አጽናናው። ስሙን ጠርተው መታሰቢያ ለሚያደርጉለትም በረከትን እንደሚያገኝ ቃል ኪዳን ሰጠው ። እግዚአብሔር አምላካችን የሕጻኑ ቅዱስ ቂርቆስና የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣን በረከታቸውንና ረድኤታቸውን ያድለን አሜን። ቅዱስ ቂርቆስና ቅድስት ኢየሉጣ በእግዚአብሔር ቸርነት በቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት በእሳት ከመጣል በንፍር ውሃ ከመለብለብ ከዳኑ በኋላ እለስክንድሮስ መከራውን ፈርተው ይመለሳሉ ብሎ በሀብለ ሰናስል እያሰረ በችንካር እየቸነከረ ሲያሰቃያቸው ቆየ፡፡ የማይሆንለት ሲሆን እጅ እግራቸውን አስሮ ከዝግ ቤት አስቀመጣቸው፡፡ ጌታም የመከራቸውን ጽናት የትዕግስታቸውን ብዛት አይቶ ከመከራ ሊያሳርፋቸው ሽቶ በመንፈቀ ሌሊት ተገልጾ፤ በመጣ ጊዜ “ሰላም ለከ ኦ ፍቁርየ ቂርቆስ” ወዳጄ ቂርቆስ ሆይ ሰላም ላንተ ይሁን፤ ብሎ ሠላምታ ከሰጠው በኋላ የመከራህን ጽናት፣ የትዕግስትህን ብዛት አይቼ ቃል ኪዳን ልገባልህ ነው።” “ዘመጠነዝ ገድለ ተጋዲልየ ምንተኑ ትዔስየኒ” በሕፃንነቴ ይህን ያህል ተጋድዬ የምትሰጠኝ ምንድነው?” አለው። “አዐሥየከ ዘሀሎ ውስተ መልብከ” በልብህ ያለውን ሁሉ እሰጥሃለሁ አለው። እንኪያስ በስሜ ቤተ ክርስቲያን ከታነጸበት ረሃብ፣ ቸነፈር፣ የሰው በሽታ፣ የከብት እልቂት፣ የእኅል የውሃ ጥፋት፣ አይሁን አለ። ጌታም ይሁንልህ በማለት ቃል ኪዳን ገብቶላታል፡፡ ደግሞም “ኢትቅብር ሥጋየ በዲበ ምድር” ሥጋዬ በምድር አይቀበር አለው። “አልቦ ዘይፈደፍደከ ዘእንበለ መንበረ መንግሥትየ ወማርያም ወላዲትየ ወዮሐንስ መጥምቅየ” (ከመንበረ መንግስቴ፣ ከማርያም እናቴ ከዮሐንስ መጥምቅም በቀር በመንግሥተ ሰማያት የሚበልጥህ የለም።) “ወዓዲ ከመ ኢይስማን ሥጋከ ዲበ ሠረገላ ኤልያስ አነብረከ” (ሥጋህን እንዳይፈርስ በኤልያስ ሠረገላ አኖርልሃለሁ) ብሎ ተስፋውን ነግሮታል። እናቱ ቅድስት ኢየሉጣ በመኮንኑ በሰይፍ ጥር ፲፮ በሰማዕትነት ያረፈች ሲሆን ቅዱስ ቂርቆስን ግን ተመለስ ቢለው አልመለስም እምነቴንም አልክድም ባለው ጊዜ ሰይፍ ጃግሬውን ጠርቶ በጥር ፲፭ አስገድሎት ሰማዕትነትን ተቀብሏል፡፡ የእናቱ የቅድስት ኢየሉጣ መታሰቢያዋ ዕለት በየወሩ በ፲፮ እመቤታችን ቃል ኪዳን በተቀበለችበት ቀን በሚታሰብበት የቅድስት ኪዳነ ምህረት ቀን ይታሰባል። የመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ምልጃና ጸሎት፤ የቅዱስ ቂርቆስና የቅድስት ኢየሉጣ በረከታቸው ቃል ኪዳናቸው ይድረሰን በእውነት ይጠብቀን ለዘለዓለሙ አሜን፨ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
646
5
እንኳን ለቅዱስ ቂርቆስ ወኢየሉጣና ለሊቀ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ) #ሐምሌ_፲፱#በዓለ_ቅዱስ_ገብርኤል_ወቅዱስ_ቂርቆስ_ወቅድስት_ኢየሉጣ_ወሥርዐተ_ማኅሌት፡፡     ቅዱስ ገብርኤል ሊቀ መላእክት ✼ ነቢዩ ዳንኤል “ዐይኖቼንም አነሣሁ” አለና አስከትሎ “እነሆም በፍታ የለበሰውን ጥሩም የአፌዝን ወርቅ በወገቡ ላይ የታጠቀውን ሰው አየሁ፡፡ አካሉም እንደ ቢረሌ ይመስል ነበር፤ ፊቱም እንደ መብረቅ አምሳያ ነበረ፤ ዐይኖቹም #እንደሚንበለበል ፋና፣ ክንዶቹና እግሮቹም እንደ ጋለ ናስ፣ የቃሉም #ድምፅ እንደ ብዙ #ሕዝብ ድምፅ ነበረ፡፡… ይህንንም ታላቅ ራእይ አየሁ፤ ኃይልም አልቀረልኝም፤ ክብሬም ወደ ውርደት ተለወጠብኝ #ኃይልም አጣሁ፡፡ የቃሉንም ድምፅ ሰማሁ፤ የቃሉን ድምፅ በሰማሁ ጊዜ ደንግጬ በምደር ላይ #በግምባሬ_ተደፋሁ” አለ፡፡(ዳን.10፥5-9) ነቢዩ ዳንኤል እንዲህ ብሎ የተናገረው የመላእክትአለቃ የቅዱስ #ገብርኤልን አስፈሪ ግርማ በተመለከተ ጊዜ ነበር፡፡ ✤ ገብርኤል የሚለው ቃል የሁለት ቃለት ጥምር ነው እነዚህም #ገብር እና #ኤል ሲሆኑ ትርጕማቸውም ገብር #አገልጋይ ማለት ሲሆን ኤል ማለት ደግሞ አምላክ ማለት ነው፤ በተገኛኘ ገብርኤል ማለት #የአምላክ_አገልጋይ /የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል የአምላክ አገልጋይ ማለት ነው። “እነሆ ከዋነኞቹ አለቆች” አንዱ ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ”(ዳን.10፥13) ብሎ በተናገረው ንግግሩ በመላእክት ላይ የተሾሙ ሌሎች አለቆች እንዳሉ ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቅዱሳን መላእክት ዘንድ ስላሉት ነገዶች ሲገልጽ “… በሰማይ ያለውን በምደር ያለውን የሚታየውንና የማይታየውን መናብርትም ቢሆኑ አጋእዝትም ቢሆኑ መኳንንትም ቢሆኑ ቀደምትም ቢሆኑ ሁሉም በእጁ ሆነ፤ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ ተፈጠረ” (ቈላ.1፥16) በማለት ይዘረዝራቸዋል፡፡ ከዚህ ተነሥተን መላእክት በተለያዩ ዐበይት ነገዶች የተከፈሉና ለእያንዳንዱም ነገድ የራሱ የሆነ አለቃ እንዳለው ማስተዋል እንችላለን፡፡ ቅዱስ ገብርኤልም ከእነዚህ ዐበይት የመላእክት ነገዶች መካከል አንዱ በሆነው #እርባብ በሚባለው ዐቢይ ነገድ ላይ የተሾመ ሲሆን ከ100ው ነገደ መላእክት መካከል ከበታቹ የሚመራቸው ዐሥር ነገደ መላእክት አሉት፤ ከተማቸውም በሰማየ #ራማ ነው፡፡ ✼ ቅዱሳን መላእክት በቅዱስ ሚካኤል ፊት አውራሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል ከመንሳታቸው አስቀድሞ ቅዱስ ገብርኤል፣ እንደ አምላክ ሊመለክ የወደደውን ሳጥናኤልን በመቃወም ‹‹#ንቁም_በበህላዌነ_እስከ_ንረክቦ_ለአምላክነ - “አይዞአችሁ ፈጣሪያችን እስክናገኘው፣ እስክናውቀው ድረስ በያለንበት ጸንተን እንቁም፡፡” (አክሲማሮስ ገጽ.35) በማለት #መላእክትን_ያረጋጋ_መልአክ_ነው፡፡ በተወዳጁ መልአክ በቅዱስ ሚካኤል መሪነት የሰው ልጆች ጠላት የሆነውን ዲያብሎስን ተዋግተው ድል እንዲያደርጉ ወደ ጥልቁ እንዲጣል አድርጓል ራእ12፥7፤ ነቢዩ ኢሳይያስ በሰማያት የሳጥናኤል ትዕቢትና ውድቀት ምን እንደሚመስል ሲጽፍልን “አንተ በንጋት የሚወጣ አጥቢያ ኮከብ ሆይ እንዴት ከሰማይ ወደቅህ! ወደ አሕዛብ መልእክትን የላክ አንተሆይ እንዴት እስከ ምድር ድረስ ተቀጠቀጥህ! አንተም በልብህ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ዙፋኔንም ከእግዚአብሔር ከዋክብት በላይ ከፍ ከፍ አደረጋለሁ፤… በልዑልም እመሰላለሁ አልህ፡፡ ዛሬ ግን ወደ ሲኦል ትወድቃለህ፤ ወደ ምድር ጥልቅም ትወርዳለህ” (ኢሳ.1416) በማለት ገለጠልን፤ ወደ ምድር የጣሉት በመላእክት አለቃ በቅዱስ ሚካኤል  እና በቅዱስ ገብርኤል  መሪነት   ነበር፡፡ ✼ ቅዱስ ገብርኤል ወንጌላዊው ቅዱስ ሉቃስ ከሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው ብሏል ሉቃ 1፥19፤ ታላቁ ነቢይ ሄኖክም ስለ ነገረ መላእክት በተናገረበት አንቀጽ እንዲህ ሲል መስክሯል ‹‹በአበቦች ላይ በገነትም በጻድቃን ላይ #በኪሩቤልም ላይ የተሾሙ ከከበሩ መላእክት አንዱ #ገብርኤል ነው፡፡›› ሄኖክ 6፥7፤ ‹‹በሦስተኛውም በመላእክት ሁሉ ላይ የተሾመ ቅዱስ ገብርኤል ነው››ሄኖክ 10፥14 እያለ የመልአኩን ክብር ተናግሯል፡፡ ቅዱስ ገብርኤል ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ ለተጠሩት መንፈሳዊ እውቀቱን የሚያካፍላቸው መልአክ ብቻ አይደለም፤ ለእግዚአብሔር በመገዛታቸው ምክንያት ከአላውያን ገዢዎች ከሚደርስባቸው መከራም የሚታደጋቸው መልአክም ነው፡፡ ነገር ግን ያደረጋቸው ተዓምራቶች በመጽሐፍ ቅዱስ፣ በመልክኡ፣ በድርሳኑ፣ በገድሉ፣ በተዓምሩ የተጻፉ ቢሆንም ሐምሌ 19 እና ታኅሣሥ 19 ያደረጋቸውን ተራዳኢነት  ፡- ✤✤✤ ሐምሌ 19 ቀን ሕፃኑ ቅዱስ #ቂርቆስና እናቱ ቅድስት #እየሉጣ በሰማዕትነት መከራ የተቀበሉበት፤ ሊቀ መላእክት  ቅዱስ #ገብርኤል ደግሞ #ከእቶን እሳት ያዳናቸው እለት ነው:: ✤✼፠ #ታኅሣሥ_19 አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) ያዳናቸው ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ አናንያና(ሚሳቅ)፣ አዛርያ(ሲድራቅ) እና ሚሳኤል(አብደናጎ) የፋርስ ባቢሎን ንጉሥ የነበረው ናብከደነፆር በዱራ(አዱራን) በሚባል ስፍራ ላይ ላቆመው ጣዖት አንሰግድም በማለታቸው ወደ እቶን እሳት እንዲጣሉ አድርጓቸዋል ፤ በመልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ተራዳኢነት ግን ከእቶን እሳቱ የልብሳቸው ዘርፍ እንኳን እሳት ሳይነካው ድነዋል፡፡ (ይህንን በዓል የምናከብረው ታኅሣሥ 19 ስለሆነ ታሪኩን በስፋት ለመረዳት የታኅሳስ 19 ስንክሳርን ወይም የታኅሣሥ ወር ልጥፈችንን ወደ ሃሏ  በመመለስ ይመልከቱ ፡፡)
513
6
#ሐምሌ_7 #ቅድስት_ሥላሴ ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም፡፡ የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3፡፡ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰግደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ…›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡ ያች ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ ሉቃ 1፡35፡፡ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡ ሥሉስ ቅዱስን የአብርሃሙ ሥላሴን በምግባር በሃይማኖት ሆነን እናገለግል ዘንድ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን! https://t.me/zemariian
1 317
7
✤ #እረፍታቸው የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም እንዲህ ኾነ፤ በዘመኑ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረው የሮም ንጉሥ ወደ አካይያ ዘምቶ ድል አድርጎ በደስታ ወደ ሮሜ ሲመለስ መኳንንቱን ለማስደሰት፤ ጣዖታቱንም ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ትጥቁን ለውጦ ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?›› ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም እሔዳለሁ›› አለው። ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› ባለው ጊዜም ‹‹አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ›› ሲል መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድ ነበር። ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል፤›› (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡ በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡ እንደ ሥርዓታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን ‹‹እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ሐምሌ ፭ ቀን ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ በመስቀል ላይ ሳለም ተከታዮቹን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ ካዘዛቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ ሥጋውንም መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ሽቱ ቀብቶ፣ በነጭ ሐር ገንዞ ዛሬ ቫቲካን በምትባለዋ ስፍራ በክብር ቀብሮታል፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ ከእዚያም እግዚአብሔር በሞቱ እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም አደባባይ በጨካኙ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት ቁልቁል (እንደ አምላኬ አልሰቀልም ብሎ) በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡           ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ ጳውሎስ ለ 2 ዓመት ከ6 ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት አንገቱን በሠይፍ ተሠይፎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይክፈለን፤ አሜን፡፡ #አቢያተ_ክርስቲያናቱ፤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ-ወጳውሎስ፤ ከፒያሳ ወደ አስኮ በሚወስደው መስመር መንገድ ላይ የሚገኝ፡፡ #ሰዋስወ_ብርሃን_ቅዱስ-ጳውሎስ_ገዳም፤ ከ3ቱ መንፈሳውያኝ ኮሌጆች አንዱና ዋነኛው የሚገኝበት፡፡ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ 18ት ማዞሪያ ብላችሁ ስትሄዱ የሚገኝ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
1 235
8
እንኳን ለሐዋርያት (የሰኔ) ጾም ፍቺ፤ እንዲሁም ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ_ወሥርዐተ_ማኅሌት_ዘሐምሌ_፭፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ፤ በገሊላ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ የአባቱ ስም ዮና የእናቱ ስም ሃውኒን ይባላል፡፡ ከ 5 ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ነው የመጀመሪያው ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዷ ስም እንዳወጣችለት ይነገራል፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ፤ ነገዱ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ነው አባቱ ዮስአል ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ ጠርሴስ በንግድ የታወቀች የኬልቅያ ዋና ከተማ ናት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ  በ15 ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሐገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀ የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዐት እየተማረ እስከ 3ዐ ዓመቱ ቆየ፡፡  በ3ዐ ዓመቱ የአይሁድን ሸንጐ አባል ሆኖ ተቈጠረ፡፡ ✤ #ለአገልግሎት_አጠራራቸው ✤✼ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ ማሥገር ጀመረ፡፡ ለደቀመዛሙርትነት ሲመረጥ እድሜው 55 ዓመት ሲሆን ወደጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡን ታንኳውን እንዲህም አባቱን ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ በቂሳርያ ከተማ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ በጠየቀ ጊዜ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረ ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን አንተ ጴጥሮስ ነህ ብሎታል ይህን በጽርዕ ቋንቋ «ዐለት» ማለት ነው በአረማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለ በመሆኑ ጌታችን ለደቀመዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 16፥23 በኋላም ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው እንኳን ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም በማለት የተናገረ ሐዋርያ ነው፡፡ (ማቴ 26፥34) ነገር ግን 3 ጊዜ ጌታችንን አላውቀውም ብሎ ካደ፤ ዶሮ በጮኸና አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ ንስሐ ገባ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለየው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሣ ወደማስገሩ ተሠማራ ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢከዳው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው አውቆ ትወደኛለህ ተብሎ ሲጠየቅ አንተ ታውቃለህ ነበረ መልሱ የራሱ እውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኀዳጌ በቀል /በቀልን የሚተው/ ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንሰሐ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ ጠቦቶቼን ጠብቅ በጐቼን አሠማራ በማለት አደራውን አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፥15-17 ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ በአይሁድ ሸንጐ አባልነት ለ2 ዓመታት በሠራበት ወቅት እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመኾኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው፡፡  በ32 ዓመት ዕድሜው ከኢየሩሳሌም 223 ኪ.ሜ ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ ጠይቆ ካገኘ በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና ሳዖል፥ ሳዖል ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ የሰማው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ጌታ ሆይ ማን ነህ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል ሲል መድኀኒታችን ተናገረው፡፡ ያንን በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ ሲል ጠየቀው ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው፡፡ የሐዋ 9፥1 የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም ነበር፡፡ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ ለ3 ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራዕይ ተገለጠለት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና  እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡ ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት ጊዜ የመጡ ናቸው፡፡ ያን ስደት ያስነሳው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው፡፡ በዚህ በቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ነበርና ነው፡፡ ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረውም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሐገር ሄደ፥ ለሦስት ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየም በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ። በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት፡፡ በዚያም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሱ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኩል ወደ ትውልድ ሐገሩ ጠርሴስ ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለ9 ዓመታት ቆይቷል፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ፡፡ ከዚህም በኋላ ሐዋርያው ሦስት ታላላቅ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን አድርጓል፡፡ በመጀመሪያው ጉዞው ወደ 2,ዐዐዐ ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፤ ይህም የተከናወነው በ46 ዓ.ም. ነው፡፡ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ18 በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ5ዐ ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡  በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ2ዐ በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ54 ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ ብዙም ጊዜ በቁም እሥር በብዙም መከራ ሥቃይ እንግልት ያሳለፈ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡
977
9
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 የግቢ ጉባኤያችን አባል የሆነችው የእህታችን ዮሐናን በየነ (የ2ኛ ዓመት Marketing Management ተማሪ) አያት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ልዑል እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ከቅዱሳኑ ጋር ያሳርፍልን፤ ለእህታችንና ለቤተሰቦቿም ፍጹም መጽናናትን ያድልልን። በመኖሪያ ቤታቸው መድረስ የምትችሉ አሳውቁንና ስንሄድ እንነግራችኋለን። 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ
1 393
10
የወርኃ ሰኔ የእመቤታችን ጽዋ እና የሥራ አስፈፃሚዎች ርክክብ መርሃግብር ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ገርጂ ማርያም ፤ አዲስ አበባ ፤ ኢትዮጵያ
የወርኃ ሰኔ የእመቤታችን ጽዋ እና የሥራ አስፈፃሚዎች ርክክብ መርሃግብር ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ገርጂ ማርያም ፤ አዲስ አበባ ፤ ኢትዮጵያ
1 289
11
የቀረጻችሁት ቪዲዮ ፎቶ ካለ እንደ ፋይል ስለሚቀመጥ @Fiyona_ayche በዚህ አካውንት እንድትልኩልን በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን🙏
1 150
12
"እግዚአብሔር እስከዚህ ረድቶናል!" (1ሳሙ 7፥12) የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ቤተሰቦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ያደረግነው የዓመቱ ማጠቃለያ መንፈሳዊ ጉዞ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእመቤታችን ድንግል ማርያም ጥበቃ በሰላምና በታላቅ በረከት ተጠናቋል። በጉዞው ላይ ተገኝታችሁ በጸሎት፣ በዝማሬና በክርስቲያናዊ ፍቅር ቀኑን የበረከት ላደረጋችሁ ተጓዦች በሙሉ፣ እንዲሁም መርሃ ግብሩ እንዲሳካ ከጀርባ ሆናችሁ በሃሳብ፣ በገንዘብና በጸሎት ለደገፋችሁን በሙሉ ግቢ ጉባኤያችን ከልብ የመነጨ ምስጋናዋን ታቀርባለች። የተቀበልነው በረከትና ያሳለፍነው የኅብረት ጊዜ በሕይወታችን ላይ ፍሬ ሆኖ እንዲቀር የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 369
13
1000277472574 እንጦጦ ደብረ ኃይል ራጉኤል የአቅማችሁን አግዙ🙏
1 190
14
"ሥርዓትስ ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።"  1ቆሮ 14፥ 40 🚌 የጉዞ ማሳሰቢያ የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላትና ተጓዦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን የምናደርገው ጉዞ የበረከትና የሰላም ይሆንልን ዘንድ፣ ተጓዦች በሙሉ ወደተዘጋጀው መርሃ ግብር ሲመጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና መንፈሳዊ ሥርዓቶች እንዲያከብሩና እንዲተገብሩ ግቢ ጉባኤያችን በአክብሮት ታሳስባለች። 1. በሰዓት መገኘት፦ የመነሻ ሰዓት ጠዋት ከነጋቱ 1:00 በመሆኑ፣ ሁሉም ተጓዥ በመነሻ ቦታው (ገርጂ ማርያም) በሰዓቱ እንዲገኝ እናሳስባለን። 2. በፆም መምጣት፦ በጉዞው ላይ ጸበልና የበረከት ተግባራት ስላሉ፣ የጤና እክል ከሌለባችሁ በስተቀር ጠዋት ሳይመገቡ መምጣት ይመረጣል። 3. ክርስቲያናዊ አለባበስ፦ የቤተክርስቲያንን ሥርዓት የጠበቀ አለባበስ (በተለይም ነጭ ነጠላ በመልበስ) እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። የሰላምና የበረከት ጉዞ ይሁንልን! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 092
15
ትኬት ያልገዛችሁ ወንድምና እህቶች ነገ ጠዋትም ቀድማችሁ በመምጣት ትኬት ማግኘት ስለምትችሁ እንዳትቀሩ ፤ አደራ ! ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318
1 001
16
"ሥርዓትስ ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።" 1ቆሮ 14፥ 40 🚌 የጉዞ ማሳሰቢያ የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላትና ተጓዦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን የምናደርገው ጉዞ የበረከትና የሰላም ይሆንልን ዘንድ፣ ተጓዦች በሙሉ ወደተዘጋጀው መርሃ ግብር ሲመጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና መንፈሳዊ ሥርዓቶች እንዲያከብሩና እንዲተገብሩ ግቢ ጉባኤያችን በአክብሮት ታሳስባለች። ፩ 1. በሰዓት መገኘት (Punctuality) የጉዞው መነሻ ሰዓት ጠዋት ከነጋቱ 11:30 በመሆኑ፣ ተጓዦች በሙሉ ያለምንም መዘግየት በተጠቀሰው ሰዓት ላይ በመነሻ ቦታው (ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል) እንድትገኙ እናሳስባለን (image_ac48ee.jpg)። ሰዓት ማክበር የወንድሞቻችንንና የእህቶቻችንን ጊዜ ከመቆጠብ ባለፈ የመርሃ ግብሩ ስኬት መሠረት ነው። 2. ምግብ አለመብላት (Fasting before Blessings) በጉዞው ላይ ጸበል፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የበረከት ተግባራት ስለሚኖሩ፣ አስገዳጅ የጤና ሁኔታ ካላጋጠማችሁ በስተቀር ጠዋት ሳይመገቡ (በፆም) መምጣት ይመረጣል (image_ac48d3.jpg)። ጸበል ለመጠመቅና በረከትን ለመቀበል ራስን ማዘጋጀት መንፈሳዊ ሥርዓታችን ነው። 3. ክርስቲያናዊ አለባበስ (Christian Attire) ወደ ቅዱሱ ስፍራ የምናደርገው ጉዞ በመሆኑ፣ ተጓዦች በሙሉ የቤተክርስቲያንን ሥርዓትና ክብር የጠበቀ፣ ክርስቲያናዊ አለባበስ (በተለይም ነጭ ነጠላ በመጎናጸፍ) እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። አለባበሳችን ለቦታው ያለንን ክብርና ውስጣዊ ስብዕናችንን የሚገልጽ መሆን ይኖርበታል። "እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነውና እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም።" እነዚህን መሠረታዊ የጉዞ ማሳሰቢያዎች በተግባር በመተርጎም የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ እያሳሰብን፣ ጉዟችንን የሰላምና የፍሬ ያደርግልን ዘንድ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን። 🙏 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
117
17
ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-10:00
ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-10:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ቦታ ይያዙ ትኬቱን ለማግኘት 0942139509 0972237318
1 325
18
"እግዚአብሔር አምላክን አመስግኑት... እረኛንና ጠባቂን ሰጥቶናልና።" 📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉✨ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ ስንጠይቅበት የሰነበትነው የዕጣ ማውጣት ሥርዓት በዛሬው እሮብ ዕለት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና በሰላም ተጠናቋል። እግዚአብሔር አምላክ ለጉባዔያችን የሚበጁትን፣ የወጣትነት ጉልበታቸውን ለአገልግሎት የሚሰጡትን የ2019 ዓ.ም አዲሶቹን ሥራ አስፈጻሚዎች (አገልጋዮች) በዕጣው ገልጦልናል። ይህ በጸሎት የዘራነው መንፈሳዊ ፍሬ የሚቀጥለው ቅዳሜ (የኃላፊነት ርክክብ በሚደረግበት ዕለት) በይፋ የሚሰየም ይሆናል። ስለሆነም፣ መላው አባላት በአካል ተገኝታችሁ አዲሶቹን መሪዎች የምንቀበልበት፣ ነባሮቹን ደግሞ ስለ ደከሙበት አገልግሎት የምናመሰግንበት የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር የሚመጣው ቅዳሜ ስለሚከናወን፣ ሁላችሁም በታላቅ ደስታና ዝግጅት እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አዲሶቹን አገልጋዮች እግዚአብሔር በረድኤት ያጽናቸው፤ ለጉባዔያችንም የሰላምና የፍሬ ዘመን ያድርግልን! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 067
19
"የሁሉን ልብ የምታውቅ ጌታ ሆይ፤ የመረጥኸውን አንዱን አሳይ።" (ሐዋ. 1፥24) 📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባዔ አባላት በሙሉ✨ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን የግቢ ጉባዔያችን የ2018 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎች የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው ኃላፊነታቸውን ለቀጣዩ ታማኝ ትውልድ የሚያስረክቡበት ልዩ ወቅት ላይ እንገኛለን። የፊታችን ቅዳሜ የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር ከመከናወኑ በፊት፣ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ በዕጣ የምንጠይቅበት ልዩ መንፈሳዊ ሥርዓት ይኖረናል። የክርስቶስ ማኅበር የሆነውን ግቢ ጉባዔያችንን በቅንነትና በትሕትና የሚያገለግሉትን አዲሶቹን መሪዎች እግዚአብሔር በዕጣው የሚገልጥበት ዕለት ደርሷል። ስለሆነም፣ እያንዳንዳችን በጸሎትና በአካል ተገኝተን የቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት የምንከተልበት የዕጣ ማውጣት መርኃ-ግብር የተዘጋጀ በመሆኑ፣ መላው አባላት ሳይቀሩ እንዲገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡ 📅 የዕጣው ቀን፦ ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም 🕕 ሰዓት፦ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ የአገልግሎት ርክክብ ቀን፦ ቅዳሜ ይህ የአገልግሎት ሽግግር ሰላማዊ፣ መንፈሳዊና የተባረከ ይሆን ዘንድ የእያንዳንዱ አባል በጸሎት ማገዝና በአካል መገኘት እጅግ አስፈላጊ ነው። ጉባዔው የሁላችንም ነውና ይህንን ታላቅ ዕለት በጉጉትና በጸሎት እንጠብቅ! እግዚአብሔር ለጉባዔው የሚበጀውን እውነተኛ አገልጋይ በዕጣው ይግለጥልን፤ እስከዚያው በጸሎት እንበርታ! ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ
1 067
20
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦ ❝ሃሌ ሉያ የእግዚአብሔር ቤት ሆይ ተቀደሺ ኃይልንም ልበሺ እነሆ በኃይሉ የሚያበራልሽ ንጉሥሽ መጥቶአልና! ይህችን ቤት አብ አስቀድሞ አነጻት ይህችን ቤት ወልድ አነጻት ይህችን ቤት መንፈስ ቅዱስ ፈጸማት❞ ምልጣን ዘሰኔ 21 ✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል -"ሕንጸታ ቤተክርስቲያን" በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያዊ ቤተክርስቲያን ምሥረታን ለግቢ ጉባዔያችን ደግሞ የ2018 ዓ.ም የሥራ አስፈጻሚዎች ልዩ የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ሰኔ 27 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 165