uz
Feedback
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

Kanalga Telegram’da o‘tish

በኢ.ኦ.ተ.ቤ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። በግቢ ጉባኤያችን የሚከናወኑ ተግባራት፣ መረጃዎችንና መልእክቶችን ለውድ አባላቶቹ ያደርሳል። Instagram: https://www.instagram.com/unitygebigubae TikTok: https://www.tiktok.com/@unitygebigubae

Ko'proq ko'rsatish
2 124
Obunachilar
+224 soatlar
+67 kunlar
-530 kunlar
Obunachilarni jalb qilish
Iyul '26
Iyul '26
+21
0 kanalda
Iyun '26
+40
0 kanalda
Get PRO
May '26
+64
0 kanalda
Get PRO
Aprel '26
+44
0 kanalda
Get PRO
Mart '26
+196
0 kanalda
Get PRO
Fevral '26
+68
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '26
+53
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '25
+59
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '25
+94
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '25
+130
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '25
+17
0 kanalda
Get PRO
Avgust '25
+14
0 kanalda
Get PRO
Iyul '25
+16
0 kanalda
Get PRO
Iyun '25
+30
0 kanalda
Get PRO
May '25
+29
0 kanalda
Get PRO
Aprel '25
+42
0 kanalda
Get PRO
Mart '25
+103
0 kanalda
Get PRO
Fevral '25
+47
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '25
+85
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '24
+112
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '24
+216
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '24
+125
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '24
+46
0 kanalda
Get PRO
Avgust '24
+38
0 kanalda
Get PRO
Iyul '24
+20
0 kanalda
Get PRO
Iyun '24
+42
0 kanalda
Get PRO
May '24
+34
0 kanalda
Get PRO
Aprel '24
+47
0 kanalda
Get PRO
Mart '24
+75
0 kanalda
Get PRO
Fevral '24
+60
1 kanalda
Get PRO
Yanvar '24
+85
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '23
+105
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '23
+41
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '23
+35
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '23
+15
0 kanalda
Get PRO
Avgust '23
+15
0 kanalda
Get PRO
Iyul '23
+20
0 kanalda
Get PRO
Iyun '23
+26
0 kanalda
Get PRO
May '23
+28
0 kanalda
Get PRO
Aprel '23
+22
0 kanalda
Get PRO
Mart '23
+30
0 kanalda
Get PRO
Fevral '23
+44
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '23
+12
0 kanalda
Get PRO
Dekabr '22
+20
0 kanalda
Get PRO
Noyabr '22
+29
0 kanalda
Get PRO
Oktabr '22
+33
0 kanalda
Get PRO
Sentabr '22
+9
0 kanalda
Get PRO
Avgust '22
+19
0 kanalda
Get PRO
Iyul '22
+8
0 kanalda
Get PRO
Iyun '22
+14
0 kanalda
Get PRO
May '22
+16
0 kanalda
Get PRO
Aprel '22
+4
0 kanalda
Get PRO
Mart '22
+14
0 kanalda
Get PRO
Fevral '22
+6
0 kanalda
Get PRO
Yanvar '22
+328
0 kanalda
Sana
Obunachilarni jalb qilish
Esdaliklar
Kanallar
16 Iyul0
15 Iyul+3
14 Iyul+2
13 Iyul+3
12 Iyul+3
11 Iyul0
10 Iyul+1
09 Iyul+2
08 Iyul0
07 Iyul+1
06 Iyul0
05 Iyul+3
04 Iyul0
03 Iyul+1
02 Iyul0
01 Iyul+2
Kanal postlari
#ሐምሌ_7 #ቅድስት_ሥላሴ ሐምሌ ሰባት በዚች ቀን ሥሉስ ቅዱስ በአብርሃም ቤት የተገለጡበት ነው፡፡ አብ ወልድ መንፈስ ቅዱስ በስም በአካል በግብር ሦስትነት በባሕርይ በሕልውናና በፈቃድ አንድነት የጸኑ ናቸው፡፡ በዚህ ጊዜ ተገኙ፣ በዚህ ጊዜ ያልፋሉ አይባሉም መጀመሪያም መጨረሻም እነርሱ ናቸውና፡፡ ርሕሩሐን ናቸውና በእናት ሥርዓት ‹‹ቅድስት ሥላሴ›› እንላቸዋለን፡፡ የሚጠላቸው (የማያምንባቸውን) አይጠሉም፡፡ የሚወዳቸውን ግን እጽፍ ድርብ ይወዱታል፣ በቤቱም መጥተው ያድራሉ፡፡ ከፍጥረታት ወገን ከእመቤታችን ቀጥሎ የአብርሃምን ያህል በሥላሴ ዘንድ የተወደደ ፍጡር የለም፡፡ አባታችን ቅዱስ አብርሃም የደግነት ሁሉ አባት ነውና በኬብሮን በመምሬ ዛፍ ሥር ሥላሴን ተቀብሎ አስተናግዷል፡፡ አባታችን አብርሃም በ99 ዓመቱ እናታችን ሣራ በ89 ዓመቷ ሥላሴን በድንኳናቸው አስተናገዱ፡፡ አብርሃም እግራቸውን አጠበ፡፡ በጀርባውም አዘላቸው፡፡ ምሳቸውንም አቀረበላቸው፡፡ እነርሱም እንደሚበሉ ሆኑለት፡፡ በዚያው ዕለትም የይስሃቅን መወለድ አበሠሩት፡፡ አብርሃም ከደግነቱና እንግዳ ከመውደዱ የተነሣ በተመሳቀለ ጎዳና ላይ ድንኳን ሠርቶ የወጣ የመረደውን፣ የመጣ የሄደውን ሁሉ እየተቀበለ እግዚአብሔርን እያገለገለ የሚኖር ጻድቅ ነበር፡፡ ለዚህም ነው አብርሃም በወይራ ግራር (በመምሬ) ዛፍ ሥር ተቀምጦ ሳለ እግዚአብሔር አንድነቱን ሦስትነቱን የገለጠለት፡፡ ዘፍ 18፡1-25፣ ሮሜ 4፡-3፡፡ ቀትር ሰዓት ላይ በድንኳኑ ደጅ ተቀምጦ እንግዳ ሲጠብቅ እግዚአብሔር ታየው ተነጋገረው፡፡ አንገቱን ቀና አድርጎ ዐይኑን አራምዶ በተመለከተ ጊዜ እነሆ ሦስት ሰዎች ከበላዩ ባለ ተራራ ላይ ቆመው አያቸው፣ ወደ እርሱም ሲወርዱ አይቶ ፈጥኖ ሄዶ ከሰግደላቸው በኋላ ‹‹አቤቱ በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ እንደሆነ ባሪያህን አትለፈኝ ብዬ እለምናለሁ፤ ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ…›› እያለ በትሕትና በመጋበዝ ወደ ድንኳኑ አስገብቶ በሚገባ ጋበዛቸው፡፡ ‹‹በፊትህስ ሞገስ አግኝቼ›› ብሎ አንድነታቸውን፣ ‹‹ጥቂት ውኃ ይምጣላችሁ እግራችሁን ታጠቡ›› ብሎ የሦስትነታቸውን ምስጢር ገልጾአል፡፡ ያች ሥላሴ የገቡባት የአብርሃም ድንኳን የእመቤታችን ምሳሌ ናት፡፡ ሥላሴ ወደ አብርሃም ድንኳን እንደገቡ ሁሉ በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያምም አብ ለአጽንዖ፣ መንፈስ ቅዱስ ለአንጽሖ፣ ወልድ በተለየ አካሉ ሥጋዋን ለመዋሐድ የማደራቸው ምሳሌ በመሆኑ አማናዊቷ የሥላሴ ማደሪያ የአብርሃም ድንኳን እመቤታችን ናት፡፡ ሉቃ 1፡35፡፡ እግዚአብሔርም አብርሃምን የዛሬ ዓመት ልጅ እንደሚወልድ ነግሮት በዓመቱ ይስሐቅን ወልዷል፡፡ ሁለቱ ሰዎች ከአብርሃም ድንኳን ወጥተው ወደ ሰዶም ወደ ገሞራ ሄዱ፣ አብርሃምም ይሸኛቸው ዘንድ አብሯቸው ሄደ፡፡ የሄዱትም ሁለቱ ሰዎች አብና መንፈስ ቅዱስ ናቸው፡፡ ነገር ግን አንዱ ወልድ በአብርሃም ቤት ቀርቷል ይኸውም ከቤተ አብርሃም ሰው እንደሚሆን ለማጠየቅ ነው፡፡ አብርሃምም ተመልሶ በእግዚአብሔር ፊት ቆመ፡፡ እግዚአብሔርም የሚሠራውን ሁሉ ከአብርሃም አይሠውርም ነበርና የሰዶምን የገሞራን ጥፋት ነገረው፡፡ አብርሃምም ይቅር እንዲላቸው አብዝቶ ለመነላቸው፡፡ ሥሉስ ቅዱስን የአብርሃሙ ሥላሴን በምግባር በሃይማኖት ሆነን እናገለግል ዘንድ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን! https://t.me/zemariian

2
✤ #እረፍታቸው የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም እንዲህ ኾነ፤ በዘመኑ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረው የሮም ንጉሥ ወደ አካይያ ዘምቶ ድል አድርጎ በደስታ ወደ ሮሜ ሲመለስ መኳንንቱን ለማስደሰት፤ ጣዖታቱንም ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ትጥቁን ለውጦ ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?›› ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም እሔዳለሁ›› አለው። ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› ባለው ጊዜም ‹‹አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ›› ሲል መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድ ነበር። ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል፤›› (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡ በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡ እንደ ሥርዓታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን ‹‹እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ሐምሌ ፭ ቀን ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ በመስቀል ላይ ሳለም ተከታዮቹን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ ካዘዛቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ ሥጋውንም መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ሽቱ ቀብቶ፣ በነጭ ሐር ገንዞ ዛሬ ቫቲካን በምትባለዋ ስፍራ በክብር ቀብሮታል፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ ከእዚያም እግዚአብሔር በሞቱ እንደሚያከብረው ነግሮት ወደ ሰማይ ዐረገ፡፡ በመጨረሻም ቅዱስ ጴጥሮስ በሮም አደባባይ በጨካኙ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት ቁልቁል (እንደ አምላኬ አልሰቀልም ብሎ) በመስቀል ላይ ተሰቅሎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት ዐረፈ፡፡           ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ ጳውሎስ ለ 2 ዓመት ከ6 ወር በጨለማ ቤት ታሥሮ ከቆየ በኋላ በ74 ዓመት ዕድሜው በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ በኔሮን ቄሳር ዘመነ መንግሥት አንገቱን በሠይፍ ተሠይፎ ሐምሌ 5 ቀን በ67 ዓ.ም. በሰማዕትነት አረፈ፡፡ አምላካችን እግዚአብሔር ከቅዱስ ጴጥሮስና ከቅዱስ ጳውሎስ ረድኤት በረከታቸው ይክፈለን፤ አሜን፡፡ #አቢያተ_ክርስቲያናቱ፤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ-ወጳውሎስ፤ ከፒያሳ ወደ አስኮ በሚወስደው መስመር መንገድ ላይ የሚገኝ፡፡ #ሰዋስወ_ብርሃን_ቅዱስ-ጳውሎስ_ገዳም፤ ከ3ቱ መንፈሳውያኝ ኮሌጆች አንዱና ዋነኛው የሚገኝበት፡፡ ከመርካቶ አውቶቡስ ተራ 18ት ማዞሪያ ብላችሁ ስትሄዱ የሚገኝ፡፡ /በፍኖተ ሕይወት ሰ.ት.ቤት ሚድያና ሕዝብ ግንኙነት ዋና ማስተባበሪያ ክፍል የተዘጋጀ።/ • Facebook 👉 m.facebook.com/FinoteHiwotSundaySchool • Telegram 👉 t.me/finotehiwott • Tiktok 👉 tiktok.com/@finotehiwot  • YouTube 👉 m.youtube.com/@finotehiwot1958
590
3
እንኳን ለሐዋርያት (የሰኔ) ጾም ፍቺ፤ እንዲሁም ለብርሃናተ ዓለም ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ በዓለ ዕረፍት አደረሳችሁ፡፡ ✤✤ #ብርሃናተ_ዓለም_ጴጥሮስ_ወጳውሎስ_ወሥርዐተ_ማኅሌት_ዘሐምሌ_፭፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጴጥሮስ፤ በገሊላ ባሕር ዳርቻ በምትገኘው በቤተሳይዳ ተወለደ፡፡ የአባቱ ስም ዮና የእናቱ ስም ሃውኒን ይባላል፡፡ ከ 5 ዓመቱ ጀምሮ ያደገው በቅፍርናሆም ከተማ ነው የመጀመሪያው ስሙ ስምዖን ሲሆን ይህንንም እናቱ በነገዷ ስም እንዳወጣችለት ይነገራል፡፡ ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ፤ ነገዱ ከዕብራውያን ከብንያም ነገድ ነው አባቱ ዮስአል ሲሆን የተወለደውም በጠርሴስ ከተማ ነው፡፡ ጠርሴስ በንግድ የታወቀች የኬልቅያ ዋና ከተማ ናት፡፡ ሮማውያን በሥራቸው ለሚተዳደሩት ሕዝቦች ሮማዊ ዜግነት ይሰጡ ስለነበር የቅዱስ ጳውሎስ አባት በዜግነት ሮማዊ ነበር፡፡ ይህም ለቅዱስ ጳውሎስ ተላልፎለታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ  በ15 ዓመት ዕድሜው ወደ ትውልድ ሐገሩ በመመለስ በኢየሩሳሌም ከነበረው የታወቀ የገማልያል ትምህርት ቤት ገባ፡፡ በዚያም የአይሁድን ሕግና ሥርዐት እየተማረ እስከ 3ዐ ዓመቱ ቆየ፡፡  በ3ዐ ዓመቱ የአይሁድን ሸንጐ አባል ሆኖ ተቈጠረ፡፡ ✤ #ለአገልግሎት_አጠራራቸው ✤✼ ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በጐልማሳነቱ ከወንድሙ ከእንድርያስ ጋር በገሊላ ባሕር ዓሣ ማሥገር ጀመረ፡፡ ለደቀመዛሙርትነት ሲመረጥ እድሜው 55 ዓመት ሲሆን ወደጌታችን ያመጣውም ወንድሙ እንድርያስ ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ለሐዋርያነት ሲጠራ መተዳደሪያው የነበረውን መረቡን ታንኳውን እንዲህም አባቱን ትቶ ጌታውን የተከተለ ሐዋርያ ነው፡፡ በቂሳርያ ከተማ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ማን ትሉኛላችሁ ብሎ በጠየቀ ጊዜ አንተ የሕያው የእግዚአብሔር ልጅ ነህ ብሎ ለአይሁድ ሊቃውንት የተሰወረ ምሥጢረ ተዋሕዶ ገልጦ በመመስከሩ ጌታችን አንተ ጴጥሮስ ነህ ብሎታል ይህን በጽርዕ ቋንቋ «ዐለት» ማለት ነው በአረማይክ ደግሞ ኬፋ ይባላል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ጌታን ይወድ ነበር፡፡ ፍቅሩ ግን ቅንዓት የተቀላቀለ በመሆኑ ጌታችን ለደቀመዛሙርቱ የሞቱን ነገር ቀድሞ ሲነግራቸው አይሁንብህ በማለት ተከራክሯል፡፡ ማቴ 16፥23 በኋላም ሁሉም በአንተ ቢሰናከሉ እኔ ከቶ አልሰናከልም ብሎ በራሱ ቅንዓት ተማምኖ ተናግሮ ነበር፡፡ ጌታችን ዶሮ ሳይጮህ ሦስት ጊዜ ትክደኛለህ ያለው እንኳን ከአንተ ጋር መሞት እንኳ የሚያስፈልገኝ ቢሆን ከቶ አልክድህም በማለት የተናገረ ሐዋርያ ነው፡፡ (ማቴ 26፥34) ነገር ግን 3 ጊዜ ጌታችንን አላውቀውም ብሎ ካደ፤ ዶሮ በጮኸና አምላኩን መበደሉን እንዳወቀ ከግቢው ወጥቶ አለቀሰ ንስሐ ገባ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በዕድሜው ታላቅነት በሐዋርያት ዘንድ እንደ አባት ይታይ ስለነበር ጌታ በተለየው ጊዜ ሐዋርያቱን ሊመግብ ወደሚያውቀው ሙያ ዓሣ ወደማስገሩ ተሠማራ ጌታም አስቀድሞ የመረጠው እርሱ ነውና ቢከዳው እንኳን በንስሐ በመመለሱ ንስሐውን መቀበሉን ዛሬም እንደሚወደው ይገልጽለትም ዘንድ በጥብርያዶስ ባሕር ተገለጠለት፡፡ ሦስት ጊዜ ክዶት ነበርና ቀኖና ሰጠው፡፡ አሁን ቅዱስ ጴጥሮስ በራስ መተማመኑ እንዳላዋጣው አውቆ ትወደኛለህ ተብሎ ሲጠየቅ አንተ ታውቃለህ ነበረ መልሱ የራሱ እውቀት የት እንዳደረሰው ያውቃልና ጌታችንም ኀዳጌ በቀል /በቀልን የሚተው/ ነውና ዛሬም እንደሚወደው በንሰሐ ተመልሷልና ዛሬም ለእርሱ የሰጠውን ክብር እንደማያጐልበት ሲነግረው ግልገሎቼን አሠማራ ጠቦቶቼን ጠብቅ በጐቼን አሠማራ በማለት አደራውን አስረከበው፡፡ ዮሐ 21፥15-17 ✼ #ሐዋርያው_ቅዱስ_ጳውሎስ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሚያስተምርበት ዘመን ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም ስለነበረ በአይሁድ ሸንጐ አባልነት ለ2 ዓመታት በሠራበት ወቅት እምነቱ ቀናተኛ ፈሪሳዊ በመኾኑ ክርስቲያኖችን በማናቸውም አጋጣሚ ይቃወም ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተወግሮ በሰማዕትነት ሲያርፍም የወጋሪዎችን ልብስ ይጠብቅ የነበረው እርሱ ነው፡፡  በ32 ዓመት ዕድሜው ከኢየሩሳሌም 223 ኪ.ሜ ርቀት በስተሰሜን በኩል በምትገኘው የደማስቆ ከተማ ብዙ ክርስቲያኖች መኖራቸውን ሲሰማ ወደ ሊቀ ካህናቱ ቀርቦ ክርስቲያኖችን ለማጥፋት የሚያስችለውን የፈቃድ ደብዳቤ ጠይቆ ካገኘ በኋላ ጭፍሮችን አስከትሎ ወደ ደማስቆ አመራ፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስ ወደ ከተማዋ ለመድረስ ጥቂት ሲቀረው ነበር ከሰማይ የወረደው ብርሃን አካባቢውን ያለበሰውና ሳዖል፥ ሳዖል ስለምን ታሳድደኛለህ? የሚለውን ድምፅ የሰማው፡፡ ሐዋርያው ጳውሎስም ጌታ ሆይ ማን ነህ? ብሎ ጠየቀ የምታሳድደኝ እኔ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ የመውጊያውን ብረት ብትቃወም ለአንተ ይብስብሃል ሲል መድኀኒታችን ተናገረው፡፡ ያንን በወደቀበት ሆኖ እየተንቀጠቀጠ ጌታ ሆይ ምን አደርግ ዘንድ ትወዳለህ ሲል ጠየቀው ከዚህ በኋላ ተነሥቶ ወደ ደማስቆ እንዲገባ ተነገረው፡፡ የሐዋ 9፥1 የሐዋርያው ዓይኖች ለማየት አልቻሉም ነበር፡፡ እየተመራ ወደ ደማስቆ ገባ ለ3 ቀናት ያህልም እህል ሳይቀምስ ቆየ በዚያች ዕለት እግዚአብሔር አምላክ በደማስቆ ለሚገኘው እና ሐናንያ ለተባለው አባት በራዕይ ተገለጠለት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም ያለበትን አድራሻ ነገረውና  እንዲያጠምቀው አዘዘው፡፡ ሐናንያ አስቀድሞ የቅዱስ ጳውሎስን ማንነት ያውቃል፡፡ አብዛኞቹ በደማስቆ የሚገኙት ክርስቲያኖች ከኢየሩሳሌም በስደት ጊዜ የመጡ ናቸው፡፡ ያን ስደት ያስነሳው ደግሞ በቅዱስ እስጢፋኖስ ላይ የደረሰው መከራ ነው፡፡ በዚህ በቅዱስ እስጢፋኖስ ሰማዕትነት ደግሞ ዋናው ተዋናይ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ ነበርና ነው፡፡ ሐናንያ ቅዱስ ጳውሎስን ካጠመቀውና ካስተማረውም በኋላ ቅዱስ ጳውሎስ ወደ ዓረብ ሐገር ሄደ፥ ለሦስት ዓመታት በዓረቢያ በረሃ ከቆየም በኋላ ወደ ደማስቆ ከተማ ተመለሰ። በዚያም በነበሩ አይሁድ መካከል በፊት ያሳድደው የነበረውን ኢየሱስ ክርስቶስን መስበክ ጀመረ፡፡ ከዚያ በፊት በፈሪሳዊነቱና ለአይሁድ ሕግ በነበረው ቅንዓት የሚታወቀው ጳውሎስ ዛሬ ወንጌል ሲሰብክ በማየታቸው አይሁድ ተነሡበት፡፡ በዚያም የተነሣ የደማስቆ ክርስቲያኖች በቅርጫት አውርደው ወደ ኢየሩሳሌም ላኩት፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ አይሁድ ጳውሎስን እንደሚያውቁት እና እንደለመዱት ሆኖ ስላላገኙት ሊገድሉት ተነሱ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ ክርስቲያኖች የቅዱስ ጳውሎስን መመለስ ሊያምኑ አልቻሉም፡፡ በመጨረሻ ግን በርናባስ ወደ ሐዋርያት ዘንድ ወስዶ የጳውሎስን መመለስ በመተረክ እንዲያምኑት አደረጋቸው፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በኢየሩሳሌም በድፍረት በማስተማሩ አይሁድ ስለተቃወሙት ከተማዋን ትቶ በቂሳርያ በኩል ወደ ትውልድ ሐገሩ ጠርሴስ ተመለሰ፡፡ ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በጠርሴስ ከተማ ለ9 ዓመታት ቆይቷል፡፡ ከኢየሩሳሌም ውጭ የአሕዛብ ከተማ በነበረችው በአንጾኪያ የክርስትና ሃይማኖት ተስፋፋ፡፡ ከዚህም በኋላ ሐዋርያው ሦስት ታላላቅ ሐዋርያዊ ጉዞዎችን አድርጓል፡፡ በመጀመሪያው ጉዞው ወደ 2,ዐዐዐ ኪ.ሜ የሚደርስ መንገድ በእግር ተጉዟል፤ ይህም የተከናወነው በ46 ዓ.ም. ነው፡፡ በሁለተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ18 በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ5ዐ ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡  በሦስተኛው ሐዋርያዊ ጉዞው ከ2ዐ በላይ ከተሞችን ሸፍኗል፤ ጉዞውም በ54 ዓ.ም. የተደረገ ነው፡፡ ብዙም ጊዜ በቁም እሥር በብዙም መከራ ሥቃይ እንግልት ያሳለፈ ታላቅ ሐዋርያ ነው፡፡
541
4
🕯 የሐዘን መግለጫ 🕯 የግቢ ጉባኤያችን አባል የሆነችው የእህታችን ዮሐናን በየነ (የ2ኛ ዓመት Marketing Management ተማሪ) አያት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል። ልዑል እግዚአብሔር ነፍሳቸውን በአፀደ ገነት ከቅዱሳኑ ጋር ያሳርፍልን፤ ለእህታችንና ለቤተሰቦቿም ፍጹም መጽናናትን ያድልልን። በመኖሪያ ቤታቸው መድረስ የምትችሉ አሳውቁንና ስንሄድ እንነግራችኋለን። 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ
984
5
የወርኃ ሰኔ የእመቤታችን ጽዋ እና የሥራ አስፈፃሚዎች ርክክብ መርሃግብር ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ገርጂ ማርያም ፤ አዲስ አበባ ፤ ኢትዮጵያ
የወርኃ ሰኔ የእመቤታችን ጽዋ እና የሥራ አስፈፃሚዎች ርክክብ መርሃግብር ሰኔ 27/2018 ዓ.ም ገርጂ ማርያም ፤ አዲስ አበባ ፤ ኢትዮጵያ
997
6
የቀረጻችሁት ቪዲዮ ፎቶ ካለ እንደ ፋይል ስለሚቀመጥ @Fiyona_ayche በዚህ አካውንት እንድትልኩልን በእግዚአብሔር ስም እናሳስባለን🙏
977
7
"እግዚአብሔር እስከዚህ ረድቶናል!" (1ሳሙ 7፥12) የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ቤተሰቦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ያደረግነው የዓመቱ ማጠቃለያ መንፈሳዊ ጉዞ በእግዚአብሔር ቸርነት፣ በእመቤታችን ድንግል ማርያም ጥበቃ በሰላምና በታላቅ በረከት ተጠናቋል። በጉዞው ላይ ተገኝታችሁ በጸሎት፣ በዝማሬና በክርስቲያናዊ ፍቅር ቀኑን የበረከት ላደረጋችሁ ተጓዦች በሙሉ፣ እንዲሁም መርሃ ግብሩ እንዲሳካ ከጀርባ ሆናችሁ በሃሳብ፣ በገንዘብና በጸሎት ለደገፋችሁን በሙሉ ግቢ ጉባኤያችን ከልብ የመነጨ ምስጋናዋን ታቀርባለች። የተቀበልነው በረከትና ያሳለፍነው የኅብረት ጊዜ በሕይወታችን ላይ ፍሬ ሆኖ እንዲቀር የአምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ይሁንልን። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 000
8
1000277472574 እንጦጦ ደብረ ኃይል ራጉኤል የአቅማችሁን አግዙ🙏
994
9
"ሥርዓትስ ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።"  1ቆሮ 14፥ 40 🚌 የጉዞ ማሳሰቢያ የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላትና ተጓዦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን የምናደርገው ጉዞ የበረከትና የሰላም ይሆንልን ዘንድ፣ ተጓዦች በሙሉ ወደተዘጋጀው መርሃ ግብር ሲመጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና መንፈሳዊ ሥርዓቶች እንዲያከብሩና እንዲተገብሩ ግቢ ጉባኤያችን በአክብሮት ታሳስባለች። 1. በሰዓት መገኘት፦ የመነሻ ሰዓት ጠዋት ከነጋቱ 1:00 በመሆኑ፣ ሁሉም ተጓዥ በመነሻ ቦታው (ገርጂ ማርያም) በሰዓቱ እንዲገኝ እናሳስባለን። 2. በፆም መምጣት፦ በጉዞው ላይ ጸበልና የበረከት ተግባራት ስላሉ፣ የጤና እክል ከሌለባችሁ በስተቀር ጠዋት ሳይመገቡ መምጣት ይመረጣል። 3. ክርስቲያናዊ አለባበስ፦ የቤተክርስቲያንን ሥርዓት የጠበቀ አለባበስ (በተለይም ነጭ ነጠላ በመልበስ) እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። የሰላምና የበረከት ጉዞ ይሁንልን! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
921
10
ትኬት ያልገዛችሁ ወንድምና እህቶች ነገ ጠዋትም ቀድማችሁ በመምጣት ትኬት ማግኘት ስለምትችሁ እንዳትቀሩ ፤ አደራ ! ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318
856
11
"ሥርዓትስ ሁሉ በአገባብና በሥርዓት ይሁን።" 1ቆሮ 14፥ 40 🚌 የጉዞ ማሳሰቢያ የተወደዳችሁ የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላትና ተጓዦች፤ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን የምናደርገው ጉዞ የበረከትና የሰላም ይሆንልን ዘንድ፣ ተጓዦች በሙሉ ወደተዘጋጀው መርሃ ግብር ሲመጡ የሚከተሉትን ዋና ዋና መንፈሳዊ ሥርዓቶች እንዲያከብሩና እንዲተገብሩ ግቢ ጉባኤያችን በአክብሮት ታሳስባለች። ፩ 1. በሰዓት መገኘት (Punctuality) የጉዞው መነሻ ሰዓት ጠዋት ከነጋቱ 11:30 በመሆኑ፣ ተጓዦች በሙሉ ያለምንም መዘግየት በተጠቀሰው ሰዓት ላይ በመነሻ ቦታው (ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል) እንድትገኙ እናሳስባለን (image_ac48ee.jpg)። ሰዓት ማክበር የወንድሞቻችንንና የእህቶቻችንን ጊዜ ከመቆጠብ ባለፈ የመርሃ ግብሩ ስኬት መሠረት ነው። 2. ምግብ አለመብላት (Fasting before Blessings) በጉዞው ላይ ጸበል፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ የበረከት ተግባራት ስለሚኖሩ፣ አስገዳጅ የጤና ሁኔታ ካላጋጠማችሁ በስተቀር ጠዋት ሳይመገቡ (በፆም) መምጣት ይመረጣል (image_ac48d3.jpg)። ጸበል ለመጠመቅና በረከትን ለመቀበል ራስን ማዘጋጀት መንፈሳዊ ሥርዓታችን ነው። 3. ክርስቲያናዊ አለባበስ (Christian Attire) ወደ ቅዱሱ ስፍራ የምናደርገው ጉዞ በመሆኑ፣ ተጓዦች በሙሉ የቤተክርስቲያንን ሥርዓትና ክብር የጠበቀ፣ ክርስቲያናዊ አለባበስ (በተለይም ነጭ ነጠላ በመጎናጸፍ) እንድትገኙ በጥብቅ እናሳስባለን። አለባበሳችን ለቦታው ያለንን ክብርና ውስጣዊ ስብዕናችንን የሚገልጽ መሆን ይኖርበታል። "እግዚአብሔር የሰላም አምላክ ነውና እንጂ የሁከት አምላክ አይደለም።" እነዚህን መሠረታዊ የጉዞ ማሳሰቢያዎች በተግባር በመተርጎም የበረከቱ ተሳታፊ እንድትሆኑ እያሳሰብን፣ ጉዟችንን የሰላምና የፍሬ ያደርግልን ዘንድ የልዑል እግዚአብሔር ፈቃድ ይሁንልን። 🙏 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
117
12
ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-10:00
ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-10:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ቦታ ይያዙ ትኬቱን ለማግኘት 0942139509 0972237318
1 133
13
"እግዚአብሔር አምላክን አመስግኑት... እረኛንና ጠባቂን ሰጥቶናልና።" 📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉✨ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ ስንጠይቅበት የሰነበትነው የዕጣ ማውጣት ሥርዓት በዛሬው እሮብ ዕለት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና በሰላም ተጠናቋል። እግዚአብሔር አምላክ ለጉባዔያችን የሚበጁትን፣ የወጣትነት ጉልበታቸውን ለአገልግሎት የሚሰጡትን የ2019 ዓ.ም አዲሶቹን ሥራ አስፈጻሚዎች (አገልጋዮች) በዕጣው ገልጦልናል። ይህ በጸሎት የዘራነው መንፈሳዊ ፍሬ የሚቀጥለው ቅዳሜ (የኃላፊነት ርክክብ በሚደረግበት ዕለት) በይፋ የሚሰየም ይሆናል። ስለሆነም፣ መላው አባላት በአካል ተገኝታችሁ አዲሶቹን መሪዎች የምንቀበልበት፣ ነባሮቹን ደግሞ ስለ ደከሙበት አገልግሎት የምናመሰግንበት የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር የሚመጣው ቅዳሜ ስለሚከናወን፣ ሁላችሁም በታላቅ ደስታና ዝግጅት እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አዲሶቹን አገልጋዮች እግዚአብሔር በረድኤት ያጽናቸው፤ ለጉባዔያችንም የሰላምና የፍሬ ዘመን ያድርግልን! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
958
14
"የሁሉን ልብ የምታውቅ ጌታ ሆይ፤ የመረጥኸውን አንዱን አሳይ።" (ሐዋ. 1፥24) 📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባዔ አባላት በሙሉ✨ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን የግቢ ጉባዔያችን የ2018 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎች የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው ኃላፊነታቸውን ለቀጣዩ ታማኝ ትውልድ የሚያስረክቡበት ልዩ ወቅት ላይ እንገኛለን። የፊታችን ቅዳሜ የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር ከመከናወኑ በፊት፣ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ በዕጣ የምንጠይቅበት ልዩ መንፈሳዊ ሥርዓት ይኖረናል። የክርስቶስ ማኅበር የሆነውን ግቢ ጉባዔያችንን በቅንነትና በትሕትና የሚያገለግሉትን አዲሶቹን መሪዎች እግዚአብሔር በዕጣው የሚገልጥበት ዕለት ደርሷል። ስለሆነም፣ እያንዳንዳችን በጸሎትና በአካል ተገኝተን የቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት የምንከተልበት የዕጣ ማውጣት መርኃ-ግብር የተዘጋጀ በመሆኑ፣ መላው አባላት ሳይቀሩ እንዲገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡ 📅 የዕጣው ቀን፦ ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም 🕕 ሰዓት፦ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ የአገልግሎት ርክክብ ቀን፦ ቅዳሜ ይህ የአገልግሎት ሽግግር ሰላማዊ፣ መንፈሳዊና የተባረከ ይሆን ዘንድ የእያንዳንዱ አባል በጸሎት ማገዝና በአካል መገኘት እጅግ አስፈላጊ ነው። ጉባዔው የሁላችንም ነውና ይህንን ታላቅ ዕለት በጉጉትና በጸሎት እንጠብቅ! እግዚአብሔር ለጉባዔው የሚበጀውን እውነተኛ አገልጋይ በዕጣው ይግለጥልን፤ እስከዚያው በጸሎት እንበርታ! ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ
1 005
15
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦ ❝ሃሌ ሉያ የእግዚአብሔር ቤት ሆይ ተቀደሺ ኃይልንም ልበሺ እነሆ በኃይሉ የሚያበራልሽ ንጉሥሽ መጥቶአልና! ይህችን ቤት አብ አስቀድሞ አነጻት ይህችን ቤት ወልድ አነጻት ይህችን ቤት መንፈስ ቅዱስ ፈጸማት❞ ምልጣን ዘሰኔ 21 ✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል -"ሕንጸታ ቤተክርስቲያን" በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያዊ ቤተክርስቲያን ምሥረታን ለግቢ ጉባዔያችን ደግሞ የ2018 ዓ.ም የሥራ አስፈጻሚዎች ልዩ የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ሰኔ 27 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
1 101
16
ቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን የምትመስዪ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሆይ፤ ሰላምታ ይገባሻል። ቤተክርስቲያን አራት መሠረታዊ ባህርያት ቅድስትነት፣አንድነት፣ኩልሐዊነት እና ሐዋርያዊነት አላት። ቅድስትነቷ፦ የቅድስናዋ ምንጩ ራሷ እና አካሏ ከሆነላት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ ሲሆን፣አካሉ ያደረጋት ጌታ የሞተላት እርሷን ይቀድስ ዘንድ ነው። "ለቤተክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ ሆይ፣አቤቱ ይህንን በማድረግህ በከበረ ደምህ ቀደስካት" እንዲል ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ፣አንድም ደግሞ መንፈስቅዱስ ቤተክርስቲያንን ስለቀደሳት እና ስለሚያኖራት አካላቶቿም በሚስጢራት በኩል ቅድስናን እና ሱታፌን ከክርስቶስ ስለሚያገኙባት ቅድስት ትባላለች። አንድነቷን፦ ስናይ ደግሞ ቤተክርስቲያን ሥላሴያዊ ሕይወት ነው ያላት፤ጌታ ኢየሱስ በጸሎቱ ላይ እንዲህ ብሎ ሲጸልይ እናያለን“እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።”(ዮሐ17፥22-23) ብሎ እንደጸለየ በሥላሴ አካላት በኩል አንድ ትሆናለች፤የአንድነቷ ምንጭ ራሱ ሥላሴያዊው የእግዚአብሔር አኗኗር ነው።አንድም መለኮት ከሥጋ ጋር በሥጋዌ ጊዜ አንድ እንደሆነ እና ለዘለዓለም በተዋሕዶ እንደሚኖር፣ቤተክርስቲያንም በአንድ ሀሳብ፣በአንድ ትምህርት፣በአንድ ጥምቀት፣በአንድ ሜሮን፣በአንድ ቁርባን እና በሐዋርያዊ ክህነት ለዘለዓለም በአንድነት ትኖራለች። ኩልሐዊነቷ፦ በኹሉ በመሆኗ፤ በምልአት በመሆኗ እና ኩልሐዊ እውነት ውስጥ መኖሯ ነው። ቤተክርስቲያን ወሰን፣ ስልጣን፣ተራራ እና ሸለቆ አይገድባትም አያግዳትምም። ምድራዊ ልጅ እና አባትን ተራራ እና ባህር ሊለያያቸው ይችላል፣ነገር ግን በአንድ እምነት እና በመንፈስቅዱስ ሙቀትነት የምትኖር ቤተክርስቲያን ግን ከአጽናፍ ዓለም የሰፋች በመኾኗ በኹሉ ትገኛለች በኹሉ ትኖራለች። በሚስጢራት በኩል ዓለምአቀፏ ኩልሐዊት ቤተክርስቲያን(Universal Church) በአጥቢያ ቤተክርስቲያን(Local Church) ተገልጣ ትኖራለች። ቤተክርስቲያን ድኅነት ባለበት ሁሉ አለች ቅዱስ ሄሬኔዎስ ይህንን ሲያጠናክርልን እንዲህ ይላል፤ "ቤተክርስቲያን ባለችበት ኹሉ የእግዚአብሔር መንፈስ አለ፣መንፈስን ቅዱስ ባለበት ኹሉ ቤተክርስቲያን አለች" (Against Heresies 3፡24) ሐዋርያዊነቷ፦ መናፍቃንም ራሳቸውን ቤተክርስቲያን ብለው ይጠራሉ በመሆኑም ቤተክርስቲያን ከእነርሱ የምትለይበት መለያዋ ሐዋርያዊነቷ ነው፣ለመናፍቃኖች “ቤተክርስቲያን" መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ በኩል አልተገለጠም፣ለቤተክርስቲያን ግን ራሱን በሐዋርያት ሲገልጽ እና በተተኪያቸው በመግቦቱ ሲኖር እና በሙቀቱ ሲያኖራት እናያለን። "ቤተክርስቲያን በሐዋርያት በኩል ያሉትን ታመላክታለች፣መንፈስቅዱስ በሐዋርያት እንደተናገረ ሁሉ፣በልጆቻቸው በኩልም ይናገራል።" እንዲለን ሶርያዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ ዘዳራ ሐዋርያዊነቷ ከኩልሐዊነቷ ጋር አንድ የሚሆን ነው፣ሐዋርያዊነቷ የክርስቶስ ተከታይ መኾኗ፣የተገለጠውን አንዱን ሃይማኖት ሁሌም እንደምትኖረው፣የሐዋርያትን አሰረ ፍኖት ክህነትን እና ትምህርታቸውን (Apostolic Succession And Apostolic Teaching) የመያዟ መገለጫ ነው። ቤተክርስቲያን እነዚህ አራት መሠረታዊ መለያዎች ያሏት ሲሆን፣ ሥላሴያዊ በሆነው አኗኗር ትኖራለች በእግዚአብሔር አብ ለልጁ ማደሪያነት የተመረጠች፣ በእግዚአብሔር ወልድ ሞት በኩል የተቀደሰች፣ በእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ሕይወትነት እና ሙቀትነት የምትኖር ናት።
1 042
17
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል - "ሕንጸታ ቤተክርስቲያን" በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉን ከዋዜማው ጀምሮ በገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ቤተክርስቲያን በማኅሌት ፣በቅዳሴ፣ በንግሥ፣ በልዩ የዓውደ ምኅረት ጉባዔ፣... በኅብረት እንድናከብር ዘንድ ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
856
18
Matn yo'q...
1 196
19
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1 እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁ
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1 እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እያልን በግቢ ጉባዔያችን በዓቢይ ጾም ጉዞ አስበን እግዚአብሔር አልፈቀደምና እንደተሰረዘ ይታወቃል። እንደ አምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ከፈተና በኋላ የዓመቱ መርኃግብር ማጠቃለያ ጉዞ ለማድረግ አስበናል። በአሁኑ የምናደርገው መንፈሳዊ ጉዞ ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን ሲሆን ቀኑም ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም ነው ። በጉዞው ላይ ጸሎት ፣ የሕብረት ዝማሬ ፣ ጥያቄና መልስ ፣ የእግር ጉዞ ፣ ገዳሙን መጎብኘት ፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ አስተማሪና ቤተሰባዊ መርኃግብራት ይኖሩናል። የጉዞው ዋጋ አጋፔን(ምሣን) ጨምሮ 400 ብር ብቻ እንደሆነ እየገለፅን በጉዞው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ከወዲሁ ትኬቱን እንድትገዙ እናሳስባለን። ትኬቱ በአካል መምጣት ለምትችሉ በግቢ ጉባኤ ቢሯችን ማግኘት ትችላላቹ። በአካል መምጣት የማትችሉ ደግሞ 1000529652767 (CBE ፋሲካ አይችሉህም) ወይም 0942139509  (Telebirr Fiyona ) በነዚህ አካውንት በመክፈል የከፈላቹበትን ደረሰኝ በ @Fiyona_ayche ቴሌግራም አካውንት በመላክ መመዝገብ ይችላሉ:: የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-11:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318 ይደዉሉ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
639
20
እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጠባቂ [መልአከ ዑቃቤ] ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፍ.18፥16 ትርጓሜ)። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብጽ ሲያወጣ እንዲረዳቸው የላከው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፀ.23፥23 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት የሚከተሉት ናቸው። 1. አጋዕዝት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 2. ኪሩቤል=ቅዱስ ኪሩብ=ኢዮር 3. ሱራፌል=ቅዱስ ሱራፊ=ኢዮር 4. ኀይላት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 5. አርባብ=ቅዱስ ገብርኤል=ራማ 6. መናብርት=ቅዱስ ሩፋኤል=ራማ 7. ሥልጣናት=ቅዱስ ሱርያል=ራማ 8. መኳንንት=ቅዱስ ሰዳካኤል/ክያል=ኤረር 9. ሊቃናት=ቅዱስ ሰላታኤል/ትያል=ኤረር 10. መላእክት=ቅዱስ አናንኤል/ያል=ኤረር ሳጥናኤል ከወረደ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል የአጋዕዝትም አለቃ ነው። በተጨማሪም የሁሉም ነገድ አለቃ ነው። እስራኤላውያንን ከሰናክሬም ያዳናቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው። ቅዱስ ሚካኤል ለመዓት እንጂ ለምሕረት የማይታዘዙ የዐሥራ ሁለቱ ነገድ የሌጌዎን አለቃም ነው። ነቢዩ ዳንኤልን የረዳ መልአክም ቅዱስ ሚካኤል ነው። "ወናሁ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት ቀደምት መጽአ ይርድአኒ" እንዲል (ዳን.10፥13)። ዐሥሩም ነገድ በአንድ ላይ መላእክት ይባላሉ። እንዲሁም ደግሞ በተለየ አንዱ ነገድ መላእክት ይባላል። በተመሳሳይ መልኩ ኪሩቤል የሚባል ነገድ አለ። እንዲሁም እግዚአብሔር በዘፈቀደ የሚገለጥበትን መንበር የሚሸከሙ ኪሩቤል የሚባሉ አራት መላእክት አሉ (ራእ.14፥3)። በመንበሩ ዙሪያ ሆነው የሚያጥኑ 24 ካህናተ ሰማይ አሉ (ራእ.4፥4)። ከነገድ አለቆች በተጨማሪ ለመቶው ነገድ ሰባት ሊቃነ መላእክት አሉ። እነዚህም፦        ፩. ቅዱስ ሚካኤል        ፪. ቅዱስ ገብርኤል        ፫. ቅዱስ ራጉኤል        ፬. ቅዱስ ዑራኤል (ዑርኤል)        ፭. ቅዱስ ሩፋኤል        ፮. ቅዱስ ፋኑኤል        ፯. ቅዱስ ሳቁኤል (አፍኒን) ቅዱሳን መላእክት እኛ የሰው ልጆች እንድን ዘንድ በብዙ ነገር የሚረዱን በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የስማቸው ትርጉም እንደሚከተለው ነው። 🌿ሚካኤል=መሓሪ ወመስተሣህል/ዕፁብ ነገር/መኑ ከማከ         🍀ገብርኤል=አምላክ ወሰብእ         🌴ሩፋኤል=ፈውሰ እግዚአብሔር         ☘️ዑራኤል=ብርሃነ እግዚአብሔር          🌱ፋኑኤል=ማኅፈደ እግዚአብሔር          🍃ራጉኤል=ራእየ እግዚአብሔር          🌾ሠረቃኤል=ወሀቤ አእምሮ/ፀዋሬ ስም ሚካኤል በምሕረት ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ዑራኤል በመብረቅ በነጎድጓድ የተሾመ መልአክ ነው። ሩፋኤል በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ነው። ራጉኤል አጋንንትን የሚበቀል መልአክ ነው። ሠረቃኤል አእምሮ ባጡ ሰዎች ላይ የተሾመ ነው። ገብርኤል አጋንንት መርዝ እንዳይበጠብጡ በምንጮች ላይ የተሾመ መልአክ ነው (መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ 6 ከቁጥር 1 እስከ 10)። የመላእክት ሥራ ከዚህ በጠቀስነው ብቻ የተወሰነ ሆኖ አይደለም በጸናው መናገር ነው እንጂ። ሊቃውንትም ምግብናቸውን መሠረት አድርገው ቅዱስ ሚካኤልን መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ገብርኤልን መጋቤ ሐዲስ ይሏቸዋል (ዘፀ.14፥19 ትርጓሜ፤ ሉቃ.13፥9 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም ያስቡልናል። ማር ይስሐቅ አንቀጽ ካልእ ላይ "ታላቅ ወንድም ለታናሹ እንዲያዝን መላእክትም ያዝኑልናል" ይላል። ቅዱሳን መላእክት እውነት ደስ የሚያሰኛቸው እውነተኞች ናቸው። ቅዱስ ገብርኤል በእያለንበት እንቁም ብሎ ዓለመ መላእክትን ስላረጋጋ ድንግል ማርያምን የምሥራች ለማለት ተመረጠ። በዚህም ምክንያት መልአከ ሰላም ይባላል። ለዓለም ደስታ የሚሆን የአምላክን ሰው መሆን ስለተናገረም መልአከ ፍሥሓ ይባላል። በብሉይ ኪዳን ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነ መልአክ ነው። ሩፋኤል ጦብያን፣ ጦቢትን፣ ሣራ ወለተ ራጉኤልን የረዳ መልአክ ነው። ዑርኤል ለዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዐ ልቡናን ያጠጣና በብዙ ነገር የረዳው መልአክ ነው። በዕለተ ስቅለት የክርስቶስን ደም በብርሃን ጽዋዕ ተቀብሎ የረጨ መልአክ ነው። በጠቅላላው ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር እየታዘዙ ለቅዱሳን ረድኤትን የሚሰጡ፣ ሰዎችን ከክፉ ነገር የሚያድኑ፣ ጸጋን በረከትን የሚያድሉ በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የጸጋ ምስጋናን እናመሰግናቸዋለን። ብዙ ጊዜ መላእክት ለሰው ሲገለጹ ፍርሀትን ከሰው ለማራቅ አትፍራ ብለው ይጀምራሉ። ቅዱስ ሚካኤል በሐዲስ ኪዳንም አፎምያን፣ ባሕራንን ረድቷል። ለእንጦንስ ሥርዓተ ምንኩስናን አስተምሯል። ብዙ ቅዱሳን ሰማዕታትን ቅዱሳን መነኰሳትን ረድቷል አጽናንቷል። እኛንም በተሰጠው የረድኤት፣ የምልጃ ጸጋ ይጠብቀን ይርዳን።
1 604