ar
Feedback
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

الذهاب إلى القناة على Telegram

በኢ.ኦ.ተ.ቤ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። በግቢ ጉባኤያችን የሚከናወኑ ተግባራት፣ መረጃዎችንና መልእክቶችን ለውድ አባላቶቹ ያደርሳል። Instagram: https://www.instagram.com/unitygebigubae TikTok: https://www.tiktok.com/@unitygebigubae

إظهار المزيد
2 122
المشتركون
-124 ساعات
-47 أيام
+230 أيام
أرشيف المشاركات
ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉
ወደ ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን
ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-10:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል
ያለን ቦታ ውስን ስለሆነ ቀድመው ቦታ ይያዙ
ትኬቱን ለማግኘት 0942139509 0972237318

"እግዚአብሔር አምላክን አመስግኑት... እረኛንና ጠባቂን ሰጥቶናልና።"
📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት በሙሉ፤ እንኳን ደስ አላችሁ! 🎉✨ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ ስንጠይቅበት የሰነበትነው የዕጣ ማውጣት ሥርዓት በዛሬው እሮብ ዕለት በታላቅ መንፈሳዊ ሥነ-ሥርዓትና በሰላም ተጠናቋል። እግዚአብሔር አምላክ ለጉባዔያችን የሚበጁትን፣ የወጣትነት ጉልበታቸውን ለአገልግሎት የሚሰጡትን የ2019 ዓ.ም አዲሶቹን ሥራ አስፈጻሚዎች (አገልጋዮች) በዕጣው ገልጦልናል። ይህ በጸሎት የዘራነው መንፈሳዊ ፍሬ የሚቀጥለው ቅዳሜ (የኃላፊነት ርክክብ በሚደረግበት ዕለት) በይፋ የሚሰየም ይሆናል። ስለሆነም፣ መላው አባላት በአካል ተገኝታችሁ አዲሶቹን መሪዎች የምንቀበልበት፣ ነባሮቹን ደግሞ ስለ ደከሙበት አገልግሎት የምናመሰግንበት የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር የሚመጣው ቅዳሜ ስለሚከናወን፣ ሁላችሁም በታላቅ ደስታና ዝግጅት እንድትገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። አዲሶቹን አገልጋዮች እግዚአብሔር በረድኤት ያጽናቸው፤ ለጉባዔያችንም የሰላምና የፍሬ ዘመን ያድርግልን! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

"የሁሉን ልብ የምታውቅ ጌታ ሆይ፤ የመረጥኸውን አንዱን አሳይ።" (ሐዋ. 1፥24)
📢 ለመላው የዩኒቲ ግቢ ጉባዔ አባላት በሙሉ✨ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችሁ ጋር ይሁን እያልን የግቢ ጉባዔያችን የ2018 ዓ.ም ሥራ አስፈጻሚዎች የአገልግሎት ዘመናቸውን አጠናቀው ኃላፊነታቸውን ለቀጣዩ ታማኝ ትውልድ የሚያስረክቡበት ልዩ ወቅት ላይ እንገኛለን። የፊታችን ቅዳሜ የአገልግሎት ኃላፊነት ርክክብ መርኃ-ግብር ከመከናወኑ በፊት፣ የባለቤቱን የእግዚአብሔርን ፍጹም ፈቃድ በዕጣ የምንጠይቅበት ልዩ መንፈሳዊ ሥርዓት ይኖረናል። የክርስቶስ ማኅበር የሆነውን ግቢ ጉባዔያችንን በቅንነትና በትሕትና የሚያገለግሉትን አዲሶቹን መሪዎች እግዚአብሔር በዕጣው የሚገልጥበት ዕለት ደርሷል። ስለሆነም፣ እያንዳንዳችን በጸሎትና በአካል ተገኝተን የቅዱሳን ሐዋርያትን አብነት የምንከተልበት የዕጣ ማውጣት መርኃ-ግብር የተዘጋጀ በመሆኑ፣ መላው አባላት ሳይቀሩ እንዲገኙ ጥሪያችንን እናስተላልፋለን፡ 📅 የዕጣው ቀን፦ ረቡዕ ሰኔ 24 ቀን 2018 ዓ.ም 🕕 ሰዓት፦ ከቀኑ 6፡00 ሰዓት ጀምሮ የአገልግሎት ርክክብ ቀን፦ ቅዳሜ ይህ የአገልግሎት ሽግግር ሰላማዊ፣ መንፈሳዊና የተባረከ ይሆን ዘንድ የእያንዳንዱ አባል በጸሎት ማገዝና በአካል መገኘት እጅግ አስፈላጊ ነው። ጉባዔው የሁላችንም ነውና ይህንን ታላቅ ዕለት በጉጉትና በጸሎት እንጠብቅ! እግዚአብሔር ለጉባዔው የሚበጀውን እውነተኛ አገልጋይ በዕጣው ይግለጥልን፤ እስከዚያው በጸሎት እንበርታ! ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ

❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦
❝ሃሌ ሉያ ተቀደሲ ወንስኢ ኃይለ ኦ ቤተ እግዚአብሔር እስመ ናሁ ንጉሥኪ በጽሐ ዘያበርሕ ለኪ በኃይሉ ለዛቲ ቤት ሳረራ አብ ቀዲሙ ለዛቲ ቤት ሐነጻ ወልድ ለዛቲ ቤት ወፈጸማ መንፈስ ቅዱስ❞ ትርጉም፦ ❝ሃሌ ሉያ የእግዚአብሔር ቤት ሆይ ተቀደሺ ኃይልንም ልበሺ እነሆ በኃይሉ የሚያበራልሽ ንጉሥሽ መጥቶአልና! ይህችን ቤት አብ አስቀድሞ አነጻት ይህችን ቤት ወልድ አነጻት ይህችን ቤት መንፈስ ቅዱስ ፈጸማት❞ ምልጣን ዘሰኔ 21
✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል -"ሕንጸታ ቤተክርስቲያን" በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያዊ ቤተክርስቲያን ምሥረታን ለግቢ ጉባዔያችን ደግሞ የ2018 ዓ.ም የሥራ አስፈጻሚዎች ልዩ የርክክብ ሥነ-ሥርዓት ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ሰኔ 27 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

ቅድስት ቤተክርስቲያን ሰላም ለኪ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምሳለ ኢየሩሳሌም ሰማያዊት ሰማያዊት ኢየሩሳሌምን የምትመስዪ፣ ቅድስት ቤተ ክርስቲያን ሆይ፤ ሰላምታ ይገባሻል። ቤተክርስቲያን አራት መሠረታዊ ባህርያት ቅድስትነት፣አንድነት፣ኩልሐዊነት እና ሐዋርያዊነት አላት። ቅድስትነቷ፦ የቅድስናዋ ምንጩ ራሷ እና አካሏ ከሆነላት ከጌታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ የተነሳ ሲሆን፣አካሉ ያደረጋት ጌታ የሞተላት እርሷን ይቀድስ ዘንድ ነው። "ለቤተክርስቲያን ስትል በአደባባይ በጥፊ የተመታህ ሆይ፣አቤቱ ይህንን በማድረግህ በከበረ ደምህ ቀደስካት" እንዲል ኢትዮጵያዊው ሊቅ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ፣አንድም ደግሞ መንፈስቅዱስ ቤተክርስቲያንን ስለቀደሳት እና ስለሚያኖራት አካላቶቿም በሚስጢራት በኩል ቅድስናን እና ሱታፌን ከክርስቶስ ስለሚያገኙባት ቅድስት ትባላለች። አንድነቷን፦ ስናይ ደግሞ ቤተክርስቲያን ሥላሴያዊ ሕይወት ነው ያላት፤ጌታ ኢየሱስ በጸሎቱ ላይ እንዲህ ብሎ ሲጸልይ እናያለን“እኛም አንድ እንደ ሆንን አንድ ይሆኑ ዘንድ፤ እኔም በእነርሱ አንተም በእኔ ስትሆን፥ በአንድ ፍጹማን እንዲሆኑ፥ የሰጠኸኝን ክብር እኔ ሰጥቻቸዋለሁ፤ እንዲሁም ዓለም አንተ እንደ ላክኸኝ በወደድኸኝም መጠን እነርሱን እንደ ወደድሃቸው ያውቃል።”(ዮሐ17፥22-23) ብሎ እንደጸለየ በሥላሴ አካላት በኩል አንድ ትሆናለች፤የአንድነቷ ምንጭ ራሱ ሥላሴያዊው የእግዚአብሔር አኗኗር ነው።አንድም መለኮት ከሥጋ ጋር በሥጋዌ ጊዜ አንድ እንደሆነ እና ለዘለዓለም በተዋሕዶ እንደሚኖር፣ቤተክርስቲያንም በአንድ ሀሳብ፣በአንድ ትምህርት፣በአንድ ጥምቀት፣በአንድ ሜሮን፣በአንድ ቁርባን እና በሐዋርያዊ ክህነት ለዘለዓለም በአንድነት ትኖራለች። ኩልሐዊነቷ፦ በኹሉ በመሆኗ፤ በምልአት በመሆኗ እና ኩልሐዊ እውነት ውስጥ መኖሯ ነው። ቤተክርስቲያን ወሰን፣ ስልጣን፣ተራራ እና ሸለቆ አይገድባትም አያግዳትምም። ምድራዊ ልጅ እና አባትን ተራራ እና ባህር ሊለያያቸው ይችላል፣ነገር ግን በአንድ እምነት እና በመንፈስቅዱስ ሙቀትነት የምትኖር ቤተክርስቲያን ግን ከአጽናፍ ዓለም የሰፋች በመኾኗ በኹሉ ትገኛለች በኹሉ ትኖራለች። በሚስጢራት በኩል ዓለምአቀፏ ኩልሐዊት ቤተክርስቲያን(Universal Church) በአጥቢያ ቤተክርስቲያን(Local Church) ተገልጣ ትኖራለች። ቤተክርስቲያን ድኅነት ባለበት ሁሉ አለች ቅዱስ ሄሬኔዎስ ይህንን ሲያጠናክርልን እንዲህ ይላል፤ "ቤተክርስቲያን ባለችበት ኹሉ የእግዚአብሔር መንፈስ አለ፣መንፈስን ቅዱስ ባለበት ኹሉ ቤተክርስቲያን አለች" (Against Heresies 3፡24) ሐዋርያዊነቷ፦ መናፍቃንም ራሳቸውን ቤተክርስቲያን ብለው ይጠራሉ በመሆኑም ቤተክርስቲያን ከእነርሱ የምትለይበት መለያዋ ሐዋርያዊነቷ ነው፣ለመናፍቃኖች “ቤተክርስቲያን" መንፈስ ቅዱስ በእነርሱ በኩል አልተገለጠም፣ለቤተክርስቲያን ግን ራሱን በሐዋርያት ሲገልጽ እና በተተኪያቸው በመግቦቱ ሲኖር እና በሙቀቱ ሲያኖራት እናያለን። "ቤተክርስቲያን በሐዋርያት በኩል ያሉትን ታመላክታለች፣መንፈስቅዱስ በሐዋርያት እንደተናገረ ሁሉ፣በልጆቻቸው በኩልም ይናገራል።" እንዲለን ሶርያዊው ሊቅ ቅዱስ ዮሐንስ ዘዳራ ሐዋርያዊነቷ ከኩልሐዊነቷ ጋር አንድ የሚሆን ነው፣ሐዋርያዊነቷ የክርስቶስ ተከታይ መኾኗ፣የተገለጠውን አንዱን ሃይማኖት ሁሌም እንደምትኖረው፣የሐዋርያትን አሰረ ፍኖት ክህነትን እና ትምህርታቸውን (Apostolic Succession And Apostolic Teaching) የመያዟ መገለጫ ነው። ቤተክርስቲያን እነዚህ አራት መሠረታዊ መለያዎች ያሏት ሲሆን፣ ሥላሴያዊ በሆነው አኗኗር ትኖራለች በእግዚአብሔር አብ ለልጁ ማደሪያነት የተመረጠች፣ በእግዚአብሔር ወልድ ሞት በኩል የተቀደሰች፣ በእግዚአብሔር መንፈስቅዱስ ሕይወትነት እና ሙቀትነት የምትኖር ናት።

እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል - "ሕንጸታ ቤተክርስቲያን" በሰላም አደረሳችሁ ! በዓሉን ከዋዜማው ጀምሮ በገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ቤተክርስቲያን በማኅሌት ፣በቅዳሴ፣ በንግሥ፣ በልዩ የዓውደ ምኅረት ጉባዔ፣... በኅብረት እንድናከብር ዘንድ ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1 እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁ
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1
እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እያልን በግቢ ጉባዔያችን በዓቢይ ጾም ጉዞ አስበን እግዚአብሔር አልፈቀደምና እንደተሰረዘ ይታወቃል። እንደ አምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ከፈተና በኋላ የዓመቱ መርኃግብር ማጠቃለያ ጉዞ ለማድረግ አስበናል። በአሁኑ የምናደርገው መንፈሳዊ ጉዞ ወደ
ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን
ሲሆን ቀኑም ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም ነው ። በጉዞው ላይ ጸሎት ፣ የሕብረት ዝማሬ ፣ ጥያቄና መልስ ፣ የእግር ጉዞ ፣ ገዳሙን መጎብኘት ፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ አስተማሪና ቤተሰባዊ መርኃግብራት ይኖሩናል። የጉዞው ዋጋ አጋፔን(ምሣን) ጨምሮ 400 ብር ብቻ እንደሆነ እየገለፅን በጉዞው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ከወዲሁ ትኬቱን እንድትገዙ እናሳስባለን። ትኬቱ በአካል መምጣት ለምትችሉ በግቢ ጉባኤ ቢሯችን ማግኘት ትችላላቹ። በአካል መምጣት የማትችሉ ደግሞ 1000529652767 (CBE ፋሲካ አይችሉህም) ወይም 0942139509  (Telebirr Fiyona ) በነዚህ አካውንት በመክፈል የከፈላቹበትን ደረሰኝ በ @Fiyona_ayche ቴሌግራም አካውንት በመላክ መመዝገብ ይችላሉ:: የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-11:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318 ይደዉሉ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጠባቂ [መልአከ ዑቃቤ] ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፍ.18፥16 ትርጓሜ)። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብጽ ሲያወጣ እንዲረዳቸው የላከው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፀ.23፥23 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት የሚከተሉት ናቸው። 1. አጋዕዝት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 2. ኪሩቤል=ቅዱስ ኪሩብ=ኢዮር 3. ሱራፌል=ቅዱስ ሱራፊ=ኢዮር 4. ኀይላት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 5. አርባብ=ቅዱስ ገብርኤል=ራማ 6. መናብርት=ቅዱስ ሩፋኤል=ራማ 7. ሥልጣናት=ቅዱስ ሱርያል=ራማ 8. መኳንንት=ቅዱስ ሰዳካኤል/ክያል=ኤረር 9. ሊቃናት=ቅዱስ ሰላታኤል/ትያል=ኤረር 10. መላእክት=ቅዱስ አናንኤል/ያል=ኤረር ሳጥናኤል ከወረደ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል የአጋዕዝትም አለቃ ነው። በተጨማሪም የሁሉም ነገድ አለቃ ነው። እስራኤላውያንን ከሰናክሬም ያዳናቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው። ቅዱስ ሚካኤል ለመዓት እንጂ ለምሕረት የማይታዘዙ የዐሥራ ሁለቱ ነገድ የሌጌዎን አለቃም ነው። ነቢዩ ዳንኤልን የረዳ መልአክም ቅዱስ ሚካኤል ነው። "ወናሁ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት ቀደምት መጽአ ይርድአኒ" እንዲል (ዳን.10፥13)። ዐሥሩም ነገድ በአንድ ላይ መላእክት ይባላሉ። እንዲሁም ደግሞ በተለየ አንዱ ነገድ መላእክት ይባላል። በተመሳሳይ መልኩ ኪሩቤል የሚባል ነገድ አለ። እንዲሁም እግዚአብሔር በዘፈቀደ የሚገለጥበትን መንበር የሚሸከሙ ኪሩቤል የሚባሉ አራት መላእክት አሉ (ራእ.14፥3)። በመንበሩ ዙሪያ ሆነው የሚያጥኑ 24 ካህናተ ሰማይ አሉ (ራእ.4፥4)። ከነገድ አለቆች በተጨማሪ ለመቶው ነገድ ሰባት ሊቃነ መላእክት አሉ። እነዚህም፦        ፩. ቅዱስ ሚካኤል        ፪. ቅዱስ ገብርኤል        ፫. ቅዱስ ራጉኤል        ፬. ቅዱስ ዑራኤል (ዑርኤል)        ፭. ቅዱስ ሩፋኤል        ፮. ቅዱስ ፋኑኤል        ፯. ቅዱስ ሳቁኤል (አፍኒን) ቅዱሳን መላእክት እኛ የሰው ልጆች እንድን ዘንድ በብዙ ነገር የሚረዱን በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የስማቸው ትርጉም እንደሚከተለው ነው። 🌿ሚካኤል=መሓሪ ወመስተሣህል/ዕፁብ ነገር/መኑ ከማከ         🍀ገብርኤል=አምላክ ወሰብእ         🌴ሩፋኤል=ፈውሰ እግዚአብሔር         ☘️ዑራኤል=ብርሃነ እግዚአብሔር          🌱ፋኑኤል=ማኅፈደ እግዚአብሔር          🍃ራጉኤል=ራእየ እግዚአብሔር          🌾ሠረቃኤል=ወሀቤ አእምሮ/ፀዋሬ ስም ሚካኤል በምሕረት ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ዑራኤል በመብረቅ በነጎድጓድ የተሾመ መልአክ ነው። ሩፋኤል በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ነው። ራጉኤል አጋንንትን የሚበቀል መልአክ ነው። ሠረቃኤል አእምሮ ባጡ ሰዎች ላይ የተሾመ ነው። ገብርኤል አጋንንት መርዝ እንዳይበጠብጡ በምንጮች ላይ የተሾመ መልአክ ነው (መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ 6 ከቁጥር 1 እስከ 10)። የመላእክት ሥራ ከዚህ በጠቀስነው ብቻ የተወሰነ ሆኖ አይደለም በጸናው መናገር ነው እንጂ። ሊቃውንትም ምግብናቸውን መሠረት አድርገው ቅዱስ ሚካኤልን መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ገብርኤልን መጋቤ ሐዲስ ይሏቸዋል (ዘፀ.14፥19 ትርጓሜ፤ ሉቃ.13፥9 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም ያስቡልናል። ማር ይስሐቅ አንቀጽ ካልእ ላይ "ታላቅ ወንድም ለታናሹ እንዲያዝን መላእክትም ያዝኑልናል" ይላል። ቅዱሳን መላእክት እውነት ደስ የሚያሰኛቸው እውነተኞች ናቸው። ቅዱስ ገብርኤል በእያለንበት እንቁም ብሎ ዓለመ መላእክትን ስላረጋጋ ድንግል ማርያምን የምሥራች ለማለት ተመረጠ። በዚህም ምክንያት መልአከ ሰላም ይባላል። ለዓለም ደስታ የሚሆን የአምላክን ሰው መሆን ስለተናገረም መልአከ ፍሥሓ ይባላል። በብሉይ ኪዳን ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነ መልአክ ነው። ሩፋኤል ጦብያን፣ ጦቢትን፣ ሣራ ወለተ ራጉኤልን የረዳ መልአክ ነው። ዑርኤል ለዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዐ ልቡናን ያጠጣና በብዙ ነገር የረዳው መልአክ ነው። በዕለተ ስቅለት የክርስቶስን ደም በብርሃን ጽዋዕ ተቀብሎ የረጨ መልአክ ነው። በጠቅላላው ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር እየታዘዙ ለቅዱሳን ረድኤትን የሚሰጡ፣ ሰዎችን ከክፉ ነገር የሚያድኑ፣ ጸጋን በረከትን የሚያድሉ በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የጸጋ ምስጋናን እናመሰግናቸዋለን። ብዙ ጊዜ መላእክት ለሰው ሲገለጹ ፍርሀትን ከሰው ለማራቅ አትፍራ ብለው ይጀምራሉ። ቅዱስ ሚካኤል በሐዲስ ኪዳንም አፎምያን፣ ባሕራንን ረድቷል። ለእንጦንስ ሥርዓተ ምንኩስናን አስተምሯል። ብዙ ቅዱሳን ሰማዕታትን ቅዱሳን መነኰሳትን ረድቷል አጽናንቷል። እኛንም በተሰጠው የረድኤት፣ የምልጃ ጸጋ ይጠብቀን ይርዳን።

እንኳን ለመልአኩ ለቅዱስ ሚካኤል በዓል አደረሳችሁ። የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ጠባቂ [መልአከ ዑቃቤ] ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፍ.18፥16 ትርጓሜ)። እግዚአብሔር እስራኤላውያንን ከግብጽ ሲያወጣ እንዲረዳቸው የላከው መልአክ ቅዱስ ሚካኤል ነበር (ዘፀ.23፥23 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት የሚከተሉት ናቸው። 1. አጋዕዝት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 2. ኪሩቤል=ቅዱስ ኪሩብ=ኢዮር 3. ሱራፌል=ቅዱስ ሱራፊ=ኢዮር 4. ኀይላት=ቅዱስ ሚካኤል=ኢዮር 5. አርባብ=ቅዱስ ገብርኤል=ራማ 6. መናብርት=ቅዱስ ሩፋኤል=ራማ 7. ሥልጣናት=ቅዱስ ሱርያል=ራማ 8. መኳንንት=ቅዱስ ሰዳካኤል/ክያል=ኤረር 9. ሊቃናት=ቅዱስ ሰላታኤል/ትያል=ኤረር 10. መላእክት=ቅዱስ አናንኤል/ያል=ኤረር ሳጥናኤል ከወረደ በኋላ ቅዱስ ሚካኤል የአጋዕዝትም አለቃ ነው። በተጨማሪም የሁሉም ነገድ አለቃ ነው። እስራኤላውያንን ከሰናክሬም ያዳናቸው ቅዱስ ሚካኤል ነው። ቅዱስ ሚካኤል ለመዓት እንጂ ለምሕረት የማይታዘዙ የዐሥራ ሁለቱ ነገድ የሌጌዎን አለቃም ነው። ነቢዩ ዳንኤልን የረዳ መልአክም ቅዱስ ሚካኤል ነው። "ወናሁ ሚካኤል አሐዱ እመላእክት ቀደምት መጽአ ይርድአኒ" እንዲል (ዳን.10፥13)። ዐሥሩም ነገድ በአንድ ላይ መላእክት ይባላሉ። እንዲሁም ደግሞ በተለየ አንዱ ነገድ መላእክት ይባላል። በተመሳሳይ መልኩ ኪሩቤል የሚባል ነገድ አለ። እንዲሁም እግዚአብሔር በዘፈቀደ የሚገለጥበትን መንበር የሚሸከሙ ኪሩቤል የሚባሉ አራት መላእክት አሉ (ራእ.14፥3)። በመንበሩ ዙሪያ ሆነው የሚያጥኑ 24 ካህናተ ሰማይ አሉ (ራእ.4፥4)። ከነገድ አለቆች በተጨማሪ ለመቶው ነገድ ሰባት ሊቃነ መላእክት አሉ። እነዚህም፦        ፩. ቅዱስ ሚካኤል        ፪. ቅዱስ ገብርኤል        ፫. ቅዱስ ራጉኤል        ፬. ቅዱስ ዑራኤል (ዑርኤል)        ፭. ቅዱስ ሩፋኤል        ፮. ቅዱስ ፋኑኤል        ፯. ቅዱስ ሳቁኤል (አፍኒን) ቅዱሳን መላእክት እኛ የሰው ልጆች እንድን ዘንድ በብዙ ነገር የሚረዱን በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የስማቸው ትርጉም እንደሚከተለው ነው። 🌿ሚካኤል=መሓሪ ወመስተሣህል/ዕፁብ ነገር/መኑ ከማከ         🍀ገብርኤል=አምላክ ወሰብእ         🌴ሩፋኤል=ፈውሰ እግዚአብሔር         ☘️ዑራኤል=ብርሃነ እግዚአብሔር          🌱ፋኑኤል=ማኅፈደ እግዚአብሔር          🍃ራጉኤል=ራእየ እግዚአብሔር          🌾ሠረቃኤል=ወሀቤ አእምሮ/ፀዋሬ ስም ሚካኤል በምሕረት ላይ የተሾመ መልአክ ነው። ዑራኤል በመብረቅ በነጎድጓድ የተሾመ መልአክ ነው። ሩፋኤል በሰው ቁስል ላይ የተሾመ ነው። ራጉኤል አጋንንትን የሚበቀል መልአክ ነው። ሠረቃኤል አእምሮ ባጡ ሰዎች ላይ የተሾመ ነው። ገብርኤል አጋንንት መርዝ እንዳይበጠብጡ በምንጮች ላይ የተሾመ መልአክ ነው (መጽሐፈ ሄኖክ ምዕራፍ 6 ከቁጥር 1 እስከ 10)። የመላእክት ሥራ ከዚህ በጠቀስነው ብቻ የተወሰነ ሆኖ አይደለም በጸናው መናገር ነው እንጂ። ሊቃውንትም ምግብናቸውን መሠረት አድርገው ቅዱስ ሚካኤልን መጋቤ ብሉይ ቅዱስ ገብርኤልን መጋቤ ሐዲስ ይሏቸዋል (ዘፀ.14፥19 ትርጓሜ፤ ሉቃ.13፥9 ትርጓሜ)። ቅዱሳን መላእክት እንደ ታላቅ ወንድም ያስቡልናል። ማር ይስሐቅ አንቀጽ ካልእ ላይ "ታላቅ ወንድም ለታናሹ እንዲያዝን መላእክትም ያዝኑልናል" ይላል። ቅዱሳን መላእክት እውነት ደስ የሚያሰኛቸው እውነተኞች ናቸው። ቅዱስ ገብርኤል በእያለንበት እንቁም ብሎ ዓለመ መላእክትን ስላረጋጋ ድንግል ማርያምን የምሥራች ለማለት ተመረጠ። በዚህም ምክንያት መልአከ ሰላም ይባላል። ለዓለም ደስታ የሚሆን የአምላክን ሰው መሆን ስለተናገረም መልአከ ፍሥሓ ይባላል። በብሉይ ኪዳን ሠለስቱ ደቂቅን ከእሳት ያዳነ መልአክ ነው። ሩፋኤል ጦብያን፣ ጦቢትን፣ ሣራ ወለተ ራጉኤልን የረዳ መልአክ ነው። ዑርኤል ለዕዝራ ሱቱኤል ጽዋዐ ልቡናን ያጠጣና በብዙ ነገር የረዳው መልአክ ነው። በዕለተ ስቅለት የክርስቶስን ደም በብርሃን ጽዋዕ ተቀብሎ የረጨ መልአክ ነው። በጠቅላላው ቅዱሳን መላእክት ከእግዚአብሔር እየታዘዙ ለቅዱሳን ረድኤትን የሚሰጡ፣ ሰዎችን ከክፉ ነገር የሚያድኑ፣ ጸጋን በረከትን የሚያድሉ በመሆናቸው የጸጋ ክብርን እናከብራቸዋለን። የጸጋ ምስጋናን እናመሰግናቸዋለን። ብዙ ጊዜ መላእክት ለሰው ሲገለጹ ፍርሀትን ከሰው ለማራቅ አትፍራ ብለው ይጀምራሉ። ቅዱስ ሚካኤል በሐዲስ ኪዳንም አፎምያን፣ ባሕራንን ረድቷል። ለእንጦንስ ሥርዓተ ምንኩስናን አስተምሯል። ብዙ ቅዱሳን ሰማዕታትን ቅዱሳን መነኰሳትን ረድቷል አጽናንቷል። እኛንም በተሰጠው የረድኤት፣ የምልጃ ጸጋ ይጠብቀን ይርዳን።

"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1 እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁ
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1
እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እያልን በግቢ ጉባዔያችን በዓቢይ ጾም ጉዞ አስበን እግዚአብሔር አልፈቀደምና እንደተሰረዘ ይታወቃል። እንደ አምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ከፈተና በኋላ የዓመቱ መርኃግብር ማጠቃለያ ጉዞ ለማድረግ አስበናል። በአሁኑ የምናደርገው መንፈሳዊ ጉዞ ወደ
ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያን
ሲሆን ቀኑም ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም ነው ። በጉዞው ላይ ጸሎት ፣ የሕብረት ዝማሬ ፣ ጥያቄና መልስ ፣ የእግር ጉዞ ፣ ገዳሙን መጎብኘት ፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ አስተማሪና ቤተሰባዊ መርኃግብራት ይኖሩናል። የጉዞው ዋጋ አጋፔን(ምሣን) ጨምሮ 400 ብር ብቻ እንደሆነ እየገለፅን በጉዞው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ከወዲሁ ትኬቱን እንድትገዙ እናሳስባለን። ትኬቱ በአካል መምጣት ለምትችሉ በግቢ ጉባኤ ቢሯችን ማግኘት ትችላላቹ። በአካል መምጣት የማትችሉ ደግሞ 1000529652767 (CBE ፋሲካ አይችሉህም) ወይም 0942139509  (Telebirr Fiyona ) በነዚህ አካውንት በመክፈል የከፈላቹበትን ደረሰኝ በ @Fiyona_ayche ቴሌግራም አካውንት በመላክ መመዝገብ ይችላሉ:: የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-11:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318 ይደዉሉ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

አቡነ ቄርሎስ ሳድሳዊ ከሚታወቁባቸው በርካታ በጎ ነገሮች አንዱ ለተማሪዎች የነበራቸው ልዩ ፍቅር እና ቅርበት ነበር። ለተማሪዎች ያላቸው በጎ አመለካከት በፓትርያርክነት ዘመናቸው አልተለያቸውም፡፡ ተማሪዎች ፈተና ሲደርስባቸው ወደ እርሳቸው እየመጡ "ጸልዩልን" ይሉአቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ የሚያጠኑበትን መጽሐፍ ይዘው መጥተው ያስባርኩ ነበር፡፡ አባ ቄርሎስም አንዳንዴ መጽሐፉን ገለጥ ያደርጉና "ይህንን አጥኑ" ብለው ይሠጧቸው ነበር፡፡ አብዛኛውም የፈተናው ጥያቄ ከዚያ ገጽ ይወጣ ነበር፡፡ እንዲሁም ለተማሪዎች ፈተና በሚፈተኑበት ጊዜ የሚገጥማቸውን የመንፈስ ጭንቀትና የአእምሮ ውጥረት በመረዳት ከፈተና በፊት የሚጸለይ ጸሎት አዘጋጅተውልናል 👇 + ጸሎት + [ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ "በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ" ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ። አሁንም ጌታ ሆይ በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡ ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታ፤ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅራኄህ የተነሣ እንደትረዳኝ እለምንሃለሁ። ጌታ ሆይ "ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል" ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ "ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም" ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ። አሜን🙏🙏🙏"] ታሪክ በማይረሳው የተወሳሰበ የትምህርት ዘመን አልፋችሁ ሰሞኑን በዩኒቨርስቲያችን የማጠቃለያ ፈተና ለምትወስዱ ወንድም እህቶቻችን ሁሉ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን 🙏 የልባችሁን ዓይን ያብራላችሁ ያጠናችሁትን ይባርክላችሁ የተማራችሁትን ያስታውሳችሁ 🙏🙏🙏 ራሳችሁን በጸሎት አረጋግታችሁ ተፈተኑ እያለች ግቢ ጉባኤያችን መልእክቷን ታስተላልፋለች !!! +++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ዕፀ ሣህል +++

አቡነ ቄርሎስ ሳድሳዊ ከሚታወቁባቸው በርካታ በጎ ነገሮች አንዱ ለተማሪዎች የነበራቸው ልዩ ፍቅር እና ቅርበት ነበር። ለተማሪዎች ያላቸው በጎ አመለካከት በፓትርያርክነት ዘመናቸው አልተለያቸውም፡፡ ተማሪዎች ፈተና ሲደርስባቸው ወደ እርሳቸው እየመጡ "ጸልዩልን" ይሉአቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ የሚያጠኑበትን መጽሐፍ ይዘው መጥተው ያስባርኩ ነበር፡፡ አባ ቄርሎስም አንዳንዴ መጽሐፉን ገለጥ ያደርጉና "ይህንን አጥኑ" ብለው ይሠጧቸው ነበር፡፡ አብዛኛውም የፈተናው ጥያቄ ከዚያ ገጽ ይወጣ ነበር፡፡ እንዲሁም ለተማሪዎች ፈተና በሚፈተኑበት ጊዜ የሚገጥማቸውን የመንፈስ ጭንቀትና የአእምሮ ውጥረት በመረዳት ከፈተና በፊት የሚጸለይ ጸሎት አዘጋጅተውልናል 👇 + ጸሎት + [ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ "በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ" ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ። አሁንም ጌታ ሆይ በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡ ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡ ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታ፤ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅራኄህ የተነሣ እንደትረዳኝ እለምንሃለሁ። ጌታ ሆይ "ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል" ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ "ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም" ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ። አሜን🙏🙏🙏"] ታሪክ በማይረሳው የተወሳሰበ የትምህርት ዘመን አልፋችሁ ሰሞኑን በዩኒቨርስቲያችን የማጠቃለያ ፈተና ለምትወስዱ ወንድም እህቶቻችን ሁሉ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን 🙏 የልባችሁን ዓይን ያብራላችሁ ያጠናችሁትን ይባርክላችሁ የተማራችሁትን ያስታውሳችሁ 🙏🙏🙏 ራሳችሁን በጸሎት አረጋግታችሁ ተፈተኑ እያለች ግቢ ጉባኤያችን መልእክቷን ታስተላልፋለች !!! +++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ዕፀ ሣህል +++

የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ከነገ ጀምሮ ፈተና የምንጀምር ወንድም እህቶቻች በሙሉ መልካም የፈተና ወቅት እንዲሆንልን፤ ፈተናውን በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን እያለች ግቢ ጉባኤያችን እናታዊ ምኞቷን ታስተላልፋለች። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ማቴ 26፥41 ወርኃዊ የመሐረነ አብ ጸሎት - የፈተና ጸሎት 🤲 የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በግቢ ጉባኤያችን
"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ማቴ 26፥41
ወርኃዊ የመሐረነ አብ ጸሎት - የፈተና ጸሎት 🤲 የእግዚአብሔር  ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በግቢ ጉባኤያችን በወሩ የመጨረሻ አርብ የመሐረነ አብ ጸሎት እንደምናደርስ ይታወቃል ። ስለሆነም የፊታችን አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 - 11፡00 በመገኘት ስለ ሀገራችን ፣ ስለ ሃይማኖታችን ፣ ስለ ማኅበራችን ፣ ፈተናችንንም በሰላም አስጀምሮ ያስፈጽመን ዘንድ በኅብረት እንጸልይ ስትል ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። ለበለጠ መረጃ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ለፈተና ዝግጅት ይረዳን ዘንድ የተለያዩ pdfs, notes, last year exams,.... እርስ በርስ በመጋራት እንድንተጋገዝ ለየዲፓርትመንቱ የተዘጋጀውን ግሩፕ ይቀላቀሉ፣ ወንድም እህቶችንም add እናድርግ 🙏 ግሩፑን ለመቀላቀል 👇👇👇 Computer Science Accounting and Finance Marketing Management Business Administration Architecture and Urban Planning Management Economics Nursing ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ