ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae
الذهاب إلى القناة على Telegram
በኢ.ኦ.ተ.ቤ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። በግቢ ጉባኤያችን የሚከናወኑ ተግባራት፣ መረጃዎችንና መልእክቶችን ለውድ አባላቶቹ ያደርሳል። Instagram: https://www.instagram.com/unitygebigubae TikTok: https://www.tiktok.com/@unitygebigubae
إظهار المزيد2 129
المشتركون
+224 ساعات
+67 أيام
+2730 أيام
أرشيف المشاركات
"ወደ እግዚአብሔር ቤት እንሂድ ባሉኝ ጊዜ ደስ አለኝ።" መዝ 121፥1እነሆ መልካም ዜና🤗 ልዩ መንፈሳዊ ጉዞ🎉 የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ ሰላመ እግዚአብሔር ከሁላችን ጋር ይሁን እያልን በግቢ ጉባዔያችን በዓቢይ ጾም ጉዞ አስበን እግዚአብሔር አልፈቀደምና እንደተሰረዘ ይታወቃል። እንደ አምላካችን ቅዱስ ፈቃድ ከፈተና በኋላ የዓመቱ መርኃግብር ማጠቃለያ ጉዞ ለማድረግ አስበናል። በአሁኑ የምናደርገው መንፈሳዊ ጉዞ ወደ
ጥንታዊው ርዕሰ አድባራት ወገዳማት እንጦጦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ራጉኤል ወኤልያስ ቤተክርስቲያንሲሆን ቀኑም ሰኔ 28፤ 2018 ዓ.ም ነው ። በጉዞው ላይ ጸሎት ፣ የሕብረት ዝማሬ ፣ ጥያቄና መልስ ፣ የእግር ጉዞ ፣ ገዳሙን መጎብኘት ፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ እንዲሁም ልዩ ልዩ አስተማሪና ቤተሰባዊ መርኃግብራት ይኖሩናል። የጉዞው ዋጋ አጋፔን(ምሣን) ጨምሮ 400 ብር ብቻ እንደሆነ እየገለፅን በጉዞው ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ከወዲሁ ትኬቱን እንድትገዙ እናሳስባለን። ትኬቱ በአካል መምጣት ለምትችሉ በግቢ ጉባኤ ቢሯችን ማግኘት ትችላላቹ። በአካል መምጣት የማትችሉ ደግሞ 1000529652767 (CBE ፋሲካ አይችሉህም) ወይም 0942139509 (Telebirr Fiyona ) በነዚህ አካውንት በመክፈል የከፈላቹበትን ደረሰኝ በ @Fiyona_ayche ቴሌግራም አካውንት በመላክ መመዝገብ ይችላሉ:: የጉዞ መነሻ ሰዓት- 1:00 መመለሻ ሰዓት-11:00 ነው። መነሻ ቦታ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ለበለጠ መረጃ 0942139509 0972237318 ይደዉሉ። ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
አቡነ ቄርሎስ ሳድሳዊ ከሚታወቁባቸው በርካታ በጎ ነገሮች አንዱ ለተማሪዎች የነበራቸው ልዩ ፍቅር እና ቅርበት ነበር። ለተማሪዎች ያላቸው በጎ አመለካከት በፓትርያርክነት ዘመናቸው አልተለያቸውም፡፡ ተማሪዎች ፈተና ሲደርስባቸው ወደ እርሳቸው እየመጡ "ጸልዩልን" ይሉአቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ የሚያጠኑበትን መጽሐፍ ይዘው መጥተው ያስባርኩ ነበር፡፡ አባ ቄርሎስም አንዳንዴ መጽሐፉን ገለጥ ያደርጉና "ይህንን አጥኑ" ብለው ይሠጧቸው ነበር፡፡ አብዛኛውም የፈተናው ጥያቄ ከዚያ ገጽ ይወጣ ነበር፡፡
እንዲሁም ለተማሪዎች ፈተና በሚፈተኑበት ጊዜ የሚገጥማቸውን የመንፈስ ጭንቀትና የአእምሮ ውጥረት በመረዳት ከፈተና በፊት የሚጸለይ ጸሎት አዘጋጅተውልናል 👇
+ ጸሎት +
[ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
"በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ" ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ።
አሁንም ጌታ ሆይ በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡
ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡
ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታ፤ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅራኄህ የተነሣ እንደትረዳኝ እለምንሃለሁ።
ጌታ ሆይ "ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል" ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ "ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም" ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ። አሜን🙏🙏🙏"]
ታሪክ በማይረሳው የተወሳሰበ የትምህርት ዘመን አልፋችሁ ሰሞኑን በዩኒቨርስቲያችን የማጠቃለያ ፈተና ለምትወስዱ ወንድም እህቶቻችን ሁሉ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን 🙏
የልባችሁን ዓይን ያብራላችሁ
ያጠናችሁትን ይባርክላችሁ
የተማራችሁትን ያስታውሳችሁ 🙏🙏🙏
ራሳችሁን በጸሎት አረጋግታችሁ ተፈተኑ እያለች ግቢ ጉባኤያችን መልእክቷን ታስተላልፋለች !!!
+++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ዕፀ ሣህል +++
አቡነ ቄርሎስ ሳድሳዊ ከሚታወቁባቸው በርካታ በጎ ነገሮች አንዱ ለተማሪዎች የነበራቸው ልዩ ፍቅር እና ቅርበት ነበር። ለተማሪዎች ያላቸው በጎ አመለካከት በፓትርያርክነት ዘመናቸው አልተለያቸውም፡፡ ተማሪዎች ፈተና ሲደርስባቸው ወደ እርሳቸው እየመጡ "ጸልዩልን" ይሉአቸው ነበር፡፡ አንዳንድ ተማሪዎች ደግሞ የሚያጠኑበትን መጽሐፍ ይዘው መጥተው ያስባርኩ ነበር፡፡ አባ ቄርሎስም አንዳንዴ መጽሐፉን ገለጥ ያደርጉና "ይህንን አጥኑ" ብለው ይሠጧቸው ነበር፡፡ አብዛኛውም የፈተናው ጥያቄ ከዚያ ገጽ ይወጣ ነበር፡፡
እንዲሁም ለተማሪዎች ፈተና በሚፈተኑበት ጊዜ የሚገጥማቸውን የመንፈስ ጭንቀትና የአእምሮ ውጥረት በመረዳት ከፈተና በፊት የሚጸለይ ጸሎት አዘጋጅተውልናል 👇
+ ጸሎት +
[ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ
"በችግርህ ቀን ጥራኝ ፤ አድንሃለሁ አንተም ታከብረኛለህ" ብለህ የአንተን መጠጊያነት መፈለግን ስላስተማርከኝ አመሰግንሃለሁ።
አሁንም ጌታ ሆይ በዚህ የፈተና ሰዓት ጥበብና ማስተዋልን ትሰጠኝ ዘንድ እማጸንሃለሁ፡፡
ይህን ፈተና በሰላም አልፍ ዘንድ ጸጋን (ሞገስን) ስጠኝ፡፡ ፈተናውን በምሠራ ጊዜ ጥልቅ የሆነ ሰላምህንና በረከትህን ስጠኝ፡፡
ጌታዬ ኢየሱስ ውጤት በሚሰጡኝ ጊዜ በመምህራኖቼ ዓይን መወደድን ትሰጠኝና ልባቸውን ታለሰልስልኝ ዘንድ እለምንሃለሁ፡፡ የከበርከው ጌታ፤ እኔ ኃጢአተኛ ነኝ ፤ ዓመቱን ሙሉ አንተን ደስ አላሰኘሁህም ፤ ውስጤንም ጭምር፤ ነገር ግን ከልቤ ደንዳናነትና ከኃጢአቶቼ የተነሣ ሳይሆን ከምሕረትህ እና ከርኅራኄህ የተነሣ እንደትረዳኝ እለምንሃለሁ።
ጌታ ሆይ "ለምኑ ይሰጣችኋል፣ እሹ ታገኛላችሁ፤ አንኳኩ ይከፈትላችኋል" ብለሃል፡፡ እናም እነሆኝ እየለመንኩ ነው፤ የምሕረትህንም ደጅ እያንኳኳሁ ነው፡፡ "ወደ እኔ የሚመጣውን ከቶ ከእኔ አላወጣውም" ብለሃልና ጸሎቴን አትናቅ፡፡በቅድስት ድንግልና በመላእክትህ ሁሉ አማላጅነት መልስልኝ። አሜን🙏🙏🙏"]
ታሪክ በማይረሳው የተወሳሰበ የትምህርት ዘመን አልፋችሁ ሰሞኑን በዩኒቨርስቲያችን የማጠቃለያ ፈተና ለምትወስዱ ወንድም እህቶቻችን ሁሉ እግዚአብሔር ከእናንተ ጋር ይሁን 🙏
የልባችሁን ዓይን ያብራላችሁ
ያጠናችሁትን ይባርክላችሁ
የተማራችሁትን ያስታውሳችሁ 🙏🙏🙏
ራሳችሁን በጸሎት አረጋግታችሁ ተፈተኑ እያለች ግቢ ጉባኤያችን መልእክቷን ታስተላልፋለች !!!
+++ ስብሐት ለእግዚአብሔር ልዑል ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክቡር ዕፀ ሣህል +++
የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ
ከነገ ጀምሮ ፈተና የምንጀምር ወንድም እህቶቻች በሙሉ መልካም የፈተና ወቅት እንዲሆንልን፤ ፈተናውን በሰላም አስጀምሮ እንዲያስፈጽመን የእግዚአብሔር ቅዱስ ፈቃዱ ይሁንልን እያለች ግቢ ጉባኤያችን እናታዊ ምኞቷን ታስተላልፋለች።
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
"ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ" ማቴ 26፥41ወርኃዊ የመሐረነ አብ ጸሎት - የፈተና ጸሎት 🤲 የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ የክርስቶስ ሰላም ከሁላችን ጋር ይሁን በግቢ ጉባኤያችን በወሩ የመጨረሻ አርብ የመሐረነ አብ ጸሎት እንደምናደርስ ይታወቃል ። ስለሆነም የፊታችን አርብ መጋቢት 25/2018 ዓ.ም ከቀኑ 10:00 - 11፡00 በመገኘት ስለ ሀገራችን ፣ ስለ ሃይማኖታችን ፣ ስለ ማኅበራችን ፣ ፈተናችንንም በሰላም አስጀምሮ ያስፈጽመን ዘንድ በኅብረት እንጸልይ ስትል ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች። ለበለጠ መረጃ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የተወደዳችሁ የልዑል እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ
ለፈተና ዝግጅት ይረዳን ዘንድ የተለያዩ pdfs, notes, last year exams,.... እርስ በርስ በመጋራት እንድንተጋገዝ ለየዲፓርትመንቱ የተዘጋጀውን ግሩፕ ይቀላቀሉ፣ ወንድም እህቶችንም add እናድርግ 🙏
ግሩፑን ለመቀላቀል 👇👇👇
Computer Science
Accounting and Finance
Marketing Management
Business Administration
Architecture and Urban Planning
Management
Economics
Nursing
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
🕊️🕊️🕊️ በዓለ ጰራቅሊጦስ 🔥🔥🔥
ጰራቅሊጦስ ማለት ቃሉ የግሪክ ሲሆን በትርጓሜ ጉባኤ ቤት ሰባት ትርጉሞች ተሰጥተውታል፡፡
1ኛ መጽንኢ- የሚያጸና፤
2ኛ ናዛዚ- የሚያረጋጋ፣
3ኛ ከሣቲ-ምሥጢር የሚገልጽ፣
4ኛ መስተፍሥሒ - የሚያስደስት፣
5ኛ መስተሥርዩ -ኃጢአትን የሚደመስስ፣
6ኛ መንጽሒ- ከበደል የሚያነጻ፣
7ኛ መጥበቢ- የሚያለብም(ጥበብን የሚሰጥ) ማለት ነው።
መንፈስ ቅዱስ መጽንኢ መባሉ
ማዕታትን ወደ ደም፣ ጻድቃንን ወደ ገዳም እንዲሄዱና ጻድቃን በገዳም፣ ሰማዕታት በዐውደ መናፍቃን ያለውን መከራ ታግሠው እንዲቀበሉ የሚያጸና መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ነው፡፡ ጌታ ከተጠመቀ በኋላ ወሰዶ መንፈስ ገዳመ፤ መንፈስ ቅዱስ ወደ ገዳም ወሰደው ማቴ 4፥1 መባሉም በጥምቀት ጊዜ የሚሰጠው ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ለጥብዐት የሚሆን ጸጋ የሚያድለን መሆኑን እና በአርባ እና በሰማንያ ቀን ባኘነው ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በዐውደ ስምዕ፣ በገዳም፣ በዚህ ዓለም ሁነን በጽናት ተጋድሏችንን እንድፈጽም የሚያደርገን ስለሆነ ነው፡፡
እግዚአብሔር የኀይል እና የፍቅር ራስንም የመግዛት መንፈስ እንጅ የፍርሐት መንፈስ አልሰጠንም 2ጢሞ 1፥7 ተብሎ መነገሩም ስለዚህ ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ ናዛዚ ስለ መባሉ፡-
ክርስቶስ አዐርግ ሰማየ ኀበ አቡየ፤ ወደ አባቴ ወደ ሰማይ ዐርጋለሁ ባላቸው ጊዜ ከተሰማቸው የኀዘን ስሜት የሚያረጋጋ ሆኖ ስለተሰጣቸው ነው፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ እስመ እመ ኢሖርኩ አነ ኢይመጽእ ኀቤክሙ ጰራቅሊጦስ ዮሐ 16÷7 ብሎ ያስተማረውን የአማርኛው መጽሐፍ ቅዱስ አጽናኙ ብሎ መተርጎሙ ከያዘው ትምህርት አንጻር ይመስላል፡፡ ለጊዜው ሐዋርያት የሙት ልጆች ትሆኑ ዘንድ አልተዋችሁም የሚለው ቃል ኪዳን የተፈጸመላቸው በርደተ መንፈስ ቅዱስ ነው። ፍጻሜው ግን ቤተ ክርስቲያን እስከ ዓለም ፍጻሜ ድረስ በምታልፍባቸው የተጋድሎ መንገድ የሚደርስባትን መከራ የሚያስረሳት መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ ከሣቲ መባሉ፦
ሰባ ሁለቱን ቋንቋ፣ ምሥጢረ ሰማይን ምሥጢረ ምድርን የሚገልጥ በአባቶቻንም አድሮ መጻሕፍትን ያጻፈ በኋላም በሚነሡ መምህራን አድሮ የተረጎመ ያራቀቀ እርሱ ነውና፡፡ ለጴጥሮስ የሐናንያን እና የስጲራ ነገር የገለጠ ሥራ 5፥1
ለቅዱስ ኤፍሬም የቅዱስ ባስልዮስን ሞት የገለጠ
ለነቢዩ ኤልሳዕ የሦርያን ቤተ መንግሥት ምሥጢርይስረዳ 2ነገ 6፥2 መንፈስ ቅዱስ ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ መስተፍሥሒ መባሉ፦
የሚያስደስት የተባለው መከራውን ሁሉ በደስታ እንዲቀበሉት የሚያደርጋቸው መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ነው ኀዘንተኞች ስንሆን ሁል ጊዜ ደስተኞች ነን 2ቆሮ 6 10 የሚለው ይህ የቅዱስ ጳውሎስ ቃል የሚያስረዳን ይህንኑ ነው፡፡ በሌላ ጊዜ ሐዋርያት ከአይሁድ ዐደባባይ ሲወጡ ተገርፈዉ፣ አሽሟጠውባቸው፣ እንዳያስተምሩ ከልክለዋቸው እንዳስወጧቸው የታወቀ ነው ነገር ግን ደስ እያላቸው ወጡ ሥራ 5:41 ይህ የመንፈስ ቅዱስ ደስታ ነው እንጅ በመብል እና በመጠጥ የተገኘ አይደለም መንፈስ ቅዱስ ያደረበት ሰው ሁልጊዜም ደስተኛ ነው ደስ ይበላችሁ የሚለውን የክርስቶስን ትምህርት በማሰብ ይደሰታል እንጅ ሌላ ምንም የሚያስደስተው የለምና ማቴ 5፥10
መንፈስ ቅዱስ መስተሥርዪ መባሉ፦
ኃጢአትን የሚያስተሠርይ መባሉ በካህናት አድሮ የሕዝቡን ኃጢአት የሚደመስስላቸው እርሱ ስለሆነ ነው፤ ጌታም ንሥዑ መንፈስ ቅዱስ ካለ በኋላ ነው ኃጢአታቸውን ይቅርያላችኋቸው ሁሉ ይቀርላቸዋል፤ ኃጢአታቸውን ይቅር ያላላችኋቸው አይቀርላቸውም ዮሐ 20፥23 ያላቸው፡፡ ስለዚህ የካህናት ሥርየተ ኃጢአትን መስጠት በጸጋ መንፈስ ቅዱስ እንደሆነ ያስረዳናል ማለት ነው፡፡
መንፈስ ቅዱስ መንጽሒ መባሉ፦
ብርሃነ ፀሐይ ከተበላሸ ምድር ላይ ቢወድቅ ምድሩን የረጠበውን አድርቆ ያነጻዋል እንጅ ብርሃነ ፀሐይ ያድፋል አይባልም።
መንፈስ ቅዱስም እንደ ብርሃነ ፀሐይ ያረፈበትን ሁሉ ይቀድሳል ያነጻል እንጅ የኃጢአተኞች ኃጢአታቸው አያረክሰውም፡፡ በኃጢአተኛ ሰው ለማደር ጥቂት ወደ ጽድቅ የምታዘነብል ነቅዐ ኀልዮ ይፈልጋል ያገኘ እንደሆነ በመጻሕፍት በመምህራን ዳኝነት ያስፋፋትና ልቡናውን ርስቱ ጉልቱ ያደርገዋል፡፡
መንፈስ ቅዱስ መጥበቢ መባሉ፦
ሰነፎችን የሚያለብማቸው፡- መባሉ ከሐዋርያት ጀምሮ ለቤተ ክርስቲያን ጥበብ መንፈሳዊን የሚሰጥ መንፈስ ቅዱስ ስለሆነ ነው፡፡
ቅዱስ ያሬድም፦
ጰራቅሊጦስ ኮነ መጥበቤ አብዳን፤ ጰራቅሊጦስ ሰነፎች ሐዋርያትን ጥበበኛ አደረጋቸው ብሎ አመስግኗል፡፡ በሌላም
የምስጋና ቃል መጥበቤ አብዳን ረዳኤ ምንዱባን ተብሏል። አብዳን የሚላቸው ሐዋርያትን ነው።
ቅዱስ ጳውሎስ አኮኑ አብዳኒሁ ለዝ ዓለም ኀረየ እግዚአብሔር 1ቆሮ 1÷27 ብሎ የጠራቸው ሐዋርያት ናቸው ጠቢባን ከሚባሉ አይሁድ እና ከግሪክ ፈላስፎች የተሻለ ጥበብ ወንጌልን የሰጣቸው ለነሱ ነውና፡፡
ከበዓሉ ረድኤት በረከትን እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ ያድለን።
ደብረ ምጥማቅ
ከግንቦት ፳፩-፳፭ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ደብረ ምጥማቅ በምትባል ቦታ በወርቅ ወንበር ላይ ተቀምጣ ለአራት ቀን ለህዝብ ለአህዛብም የታየችበት ነው።
ይህም በዓል ከ፴፫ቱ የእመቤታችን በዓላት አንዱ ሲሆን በእነዚህ ዕለታት ግብጽ ደብረ ምጥማቅ በተባለ ቦታ በተሰራች ቤተክርስቲያን እመቤታችን ቅዱሳን ጻድቃንን ፣ቅዱሳን መልአክትን አስከትላ ትገለጽላቸው ነበር።
አህዛብም ክርስቲያኖችም በግልጽ ይመለከቷት ነበር። በሀገሩ ያሉ ሰዎች ይሰበሰባሉ ድንኳን ተክለው ሰቀላ ሰርተው አጎበር ጥለው ይከትማሉ ፤እመቤታችንም ከግንቦት ፳፩ ቀን ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት ሳታቋርጥ ትገለጽላቸው ነበር፤ ህዝቡ የተለያየ ጥያቄ ይጠይቃታል አዳም አባታችንን አሳይን ይሏታል ገሚሱ ነብዩ ዳዊትን ገሚሱ ቅዱስ ጊዮርጊስን አሳይን ይሏታል አንዳንዱም ከዚህ ቀደም የሞተ ዘመዱን እንድታሳየው ይጠይቃታል፤ እርሷም ለሁሉም ፍቃዳቸውን ትፈጽምላቸው ነበር፤አዳምን ስትጠራው ከሔዋን ጋር ዳዊትን ስትጠራው ከበገናው ጋር ቅዱስ ጊዮርጊስን ስትጠራው ከጸአዳ ፈረሱ ጋር በክብር ይገለጣሉ።
የእመቤታችን ረድኤት እና በርከቷ በሁላችን ላይ ይድርብን አሜን፡፡
የአርያም ንግሥት የሰማይና የምድር እመቤት የሰውነታችንም መመኪያ ቅድስት ድንግል ማርያም በዚህች ዕለት በምድረ ግብፅ ለተከታታይ ቀናት ተገልጻለች::
ጥንተ ነገሩስ እንደ ምን ነው ቢሉ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደ ምድረ ግብፅና ኢትዮዽያ በተሰደደ ጊዜ ከድንግል እናቱ ከዮሴፍና ሰሎሜ ጋር ዛሬ ደብረ ምጥማቅ በሚባለው ቦታ ላይ አርፎ ነበር:: ቦታውን ባርኮ ለዘለዓለም ያንቺ መገለጫ ይሁን ብሎም ቃል ኪዳን ገብቶላት ነበር:: ጊዜው በደረሰ ሰዓት ደብረ ምጥማቅ ተገድሞ የበርካታ መነኮሳት ቤት ሆነ:: እመቤታችንም በልጇ በወዳጇ ፈቃድ ግንቦት ፳፩ ቀን አእላፍ መላእክትን፣ ጻድቃን ሰማዕታትን አስከትላት መጣች::
በዚያ ሕዝበ ክርስቲያንም: አሕዛብም ተሰብስበው ለ፭ ቀናት ከእመ ብርሃን ጋር ይሰነብታሉ:: እንግዲህ ልብ በሉ:-
እንኩዋን የአርያም ንግስት የአምላክ እናቱ እመቤታችንን ይቅርና በዚህ ዓለም ሰይጣን ቤቱ ያደረጋቸውን የመዝናኛው ኢንዳስትሪ ዝነኛ ሰዎችን ለማየት የዘመናችን ሰው እንዴት እንደሚቸኩል:: እመቤታችንን በአካል መመልከት አይደለም ስሟን መጥራት ነፍስን ከሥጋ መለየት የሚችል ጣዕምና ደስታ አለው:: ባይሆን ይሄ ለሚገባውና ላደለው ብቻ ነው:: የደብረ ምጥማቅና የአካባቢዋ ሰዎች ከእመቤታችን ጋር የሚቆዩባቸው ቀናት የዘለዓለም የሕይወት ስንቅ የሚይዙባቸው ናቸው:: ፈልገው የሚያጡት ጠይቀው የማይፈጸምላቸው ምንም ነገር አልነበረም:: ነቢያት ሐዋርያት ጻድቃን ሰማዕታት ደናግል መነኮሳት መላዕክትና ሊቃነ መላእክት ለድንግል ማርያም ሲሰግዱ ይታዩ ነበርና:: እመ ብርሃንም እየመላለሰች ትባርካቸው ነበር:: እነዚያ እርሷን ያዩ ዓይኖች በፊቷ የቆሙ እግሮች ክብር ይገባቸዋል:: ፭ቱ ዕለታት ሲፈጸሙ ሕዝቡ እመቤታችንን በዕንባ ይሰናበቷታል:: እመ ብርሃንም በብርሃን መስቀል ባርካቸው ከቅዱሳኑ ጋር ታርጋለች::
ለአባት እናቶቻችን የተገለጠች እመቤታችን ለእኛም በረድኤት ትገለጽልን::
ጣዕሟ በአንደበታችን ፍቅሯን በልባችን ይደርብን::
እንኳን ለእናታችን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ ክብረ በዓል - "ደብረ ምጥማቅ" በሰላም አደረሳችሁ !
በዓሉን ከዋዜማው ጀምሮ በገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ቤተክርስቲያን በማኅሌት ፣በቅዳሴ፣ በንግሥ በኅብረት እንድናከብር ዘንድ ግቢ ጉባዔያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች ።
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የግንቦት ወር የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም የጽዋ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት ስለሚኖሩ ሁላችንም ከጓደኞቻችን ጋር በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ፣ ከዕለቱም ረድኤት በረከት እንሳተፍ ዘንድ ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ግንቦት 22፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0972237318 0942139509 ዩኒቲ ግቢ ጉባዔ
እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ
ይሄን "የአባላት መረጃ መመዝገቢያ Form" የሞላው በጣም ጥቂት ሰው ነው። ያልሞላችሁ ወንድምና እህቶች ቶሎ በመሙላት አገልግሎቱን እንድታግዙ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
ሊንኩ አልሰራ ያላችሁ ካላችሁ ፣ ማንኛውንም ጥያቄ ያላችሁ ... በ @tg211215 ወይንም በ0900466948 እና 0972237318 በመደወል መጠየቅ ትችላላችሁ።
በዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት እንክብካቤ፣ ምክክርና አቅም ማጎልበቻ ክፍል
እግዚአብሔር ቤተሰቦች እንደምን አላችሁ
ይሄን Form የሞላው በጣም ጥቂት ሰው ነው። ያልሞላችሁ ወንድምና እህቶች ቶሎ በመሙላት አገልግሎቱን እንድታግዙ በእግዚአብሔር ስም እንጠይቃለን።
ሊንኩ አልሰራ ያላችሁ ካላችሁ ፣ ማንኛውንም ጥያቄ ያላችሁ ... በ@tg211215 ወይንም በ0900466948 እና 0972237318 በመደወል መጠየቅ ትችላላችሁ።
በዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት እንክብካቤ፣ ምክክርና አቅም ማጎልበቻ ክፍል
ዕርገተ ክርስቶስ
• ዕርገት በግእዝ ቋንቋ ማረግ፣ ከታች ወደ ላይ መውጣት ማለት ሲኾን የጌታችን ትንሣኤ በተከበረ
በዐርባኛው ቀን የሚውለው ዐቢይ በዓልም ዕርገት ይባላል /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፯፻፷/፡፡
• በዓለ ዕርገት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለዐርባ ቀናት በግልጽም በስውርም ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለቅዱሳት አንስት መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን፣ ምሥጢራትን፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ ማረጉን የምንዘክርበት ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡
• "እስከ ቢታንያም ወደ ውጭ አወጣቸው እጁንም አንስቶ በላያቸውም ጭኖ ባረካቸው፡፡
እየባረካቸውም ራቃቸው ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በታላቅ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም
ተመለሱ፡፡ በቤተ መቅደስም ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እና እያገለገሉ ኖሩ፡፡" ሉቃ ፳፬:፶።
ዕርገተ ክርስቶስ በሁለት ይከፈላል፡፡ እነዚህም የርኅቀት ዕርገት እና የርቀት ዕርገት ናቸው፡
የርኅቀት ዕርገት
• ርኅቀት ማለት መራቅ ማለት ነው፡፡ ክርስቶስ ከትንሣኤ በኋላ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡
“ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤
እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው እየተመለከቱት ከእነርሱ እየራቀ ሄዶ ተሰወራቸው፤ ለዚያም ነው ይህንን ዕርገት ኢትየጵያውያን ሊቃውንት የርኅቀት ዕርገት ብለው የሚጠሩት፡፡
የርቀት ዕርገት
• ይህንን ዕርገት በተመለከተ በሃይማኖተ አበው ትርጓሜ (ሃይ. አበ.፲፯፥፱) ላይ “ወተንሥአ እሙታን
አመ ሣልስት ዕለት፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በከመ ጽሑፍ በከበሩ መጻሕፍት
እንደተጻፈ እንደ ተነገረ ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ በቅዳሴ መላእክት በክብር በብርሃን
በሥልጣን ዐረገ” ካለ በኋላ የሥጋ ዕርገት በማሕፀን የቃል ዕርገት በአርባ ቀን ይላል፡፡ የቃል ዕርገት በ፵ ቀን የርኅቀት ዕርገትን ሲሆን ከትንሣኤ በኋላ በአርባ ቀን ማረጉን የሚያሳውቅ ነው፡፡ የሥጋ ዕርገት በማሕፀን ያለው ቃል ሥጋ ሲሆን የቃል ገንዘብ ማለትም ረቂቅነት፣ ምሉእነት፣ ሁሉን ቻይነት እና የመሳሰሉት የሥጋ ገንዘብ መሆናቸውን እና የሥጋ ገንዘብ የሆኑት ደግሞ የቃል ገንዘብ
መሆናቸውን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቃል ርደት የሥጋ
ዕርገት ምክንያት ናት የምንለውም ይህንን በማኅፀን የተደረገውን ረቂቅ ዕርገት ለማመልከት ነው፡፡
ሥጋ ቃልን በመዋሐዱ ግዘፉን ሳይለቅ የቃልን ረቂቅነት ገንዘቡ አድርጓልና ይህንን ምሥጢር
ሊቃውንቱ የርቀት ዕርገት ይሉታል፡፡ ይኸውም ሥጋ በማሕፀን እያለ ከቃል ጋር በመዋሐዱ በኪሩቤል
ጀርባ ተቀመጠ ማለት ነው፡፡
የዕለቱ መልዕክታት ፣ ግብረ ሐዋርያት፣
ምስባክ እና ወንጌል፦
• ዕብራውያን ፩፥፩ እስከ ፍጻሜው ድረስ ፩ኛ ጴጥሮስ ፫፥፲፰-ፍጻሜ፤ የሐዋርያት ሥራ ፩፥፩-፲፪
• የዕለቱ ምስባክ፦ ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ
/መዝ.፵፮፥፭-፮/ ትርጉም፦ በዕልልታና በመለከት ድምፅ ላረገ ለአምላካችን፣ ለጌታችንና
ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና አቅርቡ::
• የዕለቱ ወንጌል፦ ማርቆስ ፲፮፥፲፬ እስከ ፍጻሜ
• ቅዳሴ፡-ዘዲዮስቆሮስ (እምቅድመ ዓለም)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
ዕርገተ ክርስቶስ
• ዕርገት በግእዝ ቋንቋ ማረግ፣ ከታች ወደ ላይ መውጣት ማለት ሲኾን የጌታችን ትንሣኤ በተከበረ
በዐርባኛው ቀን የሚውለው ዐቢይ በዓልም ዕርገት ይባላል /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፣ ገጽ ፯፻፷/፡፡
• በዓለ ዕርገት ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሙታን ከተነሣ በኋላ ለዐርባ ቀናት በግልጽም
በስውርም ለቅዱሳን ሐዋርያትና ለቅዱሳት አንስት መጽሐፈ ኪዳንን፣ ትርጓሜ መጻሕፍትን፣
ምሥጢራትን፣ ሕግጋትንና ቀኖናተ ቤተ ክርስቲያንን ሲያስተምር ቆይቶ ወደ ቀደመ ዙፋኑ ወደ ሰማይ
ማረጉን የምንዘክርበት ታላቅ የደስታ ቀን ነው፡፡
• "እስከ ቢታንያም ወደ ውጭ አወጣቸው እጁንም አንስቶ በላያቸውም ጭኖ ባረካቸው፡፡
እየባረካቸውም ራቃቸው ወደ ሰማይም ዐረገ እነርሱም ሰገዱለትና በታላቅ ደስታ ወደ ኢየሩሳሌም
ተመለሱ፡፡ በቤተ መቅደስም ዘወትር እግዚአብሔርን እያመሰገኑ እና እያገለገሉ ኖሩ፡፡" ሉቃ ፳፬:፶።
ዕርገተ ክርስቶስ በሁለት ይከፈላል፡፡ እነዚህም የርኅቀት ዕርገት እና የርቀት ዕርገት ናቸው፡
የርኅቀት ዕርገት
• ርኅቀት ማለት መራቅ ማለት ነው፡፡ ክርስቶስ ከትንሣኤ በኋላ በአርባኛው ቀን ወደ ሰማይ ዐርጓል፡፡
“ይህንም ከተናገረ በኋላ እነርሱ እያዩት ከፍ ከፍ አለ፤ ደመናም ከዓይናቸው ሰውራ ተቀበለችው፤
እርሱም ሲሄድ ወደ ሰማይ ትኩር ብለው እየተመለከቱት ከእነርሱ እየራቀ ሄዶ ተሰወራቸው፤ ለዚያም
ነው ይህንን ዕርገት ኢትየጵያውያን ሊቃውንት የርኅቀት ዕርገት ብለው የሚጠሩት፡፡
የርቀት ዕርገት
• ይህንን ዕርገት በተመለከተ በሃይማኖተ አበው ትርጓሜ (ሃይ. አበ.፲፯፥፱) ላይ “ወተንሥአ እሙታን
አመ ሣልስት ዕለት፤ በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሣ፤ በከመ ጽሑፍ በከበሩ መጻሕፍት
እንደተጻፈ እንደ ተነገረ ዐርገ በስብሐት ውስተ ሰማያት፤ በቅዳሴ መላእክት በክብር በብርሃን
በሥልጣን ዐረገ” ካለ በኋላ የሥጋ ዕርገት በማሕፀን የቃል ዕርገት በአርባ ቀን ይላል፡፡ የቃል ዕርገት
በ፵ ቀን የርኅቀት ዕርገትን ሲሆን ከትንሣኤ በኋላ በአርባ ቀን ማረጉን የሚያሳውቅ ነው፡፡ የሥጋ
ዕርገት በማሕፀን ያለው ቃል ሥጋ ሲሆን የቃል ገንዘብ ማለትም ረቂቅነት፣ ምሉእነት፣ ሁሉን ቻይነት
እና የመሳሰሉት የሥጋ ገንዘብ መሆናቸውን እና የሥጋ ገንዘብ የሆኑት ደግሞ የቃል ገንዘብ
መሆናቸውን የሚያመለክት ቃል ነው፡፡ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የቃል ርደት የሥጋ
ዕርገት ምክንያት ናት የምንለውም ይህንን በማኅፀን የተደረገውን ረቂቅ ዕርገት ለማመልከት ነው፡፡
ሥጋ ቃልን በመዋሐዱ ግዘፉን ሳይለቅ የቃልን ረቂቅነት ገንዘቡ አድርጓልና ይህንን ምሥጢር
ሊቃውንቱ የርቀት ዕርገት ይሉታል፡፡ ይኸውም ሥጋ በማሕፀን እያለ ከቃል ጋር በመዋሐዱ በኪሩቤል
ጀርባ ተቀመጠ ማለት ነው፡፡ የዕለቱ መልዕክታት ፣ ግብረ ሐዋርያት፣
ምስባክ እና ወንጌል፦
• ዕብራውያን ፩፥፩ እስከ ፍጻሜው ድረስ ፩ኛ ጴጥሮስ ፫፥፲፰-ፍጻሜ፤ የሐዋርያት ሥራ ፩፥፩-፲፪
• የዕለቱ ምስባክ፦ ዐርገ እግዚአብሔር በይባቤ ወእግዚእነ በቃለ ቀርን ዘምሩ ለአምላክነ ዘምሩ
/መዝ.፵፮፥፭-፮/ ትርጉም፦ በዕልልታና በመለከት ድምፅ ላረገ ለአምላካችን፣ ለጌታችንና
ለመድኀኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ምስጋና አቅርቡ::
• የዕለቱ ወንጌል፦ ማርቆስ ፲፮፥፲፬ እስከ ፍጻሜ
• ቅዳሴ፡-ዘዲዮስቆሮስ (እምቅድመ ዓለም)
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
ወለወላዲቱ ድንግል
ወለመስቀሉ ክቡር!
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ
ታላቁ ሊቅ ኢትዮጵያዊው አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ ስለ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ሲያደንቅ
"እኔም ስለርሱ እላለሁ በእውት አፈወርቅ ፤አፈ ዕንቁ፤አፈ ጳዝዮን በድርሰቱ ቤተ ክርስቲያንን የሚያጌጣት አፈ ባህርይ
በእውነት አፈ መዓር በቃሉ ጣፋጭነት ምዕመናንን የሚያለመልማቸው አፈ ሦከር በእውነት በትምህርቱ መዓዛ የምስጢር በጎችን ደስ የሚያሰኛቸው አፈ ሽቱ አፈ ርኄ ነው፡፡
በእውነት በውግዘቱ ሥልጣን ከሃዲዮችን የሚቆርጥ አፈ ሰይፍ ፤አፈ መጥባህት ነው፡፡
በእውነት የማይነዋወጥ ዓምድ የማይፈርስ መሠረት በእውነት በሞገዶች መነሳት የሚዋኝ ዋናተኛ ነው፤
በእውነት የማይፈርስ ግንብ በጠላት ፊት የሚጸና አዳራሽ ነው" መጽሐፈ ምስጢር ገጽ 37
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ349 ዓ.ም. አካባቢ በሶርያ አንጾኪያ ከተማ ከ ክርስቲያን ወላጆች ተወለደ። እናቱ አንቱሳ ትባል ነበር፤ አባቱ ሴኩንዱስ ደግሞ በሮማውያን ሠራዊት ውስጥ ክቡር ጄኔራል ነበር። ገና በ18 ዓመቱ (367 ዓ.ም.) በሊባኒዮስ( Libanius) ሥር የንግግር ጥበብ ትምህርቱን፣ በአንድራጋቲዮስ(Andragathius) ሥር ደግሞ የፍልስፍና ትምህርቱን አጠናቋል።
በ368 ዓ.ም. የፋሲካ በዓል በሚከበርበት ጊዜ የአንጾኪያ ጳጳስ ሜሌቲዎስ ዮሐንስን (አፈ ወርቅን) አጥምቀው ክርስቲያን አደረጉት። ዮሐንስ አፈ ወርቅ በአንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን የንባብ አገልግሎቱን(አናጉንስጢስ) ጀመረ፤ ከጥቂት ጊዜ በኋላ ደግሞ ጥብቅ የገዳማዊ ሕይወት ለመኖር ሲል ያንን አገልግሎት አቋርጧል (372 ዓ.ም.)። ወደ ተራሮች ገለል ብሎ ለብዙ ዓመታት እንደ መነኩሴ ኖረ፤ አእምሮውንም በጌታው በኢየሱስ ክርስቶስ ትምህርት ሞላ። ሆኖም ግን፣ ጥብቅ አኗኗሩ ሆዱን በእጅጉ ስላወከው፣ እንዲሁም ከፍተኛ ቅዝቃዜ ኩላሊቶቹን ሰለጎዳው፣ በ378 ዓ.ም. ወደ አንጾኪያ ቤተ ክርስቲያን ተመልሶ የንባብ አገልግሎቱን ቀጠለ።
በ31 ዓመቱ (380/381 ዓ.ም.)፣ ጳጳስ ሜሌቲዎስ ዲያቆን ሾሙት። በ36 ዓመቱ (385/386 ዓ.ም.) ደግሞ በአንጾኪያ ጳጳስ ፍላቪያኖስ (የሜሌቲዎስ ቀጥተኛ ተከታይ) ክህነት ተሾመ።
በአንጾኪያ የነበረው የአገልግሎት ዘመኑ ባልተጠበቀ እና በድንገት ማለት ይቻላል ያበቃው የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ ኔክታሪዎስ መስከረም 27 ቀን 397 ዓ.ም. (በዘመነ ሉቃስ) ሲሞቱ እና ዮሐንስ ተክቶ እንዲሾም ሲመረጥ ነበር። የካቲት 26 ቀን 398 ዓ.ም. (በዘመነ ማቴዎስ) ዮሐንስ አፈ ወርቅ በ49 ዓመቱ በሮማ ንጉሠ ነገሥት አርካዲዮስ ንጉሣዊ ትእዛዝ እና በእስክንድርያ ሊቀ ጳጳስ ቴኦፍሎስ እጅ የቁስጥንጥንያ ሊቀ ጳጳስ ሆኖ ተሾሙ።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ወዲያው ቀሳውስቱን ማሻሻል ጀመረ፤ ምክንያቱም እነርሱ ስርሃት አልባ በሆነ በከፋ ብክለት ውስጥ ገብተው ነበርና። ለቀሳውስትና ለምእመናን መሻሻል የነበረው እሳታዊ ቅንዓት ከፍተኛ የፍርድ ቤት ባለሥልጣናትን አስከፋቸው፤ ለክርስቶስ ትምህርትና ለቤተ ክርስቲያኑ ያለው ፍቅር፣ ታማኝነት እንዲሁም የማይቀየር አቋሙ ደግሞ ሁሉንም የጠላት ኃይላት በእርሱ ላይ አንድ አደረጋቸው።
በዚህም ምክያት ብዙ እንግልት እና ተደጋጋሚ ስደት ደረሰበት፤በስደት ላይ እንዳለ፤ በመስከረም 14 ቀን 407 ዓ.ም. ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ በመጨረሻ ትንፋሹ፦ ስለሁሉም ነገር እግዚአብሔር ይመስገን፤ አሜን" በማለት በ56 ዓመቱ አረፈ።
ጸሎቱና በረከቱ ከሁላችን ጋር ይሁን። አሜን ።
ክርስቶስ ተንሥአ እሙታን፤ በዐቢይ ኃይል ወሥልጣን፤ አሰሮ ለሰይጣን፤ አግዐዞ ለአዳም፤ ሠላም እምይዕዜሰ፤ ኮነ፤ ፍስሐ ወሠላምልዩ የቤተሰብ ጉባዔ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ የፊታችን ቅዳሜ 2ኛው ዙር ልዩ "የቤተሰብ ጉባዔ" ይኖረናል። በዕለቱ ➞ጸሎት ፥ ➞ትምህርት ፥ ➞ልዩ የጨዋታ ጊዜ ፥ ➞ግጥምና ፥ ➞የኅብረት ዝማሬ ስለሚኖረን ሁላችሁም ከቤተሰባችሁ ጋር በመጠራራት እንድትገኙና ልዩ የቤተሰብ ጊዜ እንድናሳልፍ በልዑል እግዚአብሔር ጥሪያችንን እናስተላልፋለን። ጨዋታውን ያሸነፈ ቤተሰብ ሽልማት ይኖረዋል 🤗 📆 ቅዳሜ ግንቦት 15፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:20 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0972237318 0900466948 በዩኒቲ ግቢ ጉባኤ አባላት እንክብካቤ፣ ምክክርና አቅም ማጎልበቻ ክፍል
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
