ar
Feedback
ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ | Unity Gebi Gubae

الذهاب إلى القناة على Telegram

በኢ.ኦ.ተ.ቤ ሰንበት ት/ቤቶች ማደራጃ መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የዩኒቲ ግቢ ጉባኤ ይፋዊ የቴሌግራም ገጽ ነው። በግቢ ጉባኤያችን የሚከናወኑ ተግባራት፣ መረጃዎችንና መልእክቶችን ለውድ አባላቶቹ ያደርሳል። Instagram: https://www.instagram.com/unitygebigubae TikTok: https://www.tiktok.com/@unitygebigubae

إظهار المزيد
2 184
المشتركون
+224 ساعات
+167 أيام
+4130 أيام
أرشيف المشاركات
✨እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ የጽዋ መርኃግብር ይኖረናል። በ
እንኳን ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወርኃዊ በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗
እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያም ልዩ የጽዋ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ነሐሴ 23 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0912947576 0970038830 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

እንኳን አደረሳቹሁ በዓለ ፍልሰታ ወዕርገታ ለማርያም   ወፍልሰተ አጽሙ ለሊቀ  ቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ፍልሰታ የግእዝ ቃል ነው፤ #ፈለሰ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ሲሆን ትርጕሙም ተለየ፣ ሄደ፣ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ መሄድን ያመለክታል፡፡ እመቤታችን እንደ ሰው ልማድ ሞትን ትቀምስ ዘንድ ግድ ስለኾነ፤ ጻዕርና ሕማም በሌለበት አሟሟት፤ ዕዝራ በመሰንቆ፥ ዳዊት በበገና እያጫወቷት፤ በተወለደች በ64 ዓመቷ ጥር 21 ቀን #በ48 ዓ.ም. ከዚህ ዓለም በሞተ ሥጋ አርፋለች። ሐዋርያትም እንደምታርፍ በመንፈስ ቅዱስ ስለተገለጸላቸው ከያሉበት (ከየሀገረ ስብከታቸው) ወደ መኖሪያ ቤቷ (የሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ ቤት) ተሰባስበው ነበር። ነፍሷ ከሥጋዋ እንደተለየች ሥጋዋን ገንዘውና ሸፍነው ወስደው ለመቅበር ወደ #ጌቴሴማኒ ሲሄዱ አይሁድ ሰምተው መጡና ሐዋርያትን ከበቧቸው። የአይሁድ ተንኮል አስከሬኗን ከሐዋርያት እጅ ቀምተው በእሳት ለማቃጠል ነበር፤  ይህንንም ማድረግ የፈለጉበት ምክንያት፤ የሐዋርያት ትምህርት (የጌታችን ከሞት መነሳትና ለፍርድ ተመልሶ መምጣት)ከአይሁድ አልፎ ዓለም ሁሉ እያመነበት ስለመጣ እመቤታችንም ተነሥታ ዐርጋለች እያሉ ሐዋርያት ያስተምራሉ በሚል ስጋት ነበር። ‹‹የፈሩት ይነግሣል፥ የጠሉት ይወርሳል›› እንዲሉ አበው፤ የእመቤታችን ትንሣኤም ሆነ ዕርገት አይቀሬ ሁኗል። አይሁድ የእመቤታችንን ሥጋ ለመንጠቅ በሞከሩበት ጊዜም ታውፋኒያ የተባለ ጎልማሳ ሰው በጉልበቱና በድፍረቱ በአይሁድ ዘንድ ተመርጦ የእመቤታችንን ሥጋዋ ያረፈበትን ቃሬዛ ከሐዋርያት ነጥቆ መሬት ላይ ለመጣል ሲሞክር፤ የእግዚአብሔር መልአክ በእሳት ሰይፍ ሁሉቱንም እጆቹን ቀንጥሶ (ቆርጦ) ጥሏቸዋል። ነገር ግን ጥፋቱን አውቆ ወዲያው ስለተፀፀተና ይቅርታ ስለጠየቀ በአምላክ ፈቃድ በእመቤታችን አማላጅነት በቅዱስ ጴጥሮስ አማካኝነት እጆቹ እንደገና ተመልሰውለት የእመቤታችንን እመ አምላክነት (የአምላክ እናት መሆኗ)ና ክብርን ለመመስከር በቅቷል። የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሥጋ በመላእክት ተነጥቆ ከተወሰደ በኋላ በገነት ውስጥ #በዕፀ ሕይወት ሥር መቀመጡ ከዮሐንስ በስተቀር ለሌሎች ሐዋርያት ለጊዜው ምሥጢር ሆኖባቸው ቆይቶ ነበር። ቆየት ብሎ ግን ሐዋርያው ዮሐንስ ስለ እመቤታችን ሥጋ ነገራቸው። ቅዱሳን ሐዋርያትም ለእመቤታችን ካላቸው ክብርና ፍቅር የተነሳ ለምን አልቀበርናትም? ለምንስ የሥጋዋ ምሥጢር ለዮሐንስ ተገልጾ ለኛ ይደበቅብናል? በማለት እያዘኑና እየለ መኑ ከጥር 21 አንስተው ለስድስት ወራት ከዐሥር ቀናት ቆይተዋል። ከዚህም በኋላ ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ሱባዔ ይዘው ለ14 ቀናት እግዚአብሔርን በጾምና በጸሎት ጠየቁት። በመጨረሻም የነገሩትን የማይረሳ፥ የለመኑትን የማይነሳ ልጇ ጌታችን መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ነሐሴ 14 ቀን ሥጋዋን አምጥቶ ስለሰጣቸው፤ ሳይውሉ ሳያድሩ በዕለቱ በጌቴሴማኒ በታላቅ ክብርና ዝማሬ ቀበሯት። በተቀበረችም በ3ኛው ቀን በነሐሴ 16 ከተቀበረችበት መቃብር ተነሥታ ወዲያውኑ በታላቅ ክብር በመላእክት አጃቢነት ወደ ሰማይ ዐርጋለች። ጥበበኛው ሰሎሞንም “ውዴ  እንዲህ ይለኛል ሙሽራዬ ውዴ ሆይ! ተነሺ የእኔ ውብ ሆይ ነዪ አብረን እንሂድ” በማለት አመሣጥሮ የተናገረው በጥበበ እግዚአብሔር ተመርቶ እንደ ክርስቶስ ሆኖ ውዴ ያላት እመቤታችን መሆኗንና ልጇ ተነሥቶ እንደ ዐረገ እሷም መነሣቷንና ማረጓን እንረዳለን። /መሓ.፪፥፲/። እመቤታችን ባረገችበት ጊዜ ሐዋርያው #ቶማስ በመንፈስ ቅዱስ ጥበብ በደመና ተጭኖ  ከሀገረ ስብከቱ  (ሕንድ) ወደ   ኢየሩሳሌም ሲመለስ እመቤታችን በመላእክት ታጅባ ወደ ሰማይ ስታርግ ተገናኙ። በዚህ ጊዜ ቶማስ ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ ሳላይ አሁንም ደግሞ እርሷን ሳልቀብራት ከትንሣኤዋም ሳልደርስ ቀረሁ ብሎ አዘነ ከደመናው ላይ ሊወድቅም ፈለገ፤ ሆኖም እመቤታችን ዕርገቷን ከእርሱ በቀር ሌሎች አለማየታቸውን ገልጻ አረጋጋችው፤ ዕርገቷንም ለሐዋርያት እንዲነግርና ምልክትና ማስረጃ እንዲሆነው ተገንዛበት የነበረውን ሰበኗን/የከፈን ጨርቅ/ ሰጥታ አሰናበተችው።     ቶማስም መሬት ለይ ወርዶ መቀበሯን፣ ትንሣኤዋንና ዕርገቷን ያላወቀ መስሎ ሐዋርያትን ስለ እመቤታችን ሥጋ ጉዳይ ጠየቃቸው፤ እነርሱም ሱባዔ ገብተው እግዚአብሔርን በጸሎት መጠየቃቸውን፣ ከሱባዔያቸው በኋላ የእግዚአብሔር ፈቃዱ ሆኖ ሥጋዋን መላእክት አምጥተው እንደሰጧቸውና እንደቀበሯት አስረዱት። እርሱ ግን ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር›› እንዴት ሊሆን ይችላል? ሲል ተከራከራቸው። ሐዋርያትም ቶማስን ለማሳመንና ለማሳየት ወደ መቃብሯ ወሰዱት፤ ሆኖም መቃብሯ ባዶ ሆኖ አገኙትና ተደናገጡ፤ በዚህ ጊዜ ቶማስ የሆነውን ሁሉ ገልጾ ለምልክትና ለማረጋገጫ የሰጠችውን ሰበኗን /ተገንዛበት የነበረውን ጨርቅ/ አሳያቸው፤ የራሱን ድርሻም አስቀርቶ አከፋፍሎ ሰጣቸው፤ #ዛሬም_ካህናት ከእጅ መስቀላቸው ጋር የሚይዙት እራፊ ጨርቅ የሚይዙበት ምክንያት ሐዋርያት የተከፋፈሉት የእመቤታችን ሰበን ምሳሌ ነው።        ሐዋርያትም የዕርገቷን ምሥጢር ካመኑ በኋላ ዕርገቷን ለማየት በዓመቱ በተመሳሳይ ሁኔታ እንደገና ከነሐሴ 1 ቀን ጀምረው ለ፪ኛ ጊዜ ሁለት ሱባዔ ገቡ፣ እግዚአብሔርም ልመናቸውን ሰምቶ በነሐሴ ወር በ16ኛው ቀን ጌታችን ሐዋርያትን ወደ ሰማይ አውጥቷቸው እመቤታችንን አግኝተዋት ከሷ ተባርከው በታላቅ ደስታ ወደ ደብረዘይት ተመልሰዋል።

የታቦር ብርሃን ቀድሞ  የሚያበራ  የትንሣኤ ብርሃን ነው::   በፊታቸው ተለወጠ፤ ፊቱም እንደ ፀሐይ አበራ፤ ልብሶቹም እንደ ብርሃን ነጭ ሆኑ። ሙሴና ኤልያስም በግራና በቀኙ ቆመው ነበር። "ብሩህ ደመናም ጋረዳቸው፤ ከደመናውም ውስጥ እንዲህ የሚል ድምፅ መጣ፦ 'የምወደው ልጄ ይህ ነው፤ በእርሱ ደስ ይለኛል'" (ማቴዎስ 17፥1 -8)።   ክርስቶስ ለሐዋርያው እንደተገለጠው "በእግዚአብሔር መልክ" (ፊል 2፥6-7) ነበር—እርሱም ከሥላሴ አካላት አንዱ ሆኖ ነው። ይህ መገለጥ ስለዚህ የሥላሴ መገለጥ (theophany) ነበር፤ የአብ ድምፅና መንፈስ ቅዱስ በብርሃናዊው ደመና ውስጥ ተገኝተዋል።   "የታቦር ብርሃን የተፈጠረ ብርሃን አይደለም፤ እርሱ የመለኮት ያልተፈጠረ ክብር በሥጋ ልብስ በኩል ሲያበራ ነው::እንደ ፀሐይ ያበራው ፊት የቃል ፊት ነበር፤ ውበቱንም ዓለም ሊይዝ አልቻለም::” ፟ _ ቅ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ      ብርሃኑ ሥጋን አላጠፋም፤ ሥጋን አበራው እንጂ። ይህም የተዋሕዶን ምሥጢር ያሳያል—መለኮትና ትስብእት ሳይደባለቁ፣ ሳይለያዩ፣ ሳይለወጡ በአንድነት ተዋሕደው መኖራቸውን ያስረዳል።   ደቀ መዛሙርቱም ከገደል አፋፍ ላይ ወድቀዋል፤ በእሳታማው  ራእይ ተጨናንቀዋል፣ ተደንግጠዋልም። ብዙ ጊዜ ጴጥሮስ በቀኝ በኩል ተንበርክኮ እጁን ዘርግቶ ራሱን ከብርሃኑ ለመጠበቅ ሲሞክር ይታያል። ዮሐንስ በመሃል ላይ ሆኖ ጀርባውን ከብርሃኑ አዙሮ ይወድቃል። ያዕቆብ ደግሞ በግራ በኩል ሆኖ ወደ ኋላው ይወድቃል።ለምን?   "ብሩህ ደመና  ጋረዳቸው፤ የሥላሴ ምሥጢር ያለ ፍርሃት አይቀረብምና።” ቅ. ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ   በታቦር ተራራ ላይ ደቀ መዛሙርቱን የጋረደው ደመና ተራ የአየር ሁኔታ አልነበረም። እርሱ የመንፈስ ቅዱስ መገለጫ፣ የእግዚአብሔር ግርማ መኖሪያ፣ የመለኮት ጥላ ነው። በብሉይ ኪዳንም እግዚአብሔር በደመና ውስጥ ተገልጦ ነበር—በሲና ተራራ፣ በምድረ በዳ ድንኳን ላይ፣ በቤተ መቅደሱ ውስጥ። ይህ ደመና የእግዚአብሔር ልዩ መገኘት ምልክት ነው። "ፍርሃት" ማለት እዚህ ላይ የሚያስደነግጥ ሽብር ሳይሆን፣ ቅዱስ የሆነ አክብሮት ነው። የእግዚአብሔር ግርማ ሲገለጥ ፍጡር የራሱን አነስተኛነት በጥልቅ ይገነዘባል። ይህም የጥበብ መጀመሪያ የሆነው "የእግዚአብሔር ፍርሃት" ነው (መዝ. 111:10)። ነቢዩ ኢሳይያስ የእግዚአብሔርን ክብር ሲመለከት "ወዮልኝ! ጠፋሁ" ማለቱ ይህንኑ ያሳያል (ኢሳ. 6፥5)።     “ሐዋርያት ያዩትን እኛም እናየዋለን፤ ወደ ጸሎትና ወደ ንጽሕና ተራራ የምንወጣ ከሆነ።መለወጡ የእርሱ ክብር ብቻ አይደለምና፤  በእርሱ ውስጥ የሚሆነው የእኛ የራሳችን መለወጥ ተስፋ ነው።" -ቅ ጎርጎርዮስ ዘኑሲስ   ተስፋውም  የጸና ነው። በእግዚአብሔር አምሳል የተፈጠረ ሰው ሁሉ በዚያው መለኮታዊ ብርሃን እንዲያበራ ተጠርቷል። ይህ መለወጥ የሚጀምረው አሁን ነው—በጸሎት፣ በንስሐ፣ በቤተ ክርስቲያን ቅዱሳት ምሥጢራት ውስጥ—ፍጻሜውንም የሚያገኘው በሚመጣው ዘመን ነው፤ በዚያን ጊዜ ጻድቃን በአባታቸው መንግሥት እንደ ፀሐይ ያበራሉ።   ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤ ወለወላዲቱ ድንግል፤ ወለመስቀሉ ክቡር፤ይቆየን።

✅ የስራ ማስታወቂያ የስራ መደቡ መጠሪያ: Architect የስራ ልምድ : 0 - 2 ዓመት የስራ ሰዓት: ከ ጠዋቱ 2 :00 - 11:00 አድራሻ : Gerji Unity University ከፍ ብሎ ደሞዝ: በስምምነት Portfolio በ 0916832471 ይላኩ

✨እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የበዓለ ደብረታቦር ልዩ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች
እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗
እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የበዓለ ደብረታቦር ልዩ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን በድምቀት እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ነሐሴ 9 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0912947576 0970038830 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

ቅዱስ ቁርባን ከመቀበል አስቀድሞ ከቅዱስ ምሥጢር የሚቀበሉ ሁሉ እንዲህ ይበሉ፤ አቤቱ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ! ርኵስት ከሆነች ከቤቴ ጠፈር በታች ትገባ ዘንድ የሚገባኝ አይደለም። እኔ አሳዝኜሃለሁና  በፊትህም ክፉ ሥራ ሠርቻለሁና በአርኣያህና በአምሳልህ የፈጠርኸው ሥጋዬንና ነፍሴን ትእዛዝህን በማፍረስ አሳድፌአለሁና ሥራም ምንም ምን የለኝምና። ነገር ግን ስለ መፍጠርህና እኔን ለማዳን ሰው ስለ መሆንህ፣ ስለ ክቡር መስቀልህም፣ ማሕየዊት ስለ ምትሆን ስለ ሞትህ፣ በሦስተኛው ቀን ስለ መነሣትህም ጌታዬ ሆይ ከበደልና ከመርገም ሁሉ፣ ከኃጢአትና ከርኵሰትም ሁሉ ታነጻኝ ዘንድ እለምንሃለሁ እማልድሃለሁም። የቅድስናህንም ምሥጢር በተቀበልኩ ጊዜ ለወቀሳ ለመፈራረጃ አይሁንብኝ ማረኝ ይቅርም በለኝ እንጂ።   የዓለም ሕይወት ሆይ! በእርሱ የኃጢአቴን ሥርየት የነፍሴንም ሕይወት ስጠኝ እንጂ። በሁለት ወገን ድንግል በምትሆን    በወለደችህ በእመቤታችን በቅድስት ማርያም፣ በመጥምቁ በዮሐንስም አማላጅነት፣ ክቡራን በሚሆኑ በመላእክትም፣ በሰማዕታትና፣ ለበጎ ነገር በሚጋደሉ በጻድቃንም ሁሉ ጸሎት እስከ ዘላለሙ ድረስ አሜን።

በጉጉት ስንጠብቀው የነበረው ቀን እነሆ ደረሰ 🤗 በነገው ዕለት በግቢ ጉባዔያችን የሕይወት ቀን (በሕብረት ቅዱስ ቁርባን የመቀበል ቀን) እንደሆነ ይታወቃል። በመሆኑም ከቅዳሴ ሥርዓት ጀምሮ ሁላችንም በዕለቱ የሚቀበሉ ወንድም እና እህቶቻችንን በማጀብ አብረን በማስቀደስና ከቅዳሴ በኋላ ደግሞ አጋፔ (የጋራ ማዕድ) በመሳተፍ ይህንን ልዩ ቀን እንድናሳልፍ በእግዚአብሔር ስም ጥሪያችንን እናስተላልፋለን🤗 🕰 ከቀኑ 05:00 - 11:00 አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0912947576 0970038830 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

✨ የሕይወት ቀን - '1 ቀን' ብቻ ቀረው ✨ 📆 ነገ አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '1 ቀን' ብቻ ቀረው ✨ 📆 ነገ አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

ከመቁረባችን በፊት ማድረግ ያለብን ነገሮች። 1,ንስሃ መግባት እና ቀኖናን መጨረስ። 2, ለመቁረብ ንስሃ አባትን ማማከር እና ማሳወቅ። እነዚን ከጨረስን በዋላ 3, 18 ሰዓት መጾም። 4, ንፁህ ልብስ ማዘጋጀት። ⚠️ማሳሰቢያ ገላ መታጠብ፣ ጥፍር መቁረጥ፣ ጥርስ መቦረሽም ሆነ ጠዋት ተነስቶ መጉመጥመጥ፣ ፀጉር መቆረጥ (ለወንዶች) ወዘተ የሚደረጉት ከ18 ሰዓት በፊት ብቻ ነው። ለመቁረብ 18 ሰዓት መጾም ከጀመርን በዋላ እነዚን ነገሮች ማድረግ አይፈቀድም። ከቆረብን በዋላ ማድረግ ያለብን ነገሮች 1, የቆረብንበትን ልብስ አለማውለቅ። 2, ምራቅ ከአፋችን ሊነጥም ስለሚችል ብዙ አለማውራት ማውራት ካለብንም በስርዓት። 3, ከሰውነታችን ላብ እዲወጣ ከሚያደርጉ ነገሮች መራቅ ለምሳሌ እረጅም መንገድ መሄድ የመሳሰሉትን አለማድረግ። 4, እጅ አለመታጠብ ።           ⚠️ ከቆረብን በዋላ ገላን መታጠብ የሚቻለው ከ24 ሰዓት በዋላ ነው። 5, ከሶሻል ሚዲያ መራቅ በተለይ ከTikTok እና Instagram አዕምሯችን ማረፍ አለበትና። እግዚአብሔር አምላክ ፈቅዶ ለዚህ ልዩ ምሥጢር ያዘጋጀን🙏

✨ የሕይወት ቀን - '2 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '2 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

✨እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗 እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የበዓለ ደብረታቦር ልዩ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣ ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች
እንኳን ለደብረ ታቦር በዓል በሰላም አደረሳችሁ! ✨🤗
እግዚአብሔር ቢፈቅድ የፊታችን ቅዳሜ የበዓለ ደብረታቦር ልዩ መርኃግብር ይኖረናል። በዕለቱም ጸሎት፣  ትምህርተ ወንጌል ፣ ኪነጥበባዊ ዝግጅቶች ፣ የኅብረት ዝማሬ እንዲሁም ልዩ ልዩ መርኃግብራት  ስለሚኖሩ ሁላችንም ተጠራርተን በመምጣት በዓሉን አብረን በድምቀት እንድናከብር ግቢ ጉባኤያችን ጥሪዋን ታስተላልፋለች! 📆 ቅዳሜ ነሐሴ 9 ፤ 2018 ዓ.ም 🕰 ከቀኑ 06:00 ጀምሮ አድራሻ ፦ ቦሌ ገርጂ ኆኅተ ብርሃን ቅድስት ማርያም ካቴድራል ሰ/ት/ቤት አዳራሽ ለበለጠ መረጃ ፦ 0912947576 0970038830 ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

✨ የሕይወት ቀን - '4 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '4 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

✨ የሕይወት ቀን - '6 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '6 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

መልዕክተ ቅዱስ ፓትርያርክ" በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሓዱ አምላክ፣ አሜን ! በሀገር ውስጥና በመላው ዓለም የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እምነት ተከታዮች በሙሉ! የሰውን ወገን ለማዳን የልጁ ማደሪያ ትሆን ዘንድ ድንግል ማርያምን የመረጠ መፍቀሬ ሰብእ እግዚአብሔር ኣምላካችን እንኳን ለሁለት ሺሕ ዓሥራ ስምንት ዓመተ ምሕረት ጾመ ማርያም ኣደረሰን ኣደረሳችሁ! “ወእመሰ ታፈቅሩኒ ዕቀቡ ትእዛዝየ፡- ከወደዳችሁኝስ ትእዛዜን ጠብቁ" (ዮሐ.14፥15)፤ ፍቅር የሕያዋን ኣካላት ረቂቅ መገናኛ ነው፣ ሕያዋን ኣካላት በውጫዊው ግዙፍ ኣካላቸው በተወሰኑ ጊዜያትና ቦታ ይገናኛሉ ፤ ስለ ጋራ ጉዳያቸውም በጋራ ይመክራሉ፤ ይበልጥም ይቀራረባሉ፡፡ ይሁንና የሕያዋን ኣካላት ግንኙነት በኣካል በጊዜና በቦታ ብቻ የተወሰነ ኣይደለም፣ በፍቅረ መንፈስ ተገናኝተውም ይግባባሉ፣ ከኣካላዊ ግንኙነት በላይ የበለጠም ይኸው ፍቅረ መንፈስ ነው፤ ከዚህ ኣንጻር እግዚአብሔርንም ማግኘት የምንችለው በዚሁ ፍቅረ መንፈስ ሆነን በእምነት ዓይን ነው! ይህም በመሆኑ ሓዋርያው ቅዱስ ዮሓንስ በመልእክቱ “በፍቅር የሚኖር በእግዚአብሔርይኖራል፣ እግዚአብሔርም በእርሱ ይኖራል" በማለት ያስተምረናል፣ (1ዮሐ. 4፥16) ይህም ማለት ከሱ ጋር በፍቅር ስንገናኝ፤ እሱም በኛ፣ እኛም በእሱ የመኖሩ ኩነት ይፈጠራል ማለት ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ጌታችን “አፍቅሮ ለእግዚአብሔር ኣምላክከ፤- አምላክህን እግዚአብሔርን ውደደው" በማለት በፍጹም ልባችን እንድንወደው፣ እንደዚሁም ራሳችንን በምንወድበት መጠን እርስ በእርሳችን እንድንዋደድ ማዘዙን እናውቃለን፤ የመውደዳችን መለኪያ ሚዛንና መገለጫ ምልክትም ትእዛዙን ማክበርና መጠበቅ እንደሆነ “ብትወዱኝስ ትእዛዜን ጠብቁ” በማለት ኣስተምሮናል ከዚህ ኣኳያ ጌታን መውደድ ማለት ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ግዙፍ ነገር እንጂ ምናባዊና የማይታይ ድብብቆሽ ነገር ኣይደለም ማለት ነው፣ ጌታችንን የመውደድ ነገር ትእዛዙን በመጠበቅ የሚገለጽ ከሆነ ትእዛዙ ምንድን ነው? የሚለውን ማየት ኣስፈላጊ ይሆናል፤ ትእዛዙን በጥቅል ስናይ እግዚአብሔርንና ባልንጀራን በመውደድ እንደሚጠቃለል ራሱ ጌታችን ኣስገንዝቦናል፣ በተለይም በባልንጀራችን ላይ የምንከተለው መውደድ ከላይ እንደተገለጸው “እንደራስህ ኣድርገህ ውደድ" ተብለ በግልጽ ተቀምጦኣል፤ የሰው ባልንጀራ እነማን ናቸው? በሕይወት ያሉት ናቸው? ወይስ የሞቱት? ወገን ዘመድ? ወይስ የሰው ወገን በሙሉ የሚለውንም ማወቅ ኣስፈላጊ ነው፡፡ ጌታችን ነገሩን በዚህ ደረጃ ለያይቶ ኣላስቀመጠም፣ ለምን? ቢባል ባልንጀራ ማለት የተወሰነን የማኅበረ ሰብ ወገን የሚያሳይ ሳይሆን መላውን የሰው ወገን የሚገልጽ በመሆኑ፤ እንደዚሁም የሞቱም ሆኑ ያለነው ሁላችን በእሱ ፊት ሕያዋንና እርስ በእርሳችን ባልንጀሮች በመሆናችን ነው፤ በመሆኑም መዋደዳችንም ሆነ መከባበራችን በሕይወተ ሥጋ ሳለን ብቻ ሳይሆን ከዚያም በኋላ እስከ በሌለው ዕድሜ በመሆኑ ጌታችን በጊዜ በቦታና በከፊል ለይቶ ኣላስቀመጠም፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት ! ከነሐሴ ፩ ቀን ጀምሮ ለ፲፭ ቀናት የምንጾመው የጾመ ማርያም መነሻ ምክንያቱ የእግዚአብሔርትእዛዝና ፍቅር ነው፣ እግዚአብሔር ሰውን በኣጠቃላይ በተለይም ደግሞ እንደፈቃዱ የኖሩ ቅዱሳንን እንድናከብርኣዞናል ክቅዱሳን ፍጥረታት መካክል ደግሞ ቅድስት ድንግል ማርያም የመጀመሪያውን ደረጃ ትይዛለች፤ ይህም በመሆኑ ከፍጥረት ወገን ከሏ ክብር የሚደርስ ባለመኖሩ ከሁሉም ኣብልጠን እናክብራታለን፤ ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዚህ ደረጃ የድንግል ማርያምን ክብር ስትገልጽ ክእግዚአብሔርና ለባስያነ እግዚአብሔር ክሆኑ ቀደምት ኣበው ተምራ ነው! በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን የነበረው ዕውቁ ቅዱስና ዓለም ዓቀፋዊው አባት ቅዱስ ኤፍሬም የድንግል ማርያምን ክብር! ቅድስና እና ልዕልና ሲናገር “ይእቲ ተዓቢ እምኪሩቤል፡ ወትፈደፍድ እምሱራፌል፣ እስመ ኮነት ታቦተ ለአሓዱ ዘእምቅድስት ሥላሴ- እሷ ከኪሩቤል ትበልጣለች! ከሱራፌልም ትልቃለች፣ ከቅድስት ሥላሴ ኣንዱ ለሆነው ታቦት ወይም ማደሪያ ሆናለችና" በማለት አስተምሮናል፡፡ በመሆኑም ለስሟ መታሰቢያ በሆነው በዚህ ጾም ድንግል ማርያምን በዚህ ደረጃ ስናክብርትእዛዙን እንጠብቃለን፤ ትእዛዙን በመጠበቃችን ደግሞ እሱን መውደዳችንን እናረጋግጣለን ! እኛ ድንግል ማርያምን እንድንወዳት "እናታችሁ'' ብሎ እንዳዘዘ፣ እሷም ልትወደን “ልጆችዅ ተብላ ታዛለችና ስለኛ ትጸልያለች፡፡ በጸሎቷም ከመከራ ትታደገናለች፤ በኣጠቃላይ በእግዚአብሔር' በቅዱሳንና በእኛ መካከል ያለው ግንኙነት በዚህ ትእዛዝና ፍቅር በትዕይንተ ዓለም ባለች ቤተ ክርስቲያን ዘንድ የተሳሰረ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ የጾመ ፍልሰታ ለማርያም ሱባዔ የተራቡትን በመመገብ፣ የታረዙትን በማልበስ፣ የተጣሎትን በማስታረቅ፤ የታመሙትንና የታስሩትን በመጠየቅ፤ ቅዱስ ቍርባንን በመቀበልና ለኃጢኣታችን የንሥሐ ሥርየትን በመለመን ሱባዔውን ልናሳልፍ ይገባል፡፡ በመጨረሻም በሀገራችንም ሆነ በዓለም ዙሪያ ከባድ ስጋት የሆነው የፍጥረት ኣውዳሚ ጦርነትን በመለኮታዊ ጥበቡና ሥልጣኑ እንዲያስቆምልን በቅን ልቡና፤ በትሑት ሰብእና ሆነን እግዚአብሔርን በዚህ ሱባዔ እንድንጠይቀው ኣደራ ጭምር ኣባታዊ መልክታችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፤ የተባረከና የተቀደስ ጾም ያድርግልን፤ እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ! ወስብሐት ለእግዚአብሔር፣ አሜን! አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእስ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘኣኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ነሐሴ 1 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ ©EOTC TV

✨ የሕይወት ቀን - '9 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '9 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

❣ጾመ ፍልሰታ/ጾመ ማርያም/        🌺ፍልሰታ ማለት ፈለሰ፤ ተሰደደ፤ ተጓዘ፤ ከአንድ ቦታ ወደ ሌላ ቦታ ሄደ ከሚለው የግእዝ ግስ የተገኘ ቃል ሲሆን ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ «ፈለሰት ማርያም እምዘይበሊ ኀበኢይበሊ፤ ድንግል ማርያም ከሚያልፈው ዓለም ወደማያልፈው ዓለም፣ ከምድር ሕይወት ወደ ሰማያዊ ሕይወት፣ ተሻገረች» በማለት ፍልሰታ የሚለውን ቃል ትርጓሜ አመሥጥሮ ገልጾታል፡፡   🌺ጾመ ፍልሰታ ከእመቤታችን ድንግል ማርያም የዕረፍት ታሪክ ጋር የተያያዘ ነው፡፡ እመቤታችን በዚህ ዓለም ፷፬ ዓመታትን በሕይወተ ሥጋ ከቆየች በኋላ ጌታችን የእናቱን ተድላ ነፍሷን እንጂ ተድላ ሥጋዋን አይወድምና ጥር ፳፩ ቀን ፵፱ ዓመተ ምሕርት አረፈች፡፡ ዕረፍቷም እንደሌላው ሰው በሕማምና በድካም አይደለም፡፡ በገነት ዕፀዋት መዓዛ ተመስጣ ቅድስት ነፍሷ ከሥጋዋ ተለይታለች፡፡   🌺ታሪኩ በነገረ ማርያም እንደተጻፈው ሐዋርያት እመቤታችንን በአጎበር አድርገው አክብረው ወደጌቴሴማኒ መካነ መቃብር ይዘዋት ሲሄዱ አይሁድ ለምቀኝነት አያርፉም ነበርና ቀድሞ ልጇን ተነሣ ዐረገ እያሉ ሲያውኩ ኖረዋል፤  እርሷን ደግሞ ተነሣች ዐረገች እያሉ ሊያውኩን ነውና «ኑ የማርያምን ሥጋ በእሳት እናቃጥለው» ብለው በምቀኝነት ተነሱ፡፡ ከመካከላቸው አንድ ታውፋንያ የሚባል አይሁዳዊ ከሐዋርያት እጅ ለመንጠቅ ዘሎ ሄዶ የአልጋውን ሸንኮር ሲይዝ የታዘዘ መልአክ በረቂቅ ሰይፉ እጆቹን ቆረጠው፡፡ እጆቹም በአልጋው ሸንኮር ላይ ተንጠልጥለው ቀሩ፡፡ የምሕረት እናት የሆነችው ድንግል ማርያም ቅዱስ ጴጥሮስ ጸልዮ እጆቹን እንዲመልስለት ነግራው እንደነበረ አድርጎለታል፡፡   🌺የእመቤታችን ሥጋዋን መላእክት ከዮሐንስ ወንጌላዊ ጋር በገነት ከዕፀ ሕይወት ሥር ወስደው አስቀምጠውታል፡፡ ሥጋዋ ያለበትን ሐዋርያው ቅዱስ ዮሐንስ አይቶ እነርሱ ባለማየታቸው እመቤታችን ባረፈች በ፮ኛው ወር ከነሐሴ ፩ ቀን እስከ ፲፬ ቀን ድረስ ከጾሙ በኋላ በ፲፬ኛው ቀን ሥጋዋን እንደገና ከጌታ ተቀብለው በጌቴሴማኒ ባለው መቃብር ቀብረውታል፡፡   🌺ከዚህ በኋላ እንደ ልጇ በ፫ኛው ቀን ተነሥታ መላእክት እየዘመሩላት ወደሰማያት ስታርግ፤ ሐዋርያው ቶማስ ከሀገረ ስብከቱ በደመና ተጭኖ ወደ ኢየሩሳሌም ሲመለሰ ዕርገቷን በማየቱ መላእክት «እመቤትህ እርሷ ናት፤ስገድላት» አሉት፤ እርሱም «ወፈቀደ ይደቅ እምደመናሁ ይላል፤ከደመናው ሊወድቅ ወደደ» ምክንያቱም ቀድሞ የልጇን ትንሣኤ፤ ዛሬ ደግሞ የእርሷን ትንሣኤ ለማየት ብሎ ነው፡፡ እመቤታችንም «ትንሣኤየን ያየህ አንተ ነህ ሌሎቹ አላዩም» ብላ ሐዋርያት ገንዘው የቀበሩበትን የሐር ግምጃ ሰጥታ አጽናንታ ሰደደችው፡፡   🌺ቅዱስ ቶማስ ኢየሩሳሌም ሲደርስ የእመቤታችን ነገር እንዴት ሆነ ብሎ ጠየቃቸው፤እነርሱም አግኝተው እንደቀበሯት ነገሩት፤ እርሱም ያየውን ምሥጢር በልቡ ይዞ «ሞት በጥር፤ በነሐሴ መቃብር፤ ለሰሚውም አያምር፤ይህ እንዴት ይሆናል?»፤ ቢላቸው ቅዱስ ጴጥሮስ «ድሮም አንተ ተጠራጣሪ ነህ፤ማን ያርዳ የቀበረ፤ ማን ይናገር የነበረ እንዲሉ፤ ገንዘን የቀበረን እኛ እያለን እንዴት ትጠራጠራለህ» ብለው ወደ መቃብሯ ሄደው መቃብሯን ቢከፍቱት ባዶ ሆኖ አገኙት፡፡ በዚህ ተደናግጠው ተያዩ፤ በዚህ ጊዜ ቅዱስ ቶማስ «አታምኑኝም ብዬ ነው እንጂ እመቤታችን ተነሣች፤ዐረገች፤ ይኸው ምልክቱ» ብሎ ገንዘው የቀበሩበትን ሰበን አሳያቸው፤ እነርሱም አምነው ሰበኗን ለበረከት ተካፈሉት፡፡   🌺በዓመቱ ነሐሴ ፩ ቀን ሐዋርያት በመንፈሰዊ ቅናት ተነሳስተው «ቶማስ ትንሣኤዋን አይቶ እኛ ሳናይ እንዴት ይቀርብናል» በማለት ነሐሴ ፩ ቀን ሱባኤ ጀምረው በ፲፮ኛው ቀን የሐዋርያትን ሱባኤ ተቀብሎ እመቤታችንን መንበር ጴጥሮስን ተራዳኢ፣ ካህን እስጢፋኖስን ሠራዔ ዲያቆን አድርጉ ቀድሶ አቁርቧቸዋል፡፡ ከዚያ ጊዜ በኋላም ከነሐሴ ፩ እስከ ፲፭ ቀን  ጾመ ፍልሰታ ተብሎ ሁሉም የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሃይማኖት ተከታይ ይጾመዋል፡፡ 💛የጾሙ እና የትንሣኤዋ በረከት ተካፋይ ያድረገን፤ አሜን💛

✨ የሕይወት ቀን - '9 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ
የሕይወት ቀን - '9 ቀናት' ብቻ ቀረው ✨ 📆 አርብ ነሐሴ 8፤ 2018 ዓ.ም ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ

ቅዱስ ቁርባን
«ሥጋዬን የሚበላ ደሜንም የሚጠጣ የዘላለም ሕይወት አለው፤ እኔም በመጨረሻው ቀን እያስነሳዋለሁ።» (ዮሐ. 6፥54)
የተወደዳችሁ የግቢ ጉባኤያችን አባላት፤ ከጥቂት ቀናት በኋላ ሁላችንም በጋራ የምንካፈልበት የሕብረት ቅዱስ ቁርባን ቀን ይደርሳል። ቤተክርስቲያን ከምታከናውናቸው መንፈሳዊ ምስጢራት ሁሉ በላይ የሆነው፣ «የምስጢራት ሁሉ ማጽኛ ማኅተም» በመባል የሚታወቀው ምስጢረ ቁርባን የክርስትና ሕይወታችን ማዕከል እና ከእግዚአብሔር ጋር የምንዋሐድበት ታላቅ የጸጋ ድልድይ ነው። ወደዚህ አምላካዊ ማዕድ ከመቅረባችን በፊት ምስጢሩን ዘንድ የሚከተለውን ትምህርታዊ ማብራሪያ ተጋሩት፦ 1. የምስጢረ ቁርባን ትርጉምና አምላካዊ ጥበብ «ቁርባን» የሚለው ቃል የመጣው ከሱርስትና ከግሪክ ቋንቋ ሲሆን ትርጉሙ «መንፈሳዊ አምኃ (ስጦታ)፣ መባዕ፣ ወይም ለአምላክ የሚቀርብ መስዋዕት» ማለት ነው። ግብጻውያን ደግሞ «ዩክሪስት» ይሉታል፤ ይህም «የምስጋና መስዋዕት» ወይም «የጌታ እራት» ማለት ነው። በብሉይ ኪዳን ሰዎች ለአምላካቸው የበግ፣ የላምና የጊደር መስዋዕት ያቀርቡ ነበር። ለምሳሌ አባታችን አብርሃም ልጁን ይስሐቅን ለመሰዋት በወጣ ጊዜ ይስሐቅ «የመስዋዕቱ በግ ወዴት አለ?» ብሎ ሲጠይቅ፣ አብርሃም በመንፈስ ቅዱስ ተቃኝቶ «ልጄ ሆይ የመስዋዕቱን በግ እግዚአብሔር ያዘጋጃል» ብሎ ነበር (ዘፍ. 22፥7-8)። በሐዲስ ኪዳን ግን እግዚአብሔር ያዘጋጀው እውነተኛው የመስዋዕት በግ የዓለም መድኃኒት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው። የብሉይ መስዋዕት፦ ጊዜያዊ፣ በተደጋጋሚ የሚቀርብና እንስሳዊ ነበር። የሐዲስ ኪዳን ቁርባን፦ ከሰው ለእግዚአብሔር የቀረበ ሳይሆን፣ ከእግዚአብሔር ለሰው ልጅ የተሰጠ አምላካዊ ስጦታ ነው። ክርስቶስ ራሱ መስዋዕት፣ መስዋዕት አቅራቢ፣ እና መስዋዕት ተቀባይም ሆኖ አንድ ጊዜ ስለ ዓለም ሁሉ ቤዛ ሆኖ ቀርቧል። አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም እንደተናገረው፡
«ይህ ማዕድ በበግና በላም ደም እንደነበረው እንደ ቀደሙት አባቶች መስዋዕት አይደለም፤ እሳት ነው እንጂ! ፈቃዱን ለሚያደርጉ የሚያድን እሳት፣ ለዓመፀኞች ግን የሚበላ እሳት ነው።»
2. ምስጢረ ቁርባን በማን እና እንዴት ተመሠረተ? ምስጢረ ቁርባን የሰው ልጅ ፈጠራ ሳይሆን በራሱ በጌታችንና መድኃኒታችን በኢየሱስ ክርስቶስ የተመሠረተ አምላካዊ ሥርዓት ነው። ጌታችን ለሕማማትና ለሞት ከመሰጠቱ በፊት በሐሙስ ምሽት ከደቀመዛሙርቱ ጋር በነበረው እራት ላይ፦
«እንጀራውን አንስቶ ባረከ፤ ቆርሶም ለደቀመዛሙርቱ ሰጠና 'እንካችሁ ይህ ሥጋዬ ነው' አለ። ጽዋውንም አንስቶ አመስግኖ ሰጣቸው፤ 'ሁላችሁም ከእርሱ ጠጡ፤ ስለብዙዎች የኃጢአት ይቅርታ የሚፈስ የሐዲስ ኪዳን ደሜ ይህ ነው' አለ።» (ማቴ. 26፥26-28)
አይሁድና ደቀመዛሙርቱ በመጀመሪያ «ሥጋውን ልንበላ ይሰጠን ዘንድ እንዴት ይቻላል?» ብለው ቢጨነቁም፣ መንፈስ ቅዱስ ከወረደ በኋላ ግን የዚህን ምስጢር ሕይወት ሰጪነት ተረድተው በየአብያተ ክርስቲያናቱ ሲፈጽሙት ኖረዋል። 🔔 ጥሪ ለተቀደሰ ዝግጅት በንስሐ እንታጠብ፦ ወደ ንስሐ አባታችን በመሄድ የልባችንን በደል እንናዘዝ። ፍቅርን እንልበስ፦ ከወንድሞቻችንና እህቶቻችን ጋር ያለንን ቂም አስወግደን በይቅርታ እንታረቅ። ሕይወታችንን እንመርምር፦ የጌታን ሥጋና ደም ለመቀበል ልባችንን የማንኛውም አምላካዊ ጸጋ ማደሪያ አድርገን እንዘጋጅ። ከ10 ቀን በኋላ የሚጠብቀን የሕብረት ቁርባን ከጌታችን ጋር የምንዋሐድበት፣ የዘላለም ሕይወትን የምንወርስበትና መንፈሳዊ ማንነታችን የምናድስበት ልዩ ቀናችን ነው። አሁኑኑ ልባችንን በማዘጋጀት ለዚህ ታላቅ የጸጋ ማዕድ እንዘጋጅ! ዩኒቲ ግቢ ጉባኤ