EEP Communication
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication
تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 697 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 049 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 173 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 697 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 141، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 28.59%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.37% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 487 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 569 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“EEP Communication”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 03 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.
15 697
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+147 أيام
+14130 أيام
أرشيف المشاركات
15 697
ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን አከናውኗል
.....///…..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፉ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ማከናወኑን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ።
ዘርፉ በስሩ ከሚገኙ መምሪያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡
የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትን እና ያጋጠሙ ችግሮችን የጋራ በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለመስጠት ያለመ ነው።
በተጨማሪም መምሪያዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲያውቁ እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዘርፉ ሥር የሚገኙት የሕግ አገልግሎት፤ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ፣ የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
የተቋሙን ጥቅም ከመጠበቅና ከመከላከል፣ ከገጽታ ግንባታ፣ አሰራሮችን ፈትሾ ከማስተካከል፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ከማሳደግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቶቹ ተመልክቷል።
ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን በፈፀሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ባሻገር ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ምሰሶዎቹን ማህበረሰቡን በማሳተፍ በባለቤትነት እንዲጠብቃቸው ለማድረግ በቦርድ አቅጣጫ ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል።
ከግብዓትና ከሰው ኃይል እጥረት፣ ሥራዎችን ከማዘመን፣ ከአቅም ግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች እንደነበሩም ተነስቷል፡፡
አቶ ደጉማ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በመምሪያዎቹ የተከናወኑ ተግባራት ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
ሁሉም መምሪያዎች በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የበጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለባቸው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ግልፅ፣ አሳታፊና መተግበር የሚችል ዕቅድ በማዘጋጀት ለዘርፉ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን አከናውኗል
.....///…..
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፉ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ማከናወኑን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ።
ዘርፉ በስሩ ከሚገኙ መምሪያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡
የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትን እና ያጋጠሙ ችግሮችን የጋራ በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለመስጠት ያለመ ነው።
በተጨማሪም መምሪያዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲያውቁ እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡
በዘርፉ ሥር የሚገኙት የሕግ አገልግሎት፤ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ፣ የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል።
የተቋሙን ጥቅም ከመጠበቅና ከመከላከል፣ ከገጽታ ግንባታ፣ አሰራሮችን ፈትሾ ከማስተካከል፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ከማሳደግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቶቹ ተመልክቷል።
ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን በፈፀሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ባሻገር ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ምሰሶዎቹን ማህበረሰቡን በማሳተፍ በባለቤትነት እንዲጠብቃቸው ለማድረግ በቦርድ አቅጣጫ ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል።
ከግብዓትና ከሰው ኃይል እጥረት፣ ሥራዎችን ከማዘመን፣ ከአቅም ግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች እንደነበሩም ተነስቷል፡፡
አቶ ደጉማ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በመምሪያዎቹ የተከናወኑ ተግባራት ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል።
ሁሉም መምሪያዎች በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የበጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለባቸው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ግልፅ፣ አሳታፊና መተግበር የሚችል ዕቅድ በማዘጋጀት ለዘርፉ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች በእስራት ተቀጡ።
……////……
በደቡብ ወሎ ዞን በቃሉ ወረዳ 07 ቀዲዳ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀዲዳ በተባለ ቦታ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ታወር ብረት በመፍታት የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች የሰባት ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል።
ግለሰቦቹ ተገቢው ቅጣት ሊወሰንባቸው የቻለው በኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙኒኬሽን አውታር ላይ የስርቆትና ጉዳት ማድረስ ወንጀል በተፋጠነ የህግ ስነ-ስርአት አማካኝነት መሆኑን በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታውቋል።
ግለሰቦቹ በኃይል ማስተላለፊያው ላይ ባደረሱት የስርቆት ጉዳት በኮምቦልቻ፣ በደሴ ከተሞችና በ5 አጎራባች ወረዳዎች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቋረጥ ምክንያት ሆነዋል።
በተጨማሪም ከአቀስታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሃይል የሚያገኙ የምዕራብ ወሎ ወረዳዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥ በማድረግ በማህበረሰቡ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ገልጿል።
እነዚህ ግለሰቦች ኃይል እንዲቋረጥ ከማድረጋቸው ባሻገር 10 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ማድረሳቸውንም ነው ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ያስታወቀው።
የአቃቤ ህግን የሰነድና የሰው ማስረጃ እንዲሁም የተከሳሾችን የምስክር ቃል ተቀብሎ ሲመርምር የቆየው ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ጥፍተኛ በማለት ተከሳሾችን ያርማል ሌሎችንም ያስተምራል ያለውን የሰባት አመት ጽኑ እስራት በሁለቱ ተከሳሾች ላይ ወስኖባቸዋል።
መረጃውን ያገኘነው ከደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን ነው
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
የተሽከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪትን ለማዘመን የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ ነው
……////……
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሸከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪትን ለማዘመን የሚያስችሉ ተጨማሪ ሥራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ገለፀ።
ቢሮው የተሽከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪት ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ማከናወን የሚያስችል ሥልጠና ከተለያዩ የተቋሙ የሥራ ዘርፎችና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለተውጣጡ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እየሰጠ ይገኛል።
በተቋሙ የተሸከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ሥልጠናው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ላይ ተሻሽለው የቀረቡ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡
ከዚህ በፊት ተግባራዊ የተደረገው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ አንዳንድ ውስንነቶች እንደነበሩበት የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ወቅት ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒኤስ ሶፍትዌር አዳዲስ የአሰራር እና የቁጥጥር ሥርዓቶችን ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡
እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በነባሩ የጂ.ፒኤስ ሶፍትዌር የተቋሙ ተሸከርካሪዎች ለመስክ ሥራ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ ከተፈቀደላቸው የጉዞ መስመር ውጪ ቢጓዙ እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀማቸው ላይ ግልፅ የሆነ መረጃ ለማግኘት አስቸጋሪ ነበር፡፡
ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር የተሸከርካሪውን የጉዞ አቅጣጫና የፍጥነት ወሰን በመለየት እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀም ላይ አሃዛዊ መረጃዎችን በመሰብሰብ ሪፖርት እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል፡፡
ሶፍትዌሩ በአንድ አካባቢ ላይ ምን ያህል የተቋሙ ተሸከርካሪዎች እንዳሉ በካርታ በማስደገፍ መረጃዎችን ወደ ማዕከል እንደሚልክም ነው አቶ ዋለ የገለፁት፡፡
ይህም ከተሸከርካሪ ስምሪት፣ ቁጥጥር እና ነዳጅ አጠቃቀም እንዲሁም ስርቆት ጋር ተያይዘው ይነሱ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡
የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌሩ ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚያግዝ በመገንዘብ ሠልጣኞች ሥልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል፡፡
ሥልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የካሳ ሶፍዌር ትራኪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለሙያ አቶ መንበሩ ላቀው እንደተናገሩት ኩባንያው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ላለፉት ሦስት ዓመታት በጂ.ፒ.ኤስ ገጠማ እና ሶፍትዌር ሥልጠናዎች ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡
ተቋሙ ለተሸከርካሪዎቹ የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር መጠቀም መጀመሩ የአሰራር ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ወጪ ቆጣቢ የሆኑ ሥራዎችን ለማከናወን እንደሚረዳው ገልፀዋል፡፡
በሥልጠናው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞች በበኩላቸው ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር የተሽከርካሪዎችን ደህንነት በማስጠበቅና የሃበት ብክነትን በማስቀረት እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀምን በመቆጣጠር ረገድ የማይተካ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 8 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል አመንጭቷል
……..///….…
በግንባታ ላይ የሚገኘው የአሰላ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በከፊል ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ ለተቋሙ የኃይል ምርት መጨመር ምክንያት ሆኗል።
በፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ አቶ መስፍን መስቀሌ እንደገለፁት በግንባታ ላይ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግንቦት 6 ቀ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ኃይል ሲያመነጭ ቆይቷል።
በአሁኑ ወቅትም በፕሮጀክቱ ከተተከሉት 29 የንፋስ ተርባይኖች መካከል 10ሩ በተለያዩ ጊዜያት ከዋናው የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር ተገናኝተው ኃይል እያመነጩ ይገኛሉ። ይህም ፕሮጀክቱ ባለፉት ሁለት ወራት 8 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለተቋሙ ተጨማሪ የኃይል ምርት ማስገኘቱን ገልፀዋል።
ከፕሮጀክቱ የሚመነጨውን ኃይል ከመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ እና ከበቆጂ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በማጣመር ወደ ግሪዱ እንዲተላለፍ የሚከናወንበት የኦፕሬሽን ሂደት ቀድመው ከተገነቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ልዩ እንደሚያደርገው የተናገሩት አቶ መስፍን የየኦፕሬሽን ሥራውን በቀላሉ ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ዘመናዊ የዲጂታል መሳሪያዎች የተገጠሙለት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል።
በፕሮጀክቱ የሱፐርቪዥን ቴክኒሺያን የሆኑት አቶ መንግስቱ ድሌ በበኩላቸው የተርባይን ተከላና የኬብል ዝርጋታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል።
በአሁኑ ወቅትም የተርባይኖች የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ኃይል ለማመንጨት ዝግጁ መሆናቸውን በፍተሻና ሙከራ በማረጋገጥ ተርባይኖቹን በሂደት ወደ ኦፕሬሽን የማስገባቱ ሥራ እየተከናወነ ነው ብለዋል።
በዚህም እስከ አሁን 10 ተርባይኖችን በከግሪድ ጋር ማገናኘት የተቻለ ሲሆን በቀጣይ የሙከራና የፍተሻ ሥራዎችን በጥንቃቄ በማከናወን በየቀኑ አንድ ተርባይን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባታ ታቅዶ እየተሰራ ነው።
ቀሪ ተርባይኖችን በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ሥራ ተቋራጩ ተጨማሪ ባለሙያዎችን ከመመደብ ጀምሮ በፕሮጀክቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አካላት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ ነው ያሉት።
የሙከራና የፍተሻ ሥራቸው የተጠናቀቁ ተርባይኖች በሂደት ተራ በተራ ቀድመው ኃይል ወደ ማመንጨት ሥራ እንዲገቡ መደረጉ ያለውን የንፍስ ኃይል በመጠቀም ሲስተሙን ለመደገፍ እና የግሪዱን አቅም ለማረጋጋት እንደሚያግዝም የሥራ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል።
ሁሉም የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ሲጀምሩ ሀገሪቱ ከንፋስ የምታገኘውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 544 ሜጋ ዋት ከፍ በማድረግ የኃይል ስብጥሩን ለማመጣጠን ያግዛል ተብሎ ይጠበቃል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
የዘርፉን የፋይናንስ እና ግዥ የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል እንደሚሰራ ተገለፀ
…….///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የፋይናንስ እና ግዥ ሥርዓቱን ለማሻሻል እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡
የዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በ2017 በጀት ዓመት የፋይናንስ እና ግዥ አፈፃፀም እንዲሁም በ2018 ዕቅድ ዙሪያ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡
ውይይቱ የተካሔደው ተቋሙ ሁሉም የሥራ ዘርፎች እስከ በጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ድረስ የፋይናንስ ሥራቸውን አጠናቀው ሪፖርት እንዲያደርጉ ያስቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ነው።
መድረኩ የዘርፉ የፋይናንስና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በቀሩት ጥቂት ቀናት ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ሥራዎቻቸውን እንዲያጠናቅቁ ለማድረግ ያለመ ነው።
በዘርፉ የፋይናንስና ግዥ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለፁት የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በ2017 በጀት ዓመት በርካታ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን ቆይቷል።
መምሪያው የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት በፋይናንስና ግዥ የአሰራር ሥርዓት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በማረም ቀሪ ሒሳቦችን ለመዝጋት እየሰራ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት።
እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ዘርፉ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ላይ ያለውን የፋይናንስ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓትና ቅልጥፍና ማዘመን ይገባል።
በ2018 በጀት ዓመት የዘርፉን የፋይናንስና ግዥ ሥራዎች ቅንጅታዊ የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ለመተግበር መታቀዱን አቶ ሙሉቀን ገልፀዋል።
በበጀት ዓመቱ የዘርፉ የፋይናንስ አፈፃፀም ላይ ውይይት መደረጉና የጋራ መግባባት ላይ መደረሱ ለተሻለ የሥራ አፈፃፀም የሚያነሳሳ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በ2018 በጀት ዓመት የዘርፉን ውጤታማነት ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎችን ለማከናወን ከወዲሁ መዘጋጀታቸውንም ነው ያብራሩት።
በቀሪዎቹ ቀናት ተቋሙ ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የዘርፉ የፋይናንስ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
🌊 የኢትዮጵያ ኩራት የሆኑት ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በከፊል | Ethiopia's Mega Dams 🇪🇹
ከዓለም መነጋገሪያ ከሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጀምሮ ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በከፊል የሚያስቃኝ ይህን አስደናቂ ቪዲዮ ይመልከቱ።
✅ የህዳሴ ግድብ
✅ የተከዜ ግድብ
✅ ጊቤ I, II, III
✅ ገናሌ ዳዋ III
... እና ሌሎችንም ያገኙበታል።
ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ፦
👇👇👇
https://youtu.be/fdVtEERmeTY
ቻናላችንን ሰብስክራይብ (Subscribe) በማድረግ ተጨማሪ ጠቃሚ መረጃዎችን ያግኙ!
🔔 Subscribe Now 🔔
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
#PM
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ (ዶ/ር) ስለ ኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ለፓርላማ አባላት ከተናገሩት
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
~ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካነሱት ሀሳብ የተወሰደ
👉🏽 በአፍሪካ በኢነርጂ ሴክተር ላይ ከኢትዮጵያ የተሻለ የተንቀሳቀሰ ሀገር የለም፡፡
👉🏽 ኢትዮጵያ ውስጥ የሚነጨው ኢነርጂ ለሁሉም የጎረቤት ሀገራት የሚዳረስ ነው፡፡
👉🏽 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ለታችኛው የተፋሰሱ ሀገራት በረከት ነው፡፡
👉🏽 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመገንባቱ የአስዋን ግድብ አንድ ሊትር ውሃ እንኳ አልቀነሰም፡፡
👉🏽 የኢትዮጵያን ኢነርጂ በትብብር በመጠቀም በጋራ ልማት መፍጠር ይቻላል፡፡
👉🏽 ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ በመጪው መስከረም ወር ሲመረቅ ግብፅ፣ ሱዳን እና ሌሎች የተፋሰሱ ሀገራት የደስታችን ተካፋይ እንዲሆኑ ጥሪ እናቀርብላቸዋለን፡፡
👉🏽 የጊቤ 3 የኃይል ማመንጫ ሲገነባ የቱርካና ሀይቅ ይደርቃል በሚል ስጋት ከፍተኛ ተቃውሞ ሲቀርብ የነበረ ቢሆንም ግድቡ ከተጠናቀቀ በኋላ ሀይቁ እንኳን ሊደርቅ ቀርቶ ከመጠን በላይ ሞልቶ እያስቸገረ ያለበት ሁኔታ ተፈጥሯል፡፡
👉🏽 ኮይሻ፣ አይሻ፣ አሰላ እና አሉቶ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ግንባታቸው በመፋጠን ላይ ይገኛል፡፡
👉🏽 አይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ከሌላ ሀገር በተገኘ ብድር ሲገነባ ቢቆይም የብድር አቅርቦቱ በመቋረጡ ምክንያት በራስ የፋይናንስ አቅም ለመጨረስ እየተሰራ ነው፡፡
👉🏽 በ2018 ዓ.ም ከኮይሻ የኃይል ማመንጫ በስተቀር የአይሻ፣ አሰላና ሌሎች የኃይል ማመንጫዎች ይጠናቀቃሉ፡፡
👉🏽 በ2017 በጀት ዓመት የኤሌክትሪክ ሽያጭ 136 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡
👉🏽 በዓመቱ የኃይል አቅርቦት በከፍተኛ ሁኔታ እያደገ በመምጣቱ በሀገር ውስጥ ኢንዱስትሪዎች እና በውጭ የኃይል ሽያጭ ላይ ከፍተኛ ዕድገት ታይቷል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
+3
👉🏽 ኢትዮጵያ በአፍሪካ ማንም ሀገር ባላደረገው መጠን የኃይል ማመንጫ ላይ እየሰራች ነው።
👉🏽 በዚህ ዓመት ብቻ የኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት በ 40 በመቶ አድጓል።
👉🏽 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የአሰላ እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በሚቀጥለው ዓመት ይመረቃሉ።
👉🏽 አሁን ላይ ለኢነርጂ አስር ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ኢንቨስትመንት እያደረግን ነው፡፡
~~~ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካነሱት የተወሰደ
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
