uz
Feedback
EEP Communication

EEP Communication

Kanalga Telegram’da o‘tish

EEP Communication

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali EEP Communication analitikasi

EEP Communication (@eepcommuication) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 15 696 obunachidan iborat bo'lib, Texnologiyalar & Aralashmalar toifasida 8 049-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 2 173-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 15 696 obunachiga ega bo‘ldi.

02 Sentabr, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni 141 ga, so‘nggi 24 soatda esa 0 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlanmagan
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 28.59% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 16.37% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 4 487 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 2 569 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 10 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
EEP Communication

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 03 Sentabr, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Texnologiyalar & Aralashmalar toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

15 696
Obunachilar
Ma'lumot yo'q24 soatlar
+147 kun
+14130 kun
Postlar arxiv
photo content
+7

ተቋሙ ከ7 ሺ በላይ ለሚሆኑ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት ሰጥቷል፤ ….///…. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል መካከለኛ ክሊኒክ በ2017 በጀት ዓመት 7 ሺ 330 ለሚሆኑ የተቋሙ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች የህክምና አገልግሎት መስጠቱን የተቋሙ የጤና አገልግሎት ቢሮ አስታወቀ፡፡ የቢሮው ረዳት ሥራ አስኪያጅ አቶ አድማሱ ተኽልቁ እንደገለጹት የተቋሙን የሥራ መሪዎችና ሠራተኞችን ጤንነት ለማስጠበቅ ከበሽታ መከላከልና ህክምና አገልግሎት ጋር የተያያዙ ሥራዎችን በጀት ዓመቱ አከናውኗል፡፡ በበጀት ዓመቱ በክሊኒኩ 5 ሺ 132 ወንድ እና 2 ሺ 198 ሴት ሠራተኞች የህክምና አገልግሎቱን ማግኘታቸውን እና ከእነዚህም ውስጥ በላቦራቶሪ አገልግሎት 2 ሺ 485 ያህል ወንድ እና ሴት ሠራተኞች መስተናገዳቸውን አስታውቀዋል፡፡ ተቋሙ በ2017 በጀት ዓመት ግልጽ ጨረታ በማውጣትና በማወዳደር ከ 21 የህክምና ተቋሞች ጋር አዲሰ የህክምና አገልግሎት ሰምምነት በመፈራረም ከክሊኒኩ በላይ የሆኑ የጤና ችግሮች ሲያጋጥሙ ሠራተኛኞች ተልከው እንዲገለገሉ መደረጉን አስረድተዋል። በዚህም ከክሊኒኩ አቅም በላይ የሆኑ 5 ሺ 825 ሠራተኞች ወደ ተለያዩ የህክምና ተቋማት መላካቸውን እና 7 ሺ 56 ሠራተኞች ደግሞ በከነማ ፋርማሲ አገልግሎት ማግኘታቸውን ገልፀዋል። ለታላቁ ህዳሴ ግድብ ፕሮጀክት የክሊኒክ መድኃኒቶችን ከመድኃኒት ፈንድ ኤጀንሲ ግዥ በማከናወን እና ቦታው ድረስ በመሄድ የባለሙያ ድጋፍ መደረጉን የጠቆሙት አቶ አድማሱ ለወላይታ ሶዶ ቁጥር 1 እና 2 ኮንቨርተር ማከፋፈያ ጣቢያዎች የወባ መከላከል እና መቆጣጠር የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናና ህክምና መሰጠቱን ተናግረዋል፡፡ ኃላፊው አክለውም በዋናው መ/ቤት ክሊኒክ የመድኃኒት መጋዘን ውስጥ የተቀመጡ መድኃኒቶች የመጠቀሚያ ጊዚያቸው ሳያልፍ ለኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች እንዲከፋፈል ተደርጓል ብለዋል፡፡ በሰሜን ሪጅን ለስምንት እንዲሁም በምሰራቅ 2 ሪጅን ለአምስት ማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች በአቅራቢያቸው ከሚገኙ የጤና ተቋማት ጋር ስምምነት በመፍጠር የህክምና አገልግሎት እንዲያገኙ ማድረግ መቻሉን አስገንዝበዋል፡፡ እንደ አቶ አድማሱ ገለፃ በበጀት ለአጠቃላይ ህክምና ከ68 ሚሊዮን ብር በላይ ወጪ የተደረገ መሆኑን አስታውቀዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 4 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

የኃይል ተደራሽነትን የሚያጎለብቱ ሥራዎች ማከናወኑን ሪጅኑ ገለፀ ‎.....///….. የኃይል ተደራሽነትን ይበልጥ የሚያጎለብቱ የሲቪል እና የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎች ማከናወኑን የሰሜን ምስራቅ ሪጅን አስታወቀ፡፡ የሪጅኑ ዳይሬክተር አቶ በድሩ አህመድ እንደተናገሩት በሪጅኑ ውስጥ ለሚገኙ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች እና ማስተላለፊያ መስመሮች የማስፋፊያ፣የአቅም ማሳደግና የጥገና ሥራዎች ተከናውኗል፡፡ የከሚሴ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ አቅምን ለማሳደግ 50 ኤም ቪ ኤ ፓወር ትራንስፎርመር ተከላ እንዲሁም በኮምቦልቻ 2 እና በጋሸና ማከፋፈያ ጣቢያዎች የጂ አይ ኤስ ገጠማ ሥራ የተከናወነ መሆኑንም ነው ዳይሬክተሩ ያስታወቁት፡፡ የኃይል መቋረጥን ከመቀነስ አንፃር በስርቆት እና በተለያዩ ምክንያቶች ጉዳት የደረሰባቸውን ከ13 በላይ የኃይል ማስተላለፊያ ምሶሶዎች (ታዎሮች) ጥገና በማከናወን ወደ አገልግሎት እንዲመለሱ ማድረግ ተችሏል፡፡ አቶ በድሩ እንደገለፁት በአራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የሠራተኞች መኖሪያ ቤት፣ የጥበቃ ማማ እና የስቶር ግንባታ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው፡፡ የስራ ከባቢን ለሠራተኞች ምቹ ከማድረግ አንፃር ከፍተኛ የውሃ ችግር የነበረባቸው አራት የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ውሃ እንዲያገኙ ተደርጓል፡፡ የመፈፀም አቅምን ለማጎልበት የሚረዱ በመሰረታዊ ኮምፒውተር፣ በዘመናዊ የአሰራር ስርዓት እና የስራ ደህንነት ላይ ያተኮረ ስልጠና ለ143 ሠራተኞች ተሰጥቷል፡፡ የሰሜን ምስራቅ ሪጅን በአጠቃላይ ስምንት ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች በስሩ ይገኛሉ፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+3

ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን አከናውኗል ‎.....///….. ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፉ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ማከናወኑን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ‎ ‎ዘርፉ በስሩ ከሚገኙ መምሪያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ ‎ ‎የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትን እና ያጋጠሙ ችግሮችን የጋራ በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለመስጠት ያለመ ነው። ‎ ‎በተጨማሪም መምሪያዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲያውቁ እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ‎ ‎በዘርፉ ሥር የሚገኙት የሕግ አገልግሎት፤ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ፣ የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። ‎ የተቋሙን ጥቅም ከመጠበቅና ከመከላከል፣ ከገጽታ ግንባታ፣ አሰራሮችን ፈትሾ ከማስተካከል፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ከማሳደግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቶቹ ተመልክቷል። ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን በፈፀሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ባሻገር ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ምሰሶዎቹን ማህበረሰቡን በማሳተፍ በባለቤትነት እንዲጠብቃቸው ለማድረግ በቦርድ አቅጣጫ ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል። ‎ከግብዓትና ከሰው ኃይል እጥረት፣ ሥራዎችን ከማዘመን፣ ከአቅም ግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች እንደነበሩም ተነስቷል፡፡ ‌‎አቶ ደጉማ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በመምሪያዎቹ የተከናወኑ ተግባራት ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። ሁሉም መምሪያዎች በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የበጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለባቸው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ግልፅ፣ አሳታፊና መተግበር የሚችል ዕቅድ በማዘጋጀት ለዘርፉ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content

photo content
+9

ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን አከናውኗል ‎.....///….. ‎በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፉ በ2017 በጀት ዓመት ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ማከናወኑን የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አስታወቁ። ‎ ‎ዘርፉ በስሩ ከሚገኙ መምሪያዎች ጋር የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸምን ገምግሟል፡፡ ‎ ‎የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ዱጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው ዘርፉ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በበጀት ዓመቱ ያከናወኗቸውን ዋና ዋና ተግባራትን እና ያጋጠሙ ችግሮችን የጋራ በማድረግ ቀጣይ የትኩረት አቅጣጫዎችን ለመስጠት ያለመ ነው። ‎ ‎በተጨማሪም መምሪያዎቹ ያሉበትን ደረጃ እንዲያውቁ እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎችን ለማበረታታት የሚያግዝ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ ‎ ‎በዘርፉ ሥር የሚገኙት የሕግ አገልግሎት፤ የሥነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ፣ የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ እንዲሁም የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን መምሪያዎች የበጀት ዓመቱን ዕቅድ አፈጻጸማቸውን በዝርዝር አቅርበው ውይይት ተደርጎበታል። ‎ የተቋሙን ጥቅም ከመጠበቅና ከመከላከል፣ ከገጽታ ግንባታ፣ አሰራሮችን ፈትሾ ከማስተካከል፣ የሴቶችን ተሳትፎና ተጠቃሚነት ከማሳደግ፣ ብልሹ አሰራርን ከመከላከልና ከመቆጣጠር እንዲሁም ቅንጅታዊ አሰራርን ከማሳደግ አንጻር የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡ በሪፖርቶቹ ተመልክቷል። ከፍተኛ የኃይል ማስተላለፊያ ተሸካሚ የብረት ምሰሶ ስርቆትን በፈፀሙ አካላት ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንዲወሰድ ከማድረግ ባሻገር ችግሩን በዘላቂነት ለመከላከል የብረት ምሰሶዎቹን ማህበረሰቡን በማሳተፍ በባለቤትነት እንዲጠብቃቸው ለማድረግ በቦርድ አቅጣጫ ተሰጥቶ ተግባራዊ እንቅስቃሴ መጀመሩም ተገልጿል። ‎ከግብዓትና ከሰው ኃይል እጥረት፣ ሥራዎችን ከማዘመን፣ ከአቅም ግንባታ ሥራዎች ጋር በተያያዘ በበጀት ዓመቱ ያጋጠሙ ክፍተቶች እንደነበሩም ተነስቷል፡፡ ‌‎አቶ ደጉማ በሰጡት የማጠቃለያ ሀሳብ በመምሪያዎቹ የተከናወኑ ተግባራት ዘርፉ በበጀት ዓመቱ ተቋማዊ ለውጡን በሚያሳካ መልኩ ሥራዎችን ሲያከናውን መቆየቱን የሚያሳዩ ናቸው ብለዋል። ሁሉም መምሪያዎች በዕቅድ አፈፃፀሙ የታዩ ክፍተቶችን በማረም በቀጣይ የበጀት ዓመት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ መስራት አለባቸው ያሉት ሥራ አስፈፃሚው የተቋሙን ስትራቴጅክ ዕቅድ ለማሳካት የሚያስችል ግልፅ፣ አሳታፊና መተግበር የሚችል ዕቅድ በማዘጋጀት ለዘርፉ እንዲያቀርቡ አሳስበዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 3 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

photo content

በኤሌክትሪክ መሰረተ ልማት ላይ የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች  በእስራት ተቀጡ። ‎……////…… በደቡብ ወሎ ዞን ‎በቃሉ ወረዳ 07 ቀዲዳ ቀበሌ ልዩ ቦታው ቀዲዳ በተባለ ቦታ 132 ኪሎ ቮልት የኤሌክትሪክ ታወር ብረት በመፍታት የስርቆት ወንጀል የፈፀሙ ግለሰቦች የሰባት ዓመት ፅኑ እስራት ተፈርዶባቸዋል። ግለሰቦቹ ተገቢው ቅጣት ሊወሰንባቸው የቻለው በኤሌክትሪክ አገልግሎት ኮሙኒኬሽን አውታር ላይ የስርቆትና ጉዳት ማድረስ ወንጀል በተፋጠነ የህግ ስነ-ስርአት አማካኝነት መሆኑን  በአማራ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ጠቅላይ ፍርድ ቤት የደሴ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት አስታውቋል። ግለሰቦቹ በኃይል ማስተላለፊያው ላይ ባደረሱት የስርቆት ጉዳት በኮምቦልቻ፣ በደሴ ከተሞችና በ5 አጎራባች ወረዳዎች የኤሌክትሪክ ኃይል እንዲቋረጥ ምክንያት ሆነዋል። በተጨማሪም ከአቀስታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ሃይል የሚያገኙ የምዕራብ ወሎ ወረዳዎች የኤሌክትሪክ አገልግሎት እንዲቋረጥ በማድረግ በማህበረሰቡ ላይ ጉዳት ማድረሳቸውን ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ገልጿል። እነዚህ ግለሰቦች ኃይል እንዲቋረጥ ከማድረጋቸው ባሻገር 10 ነጥብ 5 ሚሊዮን ብር የሚገመት የንብረት ጉዳት ማድረሳቸውንም ነው ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ያስታወቀው። የአቃቤ ህግን የሰነድና የሰው ማስረጃ እንዲሁም የተከሳሾችን የምስክር ቃል ተቀብሎ ሲመርምር የቆየው ጠቅላይ ፍ/ቤቱ ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም በዋለው ችሎት ጥፍተኛ በማለት ተከሳሾችን ያርማል ሌሎችንም  ያስተምራል ያለውን የሰባት አመት ጽኑ እስራት  በሁለቱ ተከሳሾች ላይ ወስኖባቸዋል። መረጃውን ያገኘነው ከደቡብ ወሎ ኮሙኒኬሽን ነው 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+4

የተሽከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪትን ለማዘመን የሚያስችሉ ሥራዎች እየተሰሩ ነው ……////…… የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሸከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪትን ለማዘመን የሚያስችሉ ተጨማሪ ሥራዎች እያከናወነ እንደሚገኝ በተቋሙ የተሽከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ገለፀ። ቢሮው የተሽከርካሪ ቁጥጥር እና ስምሪት ሥራዎችን በዘመናዊ ቴክኖሎጂ በመታገዝ ማከናወን የሚያስችል ሥልጠና ከተለያዩ የተቋሙ የሥራ ዘርፎችና የኃይል ማመንጫ ጣቢያዎች ለተውጣጡ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች እየሰጠ ይገኛል። በተቋሙ የተሸከርካሪ አስተዳደር ቢሮ ሥራ አስኪያጅ አቶ ዋለ ታምሬ እንደገለፁት ሥልጠናው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ ላይ ተሻሽለው የቀረቡ ዘመናዊ የአሰራር ሥርዓቶችን ተግባራዊ ለማድረግ ያለመ ነው፡፡ ከዚህ በፊት ተግባራዊ የተደረገው የጂ.ፒ.ኤስ ቴክኖሎጂ አንዳንድ ውስንነቶች እንደነበሩበት የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ በአሁኑ ወቅት ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒኤስ ሶፍትዌር አዳዲስ የአሰራር እና የቁጥጥር ሥርዓቶችን ይዞ መምጣቱን ተናግረዋል፡፡ እንደ አቶ ዋለ ገለፃ በነባሩ የጂ.ፒኤስ ሶፍትዌር የተቋሙ ተሸከርካሪዎች ለመስክ ሥራ ወደ ተለያዩ አካባቢዎች ሲንቀሳቀሱ ከተፈቀደላቸው የጉዞ መስመር ውጪ ቢጓዙ እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀማቸው ላይ ግልፅ የሆነ መረጃ ለማግኘት አስቸጋሪ ነበር፡፡ ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር የተሸከርካሪውን የጉዞ አቅጣጫና የፍጥነት ወሰን በመለየት እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀም ላይ አሃዛዊ መረጃዎችን በመሰብሰብ ሪፖርት እንደሚያደርግ ጠቅሰዋል፡፡ ሶፍትዌሩ በአንድ አካባቢ ላይ ምን ያህል የተቋሙ ተሸከርካሪዎች እንዳሉ በካርታ በማስደገፍ መረጃዎችን ወደ ማዕከል እንደሚልክም ነው አቶ ዋለ የገለፁት፡፡ ይህም ከተሸከርካሪ ስምሪት፣ ቁጥጥር እና ነዳጅ አጠቃቀም እንዲሁም ስርቆት ጋር ተያይዘው ይነሱ የነበሩ ችግሮችን ለመቅረፍ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል፡፡ የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌሩ ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚያግዝ በመገንዘብ ሠልጣኞች ሥልጠናውን በአግባቡ በመከታተል ለተግባራዊነቱ የበኩላቸውን ሚና መወጣት እንደሚጠበቅባቸውም ሥራ አስኪያጁ አሳስበዋል፡፡ ሥልጠናውን እየሰጡ የሚገኙት የካሳ ሶፍዌር ትራኪንግ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ኩባንያ ባለሙያ አቶ መንበሩ ላቀው እንደተናገሩት ኩባንያው ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ጋር ላለፉት ሦስት ዓመታት በጂ.ፒ.ኤስ ገጠማ እና ሶፍትዌር ሥልጠናዎች ላይ እየሰራ ይገኛል፡፡ ተቋሙ ለተሸከርካሪዎቹ የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር መጠቀም መጀመሩ የአሰራር ሥርዓቱን በቴክኖሎጂ የታገዘ በማድረግ ወጪ ቆጣቢ የሆኑ ሥራዎችን ለማከናወን እንደሚረዳው ገልፀዋል፡፡ በሥልጠናው ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሠራተኞች በበኩላቸው ተሻሽሎ የቀረበው የጂ.ፒ.ኤስ ሶፍትዌር የተሽከርካሪዎችን ደህንነት በማስጠበቅና የሃበት ብክነትን በማስቀረት እንዲሁም የነዳጅ አጠቃቀምን በመቆጣጠር ረገድ የማይተካ ሚና ይጫወታል ብለዋል፡፡ 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 2 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+9

የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ 8 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት ኃይል አመንጭቷል ……..///….… በግንባታ ላይ የሚገኘው የአሰላ የነፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት በከፊል ኃይል ማመንጨት በመጀመሩ ለተቋሙ የኃይል ምርት መጨመር ምክንያት ሆኗል። በፕሮጀክቱ የኦፕሬሽን ክፍል ኃላፊ አቶ መስፍን መስቀሌ እንደገለፁት በግንባታ ላይ የሚገኘው የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ከግንቦት 6 ቀ 2017 ዓ.ም ጀምሮ በከፊል ኃይል ሲያመነጭ ቆይቷል። በአሁኑ ወቅትም በፕሮጀክቱ ከተተከሉት 29 የንፋስ ተርባይኖች መካከል 10ሩ በተለያዩ ጊዜያት ከዋናው የኃይል ቋት (ግሪድ) ጋር ተገናኝተው ኃይል እያመነጩ ይገኛሉ። ይህም ፕሮጀክቱ ባለፉት ሁለት ወራት  8 ነጥብ 9 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል በማመንጨት ለተቋሙ ተጨማሪ የኃይል ምርት ማስገኘቱን ገልፀዋል። ከፕሮጀክቱ የሚመነጨውን ኃይል ከመልካ ዋከና ኃይል ማመንጫ እና ከበቆጂ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ጋር በማጣመር ወደ ግሪዱ እንዲተላለፍ የሚከናወንበት የኦፕሬሽን ሂደት ቀድመው ከተገነቡ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶች ልዩ እንደሚያደርገው የተናገሩት አቶ መስፍን የየኦፕሬሽን ሥራውን በቀላሉ ለመቆጣጠር የሚያስችሉ ዘመናዊ የዲጂታል መሳሪያዎች የተገጠሙለት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመዋል። በፕሮጀክቱ የሱፐርቪዥን ቴክኒሺያን የሆኑት አቶ መንግስቱ ድሌ በበኩላቸው የተርባይን ተከላና የኬብል ዝርጋታ ሥራዎች ሙሉ በሙሉ መጠናቀቃቸውን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅትም የተርባይኖች የኤሌክትሮ ሜካኒካል ዕቃዎች ኃይል ለማመንጨት ዝግጁ መሆናቸውን  በፍተሻና ሙከራ በማረጋገጥ ተርባይኖቹን በሂደት  ወደ ኦፕሬሽን የማስገባቱ ሥራ  እየተከናወነ ነው ብለዋል። በዚህም እስከ አሁን 10 ተርባይኖችን በከግሪድ ጋር ማገናኘት የተቻለ ሲሆን በቀጣይ የሙከራና የፍተሻ ሥራዎችን በጥንቃቄ በማከናወን በየቀኑ አንድ ተርባይን ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባታ ታቅዶ እየተሰራ ነው። ቀሪ ተርባይኖችን በቀጣዩ አንድ ወር ውስጥ ወደ ኦፕሬሽን ለማስገባት ሥራ ተቋራጩ ተጨማሪ ባለሙያዎችን ከመመደብ ጀምሮ በፕሮጀክቱ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ አካላት በቅንጅት እየሰሩ ይገኛሉ ነው ያሉት። የሙከራና የፍተሻ ሥራቸው የተጠናቀቁ ተርባይኖች በሂደት ተራ በተራ ቀድመው ኃይል ወደ ማመንጨት ሥራ እንዲገቡ መደረጉ ያለውን የንፍስ ኃይል በመጠቀም ሲስተሙን ለመደገፍ እና የግሪዱን አቅም ለማረጋጋት እንደሚያግዝም የሥራ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል። ሁሉም የአሰላ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ሲጀምሩ ሀገሪቱ ከንፋስ የምታገኘውን የኤሌክትሪክ ኃይል ወደ 544 ሜጋ ዋት ከፍ በማድረግ የኃይል ስብጥሩን ለማመጣጠን ያግዛል ተብሎ ይጠበቃል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሐምሌ 01 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

የዘርፉን የፋይናንስ እና ግዥ የአሰራር ሥርዓት ለማሻሻል እንደሚሰራ ተገለፀ …….///…….. የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ የፋይናንስ እና ግዥ ሥርዓቱን ለማሻሻል እንደሚሰራ አስታወቀ፡፡ የዘርፉ የፋይናንስ እና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በ2017 በጀት ዓመት የፋይናንስ እና ግዥ አፈፃፀም እንዲሁም በ2018 ዕቅድ ዙሪያ ላይ ውይይት አካሂደዋል፡፡ ውይይቱ የተካሔደው ተቋሙ ሁሉም የሥራ ዘርፎች እስከ በጀት ዓመቱ ማጠናቀቂያ ድረስ የፋይናንስ ሥራቸውን አጠናቀው ሪፖርት እንዲያደርጉ ያስቀመጠውን አቅጣጫ ተከትሎ ነው። መድረኩ የዘርፉ የፋይናንስና ግዥ መምሪያ የሥራ ኃላፊዎች እና ሠራተኞች በቀሩት ጥቂት ቀናት ፈጣን የማስተካከያ እርምጃዎችን በመውሰድ ሥራዎቻቸውን እንዲያጠናቅቁ ለማድረግ ያለመ ነው። በዘርፉ የፋይናንስና ግዥ መምሪያ ዳይሬክተር አቶ ሙሉቀን ዮሴፍ በውይይት መድረኩ ላይ እንደገለፁት የኢንጅነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፍ በ2017 በጀት ዓመት በርካታ ፕሮጀክቶችን ሲያከናውን ቆይቷል። መምሪያው የበጀት ዓመቱ ከመጠናቀቁ በፊት በፋይናንስና ግዥ የአሰራር ሥርዓት ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በማረም ቀሪ ሒሳቦችን ለመዝጋት እየሰራ እንደሚገኝም ነው የተናገሩት። እንደ ዳይሬክተሩ ገለፃ ዘርፉ በሚያከናውናቸው ፕሮጀክቶች ላይ ያለውን የፋይናንስ የመረጃ ልውውጥ ሥርዓትና ቅልጥፍና ማዘመን ይገባል። በ2018 በጀት ዓመት የዘርፉን የፋይናንስና ግዥ ሥራዎች ቅንጅታዊ የአሰራር ሥርዓቶችን በመዘርጋት ለመተግበር መታቀዱን አቶ ሙሉቀን ገልፀዋል። በበጀት ዓመቱ የዘርፉ የፋይናንስ አፈፃፀም ላይ ውይይት መደረጉና የጋራ መግባባት ላይ መደረሱ ለተሻለ የሥራ አፈፃፀም የሚያነሳሳ መሆኑን የጠቆሙት ዳይሬክተሩ በ2018 በጀት ዓመት የዘርፉን ውጤታማነት ከፍ የሚያደርጉ ሥራዎችን ለማከናወን ከወዲሁ መዘጋጀታቸውንም ነው ያብራሩት። በቀሪዎቹ ቀናት ተቋሙ ያስቀመጣቸውን አቅጣጫዎች ተግባራዊ ለማድረግ ሁሉም የዘርፉ የፋይናንስ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ርብርብ ማድረግ እንደሚጠበቅባቸው አሳስበዋል። 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም

photo content
+5

🌊 የኢትዮጵያ ኩራት የሆኑት ግዙፍ የኃይል ማመንጫ ግድቦች በከፊል | Ethiopia's Mega Dams 🇪🇹 ከዓለም መነጋገሪያ ከሆነው ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብ ጀምሮ ሌሎች ግዙፍ ፕሮጀክቶችን በከፊል የሚያስቃኝ ይህን አስደናቂ ቪዲዮ ይመልከቱ። ✅ የህዳሴ ግድብ ✅ የተከዜ ግድብ ✅ ጊቤ I, II, III ✅ ገናሌ ዳዋ III ... እና ሌሎችንም ያገኙበታል። ሙሉውን ቪዲዮ ለመመልከት ከታች ያለውን ሊንክ ይጫኑ፦ 👇👇👇 https://youtu.be/fdVtEERmeTY ቻናላችንን ሰብስክራይብ (Subscribe) በማድረግ ተጨማሪ ጠቃሚ መረጃዎችን ያግኙ! 🔔 Subscribe Now 🔔 💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!” 📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric 📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication 📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia 📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power 📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia 📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power 📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et ሰኔ 28 ቀን 2017 ዓ.ም