EEP Communication
前往频道在 Telegram
📈 Telegram 频道 EEP Communication 的分析概览
频道 EEP Communication (@eepcommuication) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 15 559 名订阅者,在 技术与应用 类别中位列第 8 384,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 2 165 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 15 559 名订阅者。
根据 23 六月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 0,过去 24 小时变化为 -2,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 未认证
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 25.89%。内容发布后 24 小时内通常能获得 15.48% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 4 026 次浏览,首日通常累积 2 408 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 9。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“EEP Communication”
凭借高频更新(最新数据采集于 24 六月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 技术与应用 类别中的关键影响点。
15 559
订阅者
-224 小时
-37 天
无数据30 天
帖子存档
15 570
ጣቢያው የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጣ ነው
………///…….
በኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ወደስራ ያስገባቸው አዳዲስ የቴክኖሎጂ ውጤቶች የኃይል አቅርቦትን በማሻሻል የላቀ ድርሻ እየተወጡ መሆኑን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ።
ሥራ አስኪያጁ አቶ ጥላሁን አዘዘው እንደገለፁት ጣቢያው ለአካባቢው ማህበረሰብ እና በኢንቨስትመንት ዘርፍ ለተሰማሩ በርካታ አምራች ድርጅቶች የተሟላ ኃይል በማቅረብ ላይ ይገኛል፡፡
የጥገና ባለሙያ ተዳቻ ገናሌ በበኩላቸው ጣቢያው የተገጠመለት ጂ አይ ኤስ መቆጣጠሪያ እና ሌሎች የቴክኖሎጂ ውጤቶች ጣቢያው ኃይል ሳይቆራረጥ ደንበኞች ጋር ለማድረስ ከፍተኛ ድርሻ እንዳላቸው ተናግረዋል።
የኃይል መቋረጥ በሚከሰትበት ወቅት በቀላሉ ችግር የደረሰበትን መስመር እና የችግሩን ዓይነት እንዲሁም የችግሩን መጠን በመለየት የተሳካ፣ ፈጣንና ደህንነቱ የጠበቀ መፍትሔ ለመስጠት እንደረዳቸው ገልፀዋል።
የሆለታ ኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ከታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ በ500 ኪሎ ቮልት በደዴሳ በኩል በመቀበል ወደ 400 ኪሎ ቮልት ፤ለውጦ ለአቃቂ፣ ሰበታ እና ሱሉልታ ማከፋፈያ ጣቢያዎች፣ ለኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣ ለዳታ ማይኒንግ ድርጅቶች፣ ለደይሊ ውሃ እና ሀበሻ ሲሚንቶ ኃይል እያቀረበ ይገኛል።
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በለገጣፎ ማከፋፈያ የተከሰተው ችግር ሙሉ በሙሉ ተስተካክሏል
………///……..
በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚገኝ ትራንስፎርመር ገብቶ የሚወጣ አንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ የተነሳ በምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተጠግኖ አገልግሎት መስጠት ጀምሯል።
ከትራንስፎርመሩ ከሚወጡት ሦስት ፌዞች መካከል በአንደኛው ፌዝ ላይ የገጠመውን ችግር ምሽት 5:00 ሰዓት አካባቢ መልሶ በማገናኘት በመቻሉ ኃይል የተቋረጠባቸው አካባቢዎች በሙሉ ኃይል እንዲያገኙ ተደርጓል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በለገጣፎ ማከፋፈያ በገጠመ ችግር የምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል
………///……..
በለገጣፎ ማከፋፈያ ጣቢያ በሚገኝ ትራንስፎርመር ገብቶ የሚወጣ አንድ የኃይል ማስተላለፊያ መስመር በመበጠሱ የተነሳ በምስራቅ አዲስ አበባ አንዳንድ አካባቢዎች ኃይል ተቋርጧል።
በአንደኛው ፌዝ ላይ የገጠመውን ችግር በለገዳዲ፣ ለገጣፎ እና በየካ አባዶ እና አካባቢው ኃይል እንዲቋረጥ ምክንያት ሆኗል።
የገጠመውን ችግር በፍጥነት ለማስተካከል ርብርብ እየተደረገ ሲሆን አንዳንድ አካባቢዎችን መልሶ ማገናኘት ተችሏል።
የገጠመን ድንገተኛ ችግር ለማስተካከል የተወሰኑ ሰዓታት የሚፈልግ በመሆኑ ደንበኞች በትዕግስት እንድትጠብቁ በአክብሮት እንጠይቃለን።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ስዊች ጊሮች በራስ አቅም መቀየራቸው የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን አስችላል
………///……..
ለረጅም ዓመታት ያገለገሉ የማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎች ወይም ስዊች ጊሮች በተቋሙ የውስጥ አቅም መቀየራቸው በጣቢያዎቹ የጥገናና የኦፕሬሽን ሥራዎችን በቀላሉ ለማከናወን እንደሚያስችላቸው በቅየራ ሥራው ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎች ተናገሩ፡፡
በደቡብ አንድ ሪጅን የማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽንና ጥገና የሥራ ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ያለው አማረ እንደተናገሩት የማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያዎችን የማዘመኑ ሥራ በቴክኖሎጂው ዙሪያ ስልጠና የወሰዱ የሪጅን ማስተባበሪያ እና የሪጅን የጥገና ባለሙያዎችን በማቀናጀት ሲከናወን ነበር፡፡
ይሁን እንጂ ከዚህ በፊት ከተከናወኑ የማዘመን ሥራዎች የተገኙ የእውቀትና የቴክኖሎጅ ሽግግሮችን በመጠቀም በአሁኑ ወቅት የመቆጣጠሪያ ቅየራ ሥራው በሪጅኑ የጥገና ባለሙያዎች እና በማከፋፈያ ጣቢያ ሠራተኞች እየተከናወነ ስለመሆኑ አስረድተዋል፡፡
የማዘመን ሥራው በተቋሙ የራስ አቅም መከናወኑ ሠራተኞቹ ቴክኖሎጂውን ተላምደው የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በቀላሉ እንዲያከናወኑ ለማድረግ እንደሚያግዝም አመልክተዋል፡፡
የሻሸመኔ ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ምህረቱ ግዛው እና የይርጋለም ማከፋፈያ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ፈይሰል ዋቤ በበኩላቸው ከጣቢያዎቹ የብሬከር ቅየራ ሥራ ከኦፕሬሽን ሥራው ጋር በተያያዘ የሚከናወኑ ተግባራትን በአግባቡ ለመፈፀም የሚያስችል እውቀትና ክህሎት እየተገኘበት መሆኑን ተናግረዋል፡፡
በወላይታ ሶዶ ቁጥር አንድ ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን ባለሙያ የሆኑት ወ/ሮ እቴነሽ አሎንጄ በበኩላቸው በብሬከር ቅየራ ሥራው መሳተፋቸው የኦፕሬሽን ሥራዎችን ለማቀላጠፍ እና ለሚያጋጥሙ ቴክኒካል ችግሮች በቀላሉ መፍትሔ ለመስጠት የሚያስችል ክህሎትና ግንዛቤ መቅሰማቸውን አስረድተዋል፡፡
በደቡብ አንድ እና ሁለት ሪጅኖች የጥገና ባለሙያ የሆኑት አቶ ዘውዴ ጥላሁን እና አቶ አስቻለው ጴጥሮስ እንደተናገሩት በአሁኑ ወቅት በሪጅኖች አቅም እየተከናወነ ላለው ሥራ ከዚህ በፊት ከዋና መስሪያ ቤት ሠራተኞች ጋር በመተባበር ከተከናወነው ሥራ የተገኘው የእርስ በእርስ መማማር እና ልምድ ከፍተኛ አስተዋፅዖ አበርክቷል፡፡
በራስ አቅም እየተከናወነ ያለው የመቆጣጠሪያዎች ቅየራ ሥራ በቀጣይ ትልልቅ ፕሮጀክቶችን በራስ ባለሙያዎች መስራት እንደሚቻል ማሳያ መሆኑንም ሠራተኞችና የሥራ ኃላፊዎቹ ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠ https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር ↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠ https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ www.eep.com.et
ሚያዝያ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ዘርፉ በስሩ የሚገኙ መምሪያዎች በቅንጅት እንዲሰሩ አሳሰበ
….....///….......
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ የተሰጠውን ተልዕኮ ለማሳካት በስር የሚገኙ ሁሉም የሥራ ክፍሎች ሥራዎችን በቅንጅት መስራት እንደሚጠበቅባቸው የዘርፉ ሥራ አስፈፃሚ አቶ ዱጉማ ነዳ አሳስበዋል፡፡
በዘርፉ ሥር የሚገኙት የኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን፤ የህግ አገልግሎት፤ የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ እንዲሁም የሴቶች፣ ህፃናት እና ማህበራዊ ጉዳይ መምሪያዎች ባለፉት ዘጠኝ ወራት ያከናወኗቸውን ሥራዎች ከሥራ ክፍሎቹ የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ጋር በዛሬው ዕለት ገምግመዋል፡፡
በመድረኩ ላይ በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት በየሥራ ክፍሎቹ የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት፣ የነበሩ ጠንካራ ጎኖች፣ ያጋጠሙ ችግሮችና የተወሰዱ የመፍትሔ እርምጃዎች በዝርዝር ቀርበዋል፡፡
በሥራ ክፍሎቹ የቀረበው ሪፖርት እንዳመለከተዉ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በተከናወኑት ተግባራት የተቋሙን ገጽታ በመገንባት፣ ተጠያቂነት፤ ግልጽነት እና ፍትሀዊነት በማስፈን ረገድ የተሻለ አፈፃፀም ተመዝግቧል፡፡
ሥራ አስፈፃሚው በሰጡት የማጠቃለያ አቅጣጫ እንዳመለከቱት ተቋሙ የጀመረውን ለውጥ ለማስቀጠል፣ የተቋሙን ጥቅም ለማስጠበቅ እና ገጽታ ለመገንባት በሚያስችል መልኩ ለመቃኘት እንደዚህ ዓይነት የግምገማ መድረኮች ጥቅማቸው የጎላ ነው፡፡
ተቋሙ እያካሄደ ያለዉ ለውጥ ውጤታማ እንዲሆን ከዘርፉ ብዙ እንደሚጠበቅ በመገንዘብ በቀጣይም ለውጡን ውጤታማ ለማድረግ በተቀመጡ ደንቦችና አሰራሮች መሰረት ሥራዎችን ማከናወን እንደሚገባ አሳስበዋል፡፡
እንደ አቶ ዱጉማ ገለፃ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የነበሩ መልካም ጎኖችን በማጠናከርና ደካማ ጎኖችን በማሻሻል መምሪያዎች በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል፡፡
ከአሰራር መመሪያዎች ጋር በተያያዘ በሥራ ክፍሎች የተነሱ ሃሳቦችን በግብዓትነት በመውሰድ መመሪያዎችን በማዘጋጀትና በማስፀደቅ ወደ ሥራ ለማስገባት የሥራ ክፍሎች ጋር በጋራ እንዲሰሩ ጥሪ አቅርበዋል፡፡
ዘርፉ የጀመረውን የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል እና የተሻለ አፈፃፀም ያላቸው የሥራ ክፍሎች የሚበረታቱበት የአሰራር ሥርዓት እንደሚዘረጋ ጠቁመዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ዘርፉ የዘጠኝ ወራት የሥራ አፈጻጸሙን እየገመገመ ነው
......///.........
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኮርፖሬት ገቨርናንሰ እና ኮምፕሊያንስ ዘርፍ የ2017 በጀት ዓመት የዘጠኝ ወራት የዕቅድ አፈጻጸሙን መገምገም ጀምሯል።
የዘርፉ ሥራ አስፈጻሚ አቶ ድጉማ ነዳ እንደገለጹት ግምገማው በዘርፉ የተከናወኑ ዋና ዋና ሥራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ እና ያልተከናወኑ ሥራዎቸ ደግሞ በቀሪዎቹ ሦስት ወራት በማጠናቀቅ የበጀት ዓመቱን ዕቅድ ለማሳካት ያለመ ነው።
ግምገማው በዋነኛነት በዘጠኝ ወራት ውስጥ የተቋሙን ጥቅምን ለማስጠበቅ፣ የተቋሙን ገጽታ ለመገንባት እና በተቋሙ ውስጥ የሴቶችን ሁለንተናዊ ተሳትፎ ለማሳደግ የተከናወኑ ሥራዎች በዝርዝር ቀርበው ውይይት ይደረግባቸዋል።
ግምገማው የዘርፉን የቀጣይ ወራት የትኩረት አቅጣጫዎችን በማስቀመጥ እንደሚጠናቀቅ ይጠበቃል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በተቋሙ በቀጣዮቹ አምስት ዓመታት የሚተገበሩ ፕሮጀክቶች ይፋ ሆኑ
……////……
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የግሪድ ማዘመን፣ የዲጂታላዜሽን፣ ታዳሽ ኃይልን የማመንጨት እና የአቅም ግንባታ ሥራዎችን ለማከናወን የሚያስችል የአምስት ዓመት ፕሮጀክት ይፋ ሆነ፡፡
በፕሮጀክቶቹ ማስጀመሪያ መርሃ ግብር ላይ የተቋሙ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢ/ር አሸብር ባልቻ እንደተናገሩት ተቋሙ ለሚተገብራቸው ፕሮጀክቶች የአውሮፓ ህብረትን ጨምሮ ሌሎች አበዳሪ ተቋማት ለሰጡት ትኩረት እና ላሳዩት ፈጣን ምላሽ ምስጋና ሊቸራቸው ይገባል።
በፕሮጀክቱ ታዳሽ የሆነና የካርበን ልቀትን ለመቀነስ የሚያስችሉ የኃይል አማራጮች ማልማት እና በተቋሙ ውስጥ ባሉ ሁሉም የቢዝነስ ዘርፎች ዲጂታላይዝድ የሆኑ አሰራሮችን መተግበር እንደሚያካትት አስታውቀዋል፡፡
በኢትዮጵያ የአውሮፓ ህብረት ተጠሪና የትብብር ኃላፊ ሚስተር ሮቤርቶ ሽሊሮ በበኩላቸው ኢትዮጵያ የውሃ ኃይል ማመንጫ መሰረተ ልማት በመገንባት ብትታወቅም ያልተነኩ የፀሐይ፣ የንፋስ እና የጅኦተርማል እምቅ ሀብቶች ባለቤት እንደሆነች መገንዘባቸውን አንስተዋል፡፡
ስለሆነም ህብረቱ ከሌሎች አጋሮች ጋር በመሆን የተቋሙን የልማት ሥራዎች ለመደገፍ ቁርጠኛ መሆኑን ገልፀዋል፡፡
የትራንስሚሽን ቢዝነስ ፕሮግራም 3 ዳይሬክተርና የፕሮጀክቱ ሥራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሃይማኖት ተፈራ በበኩላቸው ፕሮጀክቶቹ ተቋሙን ወደ ተሻለ ቁመና ለማድረስ ታስበው የተቀረፁ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
በተቋሙ በአምስት ዓመት የሚተገበሩት ፕሮጀክቶች በአራት ዘርፎች ማለትም የግሪድ ማዘመንና ዕድሳት፣ ዲጅታላዜሽን፣ ታዳሽ ኃይል ልማት እና የአቅም ግንባታ ሥራዎች ላይ ትኩረት ያደረጉ መሆኑንም ነው የገለፁት፡፡
ፕሮጀክቶቹን ለማስፈፀም 270 ሚሊዮን ዩሮ እንደሚፈልግ የጠቀሱት ሥራ አስኪያጇ የፋይናንስ ምንጩ የፈረንሳይ ልማት ኤጀንሲ፣ የአውሮፓ ህብረት፣ የአውሮፓ ኢንቨስትመንት ባንክ እና የፈረንሳይ ግምጃ ቤት መሆናቸውን ጠቅሰዋል፡፡
በአምስት ዓመት የሚጠናቀቀው ይህ ፕሮጀክት 22 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ሙሉ በሙሉ የማዘመን ሥራ፣ አዲስ የመቆጣጠሪያ ማዕከል/NlDC/ ግንባታ፣ የትራንስፎርመር ወርክ ሾፕ እድሳት፣ የ1 ሺህ 590 ኪሎ ሜትር የኦፕቲካል ፋይበር መስመር ዝርጋታ እና ደረጃውን የጠበቀ የሥልጠና ማዕከል ግንባታ ሥራዎች እንደሚከናወኑ ሥራ አስኪያጇ አብራርተዋል፡፡
በሰሜን ኢትዮጵያ በተካሄደው ጦርነት የተጎዱ የአሸጎዳ የንፋስ ተርባይኖችን በመጠገን ወደ ኦፕሬሽን ለመመለስ መታቀዱንም አመልክተዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
የዕውቀት ሽግግር ለማድረግ የሚያስችል አውደ ጥናት ተካሄደ
……..///……..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ከከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ እየሰራ መሆኑን አስታወቀ፡፡
ተቋሙ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ፣ ኬቲኤች እና ቻልመርስ ከተሰኙ የሲዊዲን ዩኒቨርሲቲዎች ጋር በመተባበር የአንድ ቀን አውደጥናት አዘጋጅቷል።
አውደጥናቱ "የውሃ ኃይል ማመንጫዎችና የኦፕሬሽን ዕቅድ ለኢትዮጵያ እንዲሁም ለኢትዮጵያ የኃይል ልማት ዘርፍ አማራጭ መንገዶችና የረዥም ጊዜ ሞዴልና ትንታኔ" በሚሉ ርዕሶች በተዘጋጁ ጥናታዊ ጽሑፎች ላይ ትኩረት ያደረገ ነው።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የኢትዮ ፓዎር አካዳሚ ተወካይ ወንድወሰን ካሳ (ዶ/ር) በአውደ ጥናቱ ላይ እንደተናገሩት ተቋሙ ከከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ጋር በመተባበር ለተቋሙ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች የዕውቀት ሽግግር እንዲኖር ለማድረግ እየሰራ ይገኛል፡፡
ቀደም ሲል አካዳሚው በስልጠናዎች ላይ ብቻ ትኩረት አድርጎ ሲሰራ እንደነበር ያስታወሱት ዶ/ር ወንድወሰን ከለውጡ በኋላ ከስልጠናዎች በተጨማሪ ከተቋሙ ሥራ ጋር በተያያዘ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የተሠሩ የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን ወደ ተቋሙ በማምጣት አውደ ጥናቶችን ለማካሄድ አቅዶ እየተሰራ ስለመሆኑም አስታውቀዋል።
አውደ ጥናቱ ለሠራተኞች የዕውቀት ሽግግር ለማድረግ ከማገዙም ባለፈ የተቋሙን አሰራሮች ለመፈተሸ የሚስችል ዕድል እንደሚፈጥርም ዶ/ር ወንድወሰን አመልክተዋል።
"የውሃ ኃይል ማመንጫዎችና የኦፕሬሽን ዕቅድ ለኢትዮጵያ " በሚል ርዕሰ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በኢንኮድ ኢንጂነሪንግ ሶሉሽን ኃ/የተ/ ኩባንያ ዋና ሥራ አስኪያጅ ፍሬሕይወት ግርማ (ዶ/ር) ጥናቱ ወደ ኃይል ማመንጫ ግድቦች የገባውን ውሃ እንዴት በአግባቡ መጠቀም እንደሚቻል እና በጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሥራ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው ብለዋል፡፡
በዚህም የማመንጫ ግድቦችን ውሃ በአግባቡ ለመጠቀም የረጅም ጊዜ የኦፕሬሽን ሥራ ዕቅድ ሞዴል በመቅረፅ ተግባራዊ ማድረግ እንደሚገባ ጠቁመዋል፡፡
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ኬቲኤች ከተሰኘ የሲዊድን ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ያካሄደው ጥናት አምስት ዓመታትን የፈጀ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት እየተደረገበት ይገኛል።
"ለኢትዮጵያ የኃይል ልማት ዘርፍ አማራጭ መንገዶችና የረዥም ጊዜ ሞዴልና ትንታኔ" በሚል ርዕስ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ረዳት ፕሮፌሰር ዳዊት ሀብቱ (ዶ/ር) በበኩላቸው ጥናቱ በቀጣይ በኢትዮጵያ ሊኖር የሚችለውን የኃይል አቅርቦትና ፍላጎት እንዲሁም የኢነርጂ ልማት ዘርፉ ዕድገት መልካም አጋጣሚዎችና ተግዳሮቶችን ማሳየቱን ተናግረዋል።
ይህም ፖሊሲ አውጭዎች እና በዘርፉ የተሰማሩ ተቋማት ይህን ታሳቢ ያደረገ ሥራ እንዲያከናውኑ ግብዓት እንደሚሆን አመልክተዋል።
ለአራት ዓመታት ያህል የተካሄደውን ይህን ጥናት የሲዊዲኑ ቻልመርስ ዩኒቨርሲቲ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት በትብብር መደገፋቸውን ጠቅሰዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ የተሳተፉ ሠራተኞችና የሥራ መሪዎች በበኩላቸው አውደ ጥናቱ በተቋሙ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን በጥናት ላይ ተመስርቶ የመፍትሔ እርምጃዎችን ለመውሰድ እንደሚያስችል ጠቁመው መሠል ፕሮግራሞች በቀጣይ ተጠናክረው እንዲቀጥሉም ጠይቀዋል።
በአውደ ጥናቱ ላይ ከጀነሬሽን፣ ከትራንስሚሽን፣ ከኢንጂነሪንግና ኮንስትራክሽን ቢዝነስ ዘርፎች እንዲሁም ከኮርፖሬት ፕላኒንግ ዘርፍ የተውጣጡ የሥራ መሪዎችና ሠራተኞች ተሳትፈዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
ጣቢያው ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከ5 ሺ 430 ጊጋ ዋት ሰዓት በላይ ኃይል አመንጭቷል
……..///………
የጊቤ 3 የውሃ ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት ከዕቅዱ በላይ ኃይል ማምረቱን የጣቢያው የኦፕሬሽን ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ደጀኔ ጉታ እንዳስታወቁት ማመንጫ ጣቢያው በ2017 በጀት ዓመት ዘጠኝ ወራት 4 ሺ 725 ነጥብ 56 ጊጋ ዋት ሰዓት ኢነርጂ ለማመንጨት አቅዶ 5 ሺ 436 ነጥብ 5 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ማምረት ችሏል፡፡
ይህም ከዕቅዱ የ710 ነጥብ 94 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ15 ነጥብ 04 በመቶ እንዲሁም ከባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር የ189 ነጥብ 65 ጊጋ ዋት ሰዓት ወይም የ3 ነጥብ 61 በመቶ ብልጫ ያለው መሆኑን አቶ ደጀኔ ተናግረዋል፡፡
አስተማማኝ የኤሌክትሪክ ኃይል ለማምረት የሚያስችሉ የፍተሻና የክትትል ሥራዎች በየጊዜው መከናወናቸው፣ የኦፕሬሽን ሥራው የተቋሙ ሥራ አመራር ባፀደቀው የኦፕሬሽን ሥራዎች የአሰራር ስርዓት ማኑዋል መሰረት መከናወኑ እና የኃይል መቋረጥ አመላካቾችና ችግሮች (alarms and faults) ሲስተዋሉ ወዲያውኑ እንዲወገዱ መደረጋቸው ጣቢያው ከዕቅዱ በላይ ለማመንጨቱ ምክንያቶች እንደሆኑ ሥራ አስኪያጁ አስረድተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ መጨረሻ 6 ሺ 141 ነጥብ 49 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ለማመንጨት ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን ያስታወሱት አቶ ደጀኔ ባለፉት ዘጠኝ ወራትም ከአጠቃላይ ዕቅዱ የ88 ነጥብ 52 በመቶ አፈጻፀም ማስመዝገብ ተችሏል ብለዋል፡፡
ይህም በበጀት ዓመቱ ለማመንጨት የተያዘውን ዕቅድ ለማሳካት አመላካች እንደሆነ አስታውቀዋል፡፡
የጊቤ 3 ማመንጫ ጣቢያ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በ18 ማመንጫ ጣቢያዎች ከተመረተው የ21 ሺ 299 ነጥብ 69 ጊጋ ዋት ሰዓት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ የ25 ነጥብ 5 በመቶ ድርሻ በመያዝ የታላቁ ህዳሴ ግድበን ተከትሎ በሁለተኛ ደረጃ ላይ መቀመጡን ከኃይል ማመንጫዎች ኦፕሬሽን ዘርፍ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 570
በፕሮጀክቱ አካባቢ የተራቆቱ ቦታዎችን ወደነበሩበት የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ነው
……..///………
በኮይሻ የውሃ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት የግንባታ ሥራ የተራቆቱ ቦታዎችን ቀድሞ ወደነበሩበት ተፈጥሯዊ ይዞታ የመመለስ ሥራ እየተከናወነ መሆኑን በፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳዮች ዕቅድ ሥራ አስኪያጅ አስታወቁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ግዛቸው ደሳለኝ እንዳስታወቁት ፕሮጀክቱ የአካባቢያዊና ማህበራዊ ጉዳይ ሥራዎችን በአካባቢያዊና ማህበራዊ ተፅዕኖ ግምገማ ጥናት ምክረ ሃሳብ እና በሳይት የመልሶ ማልማት የአሰራር ሥርዓትና ዕቅድ መሰረት እያከናወነ ነው፡፡
በዚህም ለፕሮጀክቱ የግንባታ ሥራ ግብዓት የተቆፈሩ እና ተረፈ ምርቶች ተጠራቅመውባቸው የነበሩ የተለያዩ ቦታዎችን በጥናቱና በአሰራር ስርዓቱ መሰረት ወደ ተፈጥሯዊ ይዞታቸው የመመለስ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል፡፡
አቶ ግዛቸው እንዳሉት ፕሮጀክቱ ራሱን የቻለ የሥራ ቡድን እና የችግኝ ጣቢያ አቋቁሞ ከግንባታ ሥራው ጎን ለጎን የመልሶ ማልማት ሥራውን የዕለት ተዕለት ተግባራት አድርጎ እየሰራ ይገኛል፡፡
ሥራው ለአካባቢው መልክዓምድር እና ለአየር ንብረቱ ተስማሚ የሆኑ ሀገር በቀል ችግኞችን እና የአፈር መከላትን መከላከል እንደሚያስችል በሳይንሳዊ ዘዴ የተረጋገጠ "ቪቲባር" የተሰኘ ሳርን በመትከል እየተከናወነ ስለመሆኑም አስረድተዋል፡፡
የተለያዩ ማሽነሪዎችና ወርክ ሾፖች የተተከሉበት ቦታን ጨምሮ በፕሮጀክቱ ምክንያት ጉዳት የደረሰባቸው ሌሎች ቀሪ ቦታዎችን ወደ ነበሩበት የመመለሱ ሥራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አቶ ግዛቸው አረጋግጠዋል፡፡
ፕሮጀክቱ የአካባቢ ጥበቃ ሥራን ለማጠናከር በሀገሪቱ በየዓመቱ እየተካሄደ ባለው የአረንጓዴ አሻራ መርሃ ግብር ላይ በንቃት በመሳተፍ እና በጣቢያው ላይ የሚያለማቸውን ችግኞችና ሳሮችን ለአካባቢው አርሶ አደሮች እና መስተዳደሮች በማቅረብ አሻራዉን እያሳረፈ እንደሚገኝ ሥራ አስኪያጁ ጠቅሰዋል፡፡
ፕሮጀክቱ በአካባቢው ያለውን የመሰረት ልማት እጥረት ለመቅረፍ በመንገድ፣ በመጠጥ ውሃ፣ በትምህርት፣ በጤና እና በሌሎች ዘርፎች ላይ የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ የማህበራዊ ኃላፊነት ሥራዎችን ማከናወኑን አቶ ግዛቸው አስረድተዋል፡፡
በፕሮጀክቱ ሥራ ተቋራጭ ዊቢውልድ ኩባንያ ኢንቫይሮመንታል ኢንጅነር የሆኑት አቶ ይኸነው ቸኮል በበኩላቸው እየተከናወነ ካለው የሳይት መልሶ ማልማት ሥራ በተጨማሪ አካባቢውን ከከባቢ አየር ብክለት ለመጠበቅ በቆሻሻና ተረፈ ምርት አወጋገድ ላይ ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
ፕሮጀክቱ አካባቢውን ከብክለት ለመጠበቅ የሚያስችሉ የተለያዩ የአሰራር ስርዓቶችን ተግባራዊ ማድረጉንም ተናግረዋል፡፡
በዚህም ከተሸከርካሪና ማሽነሪዎች እጥበትና የሰርቪስ አገልግሎት የሚለቀቁ ዘይቶችና ዘይት ነክ ኬሚካሎች አካባቢውን እንዳይበክሉ ውሃውን ከዘይት የሚለይና የሚያጣራ ማሽን በመጠቀም ውሃው መልሶ ጥቅም ላይ የሚውልበት አሰራር መዘርጋቱን አስረድተዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም የኮንክሪት ሙሌት በሚከናወንበት ጊዜ የሚፈጠሩ የተረፈ ምርት ቆሻሻዎች አካባቢን የሚበክሉ መሆኑናቸውንና አለመሆናቸውን ናሙና በመውሰድ እንደሚረጋገጥና ጉዳት የሚያደርስ ከሆነም በሳይንሳዊ ዘዴ ተጣርቶ እንደሚለቀቅ ነው የጠቆሙት፡፡
የመልሶ ማልማት ሥራው የአካባቢውን ሥነ ምህዳር ለመጠበቅ እና በቀጣይ ሰው ሰራሽ ሀይቁ በደለል እንዳይሞላ በማድረግ ግድቡ የሚጠበቅበትን አገልግሎት በአግባቡ እንዲሰጥ ለማድረግ አስተዋጽኦ ይኖረዋል ተብሏል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
የኢትዮጵያኤሌክትሪክ ኃይል ይፋዊ የማኅበራዊ ትስስር ገጾችን በመቀላቀል ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ያግኙ
ፌስቡክ↠
https://www.facebook.com/Ethioelectric
ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
ትዊተር
↠https://twitter.com/EEPethiopia
ሊንክዲን↠
https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
ዩትዩብቻናል↠
https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ
www.eep.com.et
ሚያዝያ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
