EEP Communication
الذهاب إلى القناة على Telegram
📈 نظرة تحليلية على قناة تيليجرام EEP Communication
تُعد قناة EEP Communication (@eepcommuication) في القطاع اللغوي Amharic لاعباً نشطاً. يضم المجتمع حالياً 15 697 مشتركاً، محتلاً المرتبة 8 049 في فئة التكنولوجيات والتطبيقات والمرتبة 2 173 في منطقة Ethiopia.
📊 مؤشرات الجمهور والحراك
منذ تأسيسه في невідомо، حقق المشروع نمواً سريعاً وجمع 15 697 مشتركاً.
بحسب آخر البيانات بتاريخ 02 سبتمبر, 2026، تحافظ القناة على نشاط مستقر. خلال آخر 30 يوماً تغيّر عدد الأعضاء بمقدار 141، وفي آخر 24 ساعة بمقدار 0، مع بقاء الوصول العام مرتفعاً.
- حالة التحقق: غير موثّقة
- معدل التفاعل (ER): يبلغ متوسط تفاعل الجمهور 28.59%. وخلال أول 24 ساعة من النشر يحصد المحتوى عادةً 16.37% من ردود الفعل نسبةً إلى إجمالي المشتركين.
- وصول المنشورات: يحصل كل منشور على متوسط 4 487 مشاهدة. وخلال اليوم الأول يجمع عادةً 2 569 مشاهدة.
- التفاعلات والاستجابة: يتفاعل الجمهور بانتظام؛ متوسط التفاعلات لكل منشور يبلغ 10.
📝 الوصف وسياسة المحتوى
يصف المؤلف القناة بأنها مساحة للتعبير عن الآراء الذاتية:
“EEP Communication”
بفضل وتيرة التحديث المرتفعة (أحدث البيانات بتاريخ 03 سبتمبر, 2026) تحافظ القناة على حداثتها ومستوى وصول مرتفع. وتُظهر التحليلات تفاعلاً نشطاً من الجمهور، ما يجعلها نقطة تأثير مهمة ضمن فئة التكنولوجيات والتطبيقات.
15 697
المشتركون
لا توجد بيانات24 ساعات
+147 أيام
+14130 أيام
أرشيف المشاركات
15 697
+3
👉🏽 ኢትዮጵያ በአፍሪካ ማንም ሀገር ባላደረገው መጠን የኃይል ማመንጫ ላይ እየሰራች ነው።
👉🏽 በዚህ ዓመት ብቻ የኢንዱስትሪዎች የኃይል አቅርቦት በ 40 በመቶ አድጓል።
👉🏽 ታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብን ጨምሮ የአሰላ እና የአይሻ የንፋስ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች በሚቀጥለው ዓመት ይመረቃሉ።
👉🏽 አሁን ላይ ለኢነርጂ አስር ቢሊዮን ዶላር አካባቢ ኢንቨስትመንት እያደረግን ነው፡፡
~~~ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ካነሱት የተወሰደ
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 26 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን 65 በመቶ ለማድረስ እየተሠራ ነው
……..///…….
በኢትዮጵያ እ. ኤ. አ. በ2030 የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን 65 በመቶ ለማድረስ እየተሠራ መሆኑን የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።
በሚኒስቴሩ የኢነርጂ ዘርፍ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እንዳስታወቁት አሁን ላይ የኤሌክትሪክ ሽፋንን 54 በመቶ ማድረስ ተችሏል፡፡
ኢትዮጵያ ከውሃ፣ ከንፋስ፣ ከፀሐይ እና ከከርሰ ምድር እንፋሎት ያልተጠቀመችበት ከፍተኛ የታዳሽ ኃይል እምቅ አቅም እንዳላት የተናገሩት ሚኒስትር ዴኤታው ካላት እምቅ አቅም ውስጥ ስድስት ነጥብ አራት ጊጋ ዋት ኃይል ብቻ ጥቅም ላይ ማዋሏን ጠቅሰዋል፡፡
ይህም ሀገሪቱ በዘርፉ ካላት ሀብት አምስት በመቶ እንኳ ጥቅም ላይ እንዳልዋለ ያሳያል ብለዋል፡፡
የኃይል አቅርቦቱን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ለማድረግ የፖሊሲ ማሻሻያዎች መደረጋቸውንም ነው የገለፁት፡፡
እንደ ዶ/ር ሱልጣን ገለፃ የህብረተሰቡን የኃይል ፍላጎት ለማሟላት ንጹህና ታዳሽ ኃይል ላይ በስፋት እየተሰራ ነው፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 25 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ኢትዮጵያ ለነጠላ የኢነርጂ ገበያ ትግበራ እየሰራች ነው
……..///……..
ኢትዮጵያ ጎረቤቶቿን በኤሌክትሪክ ኃይል በማስተሳሰር ለነጠላ የኢነርጂ ገበያ ትግበራ መሠረት መሆኗን የአፍሪካ ህብረት አስታወቀ፡፡
የህብረቱ የመሠረተ ልማትና ኢነርጂ ዳይሬክተር ካሙጊሻ ካዛውራ(ዶ/ር) እንደተናገሩት ኢትዮጵያ ከሱዳን፣ ጁቡቲ፣ ኬኒያ እና ከቀሪ ጎረቤቶቿ ጋር የኃይል ትስስር እየፈጠረች ነው፡፡
የአፍሪካ የኤሌክትሪክ የነጠላ ገበያ ከፍተኛ የቴክኒክ ግምገማ ላይ ለኢትዮጵያ ጥረቶች እውቅና የሰጡት ዳይሬክተሩ ይህም ለአፍሪካ ህብረት የነጠላ ኢነርጂ ገበያ ትግበራ አቅም እየሆነች መምጣቷን የሚያሳይ ነው ብለዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 24 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
የትራንስፎርመር ጥገናው ተጠናቆ ወደ መደበኛ አገልግሎት ተመልሷል
.........///...........
በአዲስ ሴንተር ወይም በሜክሲኮ ማከፋፈያ
ትራንስፎርመር ላይ የተከናወነው አስቸኳይ ጥገና መጠናቀቁን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ 3 ሪጅን የማስተላለፊያ መስመርና ማከፋፈያ ጣቢያ የኦፕሬሽን መምሪያ አስታወቀ።
የሪጅኑ የጥገና ሥራ አስኪያጅ አቶ ታደሰ ገብሬ እንደገለፁት ከማከፋፈያ ጣቢያው ኃይል ሲያገኙ ከነበሩት አካባቢዎች አብዛኛዎቹ በቅርብ ከሚገኙ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ኃይል እንዲያገኙ ተደርጎ ጥገናው ሲከናወን ነበር።
የጥገና ሥራው ዛሬ ሌሊት 9:00 ሰዓት ላይ በመጠናቀቁ መስመሮቹን መልሶ የማገናኘት ሥራ በመሰራቱ በአሁኑ ሰዓት ሁሉም አካባቢዎች ኃይል ማግኘታቸውን አቶ ታደሰ አረጋግጠዋል።
የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ በትዕግስት የጠበቁ ደንበኞችን አመስግነዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የተሠጠ ማሳሰቢያ፡-
ዛሬ ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም ከሌሊቱ 6:00 ሰዓት ጀምሮ በአዲስ ሴንተር ወይም በሜክሲኮ ማከፋፈያ ትራንስፎርመር ላይአስቸኳይ የጥገና ሥራ ይከናወናል፡፡
ስለሆነም በሜክሲኮ፣ በአፍሪካ ህብረት፣ በቄራ፣ በገነት ሆቴል፣ በደንበል፣ በመስቀል ፍላወር፣ በወሎ ስፈር፣ በመስቀል አደባባይ በባምቢስ እና አካባቢው ኤሌክትሪክ ተቋርጦ ይቆያል።
በመሆኑም ክቡራን ደንበኞቻችን የጥገና ሥራው እስኪጠናቀቅ ድረስ ከወዲሁ ተገቢውን ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ በአክብሮት እናሳስባለን።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል!
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ሪጅኑ በአራት ማከፋፈያ ጣቢያዎች ዘመናዊ የመቆጣጠሪያ ቅየራ ሥራ አከናውኗል
…..///…..
በእርጅና ምክንያት በኦፕሬሽን ሥራ ላይ ችግር ሲፈጥሩ የነበሩ የአራት ማከፋፈያ ጣቢያ መቆጣጠሪያ ወይም ብሬከሮችን በአዲስ ጂ አይ ኤስ ዘመናዊ መቆጣጠሪያዎች የመቀየር ሥራ ማከናወኑን በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የማዕከላዊ ሦስት ሪጅን አስታወቀ፡፡
የሪጅኑ ሥራ አስኪያጅ አቶ እስማኤል ሙዘይን እንዳስታወቁት በሪጅኑ 1 ሺ 108 ነጥብ 3 ኪሎ ሜትር ርዝመት ያላቸው የማስተላለፊያ መስመሮች እና ከባለ 132 እስከ ባለ 500 ኪሎ ቮልት የቮልቴጅ መጠን ያላቸው 20 ማከፋፈያ ጣቢያዎች ይገኛሉ፡፡
በሪጅኑ ብዛት ያላቸው ማከፋፈያ ጣቢያዎች ረጅም ጊዜ ያገለገሉ ከመሆናቸው ጋር ተያይዞ ብሬከሮች በእርጅና ምክንያት በኦፕሬሽን ሥራዎች እና በኃይል አቅርቦቱ ላይ እንቅፋት ሲፈጥሩ መቆየታቸውን አስታውሰዋል፡፡
ሪጅኑ ችግሩን በመቅረፍ አስተማማኝ ኃይል ለማቅረብ በ2017 በጀት ዓመት የአሰላ፣ የአዳሚ ቱሉ፣ የወልቂጤ እና የሰበታ ሁለትን ማከፋፈያ ጣቢያዎች መቆጣጠሪያዎችን በዘመናዊ ጂ አይ ኤስ የመቆጣጠሪያ መቀየሩን ገልፀዋል፡፡
በሌሎች አራት ማከፋፈያ ጣቢያዎችም ተመሳሳይ ሥራ ለማከናወን ዕቅድ መያዙን ጠቁመዋል፡፡
አቶ እስማኤል እንደገለፁት በአዲስ ዌስት እና ወልቂጤ ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ የትራንስፎርመር ቅየራ እንዲሁም በቃሊቲ አንድ - ወረገኑ እና በሰበታ አንድ - መካኒሳ የ132 ኪሎ ቮልት ከረንት ትራንስፎርመር አቅም የማሳደግ ሥራ ተከናውኗል፡፡
ከአቅም ማሳደግና ማዘመን ሥራው ጎን ለጎን ሪጅኑ የኃይል ማስተላለፊያ መስመሮች እና ማከፋፈያ ጣቢያዎች ላይ መደበኛ የኢንስፔክሽን እና ጥገና ሥራዎችን በማከናወን እንዲሁም የውስጥ አሰራርን በማዘመን ላይ ትኩረት ሰጥቶ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በሪጅኑ የሚከናወኑ የአቅም ማሳደግ እና የማዘመን ሥራዎች የኃይል ብክነትን በመቀነስ፣ የኦፕሬሽንና የጥገና ሥራዎችን በማቀላጠፍ እና የኃይል መቋረጥ ጊዜን በማሳጠር የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለማሳደግ እንደሚረዳ አስረድተዋል፡፡
በበጀት ዓመቱ ሪጅኑ የሠራተኞችን አቅም ለማሳደግ በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ ለ421 ሠራተኞች ሥልጠና መስጠቱንም ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 20 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ተቋማቱ በአቅም ግንባታ ዙሪያ በጋራ ለመስራት ተስማሙ
…..///…..
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በሰው ሀብት ልማት፣ በምርምርና በማማከር ጉዳዮች ላይ በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የትብብር ስምምነት ተፈራረሙ፡፡
ስምምነቱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈፃሚ ኢንጂነር አሸብር ባልቻ እና የአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ ተፈራርመዋል፡፡
ኢንጂነር አሸብር ባልቻ በፊርማ ሥነ -ሥርዓቱ ወቅት እንደገለፁት ተቋሙ የአፍሪካ የታዳሽ ኃይል ማዕከል ለመሆን የያዘውን ዕቅድ ከግብ ለማድረስ በኃይል ልማት ዘርፉ የሠለጠነ ብቁ ባለሙያ ያስፈልገዋል፡፡
ስምምነቱ ተቋሙ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ጋር ያለውን የቆየ ግንኙነት በማጠናከር የተቋሙ ሠራተኞች በዩኒቨርሲቲው በኃይል ኢኮኖሚክስ እና በኃይል ምህንድስና የትምህርት መስኮች የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ተጠቃሚ የሚሆኑበትን ዕድል የሚፈጥር ነው ብለዋል፡፡
ይህም ዘርፉ የሚፈልገውን የሰለጠነ የሰው ኃይል በማፍራት ተቋሙ የያዘውን የረጅም እና የአጭር ጊዜ ዕቅድ ለማሳካት ያስችላል የሚል እምነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡
በተጨማሪም ስምምነቱ በዘርፉ ላይ በሚካሄዱ ጥናትና ምርምሮች እና በማማከር ጉዳዮች ዙሪያ በጋራ ለመስራት እንደሚያስችል የጠቆሙት ኢኒጂነር አሸብር በኃይል ልማት ዘርፍ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማዕከል ለመገንባት ተቋሙ የያዘውን ዕቅድ ለማሳካት ዩኒቨርስቲው የበኩሉን ሚና እንዲወጣም ጠይቀዋል።
የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ተጠባባቂ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሳሙኤል ክፍሌ በበኩላቸው ዩኒቨርስቲው ራስ ገዝ ከመሆኑ ጋር ተያይዞ ለሀገራዊ ፍላጎቶች ቀዳሚ ምላሽ የሚሰጥና ችግር ፈች የምርምር ሥራዎች የሚከናወኑበት እንዲሆን እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ የዳበረ ኢኮኖሚ ለመገንባት የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይልን ከመሰሉ ተቋማት ጋር በሰው ኃይል አቅም ግንባታ፣ በጥናትና ምርምር እንዲሁም በማማከር ዘርፎች ላይ በትብብር ለመስራት የሚያስችሉ የመግባቢያ ሥምምነቶች እየተፈረሙ መሆናቸውን ገልፀዋል፡፡
እንደ ዶ/ር ሳሙኤል ገለፃ ከተቋሙ ጋር የተደረገው ሥምምነት ሀገሪቱ በኃይል ልማት ዘርፉ ያላትን እምቅ አቅም በመጠቀም የኃይል ተደራሽነቱን ለማስፋት እና የአፍሪካ ሀገራትን በኃይል ለማስተሳሰር የተያዘውን እቅድ ለማሳካት በሚደረገው ጥረት ዩኒቨርሲቲው የራሱን ድርሻ እንዲወጣ የሚያስችለው ነው።
ስምምነቱ የዩኒቨርሲቲው ተማሪዎች እና መምህራን በተቋሙ የሥራ ላይ የተግባር ልምምድ የሚያደርጉበትን ምቹ ሁኔታ እንደሚፈጥርም አብራርተዋል፡፡
ትብብሩ የተሳካ ይሆን ዘንድ ተቋማቱ የሚጠበቅባቸውን ኃላፊነት በብቃት ለመወጣት ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ማከፋፈያ ጣቢያዉ የፋብሪካውን የማምረት አቅም በእጥፍ አሳድጓል
…….///…….
የገፈርሳ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ በአካባቢው ለሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች አስተማማኝ ኃይል በማቅረብ ምርትና ምርታማነት እንዲጨምር ቁልፍ ሚና እየተጫወተ መሆኑን የሙገር ሲሚንቶ ፋብሪካ አስታወቀ።
የፋብሪካው ዋና ሥራ አስኪያጅ አቶ ገዛኸኝ ደቻሳ እንደተናገሩት ማከፋፈያ ጣቢያው በአካባቢው ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በተለይም ለፋብሪካው የታጠቅ ቅርንጫፍ ትልቅ አቅም ፈጥሯል።
ፋብሪካው ሥራ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ የኃይል አቅርቦት አንዱ ፈተና እንደነበር ያስታወሱት ሥራ አስኪያጁ የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በማከፋፈያ ጣቢያው የማሻሻያ ሥራ በመስራቱና የተንቀሳቃሽ ማከፋፈያ ጣቢያ በመትከሉ የፋብሪካው የማምረት አቅም በእጥፍ ማደጉን ገልጸዋል።
ቀደም ሲል በቀን በአማካይ እስከ 5 ሺህ ቶን ሲሚንቶ ያመርት የነበረው ፋብሪካው አሁን የማምረት አቅሙ በእጥፍ አድጎ በቀን ከ10 ሺህ ቶን በላይ ሲሚንቶ ማምረት መቻሉን አስረድተዋል፡፡
ፋብሪካው ተጨማሪ ሲሚንቶ ከማምረቱ ባሻገር የማምረት አቅሙ በማደጉ ተጨማሪ የሰው ኃይል መቅጠር መጀመሩን ሥራ አስኪያጁ ተናግረዋል፡፡
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 17 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
# Update
የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመልሷል
.......///.......
አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በተወሰኑ አካባቢዎች የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ ተመልሷል።
የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት ለጠበቃችሁ ደንበኞች በሙሉ ምስጋናችንን እናቀርባለን።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
# Update
የተቋረጠው ኃይል መመለስ ጀምሯል
.......///.......
አዲስ አበባን ጨምሮ በኢትዮጵያ በከፊል የተቋረጠው ኃይል በተወሰኑ አካባቢዎች መመለስ ጀምሯል።
በተቀሩት አካባቢዎችም በየደረጃው መልሶ ኃይል የማገናኘት ስራ እየተሰራ በመሆኑ የተቋረጠው ኃይል ሙሉ በሙሉ እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትብቁ በድጋሚ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
ከፊል የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል
.......///.......
በኢትዮጵያ በተወሰኑ አካባቢዎች በሲስተም ላይ በተፈጠረ ችግር ከፊል የኃይል መቋረጥ አጋጥሟል።
አዲስ አበባን ጨምሮ በአንዳንድ የሀገሪቱ ከተሞች ያጋጠመውን የኃይል መቋረጥ ለመመለስ የብሔራዊ የኃይል መቆጣጠሪያ ማዕከል፣ የኃይል ማመንጫዎች እና የማከፋፈያ ጣቢያዎች የኦፕሬሽን ሰራተኞች ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛሉ።
ኃይል በተቋረጠባቸው አካባቢዎች የምትገኙ ደንበኞች የተቋረጠው ኃይል እስኪመለስ ድረስ በትዕግስት እንድትብቁ ጥሪያችንን እናቀርባለን።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 16 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ማጠናከር ያስፈልጋል
.....///......
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እና በጅማ ዩኒቨርሲቲ መካከከል ለረጅም ዓመት የዘለቀውን አብሮ የመስራት ልምድ አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚያስፈልግ ተገለጸ።
በኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል የጊቤ 1 ኃይል ማመንጫ ጣቢያ ሥራ አስኪያጅ አቶ ደሳለኝ ንጉሳ እንደገለጹት ሁለቱ ተቋማት ቀደም ሲል በኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና ትምህርት ክፍል ባደረጉት ስምምነት የጣቢያው ሠራተኞች በተለያዩ ጊዚያት የተጓዳኝ ትምህርት ዕድል እያገኙ ነው።
ተቋሙ ከጅማ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር በኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና በሁለተኛ ዲግሪ አሰልጥኖ ትናንት ያስመረቃቸው 20 የጣቢያው ሠራተኞች የሁለቱን ተቋማት ግንኙነት ማሳያ መሆናቸውን አመልክተዋል።
እንደ ኃላፊው ገለጻ በቀጣይ ሁለቱ ተቋማት በሌሎች ዘርፎች ላይ በጋራ በመስራት ዘርፉን ማሳደግ ይገባል።
በጅማ ዩኒቨርስቲ የቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት ሳይንቲፊክ ዳይሬክተር ኤፍሬም ዋቅጅራ በበኩላቸው ሁለቱ ተቋማት በኤሌክትሪካል ፓወር ምህንድስና ዘርፍ ጥናቶችን እና የምርምር ሥራዎችን በመሥራት ከ15 ዓመታት በላይ የዘለቀ ግንኙነት እንዳላቸው አስታውሰዋል።
ዩኒቨርሲቲው አሁን ከሚሰጠው ፕሮግራም በተጨማሪ በኮይሻ ኃይል ማመንጫ ፕሮጀክት ላይ ለሚሠሩ የተቋሙ ሠራተኞች በኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ፕሮግራም መጀመሩን ጠቅሰዋል።
በቀጣይም የተቋሙን ችግር በሚፈቱ የምርምርና አስተዳደራዊ ዘርፎች በጋራ ለመስራት ዩኒቨርስቲው ቁርጠኛ መሆኑን ገልጸዋል።
የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል በሀገሪቱ ብቸኛ ኃይል አምራች ተቋም በመሆኑ ዩኒቨርስቲው በዘርፉ ለሚያስተምራቸው ተማሪዎች የተግባር ትምህርት በመስጠት ብቁ ዜጋ ለማፍራት በሚደረገው ጥረት የበኩሉን አስተዋፅኦ እንዲያበርክትም ጠይቀዋል።
በጅማ ዩኒቨርስቲ የኢንጅነሪንግ ትምህርት ክፍል አስተባባሪ አቶ ክፍሌ ጎዳና የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል እንደ ተቋም የሚያጋጥሙትን የእውቀት ክፍተቶች በመሙላት ተቋማዊ ዕድገት ለማስመዝገብ እና ማህበራዊ ችግሮችን ለመፍታት የሚያደርገውን ጥረት አድንቀዋል።
የተቋሙ ሠራተኞች በሥራ ቦታቸው ላይ የሚያጋጥሟቸውን ችግሮች በመለየት በመመረቂያ ፅሁፋቸው ያቀረቧቸው ችግር ፈች ጥናቶች በጣቢያው ትልቅ አቅም መኖሩን አመላካች ነው ብለዋል።
ተቋሙ እነዚህን አቅሞች ተጠቅሞ የሚያካሂደውን የኤሌክትሪክ መሠረተ ልማት ግንባታዎች፣ የኦፕሬሽንና ጥገና ሥራዎች የበለጠ ፍሪያማ እንዲሆኑ ዩኒቨርሲቲው ዘርፈ ብዙ እገዛ እንደሚያደርግ አረጋግጠዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
15 697
በማከፋፈያ ጣቢያው የተከናወነው የብሬከር ቅየራ ሥራ ተጠናቀቀ
…….///…….
የሞጣ ባለ 230 ኪሎ ቮልት የማከፋፊያ ጣቢያን ለማዘመንና የኦፕሬሽን ሥራውን ለማቀላጠፍ የሚያስችል የብሬከር ቅየራ ሥራ መጠናቀቁን የጣቢያው ሥራ አስኪያጅ ገለፁ፡፡
ሥራ አስኪያጁ አቶ ተናኘ አዱኛ እንደገለፁት በማከፋፈያ ጣቢያው የጂ.አይ.ኤስ መቆጣጠሪያ ወይም ብሬከር ገጠማ ሥራ ተጠናቆ ለፍተሻና ሙከራ ዝግጁ ተደርጓል።
በዚህም ጣቢያው በቀጣዮቹ ቀናት የሙከራ ሥራውን አጠናቆ አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምር ነው የጠቆሙት።
ነባሩ ባለ 33 ኪሎ ቮልት ብሬከር ረጅም ዘመን በማገልገሉ በተደጋጋሚ የኃይል መቆራረጥ ያጋጥም እንደነበር የጠቀሱት ሥራ አስኪያጁ አዲሱ ዘመናዊ ብሬከር የኃይል መቆራረጡን በማስወገድና የቁጥጥር ሥርዓቱን በማዘመን የጣቢያውን ደህንነት እንደሚያስጠብቅ አንስተዋል።
እንደ አቶ ተናኘ ገለፃ ቀደም ሲል የነበረው መቆጣጠሪያ ችግሮች ሲያጋጥሙ የጥገና ሥራ ለማከናወን ረዘም ያለ ጊዜ ይወስድ ነበር።
የመቆጣጠሪያው መቀየር የኃይል መቆራረጥንና በጥገና ሥራዎች ላይ ያጋጥሙ የነበሩ ችግሮችን በመቅረፍ የኦፕሬሽን ሥርዓቱን ለማቀላጠፍ እንደሚረዳም ነው የተናገሩት።
በጣቢያው በተከናወነው የዘመናዊ መቆጣጠሪያ ቅየራ ሥራ አንድ ተጨማሪ ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመር ለአገልግሎት ዝግጁ መደረጉንም ነው ያብራሩት።
ይህም የጣቢያውን አቅም በማሳደግ የኃይል አቅርቦቱን አስተማማኝነት ለመጨመር እንደሚያግዝ ጠቅሰው ከደንበኞች ለሚነሱ የኃይል ፍላጎት ጥያቄዎች አስተማማኝ ምላሽ ለመስጠት ሚናው የጎላ እንደሆነም ገልፀዋል።
የሞጣ ማከፋፈያ ጣቢያ አንድ ባለ 25 ሜጋ ቮልት አምፔር ትራንስፎርመር ያለው ሲሆን በአሁኑ ወቅት ከ10 ሜጋ ዋት ያልበለጠ ኃይል ለህብረተሰቡ እያቀረበ እንደሚገኝ ተናግረዋል።
ጣቢያው በአሁኑ ወቅት አምስት ባለ 33 ኪሎ ቮልት ወጪ መስመሮች ያሉት ሲሆን አራቱ ለሞጣ፣ መርጦ ለማሪያም፣ አስተርዮ እና ፈለገ ብርሃን ከተሞች እንዲሁም በዙሪያቸው ለሚገኙ አካባቢዎች ኃይል እያቀረቡ ይገኛሉ።
ከባህር ዳር እና ደብረ ማርቆስ በ 230 ኪሎ ቮልት ኃይል ተቀብሎ በአቅራቢያው ለሚገኙ ከተሞች የሚያከፋፍለው የሞጣ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያ ዝግጁ የተደረገውን አንድ ተጨማሪ መስመር ወደ ሥራ ለማስገባት ከኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው ብለዋል።
💡 "ንፁህ ኢነርጂ ለተሻለ ህይወት!”
📌ፌስቡክ↠https://www.facebook.com/Ethioelectric
📌ቴሌግራም↠https://t.me/EEPCommuication
📌ትዊተር↠https://twitter.com/EEPethiopia
📌ሊንክዲን↠ https://www.linkedin.com/company/ethiopian-electric-power
📌ዩትዩብቻናል↠https://www.youtube.com/@ethiopowermedia
📌ቲክቶክአካውንት↠https://tiktok.com/@ethio_power
📌ድረ- ገፃችንንም ይጎብኙ https://www.eep.com.et
ሰኔ 15 ቀን 2017 ዓ.ም
