Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/
前往频道在 Telegram
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.
显示更多📈 Telegram 频道 Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ 的分析概览
频道 Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 24 870 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 9 621,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 339 位。
📊 受众指标与增长动态
自 невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 24 870 名订阅者。
根据 05 七月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -105,过去 24 小时变化为 -6,整体触达仍然可观。
- 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
- 互动率 (ER): 平均受众互动率为 10.02%。内容发布后 24 小时内通常能获得 4.95% 的反应,占订阅者总量。
- 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 493 次浏览,首日通常累积 1 232 次浏览。
- 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 5。
📝 描述与内容策略
作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
“Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.”
凭借高频更新(最新数据采集于 06 七月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。
24 870
订阅者
-624 小时
-307 天
-10530 天
帖子存档
24 866
በአዲስ አበባ 543 ትምህርት ቤቶች የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል- የአዲስ አበባ ትምህርት ቢሮ
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ ⵏበከተማው የ6ኛ ክፍል ከተማ አቀፍ ፈተና ካስፈተኑ 768 ትምህርት ቤቶች መካከል 543 ትምህርት ቤቶች ሙሉ በሙሉ ተማሪዎቻቸውን ማሳለፍ መቻላቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ አስታወቀ።
ቢሮው የ2018 የትምህርት ዘመን የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ማለፊያ ውጤት 50 በመቶ እንዲሆን ወስኗል።
የትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ፈተናውን ከወሰዱት ከ97 በመቶ በላይ የሚሆኑት ወደ ቀጣይ ክፍል ተዘዋውረዋል። 543 ትምህርት ቤቶችም የ6ኛ ክፍል ፈተና ሙሉ በሙሉ ማሳለፍ ችለዋል።
የማለፊያ ነጥብ ለመደበኛ ተማሪዎች 50 በመቶ እንዲሁም 45 በመቶ ለአካል ጉዳተኞች መወሰኑን ተናግረዋል።
በመንግስትና በግል ትምህርት ቤቶች እንዲሁም በቀንና በማታ መርሃ ግብር ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የነበሩ ከ85 ሺህ በላይ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰዳቸውን ገልጸው፤ በዘንድሮው ፈተና ሁለት ተማሪዎች 98 አማካይ ውጤት ማስመዝገባቸውን ጠቁመዋል።
459 ተማሪዎች 95 እና ከዚያ በላይ አማካይ ማስመዝገባቸውን ጠቅሰው፤አምስት ሺህ 559 የሚሆኑት ከ90 በላይ አማካይ ያስመዘገቡ ናቸው ብለዋል።
አጠቃላይ ውጤቱ ከባለፈው ዓመት ጋር ሲነጻጸር በሁለት ነጥብ አራት በመቶ እድገት ማሳየቱንም ገልጸው፣ ከዛሬ ጀምሮ ተማሪዎች ውጤታቸውን በኦላይን መመልከት የሚችሉ መሆኑን ኃላፊው ተናግረዋል።
በልጅዓለም ፍቅሬ
+++++++++++++++++
#Gazetteplus #ጋዜጣፕላስ #AddisAbaba #AddisAbabaEducation #Grade6Exam
24 866
ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኘ
+++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ│በ2018 በጀት ዓመት ከወጪ ንግድ ከ10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ መገኘቱን የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።
ሚኒስቴሩ ከተጠሪ ተቋማት ጋር የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ እያካሄደ ይገኛል።
በግምገማ መድረኩላይ የተገኙት የንግድና ቀጠናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ (ዶ/ር) እንደገለጹት፣ በሀገሪቱ የውጭ ንግድ ታሪክ ታይቶ የማይታወቅ ከፍተኛ ስኬት ተመዝግቧል።
በበጀት ዓመቱ ከወጪ ንግድ 10 ነጥብ 7 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት በተሰራው ስራ ዕቅዱን መቶ በመቶ ማሳካት ተችሏል።
ይህ ስኬት ሊመዘገብ የቻለው በሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ዋና መሥሪያ ቤትና በተጠሪ ተቋማት አማካኝነት በተከናወኑ የተቀናጁ የሪፎርም ሥራዎች፣ የወጪ ምርቶች ጥራትን በማረጋገጥና በተዘረጉ ዘመናዊ አሠራሮች መሆኑን ተናግረዋል።
በበጀት ዓመቱ 3 ነጥብ 3 ሚሊዮን ዜጎች የንግድ ፈቃድ፣ ምዝገባና ዕድሳት አገልግሎት ለመስጠት ታቅዶ፣ ከ3 ነጥብ 4 ሚሊዮን በላይ ለሚሆኑት አገልግሎት መስጠት መቻሉን ገልጸዋል።
በታደሠ ብናልፈው
የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት #ጋዜጣ_ፕላስ #የወጪ #ገቢ #ንግድ #ንግድናቀጠናዊትስስር #ኢትዮጵያ
24 866
+7
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በአርባ ምንጭ ከተማ ዛሬ የጎበኙት የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ በፎቶ‼️
#EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia
24 866
+7
ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በ2035 መቶ በመቶ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
የኤሌክትሪክ ኃይልን ተደራሽነትን ለማሳካት ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂዎች ይተገበራሉ ያሉት መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ አንደኛው ከዋናው የኃይል ማሰራጫ መስመር ኤሌክትሪክን ማዳረስ ሲሆን፣ ሁለተኛው ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሶላር (የፀሐይ) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።
የሶላር ኃይል ተጠቃሚ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በየአካባቢያቸው የመሰረተ ልማት ዕድገት እየተስፋፋ ሲመጣ ዘላቂና አስተማማኝ ወደ ሆነው ዋናው መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚሸጋገሩም ተናግረዋል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የኃይ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ 18 ቢሊዮን ዶላር ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ መስፍን፤ አስፈላጊውን በጀት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍና ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የማሰባሰብ ሥራውን ለማከናወን አቅጣጫ መቀመጡን ጠቁመዋል።
ባለፉት ዓመታት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሽፋን 65 በመቶ ማድረስ መቻሉንም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ገልጸዋል።
በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #የኤሌክትሪክ_ሽፋን #መሰረተ_ልማት #ታዳሽ_ኃይል
24 866
ኢትዮጵያ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች
++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ | ኢትዮጵያ እኤአ በ2035 መቶ በመቶ የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
በውኃና ኢነርጂ ሚኒስቴር የብሔራዊ ኤሌክትሪፊኬሽን ፕሮግራም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ለጋዜጣ ፕላስ እንደገለጹት፤ ሀገሪቱ በ2035 መቶ በመቶ የኃይል ተደራሽነትን ለማረጋገጥ የሚያስችሉ ተግባራትን እያከናወነች ትገኛለች።
የኤሌክትሪክ ኃይልን ተደራሽነትን ለማሳካት ሁለት ዋና ዋና ስትራቴጂዎች ይተገበራሉ ያሉት መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ አንደኛው ከዋናው የኃይል ማሰራጫ መስመር ኤሌክትሪክን ማዳረስ ሲሆን፣ ሁለተኛው ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ የማህበረሰብ ክፍሎችን የሶላር (የፀሐይ) ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ተጠቃሚ ማድረግ ነው ብለዋል።
የሶላር ኃይል ተጠቃሚ የሆኑ የማህበረሰብ ክፍሎች፣ በየአካባቢያቸው የመሰረተ ልማት ዕድገት እየተስፋፋ ሲመጣ ዘላቂና አስተማማኝ ወደ ሆነው ዋናው መስመር የኤሌክትሪክ ኃይል አቅርቦት እንደሚሸጋገሩም ተናግረዋል።
በሚቀጥሉት 10 ዓመታት የኃይ አቅርቦት ተደራሽነት ለማረጋገጥ 18 ቢሊዮን ዶላር ፋይናንስ እንደሚያስፈልግ የገለጹት አቶ መስፍን፤ አስፈላጊውን በጀት ከመንግሥት፣ ከግሉ ዘርፍና ከአለም አቀፍ የገንዘብ ተቋማት የማሰባሰብ ሥራውን ለማከናወን አቅጣጫ መቀመጡን ጠቁመዋል።
ባለፉት ዓመታት የኤሌክትሪክ ተደራሽነትን ለማስፋፋት በተከናወኑ ተግባራት የሀገሪቱን አጠቃላይ የኤሌክትሪክ ሽፋን 65 በመቶ ማድረስ መቻሉንም መሪ ሥራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ዳቢ ገልጸዋል።
በክብረአብ በላቸው
#ጋዜጣ_ፕላስ #ኢትዮጵያ #የኤሌክትሪክ_ሽፋን #መሰረተ_ልማት #ታዳሽ_ኃይል
24 866
+4
"ኩሪፍቱ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው"
- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
++++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ የመደመር መንግሥት የገነባቸውን መሠረተ-ልማቶች ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለፁ።
በአርባ ምንጭ ከተማ በ52,000 ካሬ ሜትር ስፋት ላይ ያረፈውን የኩሪፍቱ ሪዞርትና ስፓ ዛሬ ጎብኝተዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው ባሰፈሩት መልዕክት አርባ ምንጭ፤ የልማት ምንጭነቷ እየጎመራ ቀጥሏል! ብለዋል።
ይህ ታላቅ ፕሮጀክት 53 ቅንጡ ቪላዎችን ያካተተ ሲሆን፣ ከ300 በላይ ለሚሆኑ ዜጎች ቋሚ የሥራ ዕድል ይፈጥራል ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ መሰል ኢንቨስትመንቶች የመደመር መንግሥት የገነባቸውን መሠረተ-ልማቶች ተከትሎ የግሉ ዘርፍ ማበርከት የሚችለውን ከፍተኛ አስተዋጽኦ በግልጽ የሚያሳይ ነው ብለዋል።
የሀገራችንን የቱሪዝም አቅም ወደ ላቀ ምዕራፍ የሚያሸጋግሩ መሰል ታላላቅ ፕሮጀክቶች ላይ፣ የሀገር ውስጥና የውጭ ባለሀብቶች በስፋት እንዲሰማሩና መዋዕለ ንዋያቸውን እንዲያፈሱ ጥሪ አቅርበዋል።
#EthiopiaDelivers #InvestInEthiopia
24 866
+3
የገበታ ለሀገር ትሩፋቶች....
📌 የጎርጎራ ኢኮ ሪዞርት
📌 የወንጪ ደንዲ ኢኮ ቱሪዝም
📌 የሃላላ ኬላ ሪዞርት
📌 የጨበራ የዝሆን ዳና ሎጅ
24 866
የኢትዮጵያ የቡና ወጪ ንግድ ስኬት...
++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - ኢትዮጵያ በ2018 በጀት ዓመት ከቡና ኤክስፖርት 3 ቢሊየን የአሜሪካን ዶላር ለማግኘት የያዘችውን ዕቅድ ማሳካቷን የግብርና ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ አዲሱ አረጋ ገለፁ፡፡
በባለፈው በጀት ዓመት 2 ነጥብ 65 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ማግኘት ተችሎ ነበር። ይህን ቁጥር አመት ባልሞላ ጊዜ ማሻሻል የተቻለው መንግስት ለዘርፉ በሰጠው ትኩረት የቡናውን ምርትና ምርታማነትን የሚያሳድጉ ስራዎች ተከናውነዋል።
በተለይም ለቡና ምርት ጥራት ትኩረት መደረጉ ለዕቅድ ስኬት ድርሻው ከፍተኛ መሆኑን የግብርና ሚኒስቴር አስታውቋል።
#ከማምረትበላይ #BeyondProduction #EthiopiaDelivers #PMOEthiopia
24 866
ቱሪዝም- አዲሱ የኢኮኖሚ ሞተር
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ቱሪዝምን አሰመልክቶ ከNBC ጋር ባደረጉት ቆይታ ካነሷቸው ዋና ዋና ሀሳቦች‼️
👉 ለቱሪዝም ዘርፍ የተሰጠው ትኩረት መነሾ ራዕያችን ነው
👉 ራዕያችን የበለጸገች የተለወጠች የተከበረችና የተወደደች ሀገር ሰርተን ለልጆቻችን ማስረከብ ነው፣
👉 በዚህ ዓመት ከ1 ነጥብ 4 ሚሊየን ጎብኝ ኢትዮጵያን ጎብኝቷል፤ ከ5 ነጥብ 2 ቢሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ተገኝቷል
👉 በቀድሞ ጊዜ በነበረው የትርክት ችግር በቱሪዝም ዘርፉ አለን ከማለት ያለፈ ሥራ አልነበረም፣
👉 ቅርሶቻችን እንደ ዕዳ ከመታየት ወጥተው ታድሰው ተጠግነው ውብ ሆነው ወጥተው ምንዳ ሆነው ሀብት እያስገኙ
👉 ቅርስ የምናስመልስ የምንጠብቅ እንጅ ቅርስ የምናፈርስ አይደለንም
👉 ቱሪዝምን ከአምስቱ ዋና ዋና የትኩረት መስኮች በመመደብ በመደመር ዕሳቤ በትኩረት እየሠራበት ነው፣
👉 ባለፉት 7 ዓመታት ከዚህ ቀደም የተዘረፉ ከ35 በላይ የኢትዮጵያ ቅርሶች ተመልሰዋል
👉 እንደ ሀገር ቅርስ ከመመለስ በተጨማሪ ቅርስ በማደስ የሚጎሉትን ደግሞ ገንብተን ለአገልግሎት አብቅተናል፣
👉 ቱሪዝም ከብዘሃ የኢኮኖሚ ሴክተሮች አንዱ ተደርጎ ተወስዶ እየተሰራ ነው
👉 በዓለም ላይ በቱሪዝም ሴክተር የሚንቀሳቀሰው ሀብት መጠን በጣም ከፍተኛ ነው
👉 ለዘመናት ኢትዮጵያ አያሌ ጸጋዎች እንዳሏት እናምናለን እንናገራለን በዚህም እንኮራለን፣
👉 ቱሪዝም ላይ ኢንቨስት ማድረግ በዓለም ዓቀፍ ደረጃ ያለውን ሃብት ለመቋደስ ያስችላል
👉 ኢትዮጵያ በርካታ የቱሪዝም መስህቦች አሏት እሱን የሚያውቁ ፣ የሚያዩና የሚያሳውቁ ውስኖች ናቸው
#LandOfOrigins #Medemer #ገበታለሀገር #ገበታለትውልድ #TravelEthiopia #EcoTourism
24 866
+9
በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ዛሬ የተመረቀው የእንጦጦ-ቀበና የወንዝና የወንዝ ዳርቻ ልማት ፕሮጀክት በፎቶ
24 866
+3
16 A+ ያስመዝገበው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ የዓመቱ ኮኮብ ዘለቀ መንግስቴ
+++++++++++++++++
#ጋዜጣ_ፕላስ - የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ በዛሬው ዕለት ካሰመረቃቸው ከአንድ ሺህ 817 ተማሪዎችን መካከል የሰርቬይ ኢንጂነሪንግ ዲፓርትመንት ተማሪው ዘለቀ መንግስቴ የዓመቱ ኮከብ ተማሪ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ዩኒቨርስቲ በተለያዩ የትምህርት መስኮች ያሰለጠናቸውን አንድ ሺህ 817 ተማሪዎችን በአደዋ ድል መታሰቢያ አስመርቋል።
ተመራቂ ዘለቀ መንግስቴ በዩኒቨርሲቲ ቆይታው ከወሰዳቸው 58 ኮርሶች 16 A+ በማስመዝገብ የዋንጫና የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ ሆኗል፡፡
ዘለቀ ባለትዳና የሁለት ልጆች አባት ሲሆን፤ ለስኬቱ የቤተሰቦቹ ድጋፍ ከፍተኛ እንደነበር ጠቅሶ፤ በተለይም የባለቤቱ የዕለት ተዕለት ድጋፍ ለውጤቱ መሳካት ትልቅ እገዛ ማድረጉን ገልጿል፡፡
በየዩኒቨርሲቲ ቆይታው ከአካዳሚክ ትምህርት ባለፈ ብዙ ጥሩ ነገሮችን መማሩን የሚናገረው ዘለቀ፤ በቀጣይም በተማረበት የሞያ ዘርፍ ሀገሩን በታማኝነት ለማገልገል መዘጋጀቱን ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርስቲ ፕሬዚዳንት ንጉሥ ታደሰ (ዶ/ር) በምረቃው ወቅት ባስተላለፉት መልዕክት፤ ትምህርት የህይወት ዘመን ጉዞ መሆኑን በመገንዘብ ምሩቃን ያገኙትን እውቀትና ክህሎት በመጠቀም ሀገራቸውን እንዲሁም ህዝባቸውን በታታሪነትና በታማኝነት እንዲያገለግሉ አሳስበዋል።
ዩኒቨርሲቲው በትምህርት፣ በአጫጭር ጊዜ ስልጠናዎች፣ በጥናትና ምርምር በማህበረሰብ አገልግሎት ዘርፎች የሀገሪቱን የፐብሊክ ሴክተር ተቋማዊ አቅም ግንባታ እያጠናከረ እንደሚገኝ ጠቁመዋል።
በአማን ረሺድ
#ጋዜጣ_ፕላስ #ፕብሊክየኒቨርሲቲ #ተማሪምርቃት #ኢትዮጵያ #EthiopiaDelivers #gazetteplus #graduation
24 866
+3
አበባየሁ ደሳለኝ ትባላለች፤ የሦስተኛ ዲግሪ ተመራቂ ከልጇ ጋር
+++++++++++
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት ከሚያስመርቃቸው 6ሺህ 417 ተማሪዎች መካከል 2 ሺህ 646 ሴቶች ናቸው። 377 የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች መሆናቸው በምረቃው ስነስርዓት ላይ ተገልጿል።
现已上线!2025 年 Telegram 研究 — 年度关键洞察 
