ch
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

前往频道在 Telegram

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

显示更多

📈 Telegram 频道 Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ 的分析概览

频道 Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) 阿姆哈拉语 语言赛道中的 是活跃参与者。目前社区聚集了 24 803 名订阅者,在 新闻与媒体 类别中位列第 9 635,并在 埃塞俄比亚 地区排名第 1 389

📊 受众指标与增长动态

невідомо 创建以来,项目保持高速增长,吸引了 24 803 名订阅者。

根据 29 八月, 2026 的最新数据,频道保持稳定运转。过去 30 天订阅人数变化为 -2,过去 24 小时变化为 4,整体触达仍然可观。

  • 认证状态: 已认证(Telegram 官方确认)
  • 互动率 (ER): 平均受众互动率为 11.20%。内容发布后 24 小时内通常能获得 4.88% 的反应,占订阅者总量。
  • 帖子覆盖: 每篇帖子平均可获得 2 777 次浏览,首日通常累积 1 211 次浏览。
  • 互动与反馈: 受众积极参与,单帖平均反应数为 4

📝 描述与内容策略

作者将该频道定位为表达主观观点的平台:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

凭借高频更新(最新数据采集于 30 八月, 2026),频道始终保持新鲜度与高覆盖。分析显示受众积极互动,使其成为 新闻与媒体 类别中的关键影响点。

24 803
订阅者
+424 小时
-167
-230
帖子存档
የሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ኃይል የማመንጭት አቅም ያለው የኮይሻ ግድብ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ ደርሷል +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተ
+2
የሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ኃይል የማመንጭት አቅም ያለው የኮይሻ ግድብ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ ደርሷል +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ-በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል እየተገነባ የሚገኘውና የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ ያሳድጋል ተብሎ የሚጠበቀው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ ግንባታ አፈጻጸም ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ዋና ሥራ አስፈጻሚ ኢንጂነር አሽብር ባልቻ የተቋሙን የ2018 በጀት ዓመት አፈጻጸምና የ2019 በጀት ዓመት ዕቅድ ለመገናኛ ብዙኃን ባቀረቡበት ወቅት እንደተናገሩት፤ ግድቡን በታቀደለት ጊዜ አጠናቆ ወደ ሥራ ለማስገባት በልዩ ትኩረት እየተሠራ ይገኛል። በሦስት ቢሊዮን ዩሮ ወጪ ግንባታው እየተከናወነ የሚገኘው የኮይሻ የውኃ ኃይል ማመንጫ ግድብ በአሁኑ ወቅት አጠቃላይ አፈጻጸሙ ከ77 በመቶ በላይ መድረሱን ተናግረዋል። የኮይሻ ግድብን በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት ውስጥ ሙሉ በሙሉ ለማጠናቀቅና በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ደግሞ በከፊል ሥራ ለማስጀመር ግብ ተይዞ እየተሠራ እንደሚገኝ ገልጸዋል። የታላቁ ሕዳሴ ግድብን አንድ ሦስተኛ ያህል ኃይል የማመንጨት አቅም ያለው ይህ ግድብ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ኃይል ተደራሽነት በማሳደግ ረገድ የጎላ ሚና እንደሚኖረው ጠቁመዋል። የኮይሻ ግድብ ግንባታ ፕሮጀክት በተያዘለት ጊዜ ተጠናቆ ለአገልግሎት ሲበቃ፣ የሀገሪቱን የኤሌክትሪክ ሽፋን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ የዜጎችን የዕለት ተዕለት ሕይወት ከመቀየር ባለፈ ለዘላቂ ልማት ትልቅ ምሰሶ እንደሚሆን ይጠበቃል። #ጋዜጣ_ፕላስ #ኮይሻ_ግድብ #ኢትዮጵያ_ኤሌክትሪክ_ኃይል #የውኃ_ኃይል_ማመንጫ #የሕዳሴ_ግድብ #የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ኢትዮጵያ

የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - የጎቤ እና የሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት የወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የ
+2
የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - የጎቤ እና የሺኖዬ በዓል የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት የወጣት ወንዶችና ልጃገረዶች ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ገለጹ። የቱለማ አባ ገዳ ጌቱ ተሊላ ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ እንደገለጹት፤ የጎቤ እና የሺኖዬ ጨዋታ በኦሮሞ ባህልና እሴት መሠረት ሊከበር የሚገባውና የዘመን መለወጫ ማብሰሪያ ባህላዊ ጨዋታ ነው። ባህላዊ ጨዋታው ጥንታዊ የኦሮሞ ባህልና እሴቶችን የተከተለ መሆን እንዳለበት የጠቀሱት አባ ገዳ ጌቱ፤ ጎቤ እና ሺኖዬን ከባህላዊ እሴቱ ውጭ ለገቢ ማስገኛነት መጠቀም እንደማይቻል ተናግረዋል። የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል ዕድሜያቸው ከ18 እስከ 30 ያሉ ልጃገረዶችና ወጣቶች ተሰባስበው የሚጫወቱት ባህላዊ ጨዋታ መሆኑን የገለጹት አባ ገዳው፤ በዓሉ ከጭጋጋማው የክረምት ወራት ወደ ፀደይ ብርሃን የመሸጋገሪያ ብስራት የሚበሰርበት መሆኑንም አብራርተዋል። የዘንድሮው የጎቤ እና ሺኖዬ በዓል በኦሮሞ ሕዝብ ዘንድ ከነሐሴ 16 ቀን ጀምሮ እየተከበረ እንደሚገኝም ጠቁመዋል። ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ ጌታቸው በበኩላቸው፤ ጎቤ እና ሺኖዬ በመንገዶች ላይና ቤት ለቤት በመሄድ የአዲስ ዓመት ብስራት የሚነገርበት፣ እንዲሁም አንድነትና ፍቅር በአደባባይ የሚታይበት በዓል መሆኑን ገልጸዋል። መንግሥት ለዘርፉ የሰጠው ትኩረት በዓሉን ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ ከትውልድ ወደ ትውልድ ለማስተላለፍ የሚረዳ መሆኑንም ሀደ ሲንቄ ዘውዲቱ አክለው ተናግረዋል። በማርቆስ በላይ #ጋዜጣ_ፕላስ #ጎቤና_ሺኖዬ #የኦሮሞ_ባህል #የገዳ_ሥርዓት #ኦሮሚያ #ኢፕድ #ኢትዮጵያ

ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃ
ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል። እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮችና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ። ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq #PMOEthiopia

ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃ
ቃል ሐሳብን ይቀርጻል፤ ሐሳብ ደግሞ ዓለምን ይለውጣል። ንግግሮች የጊዜን ወሰን ሰብረው፣ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚሻገሩ የሕዝቦች የማንነት ማኅተምና የዘመን ምስክር ናቸው። በመሪዎች መነጽር ሲታይ ቃል ቀላል ድምፅ ሳይሆን፣ ታሪክን የሚወስን፣ ማኅበረሰብን የሚቀይር እና ሀገርን የሚገነባ የኃይል ምንጭ ነው። በመሪዎች ቃል ውስጥ ህዝብ የሀገርን ተስፋና የመሪዎቹን ርዕይ እንዲቃኝ ያስችላል። በኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽ/ቤት አዘጋጅነት የክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ(ዶ/ር) ከ2017 እስከ 2018 ዓ.ም ያደረጓቸውን ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን መልዕክቶች ዳግም «ከመስከረም እስከ መስከረም» በተሰኘው መጽሐፍ 8ተኛ ቅጽ በይፋ ለአንባቢያን ቀርቧል። እርስዎም በመጽሐፉ ዘልቀው ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለያየ አቅጣጫ ሀገር ለማቅናት የተጓዟቸውን የዓመት ጉዞ በተለያዩ ጊዜያት ባደረጓቸው ቁልፍ ንግግሮች እና ያስተላለፏቸውን አቅጣጫ ጠቋሚ መልዕክቶች ይቃኙ። ሙሉ መጽሐፉን ለማግኘት ይህን ማስፈንጠሪያ ይጫኑ:-https://share.google/uTjPqcMG1OFDWj7Xq #PMOEthiopia

እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper
+2
እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper

ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ ++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥ
+1
ከፍተኛ ዉጤት ላስመዘገባችሁ ተማሪዎቻችን እንኳን ደስ አላችሁ - ከንቲባ አዳነች አቤቤ ++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - በ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር 32 ነጥብ 3 በመቶ ተማሪዎችን በማሳለፍ 1ኛ ደረጃን መያዙን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል። ከንቲባ አዳነች አቤቤ እንደገለፁት በማህበራዊ ትስስር ገጻቸው፤ የዛሬ 12 ዓመት ያቋቋምነው የኦሮሚያ ልዩ አዳሪ ትምህርት ቤት ዘንድሮም ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100% ማሳለፍ ችሏል። ተማሪ ጃለላ ግርማ ኩሳ 591.6 ወጤት በማምጣት እንደ ሀገር ከፍተኛ ነጥብ በማስመዝገብ አንደኛ ወጥቷል። በከተማ አስተዳደሩም የእቴጌ መነን የሴቶችና ገላን የወንድ ተማሪዎች አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ጨምሮ 24 ትምህርት ቤቶች ያስፈተናቸውን ተማሪዎች 100 ፐርሰንት ማሳለፍ ችለዋል ብለዋል። በሀገር አቀፍ ደረጃ በማህበራዊ ሳይንስ ከሴት ተማሪዎች መካከል ከፍተኛው ውጤት 569.1 ያመጣችዉ በከተማ አስተዳደሩ ከሚገኘው ከቦሌ ሱፕር ሆሊ ሴቪየር ት/ቤት ተማሪ መቅደላዊት ሱራፌል ማሞ መሆኗንም ገልጸዋል። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በቀጣይ ከዚህ የላቀ ውጤት ለማስመዝገብ የተጀመረውን ስትራቴጂ በአግባቡ መተግበር፣ የትምህርት አመራሮች፣ ባለሙያዎችና ባለድርሻ አካላት በቅንጅት መስራት፣ ወላጆች ለተማሪዎች ውጤት መሻሻልና ለትምህርት ልማት ስራው ስኬት ባለቤት ሆኖ መስራትና ተማሪዎች ለላቀ ውጤት መትጋት ይጠበቅባቸዋል።

የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን ዛሬ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮው ማየት ይችላል - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ***** ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህ
+2
የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤትን ዛሬ ከምሽቱ አንድ ሰዓት ጀምሮው ማየት ይችላል - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ***** ጋዜጣ_ፕላስ- የ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤት የሚገለጽበት አድራሻ ይፋ ማድረጉን የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት አስታወቀ በ2018 ትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ፈተና ውጤትን ተፈታኞች ዛሬ ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 1 ሰዓት ጀምረው የሚከተሉትን አማራጭ ማስፈንጠሪያዎችን በመጠቀም ማየት እንደሚችሉ የትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ባወጣው መረጃ አስታውቋል። ተፈታኞች ቅሬታ ሲኖራቸው በአካል መምጣት ሳያስፈልግ https://result.eaes.et/complaint የሚለውን ማስፈንጠሪያ በመጠቀም ቅሬታቸውን ከነሐሴ 19 እስከ 26 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 10፡00 ሰዓት ድረስ በማቅረብ ምላሹንም በተመሳሳይ ማስፈንጠሪያ በኩል መከታተል እንደሚችሉ አመልክቷል። #Ethiopia #ExaminationResult #12Class #ExamResult #education #EthiopiaProgress

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ ++++++++++++++++++ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንኳን ለ1501ኛው የነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) የመውሊድ በዓል አደረሳችሁ። የነቢዩ መሐመድ ታሪክ ትውልድን ለበጎ ከሚቀርጹ ታሪኮች መካከል አንዱ ነው፡፡ የተጠሩበትን ዓላማ ማክበር፤ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ መክፈል፤ የተጠሩበትን ለሌሎች ማካፈል፤ የተጠሩበትን አክብሮ መኖር - እነዚህ ሁሉ ሺ መጻሕፍት የሚወጧቸው ትምህርቶች ናቸው፡፡ ነቢዩ የተጠሩበትን ዓላማ በሚገባ ስለተገነዘቡ አክብረው ኖረዋል፡፡ የተጠሩት ለተራና ርካሽ ነገር እንዳልሆነ ተገንዝበዋል፡፡ የተጠሩት ትውልድን ለመቅረጽና ታሪክን ለመቀየር መሆኑን አምነዋል፡፡ ያንንም በቃላቸው፣ በሥራቸውና በኑሯቸው አክብረውት ነኖረዋል፡፡ ለታላቅ ሀገራዊ ዓላማ ተጠርተናል ብለን የምናምን ከሆነ ይህ የነቢዩ ሕይወት ታላቅ ትምህርት ይሆነናል፡፡ የተጠራንበትን ዓላማ በንግግራችን፣ በሥራችንና በሕይወታችን እንግለጠው፡፡ ነቢዩ ለተጠሩበት ዓላማ ዋጋ ከፍለዋል፡፡ ከቦታቸው ተሰደዋል፤ ምግብና መጠለያ ተነፍገዋል፤ ከቤተሰቦቻቸው ተለይተዋል፡፡ ለሞት በሚያበቁ ፈተናዎች ውስጥ አልፈዋል፡፡ ጦርነት ተከፍቶባቸዋል፡፡ ነገር ግን ሁሉንም በአላህ ኃይል አሸንፈዋል፡፡ ክብር ያለ መከራ አይገኝምና፡፡ እውነተኛ ሰው ለዓላማው እንደ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ)ዋጋ ይከፍላል፡፡ ዓላማው የሚያስገኘውን ክብርና ጥቅም ብቻ ሳይሆን ዓላማው የሚያስከፍለውን መሥዋዕትነት ለመክፈል ዝግጁ ይሆናል፡፡ ነቢዩ መሐመድ(ሰዐወ) ከአላህ የደረሳቸውን መልእክት ለራሳቸው ብቻ አላስቀሩም፡፡ የተጠሩበትን ለሌሎች ለማካፈል ተግተዋል፡፡ መጀመሪያ በጣት ለሚቆጠሩ ሰዎች፣ በኋላም ለቅርብ ሱሐባዎች፣ በመጨረሻም ለዓለም መልእክቱን አዳርሰዋል ፡፡ እሳቸው የዘሩት ዘር እያፈራና እየጎመራ ተጉዟል፡፡ ዓላማችንን እኛ ማወቃችንና ማመናችን ብቻ ጥቅም የለውም፡፡ ሌሎች እንዲያውቁና እንዲያምኑ ልክ እንደነቢዩ ተገትተን መድከም አለብን፡፡ የነቢዩን መውሊድ ስናከብር ከሕይወታቸው እየተማርን፤ የተማርነውንም ለሀገረ መንግሥት ግንባታችን እየተጠቀምን እንዲሆን አደራ እላለሁ፡፡ በድጋሚ መልካም የመውሊድ በዓል ይሁንልን። ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ነሐሴ 19 ቀን 2018 ዓ.ም

አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሪከርድን ሰበረ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቦነስ አይረስ በተካሄደው ውድድር የግማሽ ማራቶን ሪከርድ ሰብሯ
አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ የዓለም የግማሽ ማራቶን ሪከርድን ሰበረ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ኢትዮጵያዊው አትሌት ዮሚፍ ቀጀልቻ በቦነስ አይረስ በተካሄደው ውድድር የግማሽ ማራቶን ሪከርድ ሰብሯል። አትሌቱ ርቀቱን በ56 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ በማጠናቀቅ አዲስ የዓለም ሪከርድ አስመዝግቧል። በዚህም አትሌት ዮሚፍ ዩጋንዳዊው ጃኮብ ኪፕሊሞ ከዚህ በፊት አስመዝግቦት የነበረውን 57 ደቂቃ ከ20 ሴኮንድ የዓለም ሪከርድ በ29 ሴከንዶች በማሻሻል የርቀቱ የዓለም ፈጣን አትሌት መሆኑን አረጋግጧል። #WorldAthletics #TrackAndField #Athletics #TrackNation #DiamondLeague #World #Championships #DistanceRunning #TrackField #RoadToVictory

ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለ
+2
ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ሀገራዊ ምክክሩ ለቀጣናው ሰላምና ዘላቂ ዕድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ ገለጹ። ምክክሩ ብዝሃ ድምጾች የተሰሙበትና የሀገር ፍቅር ስሜት የተንጸባረቀበት እንደሆነም ጠቅሰዋል። የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት ኡሁሩ ኬንያታ በሀገራዊ ምክክር የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ባደረጉት ንግግር፤ ኢትዮጵያ ለአፍሪካ ነፃነት ምልክት ከመሆኗም በላይ "ኢትዮጵያ በአፍሪካ ውስጥ የምትገኝ አገር ብቻ ሳትሆን የጥንታዊ የአፍሪካ ሥልጣኔ መገለጫም ናት" ብለዋል። ኢትዮጵያ ለሉዓላዊነቷና ለአንድነቷ በየጊዜው ያሳየችው ጥረት ለመላው አፍሪካውያን አብነት መሆኑን የጠቆሙት ፕሬዚዳንቱ፤ የዓድዋ ድል የኢትዮጵያ ታሪክ ቢሆንም የሁሉም አፍሪካውያን የጋራ ድል መሆኑን አብራርተዋል። ኢትዮጵያ በባህል፣ በቋንቋ፣ በታሪክ፣ በሥልጣኔ እንዲሁም በተፈጥሮ ሀብት የበለጸገች አገር መሆኗን ገልጸው፤ ለአብነትም የአክሱም ሥልጣኔን፣ የታላቁን አባይ ወንዝ፣ የዓድዋን ድልና የልዩ ልዩ ብሔር ብሔረሰቦችን ባህላዊ የዳኝነትና የአስተዳደር ሥርዓቶች ጠቅሰዋል። «አዲስ አበባ የኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን የመላው አህጉሪቱ መዲና ናት» ያሉት የቀድሞው የኬንያ ፕሬዚዳንት፤ የተካሄደው ሀገራዊ ምክክር በአገሪቱም ሆነ በቀጣናው ዘላቂ ሰላምና ዕድገት ለማረጋገጥ ወሳኝ ሚና እንደሚኖረው አስረድተዋል።

ለአንድ ወር ያህል ሲካሄድ የቆየው አገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ ፕላስ- ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ
+4
ለአንድ ወር ያህል ሲካሄድ የቆየው አገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ ፕላስ- ከሐምሌ 8 ቀን 2018 ዓ.ም. ጀምሮ ሲካሄድ የቆየው ሀገራዊ የምክክር ጉባኤ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት በአዲስ አበባ ኮንቬንሽን ማዕከል በይፋ እየተከናወነ ይገኛል። በኢትዮጵያ ሕዝብ መዝሙርና በሃይማኖት አባቶች ጸሎት በተከፈተው በዚህ የመዝጊያ ሥነ-ሥርዓት ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የቀድሞ እና የአሁኑ የአገሪቱ ፕሬዚዳንቶች፣ እንዲሁም ሌሎች ከፍተኛ የአገር መሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። በጉባኤው ላይ ከተለያዩ የአገሪቱ አካባቢዎች የተወጣጡ 4 ሺህ ተሳታፊዎች በተገኙበት በስምንት አጀንዳዎች ላይ ላለፉት ሳምንታት ሰፊ ውይይት ሲደረግ ቆይቷል። #ጋዜጣ_ፕላስ #ሀገራዊ_ምክክር #አዲስ_አበባ #NationalDialogue #ኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት #ኢትዮጵያ

ከኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርትና ተያያዥ አገልግሎቶች 474 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ተገኘ ++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ኢትዮጵያ በተጠናቀቀው 2018 በጀት ዓመት ከኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት፣ ከሀገር ውስጥ ዳታ ማይኒንግና ከቴክኖሎጂ ኩባንያዎች ሽያጭ 474 ሚሊዮን የአሜሪካን ዶላር ገቢ ማግኘቷን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ። የተቋሙ የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሞገስ መኮንን ለጋዜጣ ፕላስ እንዳስታወቁት፣ ከተገኘው አጠቃላይ ገቢ 120 ሚሊዮን ዶላር ገደማ የሚሆነው በቀጥታ ለጎረቤት ሀገራት ከተደረገ የኤሌክትሪክ ኃይል ሽያጭ የተገኘ ነው። ቀሪው በሀገር ውስጥ ሆነው የውጭ ምንዛሬ ከሚከፍሉ የዳታ ማይኒንግና የቴክኖሎጂ ተቋማት የተሰበሰበ ነው ብለዋል። ኢትዮጵያ በምሥራቅ አፍሪካ ቀጣና የኤሌክትሪክ ኃይል ትስስርን ለማጠናከር በሚደረገው ጥረት ውስጥ ዋና ተዋናይ ሆና እያገለገለች መሆኗን ያነሱት አቶ ሞገስ፤ በአሁኑ ወቅት ወደ ጅቡቲና ኬንያ የሚደረገው የኃይል ኤክስፖርት በተሳካ ሁኔታ እየቀጠለ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተለይም ከኬንያ ጋር ያለው የኃይል ትስስር አፈጻጸም ከፍተኛ ውጤት እየታየበት እንደሚገኝም ጠቅሰዋል። በሁለቱ ሀገራት ስምምነት መሠረት በከፍተኛ የኃይል ፍላጎት ሰዓታት እስከ 200 ሜጋ ዋት እንዲሁም በዝቅተኛ የፍላጎት ሰዓታት ደግሞ 65 ሜጋ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል እየቀረበ ይገኛል። የኃይል አቅርቦቱ የኬንያን የኤሌክትሪክ ሲስተም መረጋጋት ከማስጠበቅ ባሻገር፣ ሀገሪቱ ከውጭ ከምታስገባው ኢነርጂ እስከ 90 ከመቶ የሚሆነውን ከኢትዮጵያ እንድታገኝ አስችሏታል። በሌላ በኩል፣ ወደ ሱዳን ይደረግ የነበረው የኃይል ኤክስፖርት ሀገሪቱ በገባችበት የእርስ በእርስ ግጭት ምክንያት ሙሉ በሙሉ የተቋረጠ ሲሆን፤ በጦርነቱ ምክንያት በሱዳን በኩል ያለው የኢነርጂ ተሸካሚና አስተላላፊ መሠረተ ልማቶች በከፍተኛ ሁኔታ በመጎዳታቸው የኃይል አቅርቦቱ ሊቆም ችሏል። ከሱዳን ጋር የተፈጠረው የኃይል መቋረጥ ከመሠረተ ልማት ጋር ብቻ የተያያዘ እንጂ ከቀደመ ክፍያ ወይም ከውዝፍ ዕዳ ጋር የሚገናኝ አለመሆኑን አስታውቀዋል። የሀገር ውስጥ የኃይል ማመንጨት አቅምን በተመለከተ፣ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት ከተያዘለት እቅድ ውስጥ 99 ነጥብ አምስት ከመቶ ያህሉን በማሳካት ከፍተኛ አፈጻጸም ማስመዝገቡ ተጠቁሟል። ሀገሪቱ ካመነጨችው አጠቃላይ 35 ቴራ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል ውስጥ 51 ነጥብ አምስት ከመቶውን ወይም ከግማሽ በላይ የሚሆነው የተመረተው ከሕዳሴው ግድብ መሆኑንም አቶ ሞገስ ተናግረዋል። የኤሌክትሪክ ኃይል ኤክስፖርት ከውጭ ምንዛሬ ግኝት ባሻገር፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋር በሰጥቶ መቀበል መርኅ ላይ የተመሠረተ የኢኮኖሚና የሰላም ትስስር ለመፍጠር ትልቅ ሚና እየተጫወተ ይገኛል። የአፍሪካ ኅብረት የ“አጀንዳ 2063” አካል የሆነውን የፋሲሊቲዎችና የመሠረተ ልማት ትስስር ግብ ለማሳካት ኢትዮጵያ የበኩሏን ድርሻ እየተወጣች መሆኗን ያነሱት ዳይሬክተሩ፤ ኢትዮጵያ ከኃይል ሽያጭ የምታገኘው የውጭ ምንዛሬ በሀገር ውስጥ ያለውን የኤሌክትሪክ ተደራሽነት አሁን ካለበት 54 ከመቶ ለማሳደግና አዳዲስ የመሠረተ ልማት ፕሮጀክቶችን ለመገንባት በሚደረገው ጥረት ውስጥ ከፍተኛ እገዛ እንደሚያደርግም ገልጸዋል። በዮርዳኖስ ፍቅሩ

በነገው ዕለት የተጠናቀረው የመጨረሻው ሰነድ ለአራት ሺህ ተሳታፊዎች ይቀርባል -ሀገራዊ ምክር ኮሚሽን ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ዛሬ ምሽት 120ዎቹ አጠናቃሪዎች ከስምንቱም ቡድኖች የሚሰ
በነገው ዕለት የተጠናቀረው የመጨረሻው ሰነድ ለአራት ሺህ ተሳታፊዎች ይቀርባል -ሀገራዊ ምክር ኮሚሽን ++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- ዛሬ ምሽት 120ዎቹ አጠናቃሪዎች ከስምንቱም ቡድኖች የሚሰጡትን የመጨረሻ ግብዓቶች በማካተት የመጨረሻውን ሰነድ በነገው ዕለት ለ4ሺ ተሳታፊዎች እንደሚያቀርቡ ሀገራዊ ምክር ኮሚሽን ገለጸ፡፡ የምክክር ሂደቱ አንድ ትልቅ ምዕራፍ ላይ መደረሱን የሚያሳይ መሆኑን ወይዘሮ ሒሩት አስታውቀዋል። ሀገራዊ ምክር ኮሚሽን ምክትል ዋና ኮሚሽነር ሂሩት ገብረስላሴ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፤ ከስምንቱ ቡድኖች የተውጣጡ አጠናቃሪ ተሳታፊዎች ስራቸውን ሲሰሩ ቆይተዋል፡፡ የስምንቱንም ቡድን አጀንዳዎች አጠናቅሮ መሰነድ ጥንቃቄ የሚፈልግ ስራ በመሆኑ የተወሰነ ጊዜ ወስዷል ብለዋል በዚህም በትናትናው እለት የስምንቱም አጀንዳ ምክረ ሃሳቦች አንድ ወጥ የሆነ ሰነድ አዘጋጅተዋል። በዛሬው ዕለትም ለየስምንቱ ቡድኖች እየቀረበ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ ይህ ሂደትም እያንዳንዱ ቡድን ያለውን የመጨረሻ ግብዓት ማስገባት ያስችለዋል። ዛሬ ምሽት 120ዎቹ አጠናቃሪዎች የመጨረሻዎቹን ግብዓቶች በማካካተት የመጨረሻውን ሰነድ አጠናቅረው ያዘጋጃሉ ብለዋል። መላው የኢትዮጵያ ሕዝብ የተዛቡ መረጃዎችን በመስማት እንዳይወዛገብ እና ትክክለኛ የሆኑ ሚዲያዎችን እንዲሁም የኮሚሽኑን ይፋዊ መግለጫዎች ብቻ እንዲከታተል ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል። በዳግማዊት አበበ

ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክቶች ተመረቁ ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ│በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሀዊ ጉደና ወረዳ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በሆ
+2
ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ የሶላር ሚኒ ግሪድ ፕሮጀክቶች ተመረቁ ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ│በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በሀዊ ጉደና ወረዳ ከ800 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡ አራት የሶላር ሚኒ ግሪድ የኃይል ማመንጫ ፕሮጀክቶች ተመረቁ። በምርቃ መርሐግብሩ የውኃና ኢነርጂ ሚኒስትር ዴኤታ ኢንጂነር ሱልጣን ወሊ (ዶ/ር) እነደገለጹት፤ የተመረቁት ፕሮጀክቶች የውሃና ኢነርጂ ሚኒስቴር ከኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ጋር በመተባበር ያስገነቧቸው ናቸው። የሶለር ሚኒ ግሪዶቹ በምዕራብ ሀረርጌ ዞን በሀዊ ጉዲና ወረዳ ባቴ፣ ቶርባን፣ ሃሮ ኦባና ሃሎ ጎባ ቀበሌዎች ላይ የሚገኙ ሲሆን፤ ከ900 ኪሎ ዋት በላይ የማመንጨት አቅም አላቸው ብለዋል። ፕሮጀክቶቹ ከ5 ሺህ 270 በላይ አባውራዎችንና የማህበራዊ ተቋማትን ተጠቃሚ የማድረግ አቅም እንዳላቸው ያላቸው ሲሆን፤ አሁን ላይ በአራቱም ቀበሌዎች ከ840 በላይ ደንበኞች ተጠቃሚ መሆናቸውን ጠቁመዋል። ፕሮጀክቱ በሙሉ አቅሙ ደንበኞችን ተጠቃሚ ማድረግ እንዲችል የድጋፍና ክትትል ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላል ያሉት ሚኒስትር ዲኤታውበቀጣይም ከዋናው መስመር ርቀው የሚገኙ አካባቢዎችን በጸኃይ ኃይል ኢነርጂ ተደራሽ የማድረግ ስራው ተጠናክሮ እንደሚቀጥል አመላክተዋል። በሄለን ወንድምነው #የኢትዮጵያኤሌክትሪክአገልግሎት #ጋዜጣ_ፕላስ #የፀሐይኃይልማመንጫ #ምዕራብሐረርጌ #ሶላርሚኒግሪድ #ኢትዮጵያ #GazettePlus #SolarEnergy #Ethiopia

“ትግራይ ወጣቶች በየቀኑ የሚታፈሱባት ፍትሕ አልባ ክልል ሆናለች” -ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ │ ትግራይ ወጣቶች የሚሰደዱባት፣ በየቀኑ የሚታፈሱባትና በግዳጅ ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገቡባት ፍትሕ አልባ ክልል ሆናለች ሲሉ የስምረት ፓርቲ የሥራ አስፈጻሚ አባል ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ገለጹ፡፡ ፕሮፌሰር ክንደያ ገብረሕይወት ለጋዜጣ ፕላስ እንደተናገሩት፤ የሕወሓት ቡድን በቅርቡ የትግራይን ሕዝብ መብት የሚጥስ አፋኝና ሕገ-ወጥ ሕግ አውጥቷል፡፡ በዚህም ምክንያት ወጣቶች የሚሰደዱበት፣ በየቀኑ የሚታፈሱበትና ወደ ወታደራዊ ማሰልጠኛ የሚገቡበት አሰጋጭና ፍትሕ አልባ ሁኔታ መፈጠሩን ገልጸዋል፡፡ በሕገ-ወጡ የሕወሓት ቡድን ምክንያት የትግራይ ሕዝብ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ቀውስ ውስጥ ይገኛል ያሉት ፕሮፌሰር ክንደያ፤ ወጣቶች በተለያየ መንገድ ወደ አዲስ አበባ፣ ወደ ሌሎች ክልሎችና ወደ ጎረቤት ሀገራት በስደት በመውጣታቸው የክልሉ ከተሞች ወጣት አልባ እየሆኑ መጣታቸውን አስረድተዋል፡፡ ቡድኑ ትግራይንና የትግራይን ሕዝብ እንደ መያዣ (ጋሻ) አድርጎ እየተጠቀመ መሆኑን በመጠቆም፤ መሠረታዊ ሰብዓዊ መብቶች በመጣሳቸው ምክንያት ሕዝቡ በከፍተኛ ደረጃ እየተሰቃየ እንደሚገኝ ገልጸዋል፡፡ በትግራይ ክልል አመርቂና አስቻይ ሁኔታ ባለመኖሩ ምክንያት መሠረታዊ የሸቀጦች፣ የነዳጅና የሌሎች አቅርቦቶች እጥረት መከሰቱን የገለጹት ፕሮፌሰሩ፤ ይሁን እንጂ በፌዴራል መንግሥት የሚሰጡ መሠረታዊ የስልክ፣ የትራንስፖርትና ሌሎች አገልግሎቶች ቀጣይነት እንዳላቸው ተናግረዋል፡፡ በሌላ በኩል ሕገ-ወጥ የማዕድን ቁፋሮ፣ ሕገ-ወጥ የሰውና የመሣሪያ ዝውውር በየከተማው እንደሚፈጸም አብራርተው፤ በአሁኑ ወቅት ክልሉ በከፍተኛ አጠቃላይ ቀውስ ውስጥ እንደሚገኝ ጠቁመዋል፡፡ የሕወሓት ቡድን የጊዜያዊ አስተዳደሩን በማፍረስ በኃይል ሥልጣን መቆጣጠሩንና ክልሉን ጨምድዶ በመያዝ በሌሎች የሀገሪቱ አካባቢዎች ምርጫ ሲካሄድ በትግራይ እንዳይካሄድ ማድረጉንም አብራርተዋል። በማርቆስ በላይ #ጋዜጣ_ፕላስ #ትግራይ #ስምረትፓርቲ #ሕወሓት #ሰብዓዊመብት #ኢትዮጵያ #GazettePlus #Tigray #Ethiopia

እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper
+1
እንደምን አደራችሁ? #አዲስ_ዘመን_ጋዜጣ- https://press.et/e-paper