uz
Feedback
Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/

Kanalga Telegram’da o‘tish

Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Ko'proq ko'rsatish

📈 Telegram kanali Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ analitikasi

Gazette Plus / ጋዜጣ ፕላስ/ (@ethpress) Amxar til segmentidagi kanali faol ishtirokchi. Hozirda hamjamiyat 24 926 obunachidan iborat bo'lib, Yangiliklar & Media toifasida 9 734-o'rinni va Efiopiya mintaqasida 1 347-o'rinni egallagan.

📊 Auditoriya ko‘rsatkichlari va dinamika

невідомо sanasidan buyon loyiha tez o‘sib, 24 926 obunachiga ega bo‘ldi.

13 Iyun, 2026 dagi oxirgi ma’lumotlarga ko‘ra kanal barqaror faollikka ega. Oxirgi 30 kunda obunachilar soni -200 ga, so‘nggi 24 soatda esa -4 ga o‘zgardi va umumiy qamrov yuqori darajada qolmoqda.

  • Tasdiqlash holati: Tasdiqlangan (Telegram tomonidan rasmiy tasdiq)
  • Jalb etish (ER): Auditoriya o‘rtacha 13.32% darajada jalb etiladi. Nashrdan keyingi dastlabki 24 soatda kontent odatda umumiy obunachilar sonining 5.24% ini tashkil etuvchi reaksiyalarni to‘playdi.
  • Post qamrovi: Har bir post o‘rtacha 3 321 marta ko‘riladi; birinchi sutkada odatda 1 307 ta ko‘rish yig‘iladi.
  • Reaksiyalar va o‘zaro ta’sir: Auditoriya faol: har bir postga o‘rtacha 7 ta reaksiya keladi.

📝 Tavsif va kontent siyosati

Muallif resursni shaxsiy fikrni ifoda etish maydoni sifatida ta’riflaydi:
Ethiopian Press Agency, established in 1940 , is a public printing media enterprise operating in Ethiopia.

Yuqori yangilanish chastotasi (oxirgi ma’lumot 14 Iyun, 2026 da olingan) sababli kanal doimo dolzarb va katta qamrovli bo‘lib qoladi. Analitika auditoriya kontent bilan faol hamkorlik qilishini, uni Yangiliklar & Media toifasidagi muhim ta’sir nuqtasiga aylantirishini ko‘rsatadi.

24 926
Obunachilar
-424 soatlar
-487 kunlar
-20030 kunlar
Postlar arxiv
"በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል” - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮችን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት መቻሉን ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ መታቀዱንም ገልጸዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በማኅበራዊ ትሥሥር ገጽ ባሰፈሩት መልዕክት፣ “‎በሦስት ዓመታት ውስጥ ለማሳካት የታቀደውን ግብ ከሁለት ዓመት ባነሰ ጊዜ ውስጥ ማሳካት ተችሏል። ለዚህም ለመላው ኢትዮጵያውያን የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። የ“5 ሚሊዮን የኢትዮጵያ ኮደሮች” ሐምሌ 16 ቀን 2016 ዓ.ም ከተጀመረበት ጊዜ አንሥቶ በኮምፒውተር ፕሮግራሚንግ፣ በመረጃ ትንተና፣ በአንድሮይድ ሶፍትዌር ልማትና በአርቴፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ ትምህርቶች 5,005,146 ሠልጣኞች ተመዝግበው ከ3 ሚሊዮን በላይ የሚሆኑት ሥልጠናውን አጠናቀዋል ብለዋል። ይህ ስኬት የሕዝባችንን ቁርጠኝነት እና ወሰን የሌለው አቅም ማረጋገጫ ነው ብለዋል። ‎ ‎በዲጂታሉ ዓለም በልኩ ለመዘጋጀት የጀመርነው ታሪካዊ ምዕራፍ፤ የጉዟችን ማብቂያ ሳይሆን፥ ብሔራዊ ርዕያችንን ይበልጥ የምናፋጥንበት መነሻ እንደሆነም ጠቁመዋል። እስከ ነሐሴ 2018 ዓ.ም ድረስ የሠልጣኞችን ቁጥር 7 ሚሊዮን ለማድረስ የተሰነቀውን ግብ ለማሳካት፣ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ የዚህ ብሔራዊ ተልዕኮ አካል እንዲሆን ጥሪያቸውን አቅርበዋል። ‎ ‎ለወጣት ተማሪዎቻችን፤ መጭው የክረምት ወቅት ትልቅ ዕድላችሁ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ ጊዜያቸውን በዋዛ ከማሳለፍ ተቆጥበው በመመዝገብ እና በመማር ወደ ትምህርት ገበታቸው ሲመለሱ ተማሪዎች ብቻ ሳይሆኑ፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያላቸው የዲጂታል መሪዎች እንዲሆኑ አሳስበዋል። ሥልጠናዎቹ ሙሉ በሙሉ በነጻ የሚሰጡ ሲሆን፣ የምስክር ወረቀቱም በዓለም አቀፍ ደረጃ እውቅና ያለው ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ “‎የምትገነቡት ነገ የሚጀምረው ዛሬ ነው!” ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል። ‎ለመመዝገብ እዚህ ይጫኑ- ‎ethiocoders.et/

የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‼️ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባችንን ተከትሎ፣ እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት
+7
የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) መልዕክት ‼️ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባችንን ተከትሎ፣ እጅግ ዘመናዊና ፈጣን የቴክኖሎጂ ግብዓቶችን በመጠቀም የተገነቡ ቤቶችን የሚያሳይ የግንባታ ሳይት ጎብኝተናል። በዚህ ሳይት ሦስት የላቁ የግንባታ ዘዴዎች በጥምረት ጥቅም ላይ ውለዋል፤ የ3ዲ ህትመት፣ የቅድመ-ዝግጅት ቀላል የአረብ ብረት ግንባታና የኮንቴይነር መኖሪያ ቤቶች ናቸው። እያንዳንዳቸው ግንባታዎች ትክክለኛውን ቴክኖሎጂ ስንጠቀም ጥራታቸውን የጠበቁ መኖሪያ ቤቶችን ከወራትና ከዓመታት ይልቅ በጥቂት ቀናትና ሳምንታት ውስጥ ሰርቶ ማጠናቀቅ እንደሚቻል የታየበት ህያው ምስክር ናቸው። ‎ይህ አይነቱ የላቀ ፈጠራ በየትኛውም የሀገሪቱ ክፍል በቀላሉ ሊተገበር፣ ሊደገምና ሊስፋፋ የሚችል በመሆኑ የሀገራችንን የቤት ልማት ፕሮግራም አቅጣጫ በከፍተኛ ደረጃ የመቀየር ኃይል አለው። ቴክኖሎጂን ከሀገራዊ ርዕያችን ጋር አጣምረናል፤ መሰል በተግባር የተገለጡ ስራዎቻችን ደግሞ ለሀገር የሚገባውን ፈጣን ዕድገት እውን ለማድረግ በትክክለኛው አቅጣጫ ላይ በቁርጠኝነት እየተጓዝን መሆናችንን በተግባር አሳይቷል። #ኢትዮጵያ #ታዳሽኃይል Office of the Prime Minister-Ethiopia #technology #TechHouse

የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት በጀት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ እንዲሆን ተወሰነ +++++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ| የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት
የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት በጀት ከሁለት ትሪሊዮን ብር በላይ እንዲሆን ተወሰነ +++++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ| የፌዴራል መንግስት የ2019  በጀት ዓመት ረቂቅ በጀት ሁለት ነጥብ ሦስት ትሪሊዮን ብር ሆኖ ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ውሳኔ አሰለፈ። የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ የፌዴራል መንግስት የ2019 በጀት ዓመት  የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አስተላልፏል፡፡ ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግስታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ የሚውል 2,339,268,126,738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት ብር) በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ለህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ ረቂቅ በጀቱ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ በማድረግ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማህበራዊና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎችና አላማዎች፣ በመንግስት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግስትን የፋይናንስ አቅምና አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮና ሃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ መቅረቡ ተገልጿል። መስከረም ሰይፉ ++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ #gazette_plus

56ኛ መደበኛ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብስባ ውሳኔዎች +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ - የሚኒስትሮች ምክር ቤት በዛሬው ዕለት ባካሄደው 56ኛ መደበኛ ስብሰባ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ተወያይቶ ውሳኔ አሳለፈ፡፡ ✍️ የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ምክር ቤቱ በቅድሚያ የተወያየው የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና ፊስካል ማዕቀፍ ላይ ነው፡፡ የተሟላ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ተግባራዊ ከተደረገ ወዲህ የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ካሉበት ተግዳሮቶች እየተላቀቀና የኢኮኖሚው መሰረቶችም እየተጠናከሩ መጥተዋል፡፡ ማዕቀፉ በኢኮኖሚ ሪፎርሙ የተገኙ አበረታች ውጤቶችን ይበልጥ አጠናክሮ ማስቀጠል እንዲያስችልና በዋና ዋና የማክሮ ኢኮኖሚ እና ፊስካል ታሳቢዎች ላይ በመመስረት የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት በጀት ዝግጅት መነሻ ሆኖ እንዲያገለግል ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱ በማዕቀፉ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ በስራ ላይ እንዲውል በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ ✍️ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የበጀት ረቂቅ አዋጅ የ2019 በጀት ዓመት የፌዴራል መንግስት የበጀት ረቂቅ አዋጅ ላይ ነው፡፡ የ2019 የፌዴራል መንግስት በጀት የአስር አመቱ መሪ የልማት ዕቅድ አካል የሆነው የ2019-2021 የልማትና ኢንቨስትመንት ዕቅድ ላይ የተቀመጡ ግቦችንና የመካከለኛ ዘመን (2019-2023) የማክሮ ኢኮኖሚና የፊሲካል ማዕቀፍን መሰረት በማድረግ፣ የ2018 በጀት ዓመት የፕሮግራም በጀት አፈጻጸም መነሻ ፣ በቀጣይ ሊኖር የሚችለውን የማህበራዊና የኢኮኖሚ ትራንስፎርሜሽን አቅጣጫዎችና አላማዎች እንዲሁም በመንግስት የተቀመጡ ግቦችን ለማሳካት የመንግስትን የፋይናንስ አቅምና አስፈጻሚ መስሪያ ቤቶች ከተሰጣቸው ተልዕኮና ሃላፊነት አንጻር የሚያስፈልገውን ወጪ በመገምገም ተዘጋጅቶ ቀርቧል፡፡ በዚሁ መሰረትም ለመደበኛ ወጪዎች፣ ለካፒታል ወጪዎች፣ ለክልል መንግስታት ድጋፍ፣ ለዘላቂ የልማት ግቦች ማስፈጸሚያ ድጋፍ የሚውል 2,339,268,126,738 (ሁለት ትሪሊዮን፣ ሶስት መቶ ሰላሳ ዘጠኝ ቢሊዮን፣ ሁለት መቶ ስድሳ ስምንት ሚሊዮን፣ አንድ መቶ ሀያ ስድስት ሺ፣ ሰባት መቶ ሰላሳ ስምንት ብር) በጀት ለምክር ቤቱ ቀርቧል፡፡ ምክር ቤቱም በቀረበው የፌዴራል መንግስት የ2019 ረቂቅ በጀት አዋጅ ላይ በሰፊው ከተወያየበት በኋላ ግብአቶችን በማከል ወደ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እንዲተላለፍ በሙሉ ድምጽ ወስኗል፡፡ ሰኔ 2 ቀን 2018 ዓ.ም አዲስ አበባ

በብስክሌት “ሜትር ታክሲ” +++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- የታክሲ ሰልፉ ረዥም ነው። ስንት ሰዓት ነው ወረፋ የሚደርሰኝ? ታክሲ ባገኝ ደግሞ መንገዱ ይዘጋጋል። በሰዓቴ ሥራ ቦታ መገኘት ይኖርብኛል
በብስክሌት “ሜትር ታክሲ” +++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ- የታክሲ ሰልፉ ረዥም ነው። ስንት ሰዓት ነው ወረፋ የሚደርሰኝ? ታክሲ ባገኝ ደግሞ መንገዱ ይዘጋጋል። በሰዓቴ ሥራ ቦታ መገኘት ይኖርብኛል። ታዲያ ምን ይሻለኛል? ብሎ ለሚጨነቅ ሰው ጭንቀቱን የሚጋራና የሚያቃልል ችግር ፈቺ ስታርትአፕ ተፈጥሯል። ከወጪ አንፃር ገንዘብ ቆጣቢ ጤናም ለመጠበቅ የሚያስችል፤ እንግልትን የሚቀንስ ብስክሌትን በመጠቀም አዲስ ሥራ ይዘን መጥተናል ያሉ ወጣቶች ዘመን ኢኮኖሚ አነጋግራቸዋለች። ወጣቶቹ ስለ ፈጠራ ሥራቸው ያብራራሉ ። እንደ ሜትር ታክሲ አገልግሎት ብስክሌትን በማጋራት ትራንስፖርትን ማቀላጠፍ ይቻላል ብለው የተነሱ ወጣቶች ዳይናሚክ የተሰኘ አክሲዮን ማኅበር መሠረቱ። ድርጅታቸው መሥራት ካሰባቸው ሥራዎች አንዱ የትራንስፖርት ዘርፍ ነውና አንድ ለውጥ የሚያመጣ ሥራ መሥራት አለብን በሚል ሐሳብ “ፔዳል ፍላይ” የሚል ስያሜ አውጥተው ወደ ትራንስፖርት ዘርፍ ተቀላቀሉ።

ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቋል +++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ትናንት የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ወይ
ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት ተጠናቋል +++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ትናንት የተካሄደው ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ አስታወቀ። የቦርዱ ሰብሳቢ ወይዘሮ ሜላትወርቅ ኃይሉ ለብዙኃን መገናኛ በሰጡት መግለጫ፣ የድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ በስኬት ተጠናቅቋል ። በቅድመ ምርጫ፣ በምርጫ ወቅት እና የድኅረ ምርጫ ሥራዎች በአግባቡ ተከናውነዋል። የመራጮች ምዝገባ፣ የእጩዎች ምዝገባ፣ ምርጫ ለሚታዘቡ የሲቪል ማኅበረሰብ ድርጅቶች የመመዝገብ እንዲሁም ለሌሎችም አካላት ፈቃድ የመስጠት የቅድመ ምርጫ ሥራዎች በተያዘላቸው ጊዜ የተጠናቀቁ ሲሆን፤ በትናንትናው ዕለት በተካሄደው የድምጽ አሰጣጥ ሒደት በተሳካ ሁኔታ መከናወኑን አስረድተዋል። እንደ እሳቸው ገለጻ፣ ከ50 ሺህ በላይ የምርጫ ጣቢያዎች ማለዳ 12:00 ክፍት ተደርገው ድምጽ ተሰጥቶባቸዋል። የሲቪክ ማኅበራትም በየምርጫ ጣቢያዎች በመገኘት ታዝበዋል። የአፍሪካ ኅብረት እና የምሥራቅ አፍሪካ የልማት በይነ-መንግሥታት ባለስልጣን (IGAD) ታዛቢዎች ከማለዳው 12:00 ጀምሮ ሲታዘቡ ውለዋል። በብዙ አካባቢዎች የድምጽ አሰጣጥ ሒደቱ ከተጠናቀቀበት ሰዓት ጀምሮ ድምጾች የተቆጠሩ ሲሆን፤ የድምጽ አሰጣጡ ዘግይቶ በተጠናቀቀባቸው የምርጫ ጣቢያዎች ደግሞ ቆጠራ እየተከናወነ መሆኑን ጠቁመዋል። ቆጠራው እንደተጠናቀቀ አስፈላጊውን ማጣራት በማድረግ በሚቀጥሉት ቀናት ይፋ ይደረጋል። ከድምጽ አሰጣጥና ከቆጠራ ጋር በተገናኘ የሚመጡ ጥቆማዎችን በማጣራት ቦርዱ በሕግ አግባብ እርምጃ እንደሚወስድም ገልጸዋል። በአብዱረዛቅ መሐመድ #Ethiopianelection2026 #GeneralElection #EthiopiaVotes #NEBE #AfricanUnion #IGAD

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ድምፃቸውን ሰጡ ++++++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በባሕርዳር ምርጫ ክልል ህዳሴ ምርጫ ጣቢያ(
ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ድምፃቸውን ሰጡ ++++++++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ⵏ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ በባሕርዳር ምርጫ ክልል ህዳሴ ምርጫ ጣቢያ(02-1) በመገኘት ድምፃቸውን ሰጥተዋል። ሰባተኛው ጠቅላላ ምርጫ ከማለዳው 12 ሰዓት ጀምሮ በመካሄድ ላይ ሲሆን የባሕርዳር ከተማ ነዋሪዎችም በ164 የምርጫ ጣቢያዎች ድምፃቸውን እየሰጡ ይገኛሉ። በአማን ረሺድ

የኢዜማ ፓርቲ መሪ አቶ ኢዮብ መሳፍንት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ።
የኢዜማ ፓርቲ መሪ አቶ ኢዮብ መሳፍንት በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ ዘጠኝ ባህርዳር ዩኒቨርስቲ ምርጫ ጣቢያ ተገኝተው ድምጽ ሰጡ።

"ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን" -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++ #ጋዜጣ-ፕላስ | ያከበረንን አክብረን
"ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን" -ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++++++ #ጋዜጣ-ፕላስ | ያከበረንን አክብረን የመረጠንን ሰርተንለት የምናልፍ ከሆነ ሁላችንም አሸናፊ እንሆናለን ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በበሻሻ ድምፅ ሰጥተዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወቅቱ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ ህዝብ ከማለዳ ጀምሮ በመውጣት በሰልፍ ምርጫ እያካሄደ ይገኛል። ይህም የሚሻውን ለመምረጥ መካሪ እንደማያስፈልገው ማሳያ መሆኑን ተናግረዋል። እኔ ዛሬ የሚያሳስበኝ ከመራጩ በላይ ተመራጩ ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ ይህ ህዝብ በቁርጠኝነት የሚሻውን ወስኖ በዲሞክራሲያዊ መንገድ ከመረጠ በኋላ የተመረጡት ሰዎች በዚያ ልክ ታምነው እጃቸውና ልባቸው ንጹህ ሆኖ ደከመን ታከተን ሳይሉ ሰርተው የሀገር ታሪክ ለመቀየርና የህዝቡን ውለታ ለመክፈል ዝግጁነታቸው ምን ያክል ነው የሚለው ነው ሲሉ ተናግረዋል" በምርጫው ሂደት ያሸነፉ በታማኝነት ማገልገል የተሸነፉ ደግሞ ውጤቱን በጸጋ ሊቀበሉ እንደሚገባ አሳስበዋል። ++++++++++++++ @የኢትዮጵያ_ፕሬስ_ድርጅት@ጋዜጣ-ፕላስ#በምርጫብቻ#ዲሞክራሲ#ምርጫ2018#ኢትዮጵያ#አርባምንጭ #EthiopianElection 2026#ዐቢይ አሕመድ

በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድ መደበኛ ስራ እንደማይኖር ምርጫ ቦርድ አስታወቀ +++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም የ7ተኛው ጠቅላላ ምርጫ የድምፅ አሰጣጥ እንዲከናወን መወሠኑ ይታወቃል። በዚህም መሠረት በመራጭነት የተመዘገቡ ዜጎች ሁሉ በዕለቱ ድምፃቸውን ለመስጠት ይችሉ ዘንድና የደምፅ አሰጣጥ ሂደቱ ያለምንም የፀጥታ ችግር ይከናወን ዘንድ ቦርዱ የሚከተሉት ተግባራዊ እንዲሆኑ የምርጫ የፓለቲካ ፓርቲዎች ምዝገባና ሥነ-ምግባር ዐዋጅ 1162/ 2011 አንቀጽ 161 የመተባበር ግዴታ መሠረት ለመንግሥታዊና ለማንኛውም መንግሥታዊ ላልሆኑ ተቋማት ያሳውቃል። በዚህም መሠረት፤ ✍️ ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ የፌዴራል እና የክልል መንግሥታዊ ተቋማት ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ሥራ ዝግ እንዲያደርጉ፣ ✍️ ዜጎች ዕለቱን ለድምፅ መስጫ ብቻ መጠቀማቸው ስለሚያስፈልግ በፌዴራል እና በክልሎች የሚገኙ ማንኛውም መንግሥታዊ ያልሆኑና የግል ተቋማት በተመሳሳይ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓ.ም. ዝግ እንዲያደርጉ እያሳወቀ፤ ✍️ የአስቸኳይ ጊዜ አገልግሎት የሚሰጡ ተቋማት፣ ሆስፒታሎች፣ የዕለት ተዕለት አገልግሎት ሰጪዎችም (ሆቴሎች፣ ሬስቶራንቶች፣ የትራንስፓርት አገልግሎት) በዝግ ቀናት የሚያደርጉትን አገልግሎት በተመሳሳይ የሚያከናውኑ ሲሆን፤ የመተባበር ግዴታው እነዚህን ተቋማት እንቅስቃሴ መዘጋት አያስገድድም። ✍️ የትራንስፓርት አገልግሎት በተለመደው መንገድ የሚቀጥል ቢሆንም፤ ዜጎች ድምፅ ከመስጠት ውጪ ከፍተኛ እንቅስቃሴን የሚፈልጉ ሁነቶችንና ዕቅዶችን እንዳይይዙና እንቅስቃሴያቸውን ድምፅ ለመስጠት ብቻ እንዲያደርጉ ቦርዱ ያበረታታል። #ምርጫ #ኢትዮጵያ Ethiopian Press Agency /የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት/ #gazette_plus

ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላለፉ +++++++++++++++++ #ጋዜጣ_ፕላስ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል። እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሐ በዓል አደረሰን፣ አደረሳችሁ! ስለዒድ አል-አድሐ “ዐረፋ” በዓል ስናስብ ሦስት ነገሮች ቀድመው ይታወሱናል። መስዕዋትነት፣ መታዘዝና መተጋገዝ። አባት ልጁን ለመስዕዋት ያቀረበበት፤ ልጅ የአባቱን ትዕዛዝ የፈጸመበት፤ ሙስሊሞች የመተጋገዝን እሴት ለዓለም የገለጡበት በዓል ስለሆነ “ዐረፋ” በሕዝበ-ሙስሊሙ ዘንድ ትልቅ ትርጉም አለው። እስማኤል ለነብዩ ኢብራሂም የመጀመሪያ እና ተወዳጅ ልጃቸው ነው። አላህ (ሱ.ወ.) ይሄን ተወዳጅና የመጀመሪያ ልጅ እንዲሠዉለት ሲጠይቃቸው ታዘዙ እንጂ ወደኋላ አላሉም። ለመታዘዝ የሞከሩት ነገሩ ቀላል ሆኖ አይደለም። ልጅን ያህል ነገር መስዕዋት ማድረግ ምኑ ይቀላል? የአባትነት ስሜት ይተናነቃል። የሰይጣን ሹክሹክታ ይፈታተናል። የቤተዘመድን ወቀሳ እና የጎረቤትን አስተያየት መቋቋምም ይከብዳል። ነብዩ ኢብራሒም፥ በዚህ ሁሉ አጣብቂኝ ውስጥ አንድ ሐቅ ተገልጦላቸዋል። ከራስ ስሜት፣ ከሰው ሐሜት እና ከወዳጅ ፍላጎት የሚልቅ ታላቅ ዓላማ እንዳለ አምነዋል። ስለዚህም በፈተና ውስጥ ጸንተው ቆሙ፤ ቆራጥነታቸውም በተግባር ታየ። ሀገር የምትገነባው ከራስ ጥቅም በላይ በሚያስቡ እና ከግላዊ ፍላጎታቸው በላይ ለመፈጸም በቆረጡ ዜጎች ነው። የሚወዱትን ነገር እንኳን ሳይቀር ለመሠዋት ዝግጁ የሆኑ ዜጎች ሲበዙላት ሀገር ትበረታለች። እስማኤላቸውን ለመስጠት የማያመነቱ ዜጎች የሞሉባት ሀገር ጽኑ ናት። የለመድናቸው፣ የምንወዳቸው፣ የራሳችን ገንዘብ ያደረግናቸው ብዙ ነገሮች ይኖራሉ። ከእነዚህ የሚበልጥ ዓላማ ግን አለ፤ እሱም “ሀገርነት እና ሉአላዊነት” ይሰኛል። ሀገርነት የሚገነባው ከመውሰድ ይልቅ በመስጠት ነው። ሉአላዊነት የሚጸናው በፈተና ሳይወድቁ በመቆም፤ በወጀብ ሳይናወጡ መጓዝ በመቻል ነው። የእውነት ኢትዮጵያ ሲያልፍላት ማየት የምንሻ ከሆነ ምኞታችን በተግባር ይገለጥ። የሀገር ኩስመና ካሳሰበን ለግዝፈቷ እንድከም። ያጎበጣትን የድህነት ቋጥኝ ለመሸከም ትከሻችንን እናመቻች። ጎተራዋ እንዲሞላ እጃችን አፈር ይንካ። የጠየመ ገጽዋ እንዲፈካ በሥራ ሌት-ተቀን እንሰለፍ። የተቀማ ክብሯ እስኪመለስ ድርሻችንን እንወጣ። ሀገር መውደዳችን ከልብ ከሆነ መስዕዋት ለመሆን አናመንታ። የዐረፋ በዓል የመታዘዝና የመስዕዋት ብቻ ሳይሆን የመደጋገፍና የመተጋገዝ በዓል ጭምር ነው። በዐረፋ ከሚከናወነው እርድ አንድ ሦስተኛው ለምስኪኖች እንዲሰጥ የእስልምና አስተምህሮ ያዛል። በዐረፋ ሕዝበ-ሙስሊሙ ደስታና ሐዘኑን እየተጋራ በዓሉን ያከብራል። የዐረፋ እለት አንድም ሰው ተከፍቶ አያሳልፍም፤ በዐረፋ ሰሞን ማንም ሰው ተርቦና ተጠምቶ አያድርም። በዓሉ ትርጉም የሚሰጠው ሕዝበ-ሙስሊሙ ያለውን ተካፍሎ ሲያከብረው ነው። ሰዎች አስቸጋሪ ሁኔታን የሚሻገሩበት መፍትሄው መተሳሰብና መተጋገዝ እንደሆነ ከዐረፋ እንማራለን። ሀገርም ከፈተናዎችዋ በላይ እንድትሆን እኒህ እሴቶች ወሳኝ ናቸው። ዐረፋ ማኅበረሰባዊ በዓል የሚባለው ለዚህ ነው። ሰዎች በግላቸው የሚያከብሩት አይደለም። ቤተሰቡ፣ ጎረቤቱ፣ ሠፈሩ፣ ከተማው የሚያከብረው በዓል ነው። ያላቸውና የሌላቸው፤ የሚችሉና የማይችሉ፤ ታላላቆችና ታናናሾች፤ ባለ ሥልጣናትና ተራ ዜጎች፣ በአንድነት የሚያከብሩት በዓል ነው። ሰው የሚኖረው በቤቱ ውስጥ አይደለም። በማኅበረሰቡ ውስጥ ነው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥርና ትብብር ለዜጎች እና ለሀገር ደኅንነት ወሳኝ ናቸው። ማኅበረሰባዊ ትሥሥር ስለሌሎች እንድናስብ፣ ስለሌሎች እንድንሠራ እና ስለ ሌሎች ዋጋ እንድንከፍል ያደርገናል። ራሳችንን በሌሎች ጫማ ላይ አቁመን እንድናይ ያስችለናል። የሁላችንም ሰላም፣ የሁላችንም ደኅንነት እና የሁላችንም ጥቅም ካልተከበረ በቀር የግላችንን ብቻ ልናስከብር እንደማንችል ያስገነዝበናል። ስለዚህም ማኅበራዊ ግዴታን እንደ ዜግነት ግዴታ ወስደን እንድንሠራ ያደርገናል። ምርጫ ማኅበራዊና ዜግነታዊ ግዴታዎችን ከምንወጣባቸው የዴሞክራሲ መገንቢያ መሳሪያዎች መካከል ዋነኛው ነው። ያለ ሕዝብ ተሳትፎ ዴሞክራሲ አይሳካም። ያለ ምርጫም የሕዝብ ተሳትፎ ምሉዕ አይሆንም። የዴሞክራሲያችን መሰረት ጥንካሬው የሚለካው በተሳትፎአችን መጠን ነው። የዘንድሮ ሀገራዊ ምርጫ ሀገረ-መንግሥታዊ ሥርዓታችን የሚጠነክርበት መሰረት ነው። የዴሞክራሲ ልምምዳችን አንድ ደረጃ ከፍ የሚልበት፤ የቀጣይ ዓመታት የሀገራችንን እጣ-ፈንታ የምንበይንበት፤ ከምንም በላይ ብዝሃ-ድምጽ የሚሰማበት የሕግ መወሰኛ ምክርቤት የምንመሰርትበት ወሳኝ አጋጣሚ ነው። በመሆኑም በዓሉን ስናከብር ዜግነታዊ ግዴታችንን ለመወጣት ብቻ ሳይሆን በካርዳችን ዴሞክራሲያዊ መብታችንን ለማረጋገጥ እየተዘጋጀን እንዲሆን ጥሪዬን አቀርባለሁ። በድጋሚ መልካም የዐረፋ በዓል እንዲሆን እመኛለሁ! ዒድ ሙባረክ!! ኢትዮጵያ በልጆቿ ጥረት ታፍራና ተከብራ ለዘላለም ትኑር!! ፈጣሪ ኢትዮጵያና ሕዝቦቿን ይባርክ! ግንቦት 18፣ 2018 ዓ.ም

መላው የአፍሪካ ወንድም እህቶቻችን እንኳን ለአፍሪካ ቀን አደረሳችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++ HAPPY AFRICA DAY TO ALL OUR AFRICAN BROTH
+1
መላው የአፍሪካ ወንድም እህቶቻችን እንኳን ለአፍሪካ ቀን አደረሳችሁ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ++++++++++++ HAPPY AFRICA DAY TO ALL OUR AFRICAN BROTHERS AND SISTERS! 63 years ago, our forefathers gathered right here in Addis Ababa and dared to dream of a free, united Africa, and that dream still burns bright. Today, as the proud home of the African Union, Ethiopia stands shoulder to shoulder with every African nation in that same spirit of unity.The work is far from over. Let us move from words to action, from promises to progress. Africa's greatest resource has always been her people, and together, WE RISE! #AfricaDay #Africa #Ethiopia #Afrique #AfricanUnion #dayinthelife