HAILE GEBRIEL - በማለዳ ንቁ
الذهاب إلى القناة على Telegram
❤️ ቅዱሳን አባቶች እንዲህ ይላሉ **ጸጋ ያለምስጋና አያድግም ይላሉ** እግዚአብሔር ሆይ ስለሆነልኝ፣ ክፉውንም ከእኔና ከቤተሰቦቼ ስላራክልኝ 👏 አመሰግንሃለሁ ❤️ 👇👇👇 http://www.youtube.com/@haileG2239
إظهار المزيد2 303
المشتركون
-424 ساعات
-117 أيام
-1230 أيام
أرشيف المشاركات
"የተጋመደ ሰው (የቆረበ ሰው) የክርስቶስ አካል ነው፤ ሰይጣን የክርስቶስን አካል ሊነካ አይችልም።" (ቅዱስ ቄርሎስ ዘእስክንድርያ)
እመኑኝ ከዚህ ቪዲዮ በኋላ በምንም ተዓምር ተስፋ አትቆርጡም!! መምህር ግርማን ያስለቀሳቸው ጉዳይ ምንድነው! መምህር ተስፋዬ ለምን አዘነ ምን ገጥሞት ነው!! https://youtu.be/hrb_F4WK6yY
«ሰላም ውዶች እንዴት ናችሁ ያላገባችሁ "ወንዶችም ሴቶችም" በውስጥ መስመር አናግሩኝ ለትዳር ፍቃደኛ የሆናችሁ አናግሩኝ። እንደ እግዚአብሔር ፍቃድ ትዳርን የሚሰጥ የሚባርክ እሱ እግዚአብሔር ነውና ማን ያውቃል ደግሞ በመተጋገዝ ይሄንን ነገር እውን እናደርገው ይሆናል። ስለዚህ ሁላችሁም ፍቃደኛ የሆናችሁ በውስጥ መስመር አናግሩኝ።» መልካም ቀን ለሁላችሁ ይሁን! @haile_gebrie_tube_bot
«አንድ መንግሥት "የተሳካለት መንግሥት ነው" የሚባለው መቼ ነው?»
«ክብሩና ጥንካሬው ከምን የሚመጣ ነው?»
ከሕዝቡ ብዛት ነው?
ከግዛቱ ስፋት ነው?
ከተፈጥሮ ሀብቱ ዓይነት ነው?
ከሕዝቡ ዐዋቂነትና ተመራማሪነት ነው?
ከአስተዳደር ፍልስፍናው ነው?
መሪው ከተወለደበት ዘር "ጥራት" ነው?
ከጦር መሣሪያው ብዛት ነው?
ካለው ታሪክ ርዝመት ነው?
ከሚወስዳቸው ቆራጥ እርምጃዎች ነው?
ከቴክኖሎጂው ብዛት ነው?
ወይስ ከምንድነው?
ይኼ ጥያቄ፡ ለኹሉም የሰው ልጆች፥ በተለይ ደግሞ ለመሪዎች፡ አንገብጋቢ ጥያቄ ነው።
ጎርጎሬዎስ ገባሬ ተአምራት የተባለው ጻድቅ ("ሌላኛው ጎርጎሬዎስ ነው" የሚሉም አሉ)፡ ይኽን ጥያቄ ይዞ፡ በጸሎትና በሱባኤ መሃል በሃሳቡ ሲያመላልስ፡ እግዚአብሔር መልስ ሰጠው። መልሱም፡ "የነገሥታት ክብራቸው፥ ጽናታቸውና የብርታታቸው ምንጭ፡ ጽዮን ናት" የሚል ነው። ከፍጥረት አንሥቶ ያለውን የጽዮንን ታሪክም ገለጠለት። ከርሷም ጋር አብሮ፡ እፀ መስቀሉ፡ የነገሥታት ሞገሳቸው፥ ኃይላቸው፥ ድል ማድረጊያቸው መኾኑን አሳወቀው። ይኽ የሚኾንላቸው ግን፡ ነገሥታት፡ በክርስቶስ ያላቸው እምነት፡ ነቅ የሌለው ሲኾን እንደኾነ ገለጠለት። ከዚህ አንጻርም፡ የኢትዮጵያ መንግሥት፡ ከጽዮን የተነሣ፡ በምድር ካሉት ነገሥታት ኹሉ ከፍ ከፍ ያለው መንግሥት መኾኑን አስረዳው።
ጎርጎሬዎስም፡ ከእግዚአብሔር የተረዳውን ኹሉ ይዞ፡ ለ318ቱ ሊቃውንት፡ በኒቅያ ጉባኤ ላይ፡ እነርሱ እየጠየቁት፥ እርሱ እየመለሰ አስረዳቸው። የንግግራቸው ቃለ ጉባኤም፡ ዛሬ "ክብረ ነገሥት" ለምንለው መጽሓፍ፡ መነሻ ኾነ። የነገሥታት ክብር፡ ጽዮን መኾኗን፥ የነገሥታት ኃይል እፀ መስቀሉ መኾኑን ለመመስከር የተጻፈ መጽሓፍ ነው። (ድርሳነ ጽዮንም፥ ድርሳነ መስቀልም፡ ተቀራራቢ ይዘት አላቸው።)
አሁን ያለው የዓለማችን አረዳድ፡ "የአንድ መንግሥት ጥንካሬና ክብር፡ መሠረቱ፡ ኹሉን ማዳመጥና ማሳተፍ ከመቻሉ የሚመጣ ነው" የሚል ነው። "Participatory democracy" እንዲል። ይኽ ደግሞ የሰይጣንንም፥ የሰውንም፥ የእግዚአብሔርንም ሃሳብ "እያቻቻሉ" ለማስቀጠል መሞከርን ስላመጣ፡ ጦርነት በምድራችን ጨመረ እንጂ፡ አልቀነሰም።
ኢትዮጵያ፡ ዓለምን፡ ወደ ጽዮን እና ወደ ቅዱስ መስቀሉ ለመመለስ፡ ትልቁ፥ ምናልባትም ብቸኛው ዕድል አላት። ነገር ግን፡ የገዛ መሪዎቿና ሕዝቦቿ፡ የዚህ እውነት ተቃዋሚ ኾነው ስለተገኙ፡ ማንም የሚኮረኩማት አገር ለመኾን በቅታለች። አደራዋን መወጣት አልቻለችም።
ክብረ ነገሥትን፡ እንደ ኢትዮጵያውያን ፖለቲከኞችና ምሑራን የሚያብጠለጥለው የለም። መጽሓፉ ግን፡ የክብራቸውና የኃይላቸው ምንጭ ማን እንደኾነ እየነገራቸው ነበር። አገሪቱም ዐሥራትነቷ ለጽዮን ነበረ።
አልሰማ ያለው ትውልድ አልፎ፡ ለመስማት የተዘጋጀ ትውልድ እስኪመጣ፡ ምጡ ብዙ ነው።
ማርያም በሰላም ትማረንና በሽልም ታውጣን!
በዶ/ር መስከረም ለቺሳ
📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት
#በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ....
...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛል ልጆቹም ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ፡ ያመልካሉ ፡ ከዕለታት አንድ ፡ ቀን ፡ ከባልንጀሮቹ ፡ ጋራ ፡ ሊሠርቁ ፡ ሊቀሙ ፡ በረኃ ፡ ለበረኃ ፡ ሲሄዱ ፡ ዋዕየ ፡ ፀሐይ ጸናባ ቸው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ ሳለ ፡ ቀና ፡ ብሎ ፡ ፀሐይን፡ ስትባክን ፡ አይቶ ፡ አሁን ፡ ይች ፡ ፀሐይ ፡ ምን ፡ ምላክ ፡ ናት ፤ አምላክስ ፡ የኔ ፡ ጌቶች ናቸው ፡ በል ተው ፡ ጠጥተው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ የሚውሉ አላቸው ። እነሱም አሻግረው ፡ አይተው ፡ አምላክ አምላክ ፡ ትላለህ ፡ አምላክማ ፡ ከፈለገህ ፡ ያባ ኤስ ድሮስ ፡ ገዳም ፡ ያውልህ አትሄድምን ፡ አሉት ያው ፡ ተነሥቶ ፡ ሄደ ፤ ከገዳሙ ፡ ቢደርስ ፡ ግብሩን፡ ያውቃሉና ፡ ማኅበሩ ፡ ተሸበሩ ፣ አበ ፡ ምኔቱ ፡ አባ ኤስድሮስ ፡ ነው ፤ ጸጋ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጠርታ ፡ አ ምጥታዋለችና ፡ ይልቅ ፡ ተቀበሉት ፡ አላቸው : ተቀብለው ፡ አገቡት ፣ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ልጄ ፡ ምን ፡ አመ ጣህ ፡ አለው ፡ ትመክረኝ ፡ ብዬ ፡ አለ። መከረው አስተማረው ፤ አመነ ፡ ተጠመቀ ፤ ደግ ሰው ሆነ አመንኩሶታል።
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
የባለትዳሮች ከባዱ ፈተና በፍትወት መቃጠል || ሩካቤ ሥጋን የሚያስጠሉ፣ የሚከለክሉ ክፉ መናፍስቶች || ቅዱስ ቁርባንና ፈተናው || በማለዳ ንቁ 2024 😰😭 https://youtu.be/mbqbGZTOKOk
አገልጋይ ነኝ ሰይጣን አይነካኝም || የጠቋር ዓይነጥላ ሴራ ሲገለጥ || በሥራ ቦታችን መተት እንደተደረገ በምን እናውቃለን || መፍትሄዎቹስ ምንድናቸው? 😰😭😂 https://youtu.be/rplbveuTAH0
ንቁ! ክፉ የአስማትና አጋንንታዊ አሠራሮች ሲገለጡ || ጠልሰም እና ኪታብ አጋንንታዊ ናቸው || ልናውቃቸው እና ልንጠነቀቃቸው የሚገቡ ነገሮች 😭😰😂 https://youtu.be/6Tlt58M2n9Y
3ቱ ርኩሳን መናፍስትን ማሠሪያ እና መቃወሚያ መንገዶች || ጸሎት ከመጀመር አስቀድሞ መናፍስትን የማሠር ጥቅም || መናፍስትን እንዴት እንሠርhttps://youtu.be/fdtbusX_VPo
«ማግባት ያሰባችሁ ወገኖቼ ከጋብቻችሁ ቀን በፊት ምንም ነገር በሚዲያ አታውጡ እባካችሁን። ሁሉንም ግላዊ ጉዳይ የሚዲያ ሲሣይ ማድረግ ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ ከፍ ያለ ነውና እባካችሁን ይሄንን በደንብ ተጠንቀቁ አደራ።»
=> እንደተረዳሁት ከኾነ፡ ብዙዎች፡ ሰይጣን አምልኮ ሳይመስላቸው፡ "ጥበብ" በሚል ስም፡ የተራቀቁ እውነቶችን የሚማሩ የሚመስላቸው አሉ። በተለይ ብዙ ለማወቅና በሕይወታቸው ቶሎ ለመለወጥ የሚፈልጉ ወጣቶች የዚህ ተጠቂ ናቸው።
እንዲህ ያለ ዝንባሌ በውስጣችሁ ካለ፡ ስለ ሲሞን መሠሪና ስለመሰሎቹ (ግ)ኖስቲኮች (gnostics) አስተሳሰብ አንብቡ። በጣም የተራቀቀ የመጽሐፍ ቅዱስ እውቀት፥ ወይም የሠለጠነ የሰማያትና የምድር አረዳድ መስሎ፡ እልም ያለ ክሕደትን እና አምላክ የመኾን ዝንባሌን በውስጥ የሚያሳድር ነው። ብዙ ዓይነት ኖስቲኮች አሉ። ዛሬ "ብዙ የፕሮቴስታንት denomination አለ" እንደምንለው፡ ኖስቲኮችም እንደዚያው ዓይነታቸው ብዙ ነው። ሰው፡ በተመቸው፣ በተስማማው ዲኖሚኔሽናቸው በኩል ኼዶ ይጠመዳል። ሰይጣንን ስለማምለክ አያወሩም። ራስን ስለማሳደግና እውቀት ስለማግኘት፥ እንዲሁም የምድራዊና የተፈጥሮ ሕግጋትን አሸንፎ በተአምራዊ ኃይል "ነፃ" ኾኖ መኖር ስለመቻል ብቻ ነው የሚያወሩት። እና፡ እውቀታቸውና መንገዳቸው ጉዳት የሌለው የሠለጠነ ሰው አስተሳሰብ ይመስላል። ነገር ግን ሳጥናኤል "አምላክ ነኝ" ያለበትን፥ ወይም አዳምና ሔዋንን "አምላክ ትኾናላችሁ" ብሎ ያሳተበትን እውቀት ነው የያዙት። እንዲህ ያለ እውቀት፡ ብዙ ዓይነት የተራቀቁ ክፉ መናፍስትን በራስ ላይ መጎተትን ያመጣል።
እነዚህ እውቀቶች፡ ከእግዚአብሔር መንገድ የሚለዩበት አካኼዳቸው፡ ከንስሓ፥ ከስግደት፥ ከፆም፥ ከጸሎት፥ ከትጋት፥ ከቅዱስ ቁርባን የሚያርቁ መኾናቸው ነው። እነዚህን መንገዶች፡ ከአማናዊ መዳኛነታቸው ይልቅ፡ ተምሳሌታዊ ብቻ የኾኑ ነገሮች አድርጋችሁ እንድትመለከቱ ይገፋፏችኋል። የደካማና የተራቀቀ እውቀት የሌላቸው ሰዎች ተግባር (primitive practices) እንደኾኑም ሊነግሯችሁ ይሞክራሉ። "ኹሉም ድኅነት ያለው በአእምሯችሁ ውስጥ ትርጉማቸውን መረዳታችሁ ላይ ብቻ ነው" ይሏችኋል።
የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮችንም፡ "gnostic" በኾነ መነጽር አይታችሁ፡ የጥንቆላ ትምህርትን የሚደግፉ እንደኾኑ እንድታስቡ ያደርጓችኋል። ለምሳሌ፦ "ሙሴ ባሕሩን የከፈለው፡ ከግብጻውያን ምሥጢራዊ ትምህርት ቤቶች በቀሰመው ጥበብ ነው" ሊሏችሁ ይችላሉ። "እሱና የግብጽ ጠንቋዮች አንድ ትምህርት ቤት ስለኼዱ፡ ኹለቱም በትሮቻቸውን ወደእባብ መቀየር ችለዋል" ሊሉም ይችላሉ። እናም፡ በእግዚአብሔር ተአምራዊ አሠራርና በጥንቆላ መካከል ያለውን ድንበር አጥፍተው፡ ኹለቱንም "ጥበብ" በሚል ስም ይደበላልቁባችኋል።
ኹለቱ ግን ወፍራም ድንበር አላቸው። ድንበራቸውም ጽዮን ናት። የሙሴ ኃይል የመጣው፡ የግብጻውያንን ጥንቆላን ስለተማረ ሳይኾን፡ ጽዮንን፡ ጫፎቿ ሳይቃጠሉ በምትነድድ ቁጥቋጦ ምሳሌ ስላያት ነው። እሷም እመቤታችን ናት። እግዚአብሔርንማ ኹሉም ጠንቋዮች ይፈሩታል። አጋንንት ይፈሩት የለ?! ድንግል ማርያምን ግን ይጠሏታል። በጥንቆላ ውስጥ ያለ፡ እመቤታችንን ከልቡ የሚወድድ፡ ማንም የለም። ለማስመሰል ግን፡ ወዳጆቿ መስለው ሊታዩ ይችላሉ። ከርሷ ጋር የተለየ ግንኙነት እንዳላቸው ኹሉ ሊናገሩ ይችላሉ። ግን፡ አይወዷትም። ፍጹም ውሸት ነው። እሷም በሕይወታቸው ሳሉ ንስሓ ካልገቡ በቀር፡ ላታማልዳቸው ቃል ገብታለች። ከርሷ ጋር ያላቸው ልዩነት፡ የዚያን ያኽል የሰፋ ነው።
እና፡ ስለ Gnosticism (በተለይ በመጀመሪያዎቹ የክርስትና ክፍለ ዘመናት ስለነበሩት ዓይነቶቹ) አንብቡና፡ መተው ያሉባችሁን የአስተሳሰብ ዝንባሌዎች አውጥታችሁ ጣሏቸው።
እውነተኛዪቱ ጥበብ ከላይ ናት፤ ከሰው ወይም ከአጋንንት አይደለችም።
ሰማያዊቷን ጥበብ ያድለን!
በእጇ የያዘች የሃይላንድ ጸበል ወደ ደምነት ለምን ተቀየረ! ሞተው መሬት አልቀበል ያለቻቸው አባት እጅግ አሳዛኝ ታርክ!! ሁለቱ እጅን በአፍ የሚያስጭኑ ተዓምሮ https://youtu.be/RqikITIGBcA
ብርጭቆ የሚሰብር ቡዳነት ከውስጣችን የተጠናወተን እኛ ለምን እንዲህ ሆንን!? አትፍረዱብኝ ከአክስቴ ልጅ ፍቅር ይዞኛል ምን ላድርግ!! https://youtu.be/RUHndRV6GO4
መቀ'ደሰ ስላቃተን ዘወትር ከዲያብሎስ ጋር እንታገላለን!! የእኔንም ሰይጣን አውጡልኝ መምህር ግርማ ለተሳዳቢዎች!! ማወቅ የሚገባችሁ ከባባድ እውነቶች!! https://youtu.be/HD893HvPJiU
=> አዲስ ዓመት ማለት አዲስ ልብስና አዲስ ጫማ መግዛት ብቻ ሳይሆን፣ አዲስ ልብና አዲስ ሕሊና ማግኘት ነው። አሮጌው ዘመን ያለፈው በኃጢአት ከሆነ፣ አዲሱ ዓመት በንጹሕ ንስሐ መጀመር አለበት።አዲስ ዓመት ማለት የዘመን መለወጥ ሳይሆን፣ የልብ መለወጥ ነው። በኃጢአት አሮጌ የሆንከውን ማንነትህን ንስሐ በሚባል የጸጋ ሳሙና አጥበህ አዲስ ሰው ሆነህ ተቀበለው። (ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ)። ያለ ንስሐ አዲስ ዓመት መጀመር፣ በአሮጌ መያዣ አዲስ የወይን ጠጅ እንደማፍሰስ ነው፤ መያዣው ይፈነዳል።
=> ለአዲሱ ዓመት እቅድ ስታወጡ፣ ለጸሎት ግን የምትሰጡት ቦታ ካለለ እግዚአብሔር የዕቅዳችሁ መሠረት አይሆንም። ያለ ጸሎት የሚጀመር ሥራ የጠላት መጫወቻ ነው። እግዚአብሔር ቤትን ካልሠራ ሠራተኞች በከንቱ ይደክማሉ። (መዝሙር ፻፳፯፥፩)። ጠዋት ወደ ሥራህ ከመውጣትህ በፊት እግዚአብሔርን ስጠራው፣ ሰይጣን ቀኑን ሙሉ እንደ ጥላህ እየተከተለ ሊያሰናክልህ አይችልም። (ቅዱስ እንጦንዮስ)።
=> ዘመን የሚዋጀው በከንቱ ወሬ፣ በቲክቶክና በማኅበራዊ ሚዲያ ግርግር ሳይሆን በበጎ ሥራ ነው። አምስት ደቂቃ እንኳን ቢሆን ለነፍስህ የማይጠቅም ከሆነ ዘመኑን እያባከንከው ነው። ቀኖቹ ክፉዎች ናቸውና ዘመኑን ዋጁ። (ኤፌሶን ፭፥፲፮)። አዲስ ዓመት ሲመጣ ለሥጋህ ደስታ የምትጨነቀውን ያህል ለነፍስህ እድገት ብትጨነቅ ኖሮ ዛሬ መንፈሳዊ ሰው ነበርክ። ጊዜህ የዘላለም ዋጋ ያለው ነውና በአግባቡ ተጠቀምበት።
=> አሮጌው ዘመን በቂም በቀል ከተጠናቀቀ፣ አዲሱ ዘመን በረከት አይኖረውም። የጠላህ ወገን ካለ፣ የበደለህ ሰው ካለ በ2019 ዓ.ም ውስጥ ይቅርታን አውጅ። ይቅርታ ለጠላትህ ሳይሆን ለአንተ ነጻነት ነው። ያለፈው ነገር አልፎአል፤ እነሆ፥ አዲስ ሆኖአል። (፪ኛ ቆሮንቶስ ፭፥፲፯)። አዲስ ዓመትን ስትቀበል በልብህ የያዝከውን ቂም ካላራገፍክ፣ አዲሱ ዓመት በአንተ ዘንድ እንደ አሮጌው መራራ ይሆናል።" (ቅዱስ ይስሐቅ ሶርያዊ)።
=> የሚመጣውን በረከት በምጽዋት አትምበት። እግዚአብሔር የሰጠህን በማካፈል ሰማያዊ መዝገብህን አደላድል። ለድኻ የሚያበድር እግዚአብሔርን ያበድራል፤ እርሱም በጎነቱን ይከፍለዋል። (ምሳሌ ፲፱፥፲፯)። ድኻን ማብላት እንደ ቍርባን ይቆጠራል፤ ምክንያቱም ድኻው የክርስቶስ ማደሪያ ነውና። (ቅዱስ ባሲልዮስ)።
https://youtu.be/ucEXVNwBa5sራሳችንን እንድናጠፋ የሚገፋፋንን ክፉ መንፈስ በዚህ መንገድ አሸንፉ!! ትዝታው ሳሙኤል ዘንድሮም ብሶበታል ያሳዝናል!! 100% እጅግ የምታተርፉበት ተግሳጽ!!
ወላጆች ልጆቻሁን እባካችሁን ጠብቁ በተለይ አዳማና አዲስ አበባ ተጠንቀቁ!! የሰው ዋጋ ከዶሮ ዋጋ በታች ሆኗል እጅግ ያሳዝናል!! https://youtu.be/_iyCz1i6BHU
