Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community
الذهاب إلى القناة على Telegram
1 756
المشتركون
-124 ساعات
+97 أيام
+2630 أيام
أرشيف المشاركات
For Grade 12 students use the new URL address to practice online exam.
Second Semester Mathematis grade 11 worshet and assignment Final Exam 2018 E.C.pdf'
Second Semester Mathematis Grade 11 WORK SHEET AND ASSIGNMENT for Final Exam 2018 E.C
Submitted date
Thursday- Friday
04 -05/10/18 E. C
'Second Semester Mathes Grdae 9th assignment and workshet for finial exam 2018 E.pdf'
Submitted date 01/10/2018 E.C
Only answer
አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
ለ2018 ዓ.ም ከKG - 12ኛ ክፍል
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ
ከአዲስ አበባ ከተማ ትምህርት ቢሮ በተላለፈ መልዕክት መሠረት ከመጪው ሰኞ ማለትም ከ24/09/18 ዓ.ም - ረቡዕ 26/09/18 ዓ.ም ት/ቤቶች ዝግ ስለሚሆኑ ትምህርት የማይኖር መሆኑን እንገልፃለን።
ማሳሰቢያ: -
፨ ከሐሙስ ግንቦት 27/2018 ዓ.ም ጀምሮ ግን መደበኛው የመማር ማስተማር ሂደት የሚቀጥል መሆኑን እየገለፅን ወላጆችም ይህን አውቃችሁ ተማሪዎችን ወደ ትምህርት ቤት እንድትልኳቸው እናሳስባለን።
ት/ቤቱ
አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት
ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት ተከታይ
መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣
የተማሪ ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ
ውድ የእስልምና እምነት ተከታይ የሆናችሁ የት/ቤታችን መምህራን፣ የአስተዳደር ሠራተኞች፣ የተማሪ ወላጆች፣ ተማሪዎች እንዲሁም የትምህርት ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለ1447ኛው የዒድ አል አድሀ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሰላም፣ የጤናና የመተሳሳብ እንዲሆን እንመኛለን።
ዒድ ሙባረክ
ት/ቤቱ
Repost from Tikvah-University
ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ከሰኔ 23/2018 ዓ.ም እስከ ሐምሌ 17/2018 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ በትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ይፋ መደረጉ ይታወሳል።
ተፈታኞች በተደለደላችሁበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት፤ በኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም መለማመመድ ትችላላችሁ ተብሏል።
@tikvahuniversity
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
2018 E.C. SAT ANSWER KEY.pdf1.19 KB
Repost from Addis Ababa Education Bureau
ፈተናው በ6 ዙር እንደሚሰጥና በማህበራዊ ሳይንስ በሶስት ዙር በተመሳሳይ በተፈጥሮ ሳይንስ ደግሞ በሶስት ዙር በመሆኑ አንድ ኮምፒዩተር ስድስት ተማሪን ያስተናግዳል ነው ያሉት።
ተማሪዎች የፈተና ስርዓቱን እንዲለማመዱና ትምህርት ቤቶች እና ወላጆች ለተፈታኝ ተማሪዎች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉም አስገንዝበዋል።
ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://linktr.ee/aacaebc
Repost from Addis Ababa Education Bureau
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም በ667 የፈተና ማዕከላት እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ገልጻል፡፡
(ግንቦት 11/2018 ዓ.ም) የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የዘንድሮውን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በ667 የፈተና ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን አሳውቋል፡፡
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) እንደገለጹት የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተናን በ97 ዩኒቨርሲቲዎች እና በ570 የክልልና የከተማ አስተዳደሮች ማዕከላት ላይ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ይገኛል።
ከሰኔ 24 እስከ ሐምሌ 17 ቀን 2018 ዓ.ም ለሚሰጠው ፈተና መደበኛ ተማሪዎችን ጨምሮ በሁሉም ፕሮግራሞች በተፈጥሮ ሳይንስ 306 ሺህ 964 እንዲሁም በማህበራዊ ሳይንስ 257 ሺህ 255 በድምሩ 564 ሺህ 219 ተማሪዎች መመዝገባቸውን ገልጸዋል፡፡
ፈተናውን በሙሉ አቅም በበይነ መረብ ለመስጠት ዝግጅት እየተደረገ ነው ያሉት ዋና ዳይሬክተሩ ፤ በተለያዩ ምክንያቶች ቁጥራቸው አነስተኛ የሆኑ በወረቀት የሚፈተኑ ተማሪዎች እንደሚኖሩም ጠቁመዋል።
በየክልሎች ፣ በከተማ አስተዳደሮች እና የፈተና ማዕከላት ያለው አቅም የተለያየ ቢሆንም በርካታ ኮምፒዩተሮች ለፈተና ዝግጁ እየተደረጉ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
ከባለፈው አርብ ጀምሮ ለተፈታኞች የበይነ መረብ የሙከራ ፈተና መሰጠት መጀመሩን አንስተዋል።
Repost from Kolfe education official channel🇪🇹
ለ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል የመልቀቂያ ፈተና የኦንላይን ልምምድ ያድርጉ!
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ተፈታኞች ፈተና የሚለማመዱበት አድራሻ ይፋ አድርጓል።
ተፈታኞች በተደለደሉበት ክልል ወይም ከተማ አስተዳደር ትይዩ ያለውን ሊንክ በመጠቀም፣ User Name በሚለው ላይ የፈተና አዳራሽ መግቢያ ካርድ ላይ ያለውን አድሚሽን ቁጥር በማስገባት እና Password በሚለው ላይ 1234 በማስገባት በዴስክቶፕ ኮምፒውተር፣ በላፕቶፕ፣ በታብሌት፣ በስልክ እና በመሰል የኤልክትሮኒክስ መሳሪያዎች ማንኛውንም አይነት የኢንተርኔት አማራጭ በመጠቀም ከነገ ግንቦት 07/2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡00 ሰዓት ጀምሮ እስከፈተናው ድረስ መለማመመድ እንደሚችሉ ተገልጿል።
@tikvahuniversity
ግንቦት 6/2018 ዓ.ም
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ በ2018 የትምህርት ዘመን ለ12ኛ የሁለተኛ ሴሚስተር ከተማ አቀፍ ሞዴል ፈተና መስጫ ጊዜ ሰሌዳ ከዚህ በፊት ከግንቦት 10/2018 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሠጥ ተገልፆ የነበረ ቢሆንም በዛሬው ዕለት ፈተናው የሚሠጥበት ቀን ተቀይሮ ፈተናው ከረቡዕ ግንቦት 12/2018 ዓ.ም እስከ አርብ ግንቦት 14/2018 ዓ.ም እንደሚሠጥ እንገልፃለን።
ት/ቤቱ
ALPHA KERANYO SECONDARY SCHOOL_Geography Handhout 2nd.pdf1.35 MB
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
የ12ኛ ክፍል ፈተና የሚሰጥበት ቀን ይፋ ሆነ።
የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ ሠርተፊኬት (12ኛ ክፍል ፈተና) ከሰኔ 24 እስከ ሃምሌ 17 ቀን 2018 ዓ/ም ድረስ እንደሚሰጥ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አሳውቆናል።
በሌላ በኩል ፦
- የሬሜዲያል ፕሮግራም ሀገር አቀፍ ፈተና ከግንቦት 17 እስከ ግንቦት 20 ቀን 2018 ዓ/ም ➡️ ግንቦት 19 ኢድ አልአድሃ
- የቅድመ ምረቃ ትምህርት መውጫ ፈተና ከሰኔ 2 እስከ ሰኔ 12 ቀን 2018 ዓ/ም
- የድህረ ምረቃ ትምህርት መግቢያ ፈተና (NGAT) ከሃምሌ 29 እስከ ሃምሌ 30 ቀን 2018 ዓ/ም
- የመሰረታዊ የንባብና የስሌት ክህሎት ምዘና ጥናትና ምርምር መረጃ መሰብሰብ ከሚያዚያ 26 እስከ ግንቦት 7 ቀን 2018 ዓ/ም ... ይሰጣል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሚያዚያ 16 ቀን 2018 ዓ.ም
@tikvahethiopia
متاح الآن! بحث تيليغرام 2025 — أهم رؤى العام 
