ch
Feedback
Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

Alpha Keranyo Sec. & Prep. School Community

前往频道在 Telegram

+251113498906

显示更多
1 830
订阅者
无数据24 小时
-17 天
+1230 天
帖子存档
የ2019 ዓ.ም ትምህርት አጀማመርን በተመለከተ፦ መሰከረም 04/2019 ዓ.ም የተማሪዎች ክፍል ድልድል፣ የተማሪዎች ተግባርና ኃላፊነት ላይ ውይይት የሚደረግበት ቀን ይሆናል። መሰከረም 05/2019 ዓ
የ2019 ዓ.ም ትምህርት አጀማመርን በተመለከተ
መሰከረም 04/2019 ዓ.ም የተማሪዎች ክፍል ድልድል፣ የተማሪዎች ተግባርና ኃላፊነት ላይ ውይይት የሚደረግበት ቀን ይሆናል። መሰከረም 05/2019 ዓ.ም የመጀመሪያው ቀን የመጀመሪያ መደበኛ ትምህርት ክፍል ጊዜ (day one class one) የሚጀመርበት ቀን ይሆናል።
 https://t.me/kolfekeranioeducationbureau 🌼🌼መልካም አዲስ ዓመት🌻🌻🌻🌻🌻🌻

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመላው የት/ቤታችን መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ለመላው የት/ቤታችን
አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመላው የት/ቤታችን መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ለመላው የት/ቤታችን ማህበረሰብ በሙሉ እንኳን ለ2019 ዓ.ም አደረሳችሁ/አደረሰን እያልን አዲሱ አመት የሠላም፣ የጤና፣ የመተሳሰብ እና የስኬት እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። መልካም አዲስ አመት ይሁንላችሁ/ይሁንልን!!!                                                                                    ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት የተወደዳችሁ የአልፋ ቀራንዮ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች እዚህ ላይ በተጠቀሠው ሊንክ መጠይቁን በመሙላት ለትምህርት ቤቱ መሻሻል የበኩልዎን አስተዋፅዖ እንዲያበረክቱ እንጠይቃለን ለተሳትፎዎ ምስጋናችን ላቅ ያለ ነው ።

#MoE የ2018 ዓ.ም. የሁለተኛ ደረጃ ማጠናቀቂያ ሀገር አቀፍ ፈተናን ወስደው በመደበኛ የትምህርት መርሃ ግብር የከፍተኛ ትምህርት መግቢያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች የተቋምና የትምህርት መስክ ምርጫቸውን ከነሐሴ 28 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2018 ዓ.ም. ድረስ እንዲያስገቡ የትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል። ተማሪዎች ምርጫቸውን ትምህርት ቤት መሄድ ሳያስፈልጋቸው ባሉበት ሆነው በኦንላይን ማስገባት ይችላሉ። የምርጫ ማስገቢያ ድረ-ገጹ፦ student.ethernet.edu.et ነው። - በሕክምና ምክንያት ልዩ ሁኔታ ያላቸው፣ - የአካል ጉዳተኛ የሆኑ፣ - ተመሳሳይ ጾታ ያላቸው መንትያዎች - ከ6 ወር በታች ሕፃን የሚያጠቡ እናቶች ተገቢውን ሕጋዊ ማስረጃ ማያያዝ እንደሚጠበቅባቸውም ሚኒስቴሩ ገልጿል። https://t.me/kolfekeranioeducationbureau ነሐሴ 28 ቀን 2018 ዓ/ም @tikvahethiopia

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ታላቅ የምስራች ለአልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ:አንደኘኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ ለ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን አዲስ የአልፋ ቀራንዮ ዩኒፎርም መግዛት ለምትፈልጉም ሆነ ያለቀባችሁን ለመቀየር የምትፈልጉ ከኬጂ ጀማሪ አንስቶ እስከ 12ኛ ክፍል ላላችሁ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ ባለሀብቶችን በማናገር በከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ ያቀረበላችሁ ሥለሆነ አርብ ማለትም በ22/12/2018 እንድትገዙ እድሉን ያቀረብንላችሁ ቢሆንም የተጠቀማችሁ ወላጆች ቁጥራችሁ ትንሽ ነው።በመሆኑም የፊታችን ሠኞ ማለትም በ25/12/2018 ዓ.ም. በመገኘት የጨርቁን ዓይነት አይታችሁ በማረጋገጥ ለመግዛት በሚሠጣችሁ የባንክ አካውንት ከፍላችሁ ልብሳችሁን ከሒሣብ ክፍል መረከብ የምትችሉ መሆኑን ስናበስራችሁ በደስታ ነው ።                                                 ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ታላቅ የምስራች ለአልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ:አንደኘኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ ለ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን አዲስ የአልፋ ቀራንዮ ዩኒፎርም መግዛት ለምትፈልጉም ሆነ ያለቀባችሁን ለመቀየር የምትፈልጉ ከኬጂ ጀማሪ አንስቶ እስከ 12ኛ ክፍል ላላችሁ ተማሪዎች ትምህርት ቤቱ ባለሀብቶችን በማናገር በከፍተኛ የዋጋ ቅናሽ ያቀረበላችሁ ሥለሆነ የፊታችን አርብ ማለትም በ22/12/2018 ከቀኑ5:00 እስከ 9:00 ድረሰ በመገኘት የጨርቁን ዓይነት አይታችሁ በማረጋገጥ ለመግዛት በሚሠጣችሁ የባንክ አካውንት ከፍላችሁ ልብሳችሁን ከሒሣብ ክፍል መረከብ የምትችሉ መሆኑን ስናበስራችሁ በደስታ ነው ።                                                 ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት ተከታይ መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣ የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች
አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት ተከታይ              መምህራን፣ አስተዳደር ሠራተኞች፣        የተማሪዎች ወላጆች እና ተማሪዎች በሙሉ ለመላው የት/ቤታችን የእስልምና እምነት  ተከታይ ማህበረሰብ በሙሉ  እንኳን ለመውሊድ በዓል አደረሳችሁ እያልን በዓሉ የሠላም፣ የጤና እና የመተሳሰብ እንዲሆን መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። መልካም የመውሊድ በዓል! ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለአልፋ ቀራንዮ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም. የመጨረሻ ቀን እንደሆነ መልዕክት ማስተላለፋችን ይታወቃል ነገር ግን አንዳንድ ወላጆች ሳይመቻችሁ በመቅረቱ ያላስመዘገባችሁ የነባር ተማሪ ወላጆች በመኖራችሁ እና አንዲራዘምላችሁ ዳሽን ባንክንም ትምህርት ቤቱንም እየጠየቃችሁ ሥለሆነ እስከ ነሐሴ 9/2018 ዓ.ም. ያራዘምንላችሁ ሢሆን በተለይም 12ኛ ክፍሎች እድሉን ተጠቅማችሁ ቦታ ሣይሞላባችሁ ልጆቻችሁን እንድታስመዘግቡ እናሣውቃለን                                                 ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለአልፋ ቀራንዮ ሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች እና የተማሪ ወላጆች በሙሉ የ2019 ዓ.ም. የትምህርት ዘመን የተማሪዎች ምዝገባ ከተጀመረ 16 የሥራ ቀናትን አስቆጥረናል በእነዚህ ቀናት ከተመዘገቡ ተማሪዎች ከነባር ተማሪዎች ቁጥር ይልቅ የአዲስ ተማሪዎች ቁጥር ይበልጣል ስለሆነም :- 1ኛ/ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች በ2018 ዓ.ም. ከነበረው የተማሪ ቁጥር መጨመር ስለማይቻል (በመፈተኛ ኮምፒውተሮች ኔትዎርክ ምክንያት) በአዲስ ተማሪዎች መብዛት ቁጥር እንዳይሞላ በያዝነው ሣምንት እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም. ብቻ እንድትመዘገቡ እያሣሠብን ያልተመዘገበ ተማሪ ቦታ ቢሞላ ተጠያቂ አንሆንም ። 2ኛ/ የ11ኛ ክፍል ተማሪዎች የትምህርት ምረጫችሁን (Natural or Social ) በቶሎ እንድታሣውቁን መመዝገብ ይኖርባችኋል እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም ድረስ ብቻ 3ኛ/ በአጠቃላይ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያላችሁ ነባር ተማሪዎች ነባር ነን ብላችሁ እንዳትዘናጉ ምክንያቱም ትምህርት ቤቱ ማስተናገድ የሚችለውን የተማሪ ቁጥር በአዲስ የተማሪ ቁጥር እንዳይሞላ ሥጋቱ ሥላለን እስከ ሐምሌ 30/2018 ዓ.ም. ድረስ ብቻ ።                                                                  ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ ;አንደኛና መካከለኛ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በ2018 ዓ.ም. የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ፈተና ለወሰዳችሁ ተማሪዎች ላፕቶፕ አስገብታችሁ ለነበራችሁ ተማሪዎች በሙሉ ፈተናው ማለቁ የሚታወቅ ሥለሆነ ላፕቶፑን የተረከብናችሁ አካላት ወደ ሌላ አሰቸኳይ ሥራ ልንገባ በመሆኑ ንብረታችሁን መውሰድ የምትችሉት ሐሙስ ማለትም በ16/11/2018 ዓ.ም. ብቻ ሲሆን ከዚህ ቀን ውጪ ለመውሰድ የፈለጋችሁ ተማሪዎች እንደሚዘገይባችሁ እናሣውቃለን።

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት  ለ2018 ዓ.ም በመንግስት ት/ቤት (በክላስተር) የማጠናከሪያ ት/ት ለምትማሩ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ የተላለፈ ጥብቅ ማስታወቂያ 1ኛ/የክረምት ትምህርቱ የሚሠጥበት ቦታ ከዚህ በፊት ይሠጥ እንደነበረው ጄኔራል ዋቆ ጉቱ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ነው። 2ኛ/ትምህርቱን ተከታትላችሁ ስትጨርሱ የሚሰጥ ሠርትፍኬት በትምህርት ቢሮ ደረጃ እየተዘጋጀ በመሆኑ የእድሉ ተጠቃሚ እንድትሆኑ በተጨማሪ ይህን ሠርትፍኬት ያላገኘ ተማሪ በቀጣይ በየትኛውም ትምህርት ቤትመመዝገብ እና መማር እንደማይቻል መልዕክት ተላልፏል 3ኛ/ትምህርቱን ለመማር የሚያስፈልገው ለሙሉው ክረምት 1,000.00(አንድ ሺህ ብር ) ብቻ መሆኑን አውቃችሁ የዋቆ ትምህርት ቤት በሚሠጣችሁ አካውንት እንድታስገቡ እናሣውቃለን ፨ ዩኒፎርም መልበስ እና መታወቂያ መያዝ ግዴታ ነው።                                                                  ት/ቤቱ

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት  ለ2018 ዓ.ም በዋቆ ጉቱ ቁጥር ሁለት አንደኛ ደረጃ ት/ቤት (በክላስተር) የማጠናከሪያ ት/ት ለምትማሩ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል የተማሪ ወላጆች  እና ተማሪዎች በሙሉ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን መንግስት ባስቀመጠው አቅጣጫ መሠረት የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ተጨማሪ የማጠናከሪያ ትምህርት በክረምት መርሃ ግብር እንዲማሩ ማሥታወቂያ መተላለፉ የሚታወስ ነው።  በዚህም መሠረት ከነገ ረቡዕ ማለትም በ08/11/18 ዓ.ም በተጠቀሰው ትምህርት መጀመር እንዳለባችሁ አስቀድመን እያስጠነቀቅን በተያዘው ፕሮግራም የማይማር ተማሪ ካለ ማንኛውም በትምህርት ሂደት ለሚፈጠር ችግር ትምህርት ቤቱ ሃላፊነት እንደማይወስድ ከወዲሁ እናሣውቃለን ። ት/ቤቱ

የለሚ ኩራ ክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሌሊስቱ ተስፋዬ በበኩላቸው የማጠናከሪያ ትምህርቱ በክፍለ ከተማው በ10 ክላስተሮች ከመንግስትና ከግል ትምህርት ቤቶች ለተውጣጡ ተማሪዎች እንደሚሰጥ ገልጸው የማጠናከሪያ ትምህርቱ ውጤታማ እንዲሆን ጽህፈት ቤቱ በቂ ዝግጅት ማድረጉን አስረድተዋል። በከተማ አስተዳደሩ በክረምት ወቅት በሚሰጠው የማጠናከሪያ ትምህርት 51,523 ተማሪዎች ትምህርቱን እንደሚማሩና 1,800 መምህራን መመደባቸውን ቀደም ሲል መገለጹ ይታወቃል። ለተጨማሪ የመረጃ አማራጮች ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://linktr.ee/aacaebc

የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችል የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት በዛሬው እለት መሰጠት ጀመረ። (ሀምሌ 6/2
+9
የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሀገር አቀፍ ፈተና የላቀ ውጤት እንዲያስመዘግቡ የሚያስችል የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት በዛሬው እለት መሰጠት ጀመረ። (ሀምሌ 6/2018 ዓ.ም) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ ከለሚ ኩራ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈጻሚ አቶ አድማሱ ደቻሳ እንዲሁም ከምክትል ቢሮ ኃላፊ አቶ ሳምሶን መለሰ እና ከክፍለ ከተማው ትምህርት ጽህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ሌሊስቱ ተስፋዬ ጋር በመሆን በክፍለ ከተማው የማጠናከሪያ ትምህርቱ ከሚሰጥባቸው ክላስተር ማዕከላት መካከል አንዱ በሆነው ኡላ ዱላ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተገኝተው ትምህርቱን አስጀምረዋል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ክቡር ዶክተር ዘላለም ሙላቱ በክረምት ወቅት የሚሰጠው ማጠናከሪያ ትምህርት የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች በሀገር አቀፉ የ2ኛ ደረጃ መልቀቂያ ፈተና የላቀ ውጤት አስመዝግበው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት መግባት እንዲችሉ የሚያግዝ መሆኑን ገልጸው ትምህርቱ ከሰኞ እስከ አርብ ለግማሽ ቀን እንደሚሰጥ አመላክተዋል። ኃላፊው አያይዘውም የማጠናከሪያ ትምህርቱ የተማሪዎችንና ወላጆችን ፍቃደኝነት መሰረት አድርጎ የሚሰጥ መሆኑን ገልጸው ተማሪዎች በሚፈገው ደረጃ ውጤታማ እንዲሆኑ ብቃታቸው የተረጋገጠ መምህራን መመደባቸውን አብራርተዋል:: በተጨማሪም ለትምህርቱ ስኬታማነት ወላጆች ትኩረት በመስጠት ልጆቻቸዉን ወደ ትምህርት ቤት በመላካቸዉ ምስጋና አቅርበዋል፡፡

ሰላም እንደምን አላችሁ! ለመንግስት እና ለግል ት/ቤቶች በሙሉ ነገ ቀን 06/11/2018ዓ.ም የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት በሁሉም ት/ቤቶች እንደሚጀመር ይታወቃል 👉በመሆኑም ሁሉም ት/ቤቶች በ1ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ከ5ኛ ክፍል በላይ ያሉ ተማሪዎችን በት/ቤታችሁ ማጠናከሪያ ት/ት እንዲማሩ እንዲደረግ እና ከ11ኛ -12ኛ ክፍል ከTOP 30 ውጭ ያሉ ተማሪዎች በት/ቤቱ ውስጥ እና TOP 30 ተማሪዎች ደግሞ በተመረጡ ክላስተር ማዕከላት የማጠናከሪያ ትምህርቱ መሰጠት እንዲጀምር ከፍተኛ ክትትል እና ድጋፍ ይደረግ በማለት እናሳውቃለን ። የኮ/ቀ/ክ/ከ/ት/ፅ/ቤት

አልፋ ቀራንዮ ቅድመ አንደኛ፣ አንደኛ እና መካከለኛ  ደረጃ እና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት  ለ2018 ዓ.ም በክረምት መርሃ ግብር ተማሪዎች የማጠናከሪያ ት/ት እንድትማሩ በመንግስትም ሆነ በግል ትምህርት ቤት በትምህርት ቢሮ ደረጃ ተወስኗል   ፡፡ በ2018 ዓ.ም የትምህርት ዘመን በክረምት መርሃ ግብር ሁሉም የአንደኛ እና መካከለኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንዲሁም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ከ5ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ያላችሁ ተማሪዎች የክረምት የማጠናከሪያ ትምህርት መማር እንዳለባችሁ ከትምህርት ቢሮ መልዕክት የተላለፈ ሲሆን የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች(TOP 30 STUDENTS)  በየክፍላችሁ ከ1ኛ እስከ 30ኛ ደረጃ የወጣችሁ ተማሪዎች ይህም ማለት 11ኛ ክፍሎች በ2018 ዓ.ም. የ10ኛ ክፍል ተማሪ የነበራችሁ እና 12ኛ ክፍል ደግሞ በ2018 ዓ.ም. የ11ኛ ክፍል ተማሪ የነበራችሁ ስትሆኑ እናንተ የአልፋ ቀራንዮ ተማሪዎች በዋቆ ጉቱ ቁጥር 2 እንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት እንድትማሩ የተወሰነ ስለሆነ ነገ ማለትም 06/11/2018 ዓ.ም. ትምህርቱ የሚጀምር ስለሆነ ቦታው ድረስ ሄዳችሁ እንድትመዘገቡ፣ሌሎች ተማሪዎች በትምህርት ቤት ያላችሁ ደግሞ የ12ኛ ክፍል የማትሪክ ፈተና እንዳለቀ በ14/11/2018 ዓ.ም. ትምህርት ቤት በመገኘት እንድታነጋግሩን መልዕክታችን እናስተላልፋለን ፡፡    ፨ ዩኒፎርም መልበስ እና መታወቂያ መያዝ ግዴታ ነው።                                                               ት/ቤቱ